Ethiopian Truth

Ethiopian Truth በዚህ ገፅ ወቅታዊ ዜና፣ ትንታኔዎች እና መረጃዎች ይቀርቡበታል።/ This page provides current news & news analysis.

20ኛው የኦሮሚያ ስፖርት ምክር ቤት ጉባዔ በአዳማ ከተማ ተካሄደ፡፡ጥቅምት 07፣ 2018ዓ.ም  አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወሉ አብዲ የስፖርት ዘርፉን ለማጠና...
18/10/2025

20ኛው የኦሮሚያ ስፖርት ምክር ቤት ጉባዔ በአዳማ ከተማ ተካሄደ፡፡

ጥቅምት 07፣ 2018ዓ.ም አዲስ አበባ

የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወሉ አብዲ የስፖርት ዘርፉን ለማጠናከር በትኩረት እየተሰራ ነው አሉ፡፡

አቶ አወሉ አብዲ በመድረኩ እንዳሉት፦ እንደ ሀገር ለስፖርት ዘርፉ የተሰጠውን ትኩረት ተከትሎ የክልሉ መንግስት የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ለማስፋፋት በሰራቸው ስራዎች ስኬቶች ተመዝግበዋል።

በኢትዮጵያ ትልቅ እና የስፖርት ዘርፍ ምልክት የሆነው አትሌቲክስ ዳግም እንዲያንሰራራ የክልሉ ስፖርት ጉባዔ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡

የክልሉ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ሮዛ ቢያ በበኩላቸው÷ የክልሉ መንግስት ከስፖርት ዘርፍ ተጠቃሚ ለመሆን ሰፊ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ክልሉ የጠንካራ ስፖርተኞች ማዕከል መሆኑን ጠቅሰው÷ በሁሉም የስፖርት አይነቶች በርካታ ወጣት ስፖርተኞችን ለሀገር ማበርከት መቻሉን ጠቁመዋል።

ጉባዔው የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸምን ከመገምገም ባለፈ የ2018 በጀት ዓመት የስራ ማስፈጸሚያ በጀት እና ዕቅድን ተወያይቶ አፅድቋል።
#ባህልናስፖርትሚኒስቴር

 #ቻይና የአሜሪካ ጀቶች በፍጹም ከአይኔ ሊሰወሩ እንዳይችሉ የሚያደርግ ራዳር ማምረት ጀምሪያለሁ አለች ቻይና እንደ ዩናይትድ ስቴትስ F-22 ራፕተር እና F-35 የመሳሰሉትን የማይታዩ (ስቴል...
17/10/2025

#ቻይና የአሜሪካ ጀቶች በፍጹም ከአይኔ ሊሰወሩ እንዳይችሉ የሚያደርግ ራዳር ማምረት ጀምሪያለሁ አለች

ቻይና እንደ ዩናይትድ ስቴትስ F-22 ራፕተር እና F-35 የመሳሰሉትን የማይታዩ (ስቴልዝ) ተዋጊ ጄቶች መከታተል የሚያስችላት እጅግ በጣም ሚስጥራዊ የሆኑ የነጠላ-ፎቶን መመርመሪያዎችን (single-photon detectors) በጅምላ ማምረት መጀመሯን አስታወቀች።

በአንሁይ ግዛት በሚገኘው የኳንተም መረጃ ምህንድስና ቴክኖሎጂ ምርምር ማዕከል የተሰራው ይህ አዲስ ባለአራት-ቻናል መመርመሪያ (four-channel detector) አንድ ለሆነ ፎቶን (የብርሃን ትንሹ የኃይል ክፍል) ለይቶ የማወቅ ችሎታ ያለው ሲሆን፣ ይህ ደግሞ እጅግ በጣም አነስተኛ የሆኑ ምልክቶችን እንኳን ለመለየት ያስችለዋል።

የማይታዩ አውሮፕላኖች በልዩ ሽፋን እና ዲዛይን አማካኝነት የራዳር ሞገዶችን በመምጠጥ ወይም በማንሸራተት ከባህላዊ ራዳሮች ይደበቃሉ።

ይህ አዲስ ቴክኖሎጂ ግን የተለየ ነው። የኳንተም ራዳሮች ፎቶኖችን ይልካሉ። እነዚህ ፎቶኖች አውሮፕላኑን ሲመቱ የነበራቸው ባህርይ ይለወጣል። ይህ ለውጥ ደግሞ አውሮፕላኑ የውሸት ምልክት (false signal) ለመላክ ቢሞክርም እንኳ ትክክለኛ ቦታውን እንዲገለጥ ያደርጋል ነው የተባለው።

