Ethio Press

Ethio Press Media-ሚዲያ
ዜና - መዝናኛ -ታሪክ - ጤና - ማህበራዊ ጉዳይ
ወ. ዘ. ተ.
ታማኝ እና ፈጣን-የሁሉም ለሁሉም
(5)

‘’ኧረ በገብርኤል! ኧረ በገብርኤል! ምን አይነት ስህተት ነው የሠራነው? ምን አይነት ታክቲክ ነው የተጠቀምነው? አትሌቶቻችን  ከአሰልጣኞቻቸው  ጋር ምንድን ነው የተነጋገሩት? ’’ ፍቅር ይ...
15/09/2025

‘’ኧረ በገብርኤል! ኧረ በገብርኤል!

ምን አይነት ስህተት ነው የሠራነው?

ምን አይነት ታክቲክ ነው የተጠቀምነው?

አትሌቶቻችን ከአሰልጣኞቻቸው ጋር ምንድን ነው የተነጋገሩት? ’’

ፍቅር ይልቃል ከጃፓን ቶኪዮ የ3000 መሰናክል ፍጻሜን በቀጥታ በዘገበበት ወቅት የተናገረው!

እሱም አስቀድሞ እንደተናገረው የኢትዮጵያን አትሌቲክስ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ሁኖ መዘገብ ፈተና ነው፡፡

የሀገር ፍቅር ስሜት፣ ንዴት፣ እልህ፣ ቁጭት……ደምሴ ዳምጤን ነበር ያስታወሰኝ፡፡

የደምሴ አንዲያ እያነቀው ቢዘግብም ወርቁን አይቶ ፈንድቋል፡፡ የፍቅር ስሜት የብዙዎቻችን ስሜት፣ የእሱ እንቆቅልሽ የሁላችንም እንቆቅልሽ ይመስለኛል፡፡

ኢትዮጵያ በዓለም ፊት የሚያቆማትን ብቸኛ የሚባል መድረክ ቀስ በቀስ እያስረከበች ነው፡፡ ታሪክ ሁኖ ሊቀር ነው እንዴ ጎበዝ?

ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በሕይወት ባለባት ሀገር?

እኔ ተንታኝ ስላልሆንሁ ዝም ልበል፡፡

እውነት ምን ሁነን ነው?
* * *
መስከረም ጌታቸው

የ12ኛ ክፍል ውጤት ተለቋልየውጤት መመለከቻ አማራጮች 👇ዌብ ሳይት፡- https://result.eaes.et ቴሌገራም፡- https://t.me/EAESbotአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡- 62...
15/09/2025

የ12ኛ ክፍል ውጤት ተለቋል

የውጤት መመለከቻ አማራጮች 👇
ዌብ ሳይት፡- https://result.eaes.et
ቴሌገራም፡- https://t.me/EAESbot
አጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡- 6284

" የጄኔራል ታደሰ ወረደ አስተዳደር በጠባቡ የህወሀት ቡድን ቁጥጥር ስር ወድቋል"   የትግራይ ምሁራን ማህበር ------------------------------------ግሎባል ሶሳይቲ ኦፍ ት...
15/09/2025

" የጄኔራል ታደሰ ወረደ አስተዳደር በጠባቡ የህወሀት ቡድን ቁጥጥር ስር ወድቋል"
የትግራይ ምሁራን ማህበር
------------------------------------
ግሎባል ሶሳይቲ ኦፍ ትግሪያን ስኮላርስ(ጂ ኤስ ቲኤስ) ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ በክልሉ ውስጥ ‹‹የሰብአዊ መብት ጥሰቱ በከፋ ሁኔታ ላይ ይገኛል›› ብሏል፡፡

ለተመድ የሰብአዊ መብት ምክር ቤት፣ ለመንግስታቱ ድርጅት የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር፣ በአዲስ አበባ ለሚገኙ የዲፕሎማቲክ አባላት፣ ለአፍሪካ ህብረት የሰብአዊ መብትና የሰዎች ኮሚሽንና ለአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋማት በላከው በዚህ ደብዳቤ ጉዳዩ አፋጣኝ መልስ እንደሚያስፈልገውም አሳስቧል፡፡

