Ethiopian Truth

Ethiopian Truth በዚህ ገፅ ወቅታዊ ዜና፣ ትንታኔዎች እና መረጃዎች ይቀርቡበታል።/ This page provides current news & news analysis.

በአንድ በሬ የማረስ አስደናቂው የእስያ ተራራማ አካባቢዎች ባህላዊ ግብርና በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ በስፋት የሚዘዋወሩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በአንድ በሬ ወይም በአንድ የውሃ ጎሽ ብቻ በመጠቀ...
27/05/2026

በአንድ በሬ የማረስ አስደናቂው የእስያ ተራራማ አካባቢዎች ባህላዊ ግብርና

በማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ በስፋት የሚዘዋወሩ ተንቀሳቃሽ ምስሎች በአንድ በሬ ወይም በአንድ የውሃ ጎሽ ብቻ በመጠቀም ድንጋያማና ገደላማ በሆኑ የእርከን ማሳዎች ላይ የሚታረሱ አስደናቂ የግብርና ትዕይንቶችን እያሳዩ የብዙዎችን ትኩረት ይስባሉ።

ይሁን እንጂ ምስሎቹ ላይ የሚታዩት እጅግ ገደላማ መልክዓ ምድሮች፣ የገበሬዎቹ አለባበስ እና በጀርባቸው ያዘሏቸው ባህላዊ የቅርጫት ዓይነቶች ቦታው የደቡብ ምዕራብ ቻይና ተራራማ ግዛቶች ወይም የቪየትናም የገጠር መንደሮች መሆናቸውን ያረጋግጣሉ።

በእነዚህ የሩቅ ምስራቅ እስያ አካባቢዎች በአንድ እንስሳ ብቻ የመጫንና የማረስ ልማድ ለዘመናት የዘለቀ ስር የሰደደ ባህል ሲሆን፣ አሰራሩም ከአገራችን ባህላዊ የእርሻ ዘይቤ በእጅጉ የተለየና የራሱ የሆኑ አስገዳጅ ምክንያቶች ያሉት ነው።

በኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ መሬቱን በጥልቀት ለማረስ እና ከባድ የሆኑትን የእንጨት ማረሻዎች ለመጎተት የግድ ጥንድ ወይም ሁለት በሬዎችን መጥመድ የተለመደ አሰራር ነው። በአንጻሩ በእስያ ተራራማ አካባቢዎች የሚገኙ ገበሬዎች የሚጠቀሙባቸው ማረሻዎች እጅግ ቀላል፣ ከአንድ እንስሳ ጋር ብቻ በቀላሉ በገመድና በትናንሽ ቀንበሮች የሚገጣጠሙ በመሆናቸው አንድ ጠንካራ በሬ ወይም የውሃ ጎሽ ብቻውን ማሳውን በቀላሉ ሊያርሰው ይችላል።

ከዚህም በላይ እርሻዎቹ በተራራማ ሸለቆዎች ላይ የተሰሩ ጠባብ የእርከን መሬቶች በመሆናቸው፣ ሁለት በሬዎችን ጎን ለጎን አቁሞ ለማዞርና ለማረስ ምቹ አለመሆኑ ገበሬዎቹ ብቸኛ እንስሳትን የመጠቀም አማራጭ እንዲከተሉ አስገድዷቸዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ይህ ዓይነቱ ባህላዊ የእርሻ ዘዴ ረግረጋማና ጭቃማ በሆኑት የሩዝ ማሳዎች ላይ ለዘመናት ውጤታማነቱን አስመስክሯል ነው የተባለው። ገበሬዎቹ ከትውልድ ወደ ትውልድ ባስተላለፉት ጥበብ መሰረት እንስሳቱ ጠባብ በሆኑት የተራራ እርከኖች ላይ ሳይንሸራተቱና ሳይደናቀፉ በጥንቃቄ እንዲራመዱ ያሰለጥኗቸዋል።