አዲሱ መመርመሪያ ከአንድ-ቻናል አቻዎቹ ጋር ሲነፃፀር አንድ ዘጠነኛ ያህል ያነሰ መጠን ያለው ሲሆን፣ አነስተኛ ኃይልን ስለሚጠቀም በቀላሉ በተለያዩ መድረኮች ላይ ለመጫን ያመቻል።

ይህ የቴክኖሎጂ ግኝት ለአሜሪካ ስድስተኛ ትውልድ ተዋጊ ጄቶች ልማት እቅዶች አዲስ ስጋት ሊፈጥር እንደሚችል እየተነገረ ነው።

ቻይና በዚህ ወሳኝ የኳንተም ቴክኖሎጂ ዘርፍ ራሷን ችላ የአለም አቀፍ መሪ መሆን መቻሏንም አስታውቃለች።
(መናኸሪያ ሬዲዮ)

 #የኢንስቲትዩቱ አመራርና ሠራተኞች ብሔራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በሚል ርዕስ  በተዘጋጀ  ሰነድ ዙሪያ  ስልጠናዊ ውይይት አካሄዱ።ጥቅምት 7/2018 ዓ.ምቱ.ማ.ኢየቱሪዝም ማሰልጠኛ ...
17/10/2025

#የኢንስቲትዩቱ አመራርና ሠራተኞች ብሔራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ሰነድ ዙሪያ ስልጠናዊ ውይይት አካሄዱ።
ጥቅምት 7/2018 ዓ.ም
ቱ.ማ.ኢ
የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት አመራርና ሠራተኞች ብሔራዊ ጥቅምና ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በሚል ርዕስ በተዘጋጀ ሰነድ ዙሪያ ስልጠናዊ ውይይት አካሂደዋል ።
ስልጠናውን የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አቶ ጌታቸው ነጋሽ የከፈቱ ሲሆን በመልእክታቸውም ወቅታዊና ሀገራዊ በሆኑ ጉዳዮች ዙሪያ ሠራተኛው ግንዛቤ እንዲኖረውና የበኩሉን ኃላፊነት ለመወጣት እንዲችል መድረኩ መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

አቶ ጌታቸው አክለውም ሠራተኛው በብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ ላይ ውስጣዊ አንድነታችንን በማጠናከር በጋራ መቆም እንዳለበት መልእክት አስተላልፈዋል።

የስልጠና ሰነዱን የኢንስቲትዩቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ይታሰብ ስዩም ያቀረቡ ሲሆን በሰነዱ በጉልህ ከተነሱ ነጥቦች ውስጥ የኢትዮጵያ ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመናና ብሔራዊ ጥቅም፣ የብሔራዊ ጥቅም ዋነኛ ፈተናዎች፣ ለብሔራዊ ጥቅም መረጋገጥ ቁልፍ መፍትሔዎች፣ ለብሔራዊ ጥቅሞቻችን መረጋገጥ የሚጠበቅብን ሚና እና የተቋማት ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በተቋም ውጤታማነት ላይ እንዴት ተፅዕኖ እንደሚያሳርፍ በዋነኝነት ይጠቀሳሉ።

በመድረኩ በርካታ አገራዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮች የተነሱ ሲሆን በተለይ ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ጋር በተያያዘ የተሻገርነውን የአሸናፊነት ድል እና ከታሪካዊ ወደቦቻችን በተያያዘ ዓለም አጀንዳው እንዲያደርገው መደረጉ፣ ሠራተኛው በአገልጋይነት መንፈስ ሥራውን መስራት እንደሚጠበቅበት በተሳታፊዎች በኩል ተነስቶ ጥልቅ ውይይት ተደርጎበታል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያን ወደ ቀደመ ክብሯ ለመመለስ የሀገርን ገጽታ የሚገነቡ በርካታ ትልልቅ ሥራዎች እየተሰሩ ህዝቦች ከተረጅነት ራስን ወደ መቻል፣ የነዳጅ እና የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ እና ሌሎች አንኳር ፕሮጀክቶች ሥራላይ መሆናቸው ተገልጿል።
#ቱሪዝምማሰልጠኛኢንስቲትዩት

17/10/2025

BREAKING NEWS! 🛑
አረቄ ቤቶች ሙሉ ለሙሉ ሊዘጉ ነው::

ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም. (E.C.) : ቢንጎ እና አረቄ ቤቶች በአዲስ አበባ አይኖሩም ተባለ! አስተዳደሩ ቆራጥ ውሳኔ አስተላለፈ!

