Lafto wayou wereda communication

Lafto wayou wereda communication Boys will be boys

በቅሬታ አፈታትና አወሳስን ላይ ስልጠና ተሰጠ። #ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 17/2015 ****በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሀብት ልማት...
25/05/2023

በቅሬታ አፈታትና አወሳስን ላይ ስልጠና ተሰጠ።
#ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 17/2015
****
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሀብት ልማት ፅ/ቤት ለአመራርና ቡድን መሪዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቅሬታና አቤቱታ አቀራረብ ፣ ምርመራ፣ አወሳሰን እና የተጠያቂነት ስርዓት ለመወሰን የወጣ
በደንብ ቁጥር 143/2015 ላይ ስልጠና ተሰቷል።

ስልጠናዉን የሰጡት የወረዳ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሴናተር ሳሙኤል ሲሆኑ አጠቃላይ ድንጋጌዎችን፣ የቅሬታና አቤቱታ አቀራርብ ስነ-ስርዓት ላይ ትኩረት በማድረግ ስልጠናዉን ሰተዋል።

በተጨማሪም በአገልግሎት አሰጣጥ እና በባለሙያ ስምሪት ላይ ትኩረት በማድረግ የሪፎርም ዉይይት ተካሂዷል።በዉይይቱ የአገልግሎት አሰጣጥ ከ90 ቀን ተግባራት ዉስጥ አንዱ በመሆኑ በተለይ እሮብና አርብ ኮሚቴዉ የሚያደርገዉን ምልከታ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል።በምልከታዉ የተገኙ በጥንካሬና በክፍተት ተጠምሮ ሪፖርት እንደሚቀርብም የ/ቤት ሀላፊዉ አቶ ሙሉቀን ጥላሁን ገልፀዋል።እንዲሁም የስራ ቦታን ምቹና ማራኪ ለማድረግ ሁሉም ተቋማት የደንብ ልብስ በማዘጋጀት ቀልጣፋና ፍትሀዊ አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ አቶ
ሙሉቀን ገልፀዋል።

ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የግብዓት እና የሰዉ ሀይል ችግር፣ የሰራተኛ ጥቅማ ጥቅም የመሳሰሉት ጥያቄዎች ከቤቱ በስፋት ተነስተዋል።

በተነሱት ጥያቄዎች ላይ ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሀብት ልማት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ሙሉቀን ከግብዓት ጋር በተያያዘ ከፋይናንስ ፅ/ቤት ጋር በመነጋገር ለቀጣይ በጀት ዓመት ለማሟላት በእንቅስቃሴ ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

ለአምስተኛዉ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የችግኝ  መትከያ ጉድጓድ ቁፋሮ ተካሄደ። #ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 17/2015***በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ 15 ከተ...
25/05/2023

ለአምስተኛዉ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር የችግኝ
መትከያ ጉድጓድ ቁፋሮ ተካሄደ።
#ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 17/2015
***
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ 15 ከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ፅ/ቤት አስተባባሪነት በቀጣይ ክረምት ለሚካሄደዉ የአምስተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር
የችግኝ መትከያ የጉድጓድ ቁፋሮ ቅድመ ዝግጅት ስራ እያከናወነ ይገኛል።የጉድጓድ ቁፋሮዉ ከፅዳት አስተዳደር ፅ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን በአርቲስት ሀጫሉ የመንገድ ዳርቻ ላይ ባለሙያዎችንና የሽርክና ማህበራትን በማሳተፍ ተካሂዷል።

የሰላም ሰራዊት ስምሪት  … #ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 16/2015========በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ አስተዳደር  "እኔ የአካባቢዬ የሰላም ዘብ ነኝ"በሚል መሪ ሀ...
24/05/2023

የሰላም ሰራዊት ስምሪት …
#ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 16/2015
========
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ አስተዳደር "እኔ የአካባቢዬ የሰላም ዘብ ነኝ"በሚል መሪ ሀሳብ የሰላም ሰራዊቱ ሰፈሩን እና አካባቢዉን ዛሬም እንዲህ እየጠበቀ ይገኛል።

የጎዳና ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ ተከናወነ። #ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 16/2015===============በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ 15 ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት የ...
24/05/2023

የጎዳና ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ ተከናወነ።
#ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 16/2015
===============
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ 15 ደንብ ማስከበር ፅ/ቤት የደንብ መተላለፍን በተመለከተ በወረዳዉ በሁሉም ክላስተሮች የጎዳና ላይ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራ አካሂዷል።