ይህም አሰራር ሜካናይዝድ የሆኑ ትላልቅ ማሽነሪዎች በቀላሉ ሊገቡባቸው በማይችሉ ገደላማ ስፍራዎች ላይ ዋነኛ የምግብ ሰብል የሆነውን ሩዝ ለማምረት እስካሁን ድረስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል። ስለዚህ በቪዲዮዎቹ ላይ የሚታዩት አስደናቂ የአንድ በሬ እርሻዎች የእስያ ተራራማ አገራት ገበሬዎች ከተፈጥሮአዊ መልከዓ ምድር ጋር ተስማምተው ለመኖር የፈጠሩትን የቆየና የሚደነቅ ባህላዊ የግብርና ቅርስ ያሳያሉ።

ምንጭ :- መናኸሪያ ሬዲዮ

በትዳር አጋሯ ላይ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል ፈጽማ አስከሬኑን በሽንት ቤት ጉድጓድ ውስጥ በመቅበር ወንጀሉን ለመደበቅ የሞከረችው ግለሰብ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጣች። በምዕራብ ጎጃም ዞን ...
27/05/2026

በትዳር አጋሯ ላይ አሰቃቂ የግድያ ወንጀል ፈጽማ አስከሬኑን በሽንት ቤት ጉድጓድ ውስጥ በመቅበር ወንጀሉን ለመደበቅ የሞከረችው ግለሰብ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጣች።

በምዕራብ ጎጃም ዞን ደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የተፈጸመው ይህ አሰቃቂ ድርጊት በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ቁጣ መፍጠሩ ተገልጿል።

እንደ ምርመራ መዝገቡ መረጃ፤ የወንጀል ድርጊቱ የተፈጸመው በደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ለጀት ቀበሌ ልዩ ስሙ “ደብር” በተባለው አካባቢ ሲሆን፤ ተከሳሽ ወ/ሮ እታየሁ ታምር መሐሪ በትዳር አጋሯ በአቶ መንግስቱ አታላይ ላይ የግድያ ወንጀሉን ፈጽማለች።

ተከሳሿ “በተደጋጋሚ ይደበድበኛል” የሚል ቂም በመያዝ ባለቤቷ በተኛበት ሌሊት በመጥረቢያ አንገቱን ሁለት ጊዜ በመምታት ህይወቱ እንዲያልፍ ማድረጓ በምርመራ መረጃው ተመላክቷል።

ድርጊቱን ከፈጸመች በኋላም ወንጀሉን ለመደበቅ ስትል የሟቹን አስከሬን በአንሶላና በሸራ በመጠቅለል በመኖሪያ ግቢው ውስጥ በሚገኘው የሽንት ቤት ጉድጓድ ውስጥ በመክተት ቀብራዋለች። ወንጀሉ እንዳይገለጥም በጉድጓዱ ላይ አመድና አፈር በመጨመር ለመሸፈን መሞከሯ ታውቋል።

ሆኖም ከህዝብ በደረሰ ጥቆማ መነሻ የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ ባደረገው ተከታታይ ክትትልና ምርመራ የሟቹ አስከሬን ከተቀበረበት የሽንት ቤት ጉድጓድ ውስጥ ተገኝቶ ተከሳሿም ለህግ ቀርባለች።

የምዕራብ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ በኢፌድሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 539/1(ሀ) ስር “ከባድ ግድያ” በሚል ክስ መስርቶ ለፍርድ ቤት ያቀረበ ሲሆን፤ የምዕራብ ጎጃም ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤትም በግንቦት 13 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሿ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንድትቀጣ ውሳኔ ሰጥቷል።

የደምበጫ ዙሪያ ወረዳ የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ኢ/ር ጌትነት መኮንን እንደገለጹት፤ የወንጀሉ አሰቃቂነት ቢኖርም ፖሊስ ከህብረተሰቡ በተገኘ ጥቆማ መሰረት ቀንና ሌሊት በቁርጠኝነት በመስራት ወንጀሉን ሙሉ በሙሉ ማጋለጥ መቻሉን ገልጸዋል።