ጂ ኤስ ቲኤስ በዚህ ደብዳቤው በሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ የሚመራው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ‹‹በህወሀት ውስጥ ባለው ጠባብ የፖለቲካ ቡድን ቁጥጥር ውስጥ ወድቋል፡፡›› በሚል የገለፀ ሲሆን ይህም የፕሬዝደንቱን የውሳኔ ሰጪነት ሚና ዝቅ እንዳደረገው አስረድቷል፡፡ በቀድሞው ፕሬዝደንት ጌታቸው ረዳ የተመዘገቡት የሚዲያ ነፃነት፣ በነፃነት የመንቀሳቀስና ፖለቲካዊ ተሳትፎዎች በሙሉ በዚህ ጠባብ ባለው ቡድን አማካኝነት ወደኋላ መመለሳቸውን የጠቀሰው ጂ ኤስ ቲኤስ፣ ጨምሮም በደቡባዊ ትግራይ፣ በደቡብ ምስራቅ ዞን፣ በተምቤንና ሰሜን ምእራብ ትግራይ መጠነ ሰፊ በደሎች እየተፈፀሙ መሆናቸውን አስረድቷል፡፡

ከእነዚህም መካከል የሰዎች በሀይል መሰወር፣ ከፍርድ ቤት ትእዛዝ ውጭ መታሰር፣ የዘፈቀደ ግድያ፣ ካለህግ አግባብ ከስልጣን መባረር፣ ማስፈራራት እስርና ራስን በራስ የማስተዳደር መብትን ማፈን እንደሚገኙበት ጠቅሷል፡፡ ጂ ኤስ ቲኤስ ሲቀጥልም ‹‹የህወሀት ጠባብ ቡድን የመንግስት ሰራተኞችን ከስራ በማባረር፣ ተቃውሞን በማፈንና በወታደራዊ ሀይሎች የሰዎችን የመንቀሳቀስ መብት በመገደብ ፖለቲካዊ የማፅዳት እርምጃ እየወሰደ ነው›› ያለ ሲሆን ጨምሮም ይህ ቡድን ‹‹መጠነ ሰፊ የመሬት ዘረፋ፣ ህገ ወጥ የወርቅ ማውጣት፣ ህገ ወጥ ንግድ፣ ኮንትሮባንድ፣ ህገ ወጥ የሰዎች ዝውውርና የህዝብ ሀብት ዘረፋ ላይ ተሰማርቷል›› ሲል ዘርዝሯል፡፡

‹‹እነዚህ ጥሰቶች የህግ የበላይነትን ያዳክማሉ፣ ፖለቲካዊ ጠባብነትን ያመላክታሉ፣ አለመረጋጋትን ያባብሳሉ፣ ቨትግራይ ህዝብ ላይም ከባድና አስከፊ ስቃይን ያደርሳሉ›› ያለው ጂ ኤስ ቲኤስ፣ አለም አቀፍ ተቋማት እነዚህን የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንዲያወግዙም ጥሪ አቅርቧል፡፡ በጉዳዩ ላይ በገለልተኛ አካል ምርመራ እንዲደረግ ግፊት እንዲያደርጉም ጠይቋል፡፡ በተጨማሪም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ሰላማዊ ዜጎችን ለማፈን ወታደራዊ ሀይልን መጠቀሙን እንዲያቆም አለም አቀፍ ተቋማቱ ማሳሰቢያ እንዲሰጡ ጥሪ አስተላልፏል፡፡

አለም አቀፍ ድርጅቶች በዚህ ጉዳይ ላይ ለሚያደርጉት ምርመራ መረጃ ለመስጠትና ለመተባበር ፈቃደኛ መሆኑንም የጂ ኤስ ቲኤስ ደብዳቤ አስታውቋል፡፡