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ቢሮ በከተማዋ ውስጥ የሚገኙ የቢንጎ ማጫወቻ እና የአረቄ መሸጫ ቤቶችን በተመለከተ አስቸኳይ እና ቆራጥ ውሳኔ አሳለፈ።

ከዛሬ ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ አንድም የቢንጎ ማጫወቻም ሆነ የአረቄ መሸጫ ቤት መኖር የለበትም!

የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ እንዳሉት፦
"እነዚህ ቤቶች (የቢንጎ ማጫወቻ እና በየመንደሩ ያሉ አረቄ ቤቶች) የከተማው ወንጀል መፈልፈያ ቦታዎች ናቸው።"

መመሪያውም ቤቶቹ የወንጀል ምክንያት በመሆናቸው ምክንያት ከከተማው እንዲጠፉ ታስቦ ነው።

ከዚህ በፊትም ተመሳሳይ መመሪያ ተሰጥቶ እንደነበር ቢታወቅም፣ ቤቶቹ አሁንም በስራ ላይ መሆናቸው ታውቋል። አስተዳደሩ ግን አሁን ባጭር ጊዜ ውስጥ አዲስ አበባን ከእነዚህ ቤቶች ነፃ ያደርጋታል ብሏል።

ትዕዛዙን ላለማስፈፀም የሚከፈል ዋጋ፦
ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ትዕዛዙን ተፈጻሚ የማያደርጉ ኃላፊዎች ላይም ማስጠንቀቂያ "ይህንን ማስፈፀም ያልቻሉ ኃላፊዎችም በቦታቸው አይቀጥሉም!"

Via ሸገር ኤፍ ኤም 102.1
📷ፋይል ኤድዋርድ

ይህ ውሳኔ የከተማዋን ሰላም እና ፀጥታ ለማስፈን ይረዳል ብለው ያምናሉ?

አስተያየቶቻችሁን ያካፍሉን!

14/10/2025

#የተወዳጇ አርቲስት ፍቅርተ ጌታሁን ባለቤት ዘንካታው ጠበቃና የሕግ አማካሪ ደነቀ መኮንን በድንገተኛ ህመም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፣ የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ዛሬ ከቀኑ በ8 ሰዓት ሸጎሌ በሚገኘው ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን ይፈፀማል።
#ነፍስ ይማር ለቤተሰቡ በሙሉ መጽናናትን ይስጥልን

 #አትሌት መሠረት ደፋር በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ ሽልማት ተበረከተላት!የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሠረት ደፋር አሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ ላይ የአፍሪካ ኢምፓክት...
14/10/2025

#አትሌት መሠረት ደፋር በአሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ ሽልማት ተበረከተላት!

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዚዳንት አትሌት መሠረት ደፋር አሜሪካ ዋሺንግተን ዲሲ ላይ የአፍሪካ ኢምፓክት አዋርድ በአትሌቲክሱ ላበረከተቹ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሽልማት ተበርክቶለታል ።

አትሌት መሠረት ደፋር በዓለም አትሌቲክስ የዓመቱ ኮከብ አትሌት ምርጫን በሴቶች ዘርፍ ያሸነፈች የመጀመሪያዋ ኢትዮጵያዊት መሆኗ ይታወሳል፡፡

14/10/2025

5 ሚሊዮን ብር ወጪ የሆነበት የአፍሪካን አሊ የሙዚቃ አልበም ሊወጣ ነው ነው።

#ድምፃዊ አፍሪካን አሊ ሶስተኛው አልበሙን አጠናቆ ለአድማጮች ሊያድርስ መሆኑ ዛሬ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም በተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ ተገልጿል።

አልበሙ "ታይሴ ዓዳ" የተሰኘው ሲሆን ከሌሎቹ የሙዚቃ አልበሞቹ ለየት የሚያደርገው የአፋር ህዝብን ቱባ ባህልን ለአለም የሚያስተዋወቅ መሆኑ እና በተለይ ለአዲሱ ትውልድ ባህሉን እንዲያውቅ ትልቅ አስተዋፀኦ ያለው ስራ መሆኑ ተነግሯል።

የአልበሙ መጠሪያ ታይሴ ዓዳ ትርጉሙ ድንቅ ባህል ማለት እንደሆነ ድምጻዊው ተናግሯል።

በአልበሙ በቅንብር፣ ሚክሲንግ እና ማስተሪንግ ስማገኘው ሳሙኤል (ዲታ ስቱዲዮ) ስድስት ትራኮችን የሰራ ሲሆን የቀሩትን 2 ትራኮች ደግሞ መክበብ ፀጋይ (ማርዮ) ሰርቷል።