ፅ/ቤቱ በተለያዩ የጥፋት አይነቶች ማለትም አግባብ ካለዉ የመንግስት አካል ፈቃድ ሳያገኝ የመንግስትን መሬት በማነኛዉም መንገድ መያዝ፣ በህጋዊ መንገድ ከተያዘዉ የቦታ ስፋት በላይ ተጨማሪ ቦታ አስፋፍቶ መያዝ፣ ከህጋዊ አካል እዉቅና ዉጪ ህገ ወጥ ግንባታ መገንባት፣ ህገ ወጥ እርድ፣ ደረቅ ቆሻሻ ባልተፈቀደ ቦታ መጣል እና በመሳሰሉት ላይ በጎዳና በመንቀሳቀስ ለማህበረሰቡ ግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባር ተከናዉኗል።

ስለሆነም ማህበረሰቡ የተሰጠዉን ትምህርትና መመሪያ ከግንዛቤ በማስገባት ከየትኛዉም ህገ ወጥ ተግባር ራሱን እንዲያርቅ ፅ/ቤቱ በጥብቅ እያሳሰበ ይህን ተላልፎ የሚገኛዉ አካል ላይ ተቋሙ አስፈላጊዉን እርምጃ በመዉሰድ ህግ የማስከበር ስራዉን እንደሚሰራ አስገንዝቧል።

"አስተዳደሩ በባለጉዳይ ቀን ለአገልግሎት ልዩ ትኩረት በመስጠት  ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ። #ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 16/2015 ================...
24/05/2023

"አስተዳደሩ በባለጉዳይ ቀን ለአገልግሎት ልዩ ትኩረት በመስጠት ቀልጣፋና ፍትሃዊ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑ ተገለፀ።
#ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 16/2015
==================
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ 15 አስተዳደር የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ድንገተኛ ምልከታ ተደረገ።

ኮምዩኒኬሽን ፅ/ቤት ከፐብሊክ ሰርቪስና የሰዉ ሀብት ልማት ፅ/ቤት ጋር በመተባበር የሴክተር ተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ በተመለከተ ድንገተኛ ምልከታ ተደርጓል።

በየተቋማቱ አገልግሎት ፈልገው የመጡ ተገልጋዮች በሰጡት አስተያየት አስተዳደሩ በባለጉዳይ ቀን የተለይ ሰኞ፣እሮብና ዓርብ ለአገልግሎት ልዩ ትኩረት መስጠቱን የሚያመላክቱ መሠረታዊ ለውጦች መኖሩንና ቀልጣፋና ፍትሃዊ ምላሽ እያገኙ እንደሆነም በምልከታዉ ወቅት ያገኘናቸዉ ተገልጋዮች ገልፀዋል።

አክለውም በአገልግሎት ዘርፍ አንዳንድ የሚስተዋሉ ችግሮችን በማረም በቀጣይም በትኩረት መሰራት እንዳለበት ጠይቀዋል።

የአምስተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ቅድመ ዝገጅት ስራ እየተከናወነ ይገኛል። #ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 16/2015***በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ ከተማ ውበ...
24/05/2023

የአምስተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ቅድመ ዝገጅት ስራ እየተከናወነ ይገኛል።
#ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 16/2015
***
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ ከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ፅ/ቤት ከ90 ቀን እቅድ ተግባራት ዉስጥ አንዱ የሆነዉን የክረምት ችግኝ መትከያ የጉድጓድ ቁፋሮ ቅድመ ዝግጅት ስራ እያከናወነ ይገኛል።

በመሆኑም ፅ/ቤቱ ከፅዳት አስተዳደርና ከስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ፅ/ቤት የሴፍቲ ኔት ተጠቃሚዎች ጋር በጋራ በመሆን በአርቲስት ሀጫሉ የመንገድ ዳርቻ የተተከሉ ችግኞችን መኮትኮትና መንከባከብ፣ለቀጣይ የክረምት ችግኝ መትከያ ቦታ የጉድጓድ ቁፋሮ ዝግጅት እንዲሁም የተተከሉ ችግኞችን የማረምና የመንከባከብ ስራ አካሂዷል።