ዘሐበሻ

ቲክቶክ ሊታገድ 2 ቀናት ብቻ ቀርተውታል❗በአሜሪካ ከ170 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች ያሉት የቻይና ቴክኖሎጂ ካምፓኒ ባይትዳንስ ስሪት “ቲክቶክ” ፤ በአሜሪካ ለሦስተኛ ጊዜ የተራዘመለት እገዳ ...
15/09/2025

ቲክቶክ ሊታገድ 2 ቀናት ብቻ ቀርተውታል❗

በአሜሪካ ከ170 ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎች ያሉት የቻይና ቴክኖሎጂ ካምፓኒ ባይትዳንስ ስሪት “ቲክቶክ” ፤ በአሜሪካ ለሦስተኛ ጊዜ የተራዘመለት እገዳ ሊጠናቀቅ የሁለት ቀናት ዕድሜ ቀርተውታል።

ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቲክቶክ በአሜሪካ ይፈጥራል ባሉት የብሔራዊ ደህንነት አደጋ ሙሉ በሙሉ ይታገዳል የሚል ሀሳብ ሲያቀርቡ ቆይተው በኋላም በአሜሪካ ገዢ ይገኝለታል ወደሚል ቀይረውታል።

ትራምፕ ቲክቶክን ሊገዛ የሚችል የቱጃሮች ቡድን አለኝ ብለው የነበረ ቢሆንም በአሜሪካ እና በቻይና መካከል ባለው የንግድ ውዝግብ ምክኒያት እስካሁን ገዢ ሳያገኝ ቆይቶ ሦስተኛው ዕገዳው ሊጠናቀቅ ሁለት ቀናት ብቻ ቀርተውታል።

ትራምፕ እሁድ ዕለት ለጋዜጠኞች እንዳሉት "ቲክቶክን እንዲሞት ልንተወው እንችላለን። ወይንም ደግሞ... አላውቅም። ሁኔታዎች አሁን በቻይና ላይ የተመሠረቱ ነው። ብዙም ግድ የሚሰጥ ጉዳይ አይደለም " ማለታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።

ቲክቶክ በአሁን ወቅት በ23 አገራት ውስጥ ሙሉ እና ከፊል እገዳ ተጥሎበት ይገኛል።

ከፊል እገዳ ከጣሉበት መካከል ብሪታኒያን ጨምሮ የአውሮፓ ሕብረት አገራት እና አውስትራሊያ ይገኙበታል።

ትራምፕ በአሜሪካ ሙሉ በሙሉ ቲክቶክ ላይ እግድ ካስተላለፉ እነዚህ አገራትም ቲክቶክን ሙሉ በሙሉ የሚያግዱበት ሁኔታ መኖሩን ከዚህ ቀደም ብለው የወጡ ጥናቶች ያመላክታሉ።

ይህ በእንዲህ እያ'ለ ግን ከሁለት ቀናት በኋላ ዕገዳው ይጸናል ወይስ ለአራተኛ ጊዜ ይራዘማል የሚለው ጉዳይ በበርካታ አሜሪካዊያን ዘንድ በጉጉት የሚጠበቅ ውሳኔ ነው፡፡

ARTS WORLDWIDE

በአዲስ አበባ "ሿሿ" ወንጀል የሚፈጽሙ 10 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ❗------------------------የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ፣ ተሳፋሪ መስለው በተደራጀ መልኩ የማታለ...
15/09/2025

በአዲስ አበባ "ሿሿ" ወንጀል የሚፈጽሙ 10 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ❗
------------------------
የአዲስ አበባ ፖሊስ ባወጣው መግለጫ፣ ተሳፋሪ መስለው በተደራጀ መልኩ የማታለል (ሿሿ) ወንጀል ሲፈጽሙ የነበሩ 10 ግለሰቦች ከነሚኒባስ ታክሲያቸው መያዛቸውን አስታወቀ።

ተጠርጣሪዎቹ በቦሌ ክ/ከተማ ባምቢስ አካባቢ መያዛቸው የተገለጸ ሲሆን፣ በፒያሳ፣ አውቶብስ ተራ፣ አብነት፣ ጥቁር አንበሳ እና ሌሎች አካባቢዎች ወንጀሉን ሲፈጽሙ እንደነበር ታውቋል።