ኃላፊው አክለውም፤ መሰል የቤት ውስጥ ጥቃቶችና ወንጀሎች ከመፈጸማቸው በፊት በማህበረሰቡ ጥንቃቄና በፈጣን ጥቆማ መከላከል እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

መረጃው የምዕራብ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ ነው።

27/05/2026

ይሄ ፈረንጅ የዋዛ አይደለም

ከፍተኛ ደሞዝ ተከፋይ የይንቨርስቲ መምህሯ የይንቨርስቲ ጥበቃው ፕሮፖዝ አድርጓት ተቀበለችው ኡጋንዳፍቅር የት አለሽ ላላቹ ወዲህ ናት​በኡጋንዳ አንድ የጥበቃ ሰራተኛ የትራፊክ እንቅስቃሴን በሙ...
27/05/2026

ከፍተኛ ደሞዝ ተከፋይ የይንቨርስቲ መምህሯ የይንቨርስቲ ጥበቃው ፕሮፖዝ አድርጓት ተቀበለችው ኡጋንዳ
ፍቅር የት አለሽ ላላቹ ወዲህ ናት

​በኡጋንዳ አንድ የጥበቃ ሰራተኛ የትራፊክ እንቅስቃሴን በሙሉ ገትሮ፣ መኪናዎችና ፖሊሶች በደስታ እየጨበጨቡለት ለሚያፈቅራት ሴት በአውራ ጎዳና መሃል ተንበርክኮ የጋብቻ ጥያቄ አቅርቧል።

ወጣቱ የጥበቃ ሰራተኛ (ሴኩሪቲ) ሲሆን፣ ፍቅረኛው ደግሞ የዩኒቨርሲቲ መምህር (ሌክቸረር) ናት።

ጥበቃ ሰራተኛው ለ2 ዓመታት ያህል በምሽት የመምህርቷን መኖሪያ ቤት እንዲጠብቅ ተመድቦ ነበር። በዚህ መሃል ነው ፍቅር የያዛቸው።

መምህርቷ የጥበቃ ሰራተኛውን የጋብቻ ጥያቄ በደስታ የተቀበለችው ሲሆን፣ ወደፊትም ወጪውን ችላ እንደምታስተምረውና ትምህርቱን እንዲቀጥል እንደምታደርገው ቃል ገብታለታለች።

​"እውነተኛ ፍቅርና ታማኝነት የደረጃ ወይም የሙያ ልዩነት አይገድበውም!"

የመቄዶንያ ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎችና ዕቃዎች ገቡ፤ ባለ 27 ፎቅ ሕንፃ ግንባታ ሊጀመር ነው።[Ethiopian truth ግንቦት 18/2018]​ማኅበሩ በ...
26/05/2026

የመቄዶንያ ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎችና ዕቃዎች ገቡ፤ ባለ 27 ፎቅ ሕንፃ ግንባታ ሊጀመር ነው።

[Ethiopian truth ግንቦት 18/2018]

​ማኅበሩ በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ ግንባታው ለሚጀመረው ባለ 27 ፎቅ ሕንፃ የቁፋሮ ሥራ ማጠናቀቁን የገለጸ ሲሆን፥ ነገ ጋዜጠኞችና ጎብኚዎች ዕቃዎቹ ሲወርዱ እንዲመለከቱ ጥሪ አቅርቧል።

​የማኅበሩን የግንባታ አቅም በከፍተኛ ደረጃ የሚያሳድጉ 11 አዳዲስ ኮንቴይነሮች ትናንት የገቡ ሲሆን፥ እስካሁን ወደ ስፍራው የገቡት አጠቃላይ ኮንቴይነሮች ቁጥር 109 ደርሷል። በገበያ ዋጋ ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመቱት እነዚህ እንደ ሎደር፣ ታወር ክሬን እና ባቺንግ ፕላንት ያሉ ከባድ ማሽነሪዎች፤ ከተለያዩ አካላት በተደረገ ከፍተኛ ድጋፍ ማኅበሩ በ100 ሚሊዮን ብር ብቻ ሊገዛቸው ችሏል። ከተጠቀሱት ማሽነሪዎች በተጨማሪ 54 ኮንቴይነር የሚሆን ፖርሲሊንም መግባቱ ታውቋል።ታውቋል።