ከታይሴ ዓዳ አልበም ዉስጥ አራት ትራኮች በቪድዮ ክሊፕ የተሰሩ ሲሆን እነዚህ ክሊፖችን ለመስራት የአፋር ቱሪስት መዳራሻዎች ድረስ በመሄድ ባህሉን በጠበቀ መልኩ ከፍተኛ ወጪ በማውጣት መሰራታቸው ተነግሯል።

በአጠቃላይ ይህ ኣልበም ለመሰራት ከአምስት ሚልዮን ብር በላይ ወጪ ወጥቶበት የተሰራ ሲሆን የዚህን ወጪ ሙሉ በሙሉ በድምፃዊ ኢንጅነር አፍሪካን ዓሊ ፕሮዲዩስ የተደረገ ነው፡፡

ታይሴ ዓዳ አልበም ስለ አፋር ቱባ ባህል፣ ስለ ሰላም፣ ስለ ፍቅር የሚዳስስ የሙዚቃ አልበም ነው። ጥቅምት 09/2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ይመረቃል።

አፍሪካን አሊ ሙዚቀኛ፣ ኢንጀነር እንዲሁም የዩነቨርሲቲ አስተማሪ ሲሆን አፍሪካን አሊ በትምህርቱ ዘርፍ በምህንደስና በሁለት ዘርፍ የማስተርስ ዲግሪ አለው።

ቅዱስ ጊዮርጊስ  የአዲስ አበባ ከተማ ህዳሴ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ  የአዲስ አበባ ከተማ ህዳሴ ዋንጫ በቅዱስ ጊዮርጊስ አሸናፊነት ተጠናቋል።ቅዱስ ጊዮርጊስን እና መቻልን ያገናኘው የፍፃሜ ጨዋታ ...
12/10/2025

ቅዱስ ጊዮርጊስ የአዲስ አበባ ከተማ ህዳሴ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ

የአዲስ አበባ ከተማ ህዳሴ ዋንጫ በቅዱስ ጊዮርጊስ አሸናፊነት ተጠናቋል።

ቅዱስ ጊዮርጊስን እና መቻልን ያገናኘው የፍፃሜ ጨዋታ በጊዮርጊስ 2ለ1 አሸናፊነት መጠናቀቅ ችሏል።

በበርካታ ደጋፊዎች ታጅቦ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ለቅዱስ ጊዮርጊስ አሸናፊ ጌታቸው እና አዲሱ አቱላ የማሸነፊያ ግቦቹን ከመረብ አሳርፈዋል።

የመቻልን ብቸኛ ግብ የቅዱስ ጊዮርጊሱ ተከላካይ ሄኖክ ዮሐንስ በራሱ ላይ አስቆጥሯል።

12/10/2025

#አሳዛኝ ዜና
በአማራ ክልል በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን በጨፋ ሮቢት ከተማ ልዩ ስሙ ጃራ ድልድይ አከባቢ ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኢት 73290 የሆነ ታታ ባስ እና ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኢት 41157 ተሳቢ መኪና ተጋጭተው በደረሰ ዘግናኝ የትራፊክ አደጋ ለግዜው ቁጥሩ ያልታወቀ የበርካታ ሰዎች ህይዎት አልፏል በርካቶች የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በጨፋ ሮቢት ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል ።

እባካችሁ ሹፌሮች ህግና ደንብ አክብራችሁ በማሽከርከር የራሳችሁን እና የመንገደኞችን ህይዎት ጠብቁ ። 😭😭
©️Moha Wollo

 #የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከኩሪፍቱ አፍሪካ ቪሌጅ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦች ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት ተከፍቷል። በፌስቲቫሉ ላይ ከመላው ኢትዮጵያ ውስጥ ለማሳ...
12/10/2025

#የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከኩሪፍቱ አፍሪካ ቪሌጅ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦች ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት ተከፍቷል።

በፌስቲቫሉ ላይ ከመላው ኢትዮጵያ ውስጥ ለማሳያነት የተመረጡ 31 ባህላዊ ምግቦች ቀርበዋል።

ፌስቲቫሉ በዋናነት ባህል እና ባህላዊ ምግቦችን ማስተዋወቅ
፣ ወደ ገበታ እንዲመጡ ማድረግ ፣ የእርስ በርስ ትውውቅን መፍጠር ፣ የሀገር ገጽታ መገንባት እና የምግብ ቱሪዝምን የማሳደግ ፋይዳዎች ዓላማ ያደረገ ነው።