ተጠርጣሪዎቹ ታክሲ ሞልተው ከሄዱ በኋላ "አንድ የቀረ" በማለት ተሳፋሪዎችን አስገብተው፣ "ትራፊክ መጣ" ወይም "ውረድ" በማለት ግራ በማጋባት ገንዘብ፣ ስልክ እና ሌሎች ንብረቶችን እንደሚሰርቁ የግል ተበዳዮች መስክረዋል።

ከዚህ ቀደምም በተመሳሳይ ወንጀል አንዲት ግለሰብ ስልክ እንደተወሰደባት እና የተሽከርካሪውን ሰሌዳ ቁጥር ለፖሊስ መስጠቷ ተገልጿል።

ፖሊስ እስካሁን 4 ስማርት ስልኮች እንደተገኙና ሁለት ተበዳዮች ንብረታቸው እንደተወሰደባቸው ማረጋገጣቸውን ገልጿል።

በመሆኑም፣ በተመሳሳይ መንገድ ንብረት የተሰረቃችሁ ግለሰቦች ወደ የካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ በአካል ቀርበው ተጠርጣሪዎቹን በመለየት ንብረታችሁን እንድትረከቡ ጥሪ ቀርቧል።

የታክሲ ተጠቃሚው ህብረተሰብ ጥንቃቄ እንዲያደርግ እና አጠራጣሪ ነገር ሲመለከት ለፖሊስ እንዲጠቁም መልዕክት ተላልፏል።

AAP

የወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል የፍፃሜ ውድድር  ዛሬ ይካሄዳል! ዛሬ ቀን 9:55 ጀምሮ ይካሄዳል🥇🥈🥉🇪🇹ለሜቻ ግርማ 🇪🇹ሳሙኤል ፍሬው🇪🇹ጌትነት ዋለ- ኢትዮጵያ በአለም ሻምፒዮና የተሳትፎ ታ...
15/09/2025

የወንዶች 3000 ሜትር መሰናክል የፍፃሜ ውድድር ዛሬ ይካሄዳል!

ዛሬ ቀን 9:55 ጀምሮ ይካሄዳል🥇🥈🥉

🇪🇹ለሜቻ ግርማ

🇪🇹ሳሙኤል ፍሬው

🇪🇹ጌትነት ዋለ

- ኢትዮጵያ በአለም ሻምፒዮና የተሳትፎ ታሪኳ በሁለቱም ፆታዎች በ3ሺ ሜትር መሰናክል የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታ አታውቅም።

- ኬንያ በ3ሺ ሜትር መሰናክል በወንዶች 13 ጊዜ የወርቅ ሜዳሊያ በማሸነፍ ስኬታማዋ ሃገር ናት።

- የርቀቱ የወቅቱ የአለም የክብረወሰን ባለቤት 🇪🇹ለሜቻ ግርማ ዶሃ፣ዩጂን እና ቡዳፔስት ላይ ያስመዘገበውን የብር ሜዳሊያ ክብር ወደ ወርቅ ከፍ ለማድረግ ይፋለማል።

- ሞሮኳዊው ሶፊያን ኤል ባካሊ የዩጂን እና ቡዳፔስት አለም ሻምፒዮና ክብሩን ለማስጠበቅ ይወዳደራል።

በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለአሸናፊነት የሚጠበቁበት የወንዶች 10ሺህ ሜትር ፍጻሜ ዛሬ ይደረጋል፡፡ቀን 9 ሰዓት ከ30 በሚጀምረው ውድድር አትሌት በሪሁ አረ...
14/09/2025

በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ለአሸናፊነት የሚጠበቁበት የወንዶች 10ሺህ ሜትር ፍጻሜ ዛሬ ይደረጋል፡፡