"በያዝነው የአምስተኛው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራች መርሐ ግብር ላይ ዘንድሮ በጋራ ለምንተክለው 6.5 ቢልዮን ችግኝ ዝግጅት በመካሄድ ላይ ነው። የፍራፍሬ ዛፎችን በብዛት እንተክላለን።"- ጠቅላ...
23/05/2023

"በያዝነው የአምስተኛው ዓመት የአረንጓዴ ዐሻራች መርሐ ግብር ላይ ዘንድሮ በጋራ ለምንተክለው 6.5 ቢልዮን ችግኝ ዝግጅት በመካሄድ ላይ ነው። የፍራፍሬ ዛፎችን በብዛት እንተክላለን።"

- ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ

የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም በመጪዎቹ ሶስት አመታት የከተማዋ ቀዳሚ የልማት መርሐ-ግብሮች መካከል  አንዱና ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ፕሮግራም መሆኑን አቶ ጃንጥራር አባይ የአዲስ አበባ ...
22/05/2023

የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም በመጪዎቹ ሶስት አመታት የከተማዋ ቀዳሚ የልማት መርሐ-ግብሮች መካከል አንዱና ከፍተኛ ትኩረት የሚሰጠው ፕሮግራም መሆኑን አቶ ጃንጥራር አባይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አስታወቁ፡፡

ምክትል ከንቲባው ይህንን ያስታወቁት የቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራሙ ዋነኛ አጋር የሆነውና መቀመጫውን በለንደን ከተማ ያደረገው የቢግ ዊን ፊላንትሮፒ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ከሰተብርሐን አድማሱና በቅርቡ የፕሮግራሙ አጋር በመሆን ድጋፉን መለገስ የጀመረው በአሜሪካ የሚገኝ የኤልማ ፊናንትሮፒ ፕሬዝዳንት ሚስስ ሮቢን ካልደር በጽ/ቤታቸው በተገኙበት ወቅት ነው፡፡

በመጪዎቹ ሶስት አመታት በቀዳማይ ልጅነት ልማት ፕሮግራም አማካኝነት ከተማችንን ለህጻናት የተመቸች ለማድረግ የተለያዩ የህግ ማእቀፎች ተዘጋጅተዋል፤ ስትራቴጂና ፍኖተ ካርታ ተነድፏል፤ ዝርዝር እቅዶችም መዘጋጀቱን ተገልጿል።

በዚህም መሰረት በመጪዎቹ ሶስት አመታት እስከ 12000 የሚደርሱ የህጻናት መጫወቻዎች፣ 1000 ያህል ልዩ ልዩ የህጻናት እንክብካቤ ማእከላት በመንግስት፣ በህብረሰቡና በግሉ ዘርፍ እንደሚስፋፉ ተናግረዋል፡፡

ፕሮግራሙ ከ0 እስከ 6 አመት እድሜ ባላቸው ህጻናት ላይ አተኩሮ የሚሰራ እንደመሆኑ በቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት አሰጣጥ ላይም ትኩረት በማድረግ እንደሚሰራ ምክትል ከንቲባው አመልክተዋል፡፡

ይንን ተግባር ለማሳለጥና በተለይም የወላጆችን ግንዛቤና ክህሎት በማሳደግ ፕሮግራሙን ስኬታማ ለማድረግ እንዲቻል ወላጆችን በንቃት ማሳተፍ አስፈላጊ በመሆኑ ቤት ለቤት ለወላጆች ምክርና ድጋፍ የሚሰጡ 5000 ሰራተኞች ተቀጥረው እንደሚሰማሩ አስረድተዋል፤ ከነዚህ መካከልም ባሁኑ ሰዓት ከ2200 በላይ የሚሆኑት በከተማችን ሁሉም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሶስት ወራት ስልጠና በመውሰድ ላይ እንደሆኑ አብራርተዋል፡፡

ዶ/ር ከሰተብርሐን አድማሱ፣ የቢግ ዊን ፊላንትሮፔ ዋና ስራ አስፈጻሚ፣ በዚሁ ወቅት ከተማው በህጻናት ላይ የጀመረው ተግባር እጅግ የሚደነቅና ለአገራችን ብቻም ሳይሆን ለአፍሪካ ጭምር ምሳሌ ሊሆን እንደሚችል ያላቸውን እምነት ገልፀው ፕሮግራሙን በከፍተኛ ደረጃ በመደገፍ ላይ መሆናቸውን፣ ይህ ድጋፍም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል፡፡