ከዚህ በተጨማሪ የእናቶችን ሀገር በቀል እውቀት ወደ ቀጣዩ ትውልድ የማሻገር የዚህ የምግብ ፌስቲቫል ዓላማ መሆኑም ተገልጿል።

በመርሐ ግብሩ ምግቡን ያዘጋጁ እናቶች፣ የየብሔረሰቦቹ ተወካዮች ፣ ሆቴሎች እና የተለያዩ ተቋማት እየተሳተፉበት ይገኛል

የባህላዊ ምግብ ፌስቲቫሉ ኢትዮጵያ ከነሙሉ ክብሯ የታየችበት መድረክ ነው ተባለ።ቱ.ማ.ኢጥቅምት 1/2018 ዓ.ምቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት  ከኩሪፍቱ አፍሪካ ቪሌጅ ጋር በመተባበር  የኢትዮ...
12/10/2025

የባህላዊ ምግብ ፌስቲቫሉ ኢትዮጵያ ከነሙሉ ክብሯ የታየችበት መድረክ ነው ተባለ።
ቱ.ማ.ኢ
ጥቅምት 1/2018 ዓ.ም
ቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ከኩሪፍቱ አፍሪካ ቪሌጅ ጋር በመተባበር የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦች ፌስቲቫል አዘጋጅቷል።
በዝግጅቱ ላይ በክብር እንግድነት ተገኝተው ፕሮግራሙን የከፈቱት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እንደገለጹት ይህ የባህላዊ ምግብ ፌስቲቫል ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ከነሙሉ ክብሯ የተገለጸችበት ነው በማለት ገልጸውታል።
ይህን መሰል መድረክ መዘጋጀቱ ከጓዳ ያልወጡ አቅሞችን ወደ አደባባይ እንዲወጡ፣ የኢትዮጵያን ገጽታ እንዲያስተዋውቁ እና ለዜጎች በተለይም ለሴቶች የሥራ እድል የሚፈጥር በመሆኑ በመሆኑ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ገልጸዋል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ነጋሽ በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግብና መጠጦችን ለዓለም አቀፍ ማህበረሰብ እንዲተዋወቁ የጥናትና ምርምር እንዲሁም ሙያዊ የማማከር ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በዚህም በጥናት የተለዩ የኢትዮጵያውያን ባህላዊ ምግብና መጠጦች በኩሪፍቱ አፍሪካ ቪሌጅ መቅረባቸውን ገልጸዋል።

የኩሪፍቱ ሪዞርቶች ባለቤት አቶ ታድዮስ ጌታቸው የኩሪፍቱ አፍሪካ መንደር የኢትዮጵያ ባህላዊ ምግቦችን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ እያስተዋወቀ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
በፌስቲቫሉ ላይ ከሁሉም ክልሎች የተመረጡ የብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ምግቦች ቀርበዋል።

ፌስቲቫሉ በጥናት የተለዩ ባህላዊ ምግቦችን በማስተዋወቅ ወደ ገበታ እንዲመጡ ማድረግ፣ የእርስ በርስ ትውውቅን መፍጠር፣ የሀገር ገጽታ መገንባት እና የምግብ ቱሪዝምን ማሳደግ ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
በዝግጅቱ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የውጪ ሀገር አምባሳደሮች፣ ባለ ድርሻ አካላትና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
#ቱሪዝምማሰልጠኛኢንስቲትዩት

10/10/2025

Address

Addis Ababa
-

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Truth posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Truth:

Share

#ይኸ_ገጽ...

ዜና እና ዜና ትንታኔዎች ለእናንተ ለወዳጆቼ አጋራለኹ፡፡ ስለኑሮዬ፣ ስለውሎዬ… ምልከታዎቼን አሰፍራለኹ፡፡ የወደዳችሁት ላይክ በማድረግ ተከተሉኝ፣ ያልወደዳችሁት በጨዋ ደንብ ንቀፉኝ፣ ተቹኝ፣ ሞግቱኝ…እማርበታለሁና፡፡ ወዳጆቼ በሉ አብረን እንዝለቅ?!

ማንኛውንም አስተያየት፣ ጥያቄ በኢሜይል ቢያቀርቡልኝ መልሴ ፈጣን ነው፡፡

ፍሬው አበበ አደራ - ጋዜጠኛ

[email protected]