ቀን 9 ሰዓት ከ30 በሚጀምረው ውድድር አትሌት በሪሁ አረጋዊ፣ ሰለሞን ባረጋ እና ዮሚፍ ቀጀልቻ በርቀቱ ኢትዮጵያን ይወክላሉ፡፡

በሌላ በኩል ቀን 9፡05 የሴቶች 1500 ሜትር የግማሽ ፍጻሜ ውድድር የሚደረግ ሲሆን፥ በርቀቱ አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ ትሳተፋለች፡፡

ኢትዮጵያ እስካሁን በተሳተፉባቸው ርቀቶች በሴቶች ማራቶን በትዕግስት አሰፋ የብር ሜዳልያ እንዲሁም በሴቶች 10ሺህ ሜትር በጉዳፍ ጸጋይ የነሃስ ሜዳልያ አግኝታለች፡፡

"ኢትዮጵያ ችላለች"በሚል መሪ ቃል የህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ ድጋፉንና ደስታውን ለመግለፅ በመስቀል አደባባይ የድጋፍ ሰልፍ በማካሄድ ላይ ነው::
14/09/2025

"ኢትዮጵያ ችላለች"በሚል መሪ ቃል የህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን ምክንያት በማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ ድጋፉንና ደስታውን ለመግለፅ በመስቀል አደባባይ የድጋፍ ሰልፍ በማካሄድ ላይ ነው::

አትሌት ትዕግስት አሰፋ የመጀመሪያውን የብር ሜዳሊያ ለሀገሯ አስገኘች❗በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሴቶች ማራቶን ውድድር አትሌት ትዕግስት አሰፋ 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።አትሌ...
14/09/2025

አትሌት ትዕግስት አሰፋ የመጀመሪያውን የብር ሜዳሊያ ለሀገሯ አስገኘች❗

በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የሴቶች ማራቶን ውድድር አትሌት ትዕግስት አሰፋ 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።

አትሌት ትዕግስት ከኬንያዊቷ አትሌት ፔሬስ ጅፕችርችር ጋር ብርቱ ፉክክር አድርጋ ነው የብር ሜዳሊያ ለሀገሯ ያስገኘችው።

በሴቶች ብቻ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤቷ ትዕግስት አሰፋ ርቀቱን ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት 24 ደቂቃ ከ45 ሰከንድ ወስዶባታል።

ኬንያዊቷ ፔሬስ ጂፕቸርቸር ውድድሩን በቀዳሚነት በማጠናቀቅ የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች።

በነገው እለት በአዲስ አበባ መንገዶች ዝግ ይሆናሉ!!የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ ነገ በመስቀል አደባባይ ለሚደረገው የድጋፍ ሰልፍ የተወሰኑ መንገዶች ዝ...
13/09/2025

በነገው እለት በአዲስ አበባ መንገዶች ዝግ ይሆናሉ!!

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ ነገ በመስቀል አደባባይ ለሚደረገው የድጋፍ ሰልፍ የተወሰኑ መንገዶች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

የድጋፍ ሰልፍ መርሀ ግብሩን ምክንያት በማድረግ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይከሰት በከተማው የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል።

በዚህም መሠረት ከመስከረም 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ የድጋፍ ሰልፉ እስከሚያልቅ ድረስ የሚከተሉት መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ማቆም እንዲሁም ዝግ ይደረጋሉ ተብሏል።

◇ከልደታ ፍርድ ቤት ወደ መስቀል አደባባይ ሜክሲኮ አደባባይ ላይ
◇ከአትላስ ወደ ቅዱስ ዑራኤል ፒኮክ መብራት ላይ

◇ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ ጠማማ ፎቅ ላይ

◇ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መስቀለኛ ላይ)

◇ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)

◇ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)