ሚስስ ሮቢን ካልደር፣ የኤልማ ፊላንትሮፒ ፕሬዝዳንትም በበኩላቸው ከተማው በህጻናት ላይ ከጀመራቸው ፕሮግራሞች በጤናው ዘርፍና በህጻናት እንክብካቤ ማእከላት በኩል የተጀመረውን እንቅስቃሴ በአካል ለመጎብኘት እድል ማግኘታቸውን አውስተው በአስተዳደሩ ቁርጠኝነት መደሰታቸውን አስረድተዋል፡፡

"ኢትዮጵያን ለመለወጥ መፍትሔ ተኮር መሆን የግድ ነው። የተለያየ ብቃት እና ችሎታ ያላቸው ወጣቶች የፈጠራ ሥራዎቻቸውን ያቀረቡበት ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ዛሬ ተጀምሯል።እንበርታ፣ እንፍ...
22/05/2023

"ኢትዮጵያን ለመለወጥ መፍትሔ ተኮር መሆን የግድ ነው። የተለያየ ብቃት እና ችሎታ ያላቸው ወጣቶች የፈጠራ ሥራዎቻቸውን ያቀረቡበት ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ዛሬ ተጀምሯል።
እንበርታ፣ እንፍጠር፣ ፈተናን ለማለፍ መፍትሔ ላይ እናተኩር።"

- ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ

ከተማ አቀፍ የማርሻል አርት ስፖርታዊ ፌስቲቫል ተካሄደበአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያው የሆነው ከተማ አቀፍ የማርሻል አርት ስፖርታዊ ፌስቲቫል የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጨምሮ ከ15...
21/05/2023

ከተማ አቀፍ የማርሻል አርት ስፖርታዊ ፌስቲቫል ተካሄደ

በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያው የሆነው ከተማ አቀፍ የማርሻል አርት ስፖርታዊ ፌስቲቫል የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጨምሮ ከ15ሺህ በላይ የማርሽ አርት ቤተሰቦች በተገኙበት በመስቀል አደባባይ በድምቀት ተካሂዷል።

በፌስቲቫሉ ላይ የተገኙት የከተማዋ ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ባስተላለፉት መልዕክት ማርሻል አርት ስፖርት ጥበብና እውቀት በማቀናጀት የሚካሄድ ስፖርት በመሆኑ ስፖርቱን ከማስፋፋት እና ተተኪዎችን ከማፍራት በተጨማሪ ለሀገራችን ሰላም፣ አንድነት፣ ለትውልድ ግንባታ ልንጠቀምበት ይገባል ብለዋል።

የኦል ማርሻል አርት ጥምረት መመስረት ለዘርፉ ጥንካሬን ከመፍጠሩም በላይ የእርስ በእርስ ትስስርን ያጠናክራል ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶችና ስፓርት ቢሮ ኃላፊ አቶ በላይ ደጀን ጥምረቱ በአካል እና በአዕምሮ የበለጸገ፣ ጤናማ፣ አምራችና በስነ ምግባር የታነጸ ዜጋን ለመገንባት ትልቅ ድርሻ ያለው በመሆኑ ከዚህ በበለጠ ሊጠናከር ይገባዋል ብለዋል።

በመስቀል አደባባይ በተካሄደው የማርሻል አርት ፌስቲቫል ላይ ኤሊት ኢንተርያሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን፣ ጁዶ አደራጅ ኮሚቴ፣ ኢንተግሬትድ ማርሻል አርት ፌዴሬሽን፣ ውሹ ፌዴሬሽን፣ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን፣ ካራቴ ፌዴሬሽን፣ ኪክ ቦክሲንግ አስሴሽን እና ኢትዮ ዩናይትድ ኢንተርናሽናል ቴኳንዶ ፌዴሬሽን ትርኢታቸውን አቅርበዋል።

በወጣቶች ተጠቃሚነት ዙሪያ ዉይይት ተካሄደ። #ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 12/2015*****በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ ወጣትና ስፖርት ፅ/ቤት ከወጣት ሊግ ጋር በጋራ በ...
20/05/2023