​ማኅበሩ ማሽነሪዎቹን በባለቤትነት ለመግዛት የወሰነው የግንባታ መሣሪያዎችን ተከራይቶ ከመሥራት ይልቅ ወጪን በከፍተኛ ሁኔታ ለመቀነስና ግንባታዎችን ሙሉ በሙሉ በራስ አቅም ለማከናወን በማሰብ ነው። በአሁኑ ወቅት ማኅበሩ በተለያዩ 15 ቦታዎች ላይ ግንባታዎችን እያካሄደ የሚገኝ ሲሆን፥ በአዲስ አበባ በ7,000 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ለሚያርፈው ባለ 27 ፎቅ አዲስ ሕንፃ ግንባታ የሚያስፈልገው የቁፋሮ ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቋል።

አሁን የገባው ታወር ክሬንም በቀጥታ ለዚሁ ሕንፃ ግንባታ የሚውል ይሆናል።

ወደፊትም ለሕንፃዎቹ ማጠናቀቂያ የሚሆኑ እንደ ሊፍት፣ መስታወትና የኤሌክትሪክ ዕቃዎች በሂደት እንደሚገቡ ተጠቁሟል።

​የገቡት ዕቃዎችና ማሽነሪዎች በብዛት ከመጣታቸው የተነሳ የማኅበሩ መጋዘኖች የሞሉ ሲሆን፥ ዕቃዎቹ በአሁኑ ወቅት በሜዳ ላይ ጭምር እየተራገፉ ይገኛሉ።

በመሆኑም ፍላጎት ያላቸው ጋዜጠኞችና ጎብኚዎች ዛሬ በ6 ሰዓት አካባቢ በስፍራው ቢገኙ፥ ዕቃዎቹ ከኮንቴይነር ሲወርዱ ለመታዘብና ስለ ማሽነሪዎቹ ምንነት በባለሙያ የሚሰጠውን ማብራሪያ በቀጥታ ለመከታተል እንደሚችሉ ማኅበሩ ጥሪውን አስተላልፏል።

ከቀድሞ ፍቅረኛሽ ጋር ግንኙነት አለሽ በሚል የገዛ ባለቤቱን አስር ጊዜ የሰውነት ክፍሎቿን በጩቤ በመውጋት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣበምስራቅ ጉጂ ዞን አዶላ ሬዴ ወረዳ ...
26/05/2026

ከቀድሞ ፍቅረኛሽ ጋር ግንኙነት አለሽ በሚል የገዛ ባለቤቱን አስር ጊዜ የሰውነት ክፍሎቿን በጩቤ በመውጋት የግድያ ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ

በምስራቅ ጉጂ ዞን አዶላ ሬዴ ወረዳ ዲለሌሣ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ደመና ዳካ የሠላሣ ዘጠኝ አመት ወጣት ነው። ደመና ከከድጃ ብርቢርሶ ከተባለች ወጣት ጋር በትዳር ተሣስሮ መኖር ከጀመረ ዓመታት አስቆጥርዋል።የጥንዶች ጋብቻ በቤተሠብ ምርጫ ላይ ያተኮረና በተለይ የሑለቱ ትዳር አመሰራረት ገና ከጅምሩ ቤተሠቦቻቸው ባላቸው ሐብትና ንብረት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ በሑለቱ ጥንዶች በኩል ለቤተሠብ ክብርና ፍላጐት ተብሎ እንጂ በመፈቃቀድ ላይ ያልተመሠረተ ነበር።