◇ከሜትሮሎጂ ወደ ብሔራዊ ቲያትር ጎማ ቁጠባ መብራት ላይ

◇ ከተክለ ኃይማኖት አደባባይ በኢምግሬሽን ጥቁር አንበሳ ላይ

◇ከንግድ ማተሚያ ወደ ፍልውሃ ንግድ ማተሚያ መስቀለኛ ላይ

◇ከቸርችል ወደ ጥቁር አንበሳ መብራት ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ

◇ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ፓርላማ መብራት

◇ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት ሀራምቤ መብራት ላይ

◇ ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሀር መብራት

◇ ከሰንጋ ተራ 40/60 ወደ ለገሃር ሠንጋ ተራ 40/60 መታጠፊያ ላይ

◇ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ሠንጋ ተራ መብራት ሜክሲኮ አደባባይ ላይ

◇ከአረቄ ፋብሪካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ አረቄ ፋብሪካ መስቀለኛ ላይ

◇ከልደታ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ባልቻ ሆስፒታል መታጠፊያ ላይ

◇ ከቫቲካን ኤምባሲ ወደ ሳር ቤት አደባባይ ሳር ቤት አደባባይ ላይ

◇ከቅዱስ ዮሴፍ ወደ መስቀል አደባባይ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ

♡ ከቅዱስ ቂርቆስ ታቦት ማደሪያ ወደ ለገሃር ቅዱስ ቂርቆስ ታቦት ማደሪያ መብራት ላይ መንገዶቹ የሚዘጉ መሆኑ ታውቋል።

በተጠቀሱት መስመሮች ላይ ከዛሬ መስከረም 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽት 12፡00 ሠዓት ጀምሮ ተሽከርካሪን አቁሞ መሄድ ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል፡፡

 #ሚድሮክ" በዋጋ ግሽበት ድሃው ማህበረሰብ እንዳይሰቃይ የምናደርግበትን በተለይም የግብርና ስራዎች ላይ በሰፊው ስሩ " - ሼይኸ መሀመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2...
13/09/2025

#ሚድሮክ
" በዋጋ ግሽበት ድሃው ማህበረሰብ እንዳይሰቃይ የምናደርግበትን በተለይም የግብርና ስራዎች ላይ በሰፊው ስሩ " - ሼይኸ መሀመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በ2017 ዓ.ም ያከናወናቸውን ተግባራት እና ገጥመውት የነበሩ ችግሮችን የሚያሳይ አጠቃላይ አመታዊ የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ዓመታዊውን የቤተሰብ ቀን ሲያከብር አቅርቧል።

ሪፖርቱን ያቀረቡት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የእቅድና ሪፖርት ኮርፖሬት ዳይሬክተር አቶ አክሊሉ ሙሉጌታ በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች የሚስተዋሉት የጸጥታ ችግሮች በስራቸው ላይ ጫና አሳድረውባቸው እንደነበር ገልጸዋል።

አክለው " የብድር አገልግሎት ማግኘት ተቸግረን ነበር፣ ስናገኝም የወለድ ምጣኔያቸው ከፍ ማለት ተጽዕኖ አሳድሮብን ነበር " ብለዋል።

በዚህ ስነ ስርዓት ላይ 588 ለሚሆኑ ግንባር ቀደም ሰራተኞቹ ከ100ሺ እስከ 500ሺ ብር የገንዘብ ሽልማት እና እውቅና ሰጥቷል።

ዳይሬክተሩ በዝርዝር ምን አሉ ?

" በተጠናቀቀው በጀት አመት የደሴ፣ የነቀምት፣ የአሶሳና የሰመራ የዱቄት ፋብሪካዎች ግንባታ ተጠናቆ ተመርቋል። ለ6ሺህ ሰዎች በአራት የምገባ ማዕከላት በሚደረግ ድጋፍ ከ53 ሚሊዮን ብር በላይ ወጭ አድርገናል።

በማኑፋክቸሪንግ፣ ማይኒንግ እና በሆቴልና ሪዞርት ዘርፎች ከእቅድ ከፍ ያለ የሽያጭ አፈጻጸም ታይቷል፡፡ በተጨማሪም ሁሉም ዘርፎች አትራፊ ሆነዋል። ከአግሮ፣ ኮሜርስ፣ ከኮንስትራክሽን እና ሪል እስቴት በቀር ሁሉም ካቀዱት በላይ ትርፍ አስመዝግበዋል።