በወጣቶች ተጠቃሚነት ዙሪያ ዉይይት ተካሄደ።
#ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 12/2015
*****
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ ወጣትና ስፖርት ፅ/ቤት ከወጣት ሊግ ጋር በጋራ በመሆን በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራና ተጠቃሚነት ዙሪያ ዉይይት ተካሂዷል። በዉይይቱ ወጣቶች በአምስቱም ዘርፎች ተደራጅተዉ ወደ ስራ ለመግባት ያለመ በስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ፅ/ቤት የመነሻ ፁህፍ ቀርቦ ዉይይት ተደርጎበታል። በመድረኩ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳቦችና ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን የወረዳዉ ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራ ኢንተርፕራይዝና ኢንዱስትሪ ልማት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ተመስገን ለቀረቡት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል።

  3በክፍለ ከተማችን ንፋስ ስልክ ላፍቶ በሰው ተኮር የለውጥ ተግባራት ውስጥ አርሶአደሮችን እና ማህበረሰቡን በማሳተፍ እየተሰራ ያለ የክብት ማደለብና የወተት ተዋፅዖ ስራ ላይ በመሰማራት አበ...
20/05/2023

3

በክፍለ ከተማችን ንፋስ ስልክ ላፍቶ በሰው ተኮር የለውጥ ተግባራት ውስጥ አርሶአደሮችን እና ማህበረሰቡን በማሳተፍ እየተሰራ ያለ የክብት ማደለብና የወተት ተዋፅዖ ስራ ላይ በመሰማራት አበረታች ውጤቶች እየተመዘገቡ ነው።

 #የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን  #ሙስናን መከላከል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ  ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር እየመከረ ይገኛል።የአዲስ አበባ ከተማ የስነ-ምግ...
20/05/2023

#የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን #ሙስናን መከላከል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ከሚዲያ ባለሙያዎች ጋር እየመከረ ይገኛል።

የአዲስ አበባ ከተማ የስነ-ምግባርና ጸረሙስና ኮሚሽን "ሙስናን በመከላከል የሚዲያና ጋዜጠኞች ሚና" በሚል መሪ ሀሳብ ከተለያዩ የኮሙኒኬሽንና የሚዲያ ባለሙያዎች ጋር የውይይት መደረክ እያካሄደ ነው።

በውይይት መደረኩ ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ቡዜና አልቃድር፣ ሙስና በአለም አቀፍ ደረጃ የሀብት ምዝበራን በማስከተል አደገኛ ወንጀል የሆነ ድርጊት መሆኑን አስታውሰዋል።

ብልሹ አሰራር ስር በመስደዱና የዜጐች ጥቅም እየተጣሰ በመሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ በአዋጅ ኮሚሽን አቋቁሞ እየሰራ እንዳለ ተነግረዋል።

በዚህም ከተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት ጋር ሙስናን መዋጋት በሚቻልባቸው ጉዳዮች ተከታታይ የግንዛቤ ውይይቶች እየተደረጉ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ሙስናን ለመታገል የሚዲያ አካላት ዜጐችን በማስተማርና መንግስትን በማንቃት ግንባር ቀደም ሚና እንዳላቸው ጥቅሰው፣ አገር ከሙስና ጥፋት እንዲድን ይህንኑ ሚናቸውን በከፍተኛ ሃላፊነት ሊወጡ ይገባል ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በውይይት መደረኩ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አፈጉባኤ ወይዘሮ ቡዜና አልቃድርን ጨምሮ የአዲስ አበባ ከተማ የስነ-ምግባርና ጸረሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ጀማል ረዲ፣ የሚዲያ አመራሮች፣ ከተለያዩ ተቋማት የተወጣጡ የሚዲያና ኮሙኒኬሽን ባለመያዎች ተሳትፈዋል።

#ምንጭ :-Ethiopian Press Agency (ኢ ፕ ድ)

ከ90 ቀን ተግባራት ዉስጥ አንዱ የሆነዉ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ። #ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 12/2015 *****************በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ አስተዳደ...
20/05/2023

ከ90 ቀን ተግባራት ዉስጥ አንዱ የሆነዉ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።
#ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 12/2015
*****************
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ አስተዳደር ከሚያከናውናቸው የ90 ቀናት ሰው ተኮር ተግባራት ዉስጥ
አንዱ የወረዳውን ውበትና ፅዳት የመጠበቅ ስራ መሆኑ ይታወቃል።ስለሆነም በፅዳት አስተዳደር ፅ/ቤት አስተባባሪነት በየሳምንቱ የሚካሄደዉ የብሎክ የፅዳት ዘመቻ ዛሬ ተካሂዷል። ሰፈርንና አካባቢን ብሎም ከተማዋን ዉብና ፅዱ በማድረግ ምቹ እና ጤናማ አካባቢን ለመፍጠር ታሳቢ በማድረግ፤የሴፍቲኔት ሰራተኞችን፣ባለሙያዎችንና የአካባቢዉን ማህበረሰብ ያሳተፈ የብሎክ የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል።