ለዚሕ ማረጋገጫ ደግሞ ከድጃ ቀደም ሲል በፍቅረኝነት የያዘችውና በጣም የምትወደው ሰው ነበር። ከዚሁ ሰው ጋር የነበራት የፍቅር ግንኙነት በአካባቢው የታወቀና በቤተሠብ መካከል ክፍተት የፈጠረ እንደነበር የዞኑ ፖሊስ ዋና መምርያ የሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ ክፍል ኃላፊ ምክትል ኮማንደር አዲስ ቶልቻ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።ይህ አለመግባባት ቢቀጥልም እስከ ጥር 5 ቀን 2018 ዓም የተፈጠረ ነገር የለም።ጥር 5 ከጠዋቱ አምስት ሠዓት ላይ ግን ከዚሕ በፊት የነበረው ጥርጣሬ ገሐድ ወጥቶ ባል በሚስት ላይ እርምጃ ለመውሠድ የተገደደበት ቀን ሆኗል።

ደመና ለፖሊስና ለአቃቢ ሕግ በሠጠው ቃል ከቅርብ ግዚያት ወዲሕ በትዳራቸው ደስተኛ አለመሆን የመጣው ባለቤቱ ከእኔ ጋር ያላት ግንኙነት እየቀዘቀዘ በመምጣቱ ነው ይላል። ባለቤቱ ከቀድሞ ፍቅረኛዋ ጋር ያላትን ግንኙነት በተጨባጭ ማስረጃ አረጋገጥኩ የሚለው ደመና ምሽት አምስት ሠዓት ላይ ባለቤቱ በእንቅልፍ ላይ እንዳለች በቅናት ስሜት ባዘጋጀው ስለታም ጩቤ አስር የተለያየ የሰውነት ክፍሎቿን በመውጋት ህይወቷ እንዲያልፍ ያደርጋል።

ደመና ይሕንን ድርጊት ፈፅሞ ወዲያው እጁን ለፖሊስ የሠጠ ሲሆን ፖሊስም የሟች አስክሬንን ለምርመራ ወደ ሆስፒታል በመላክ የምርመራ መዝገቡን በበቂ ማስረጃ በማጠናከር ለአቃቢሕግ ይልካል።አቃቢ ህግም በከባድ የሰው መግደል ወንጀል ክስ ይመሰርታል።ክሱን የተመለከተው የምስራቅ ጉጂ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓም በዋለው ችሎት ተከሣሽ ደመና ዳካ በ24 ዓመት እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን ምክትል ኮማደር አዲስ ቶልቻ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

በኤደን ሽመልስ

👉40 ዓመት የተጠበቀው ባል‼ “ሁልጊዜ ማታ ማታ በር ሲንኳኳ በአሉ የመጣ ይመስለኛል…”​መጠበቅ ለደቂቃዎች ሲሆን ይሰለቻል፤ ለ40 ዓመታት ሲሆን ግን ስቃይ ነው። የታላቁ ደራሲ በአሉ ግርማ ...
26/05/2026

👉40 ዓመት የተጠበቀው ባል‼

“ሁልጊዜ ማታ ማታ በር ሲንኳኳ በአሉ የመጣ ይመስለኛል…”

​መጠበቅ ለደቂቃዎች ሲሆን ይሰለቻል፤ ለ40 ዓመታት ሲሆን ግን ስቃይ ነው። የታላቁ ደራሲ በአሉ ግርማ ባለቤት ወ/ሮ አልማዝ አበራ፣ ባለቤታቸው በግፍ ከተሰወረበት 1976 ዓ.ም ጀምሮ እስከ እለተ ሞታቸው (2015 ዓ.ም) ድረስ በናፍቆት እስር ቤት ቆይተዋል።

​ወይዘሮ አልማዝ ለ40 ዓመታት በየቀኑ​ ቤታቸውን አፅድተውና አሳምረው ይጠብቁ ነበር።

​ባለቤታቸው በድንገት ቢመጣ በሩ ተዘግቶ እንዳያገኘው ደጃቸውን ክፍት አድርገው ይውሉ ነበር።

​ማንኛውም የበር መኳኳት "በአሉ መጣ" የሚል ተስፋና ድንጋጤ ይፈጥርባቸው ነበር።

​ሞቱ ባልተረጋገጠበት ሁኔታ "ይመጣል" የሚል ተስፋን ሰንቆ ለግማሽ እድሜ ያህል መጠበቅ ከመክበድም በላይ መከራ ነው።

የፊልም ባለሙያዎች ይህ እውነተኛ የፍቅር ታሪክ ለፊልማችሁ ፅሁፍ አንሶ ነው? እባካችሁ አስቡበት እናንተስ ምን ትላላችሁ ውድ ተከታዮቻችን?

​ምንጭ፦ ከተለያዩ የቅርብ ሰዎቻቸው እንዲሁም በEthiopian truth አዘጋጅ የቀረበ ለዚህ ፅሁፍ ማጣቀሻ የደራሲ ውድነህ ክፍሌ የጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠ ፅሁፎችን ሀሳብ ተጠቅመናል።

የሀገርና የስፖርት ክህደት ፈጽሟል፤ በኢንተርፖልም ቢሆን እናስመልሰዋለን» — ጌታቸው መለሰየማርሻል አርት ተወዳዳሪው ሴዶ ማርሻል (Sedo Martial) ወደ አውሮፓ (ቱርክ) መኮብለሉንና ለ...
26/05/2026

የሀገርና የስፖርት ክህደት ፈጽሟል፤ በኢንተርፖልም ቢሆን እናስመልሰዋለን» — ጌታቸው መለሰ

የማርሻል አርት ተወዳዳሪው ሴዶ ማርሻል (Sedo Martial) ወደ አውሮፓ (ቱርክ) መኮብለሉንና ለመመለስ የ70 ሚሊዮን ብር ቅድመ-ሁኔታ ማስቀመጡን ተከትሎ፣ የውድድሩ አዘጋጅ ጌታቸው መለሰ ጠንከር ያለ ምላሽ ሰጥቷል።

ጌታቸው ባሰራጨው ይፋዊ የቪዲዮ መግለጫ፣ የሴዶን ድርጊት «የሀገርና የስፖርት ክህደት» ሲል ኮንኖታል።

ጌታቸው መለሰ በሰጠው መግለጫ፣ ሴዶ ማርሻል በሀገር ላይ ትልቅ ክህደት ፈጽሞ ከአገር መውጣቱን በምሬት ገልጿል። «ድርጊቱ በሀገር ላይ ብቻ ሳይሆን በጥቅሉ በስፖርቱም ላይ የተፈጸመ ትልቅ ክህደት ነው» ያለው አዘጋጁ፣ ስፖርተኛው የገባውን ውልና ቃል አጥፎ በምስጢር መኮብለሉ ከፍተኛ ቅሬታ እንዳሳደረበት አስታውቋል።

ሴዶ ማርሻል የፈለገውን ያህል ቢሸሽም ተጠያቂነት እንደማያመልጠው ያመለከተው ጌታቸው፣ ህጋዊ እርምጃዎችን መውሰድ መጀመሩን ጠቁሟል። «ምንም ማድረግ ባንችልም፣ በዓለም አቀፉ የፖሊስ ተቋም (Interpol) በኩልም ቢሆን ወደ ሀገር እንዲመለስ የበኩላችንን ጥረት እናደርጋለን» ሲል ስፖርተኛውን በህግ ተከታትሎ ለመያዝ ማቀዱን በይፋ አስታውቋል።

ይህ የአዘጋጆቹ ቁጣ የተቀሰቀሰው፣ ተወዳዳሪው ሴዶ ማርሻል በቱርክ አውሮፕላን ማረፊያ ሆኖ ባስተላለፈው ምስል «አውሬው አምልጧል፤ በነጻ ልታደባድቡኝ ነበር» በሚል የ70 ሚሊዮን ብር (የ20 ሚሊዮን ብር መኪና፣ የ30 ሚሊዮን ብር ቤት እና 20 ሚሊዮን ብር ጥሬ ገንዘብ) ቅድመ-ሁኔታዎችን ካቀረበ በኋላ ነው።