የዋዩ ወረዳ የሰላም ዘቦች
19/05/2023

የዋዩ ወረዳ የሰላም ዘቦች

የፅፈኞቹ ሌላው የግጭት መጥመቂያ ስልት ...የኢኮኖሚ አሻጥርየአንድ ሀገር እሴት መገለጫ መገኛው ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ መስተጋብሮች ናቸው፡፡ አንድ ሀገር ሀገር ሆኖ እንዲቀጥል ...
19/05/2023

የፅፈኞቹ ሌላው የግጭት መጥመቂያ ስልት ...የኢኮኖሚ አሻጥር

የአንድ ሀገር እሴት መገለጫ መገኛው ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማህበራዊ መስተጋብሮች ናቸው፡፡ አንድ ሀገር ሀገር ሆኖ እንዲቀጥል ሶስቱ ዋና ዋና አምዶች ተጣጥመው እና ተመጋግበው መቀጠላቸው የግድ እና አስፈላጊ ነው፡፡

የኢኮኖሚ መዛባት ፖለቲካውን በእጅጉ የሚጫነው ሲሆን ፖለቲካው የተረጋጋ ባልሆነ ጊዜ ሁሉ ኢኮኖሚው ተፈጥሯዊ ዑደቱ ተስተጓጉሎ በማህበራዊ ዘርፉ ትርምስ ይፈጠራል፡፡

ኢኮኖሚ ሀገር እንደ ሀገር መንግስት እንደ መንግስት እንዲቀጥል ያለው ሚና የጎላ ከመሆኑ አንፃር ስልጣን ላይ ባለ መንግስት ቅሬታ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ወይም የፖለቲካ ፓርቲዎች ከውስጥም ከውጪም ያሉ የመንግስቱ ተቃዋሚዎች ኢኮኖሚውን በመረበሽ መንግስትን ተቀባይነት ለማሳጣት እንደ አንድ የፖለቲካ መታገያ ስልት ሲጠቀሙበት ይስተዋላል፡፡

በሌላም በኩል ገንዘብ መሰብሰብ እና ብልፅግናን አላማ ያደረጉ በየደረጃው ያሉ ነጋዴዎች ያላግባብ ሀብት ለመሰብሰብ እና ይበልጥ ለመበልፀግ በማሰብ ኢኮኖሚው ጤነኛ ሆኖ እንዳይቀጥል የሚያደርጉ ተግባራቶችን የሚከወኑ ሲሆን ይህ በሙያው አጠራር የኢኮኖሚ አሻጥር /economic sabotage/ በመባል ይታወቃል፡፡

የኢኮኖሚ አሻጥር የአንድ ሀገር ኢኮኖሚ እንዳያድግ፣ ውጤታማ እንዳይሆን፣ አቅም እንዲያንሰው እና እንዲረበሽ የማድረግ ተግባር ነው፡፡ ይህ የኢኮኖሚ አሻጥርም በተለያዩ መንገዶች የሚካሄድ ሲሆን እነሱም ምርቶች ደብቆ ማከማቸት፣ የውጭ ምንዛሬ ጥቁር ገበያ፣ ኮንትሮባንድ፣ ህገ ወጥ ሃዋላ እና ህገ ወጥ የገንዘብ ዝውውር ናቸው።

ይህ ተግባር መንግስት ላይ ጫና መፍጠሪያ ዘዴ ሆኖ ሊያገለግል ይችላል እንደ ማለት ነው፡፡

አጥቂዎች ትኩረት አድርገው የሚነሱት ገበያውን ነው ዋናው ተግባራቸውም በገበያው ላይ የአቅርቦት እጥረት እንዲፈጠር ማድረግ ወይም የህብረተሰቡ የመግዛት አቅም እንዲዳካም ማድረግ ወይም ከሚፈለገው በላይ አቅርቦት እንዲኖር ማድረግ ወይም ፍላጎት እንዳይኖር ወይም እንዲቀንስ ማድረግ ወዘተ...ነው፡፡

ይህ ሁነት ገበያው ላይ እንዲገለፅ ከጀርባ አይነተ ብዙ አሻጥሮች ይሰራሉ፡፡ ገበያ በአግባቡ ካልተመራ የአንድን ሀገርን ኢኮኖሚ ለመጉዳት እና መንግስትን ለማዳከም አይነተኛ መሳሪያ ነው፡፡

በቅርብ ግዜያትም በሀገራችን አንዳንድ አካላት በአቋራጭ ስልጣን ለማግኝት ፅንፈኛ አመለካከት እና የሴራ ፓለቲካ ትርክት እየነዙ ሀሰተኛ መረጃን በማሰራጨት ዜጎችን ማታለል፣ ማደናገርና ለጉዳት ማጋለጥ፣ የህብረተሰቡን የአንድነት፣ የወንድማማችነትና የመቻቻል ባህልን ማዳከም፣ የብሔርና የሃይማኖት ግጭቶች እንዲፈጠሩ ፅንፈኛ አጀንዳዎችን ቀርፀው ሀገር ለማተራመስ የሞከሩት ሴራ በመክሸፋ አሁን ላይ የኢኮኖሚ አሻጥር እንደ አማራጭ ለመጠቀም ህዝብን በማማረር ከ መንግስት ጋር ለማቃቃር እና ሁከት ለመፍጠር መሞከራቸው አይቀሬ ነው።

በመሆኑም ይህ ድርጊት ወንጀል ከመሆኑም በላይ በሀገር እና ህዝብ ላይ ከባድ አደጋ የሚያስከትል በመሆኑ መላው ህዝብ በመገንዘብ ይህን የሚፈፅሙ አካላትን በመለየት እና ለመንግስት አካላት በማሳወቅ ሁሉም ህዝብ የዜግነት ግዴታውን ሊወጣ ይገባል።

 !🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የዋዩ ወረዳ አስተዳደር ከሚያከናውናቸው የ90 ቀናት ሰው ተኮር ተግባራት አንዱ የሆነውን የወረዳውን ውበትና ፅዳት የመጠበቅ ተግ...
19/05/2023

!
🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹🧹
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የዋዩ ወረዳ አስተዳደር ከሚያከናውናቸው የ90 ቀናት ሰው ተኮር ተግባራት አንዱ የሆነውን የወረዳውን ውበትና ፅዳት የመጠበቅ ተግባራት ሳምንታዊ የትምህርት ቤቶች የፅዳት ዘመቻ ተከናዉኗል።

በፅዳት መርሀግብሩ ላይም የወረዳው አመራሮች መምህራንና ተማሪዎች ተሳትፈዋል።ከተማችንን እንደ ስሟ አዲስ ለማድረግ ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል አካባቢውን ውብ ፅዱና ምቹ ማድረግ ይጠበቅበታል ተማሪዎችም የመማሪያ አካባቢያቸውን ፅዳትና ውበት የመጠበቅ ሀላፊነት እንዳለባቸው ተገልጿል።

ግንቦት 11-2015

የስነ ምግባርና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን ፅ/ቤት የ9 ወር ስራ አፈፃፀሙን ገመገመ። #ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 11/2015 ===============በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረ...
19/05/2023

የስነ ምግባርና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን ፅ/ቤት የ9 ወር ስራ አፈፃፀሙን ገመገመ።
#ዋዩ ወረዳ ኮምዩኒኬሽን፤ግንቦት 11/2015
===============
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ዋዩ ወረዳ15 ስነ ምግባርና ኢንስፔክሽን ኮሚሽን ፅ/ቤት የ9 ወር ስራ አፈፃፀሙን ከአባላት ጋር በመገምገም ኮንፈረንሱን አካሂዷል።

ፅ/ቤቱ በዘጠኝ ወር ዉስጥ ያከናወናቸዉን የተለያዩ ተግባራት በጥንካሬና በክፍተት ተለይቶ ዝርዝር ዉይይት ተካሂዷል። በተጨማሪም ፅ/ቤቱ የሚያከናዉናቸዉን ተግባራት እንዲሁም ስልጣንና ሀላፊነቱን በተመለከተ በኮንፈረንሱ በስፋት ተዳሷል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lafto wayou wereda communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share