ይህ በሁለቱ ወገኖች መካከል የተፈጠረው ፍጥጫ እና የ«ክህደት» ክስ በቀጣይ እንዴት እንደሚቋጭና በስፖርቱ ማህበረሰብ ዘንድ ምን ዓይነት መነቃቃትን እንደሚፈጥር ጉዳዩን በቅርበት እየተካታተልን የምናደርሳችሁ ይሆናል።

የድምፃዊ ቴዲ አፍሮ መልእክትበሀገር ውስጥና በመላው ዓለም ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታይኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል ዓዷሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ ...
26/05/2026

የድምፃዊ ቴዲ አፍሮ መልእክት

በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም ለምትገኙ የእስልምና እምነት ተከታይኢትዮጵያዊያን ወገኖቻችን በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል ዓዷሃ (አረፋ) በዓል አደረሳችሁ የሚል መልእክቴን እያስተላለፍኩ በዓሉ የሰላምና የፍቅር እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልጻለሁ፡፡

መልካም በዓል!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር! ፍቅር ያሸንፋል!

ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)

በዛሬው የኢትዮጵያ ዋንጫ የተፈጠረ አነጋጋሪ ክስተት የኢትዮጵያ መድን አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ ያሬድ ካሳዬን 33ኛ ደቂቃ ላይ ቀይረው አስወጥተዋል... ተጨዋቹ ተቀይሮ ሲወጣ በብስጭት ማል...
26/05/2026

በዛሬው የኢትዮጵያ ዋንጫ የተፈጠረ አነጋጋሪ ክስተት

የኢትዮጵያ መድን አሰልጣኝ ገብረመድህን ሀይሌ ያሬድ ካሳዬን 33ኛ ደቂቃ ላይ ቀይረው አስወጥተዋል...

ተጨዋቹ ተቀይሮ ሲወጣ በብስጭት ማልያውን አውልቆ መሬት ወርውሮታል...

ተቀያሪ ወንበር ላይ ተቀምጦም አሰልጣኙን ሲሳደብ ተስተውሏል።

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን እየወከለ የሚገኘው ያሬድ በርካታ ታዳጊዎች በሚከታተሉት ጨዋታ ላይ ያሳየው ስነምግባር በርካቶችን አስቆጥቷል።

ምንጭ:- ሸገር ስፖርት አሬና

በተጨዋቹ ባህሪ ምን ተሰማችሁ

ዓለም አቀፉ የሶሻል ሚዲያ ይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ ***************በማህበራዊ ሚዲያ ገጾቹ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮች ያሉት ታዋቂው ዓለም አቀፍ የይዘት ፈጣ...
26/05/2026

ዓለም አቀፉ የሶሻል ሚዲያ ይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ
***************

በማህበራዊ ሚዲያ ገጾቹ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ተከታዮች ያሉት ታዋቂው ዓለም አቀፍ የይዘት ፈጣሪ ዲላን ፔጅ በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ በመገኘት አስደናቂ የቆይታ ጊዜን አሳልፏል።

ዲላን ፔጅ በሐረር ቆይታው የከተማዋ ልዩ መገለጫ እና ዋነኛ የቱሪስት መስህብ የሆነውን ጅቦችን በምሽት የመመገብ ባህላዊ ትዕይንት በአካል ተገኝቶ ተሳትፎበታል።

ይህ ልዩ ሁነት የኪነ-ህንጻ እና የታሪክ መዲና በሆነችው ሐረር የሚታየውን የሰው እና የዱር አራዊት መቻቻልና ተፈጥሯዊ ትስስር እንዲሁም የማህበረሰቡን ድንቅ እንግዳ ተቀባይነት ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በድጋሚ በስፋት ያስመሰከረ አጋጣሚ መሆኑን የቱሪዝም ሚኒስቴር ያወጣው መረጃ ያመላክታል።

Address

Addis Ababa
-

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Truth posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Truth:

Share