ከድርጅቶቻችን ሽያጭና ትርፍ አፈፃፀም ሆራይዘን ፕላንቴሽን የሽያጭ እቅዱን ሙሉ በሙሉ አሳክቷል፡፡ ከኢትዮ አግሪ ሴፍት በቀር በሁሉም ኩባንያዎች ካለፈው አመት የተሻለ ሽያጭ አላቸው፡፡

በማኑፋክቸሪንግ ክላስተር ከእቅድ አንጻር ከሞሃ እና ማያ ፒፒ በቀር ሁሉም ከፍ ያለ ሽያጭ ነበራቸው። ካለፈው በጀት አመት ጋርም ሲነጻጸር ከማምኮ በቀር ሁሉም ከፍ ያለ አፈጻጸም አሳይተዋል፡፡

በተጠናቀቀው በጀት አመት ከሚድሮክ ኮንስትራክሽን እና ሚድሮክ ፋውንዴሽን በቀር ሁሉም ኩባንያዎች ከዕቅድ በላይ አትርፈዋል፡፡ ካባለፈው አመትም የተሻለ አፈጻጸም አሳይተዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ 263 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ የተገኘ ሲሆን፣ ይህም ከዕቅዱ 136 በመቶ እና ካለፈው ዓመት 39.6 በመቶ ብልጫ አለው። 75 በመቶ የሚሆነው የውጭ ምንዛሬ የተገኘው ከማዕድን ዘርፍ ነው።

1.1 ቢሊዮን ብር ለማህበራዊ አገልግሎት ወጪ ተደርጓል። ይህም አራት የዳቦና ዱቄት ፋብሪካዎችን ለማጠናቀቅ፣ ለምግብ ማዕከላት፣ ለኩላሊት እጥበት ማሽን ግዢ እና ለሌሎች ማህበራዊ ግንባታዎች የዋለ ነው።

በቋሚነት፣ በኩንትራት እና በጊዜያዊነት ተቀጥረው ለሚሰሩ ከ79 ሺህ በላይ ለሚሆኑት ሰራተኞቹ ለደሞዝ ብቻ 6.9 ቢሊዮን ብር ወጪ አድርጓል። " ብለዋል።

መርሃ ግብሩን በበየነ መረብ ቀጥታ ስርጭት እየተከታተሉ የነበሩት የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ባለቤት እና ሊቀመንበር ሼይኸ መሀመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በንግግራቸውም " የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አልቆ በመመረቁ እኛም ለልማታችን ስለምንፈልገው ደስ ብሎኛል፣ መላው የኢትዮጵያ ህዝብም እንኳን ደስ አላችሁ " ብለዋል።

አክለው " በሚድሮክ ላይ ባለፉት 5 አመታት በተደረገ ትግል እና ልፋት አሁን የተገኘው ውጤት በጣም የሚያኮራ ነው። ነገር ግን በቀጣይ የሚድሮክ ሰራተኞች ቁጥር እንዲጨምር እፈልጋለሁ " ሲሉ ነው የተናገሩት።

" ለወደፊቱም አዳዲስ ሜጋ ፕሮጀክቶች እየተሰሩ ነው፣ ያ ማለት የሰራተኞች ቁጥር ይጨምራል። ምኞቴም ኢትዮጵያ ውስጥ Middle class ማህበረሰብ እንዲኖር ነው። በሚድሮክ ላይ ተሳተፉ መልካም ነው፣ እኛም ሀገሪቱንም እንጠቅማለን " ሲሉ ገልጸዋል።

" አሁን የተገኘው ውጤት በሰራተኞች እና በስራ ሃላፊዎች ልፋት ነው፣ አሁንም በርቱ ነው " ያሉት።

" በዋጋ ግሽበት ድሃው ማህበረሰብ እንዳይሰቃይ የምናደርግበትን በተለይም የግብርና ስራዎች ላይ በሰፊው ስሩ። የኢትዮጵያ ህዝብም ይጠቀማል፣ አሁንም ወደፊትም ምኞቴ ይሄ ነው። በተገኘው ውጤት ደስ ብሎኛል አመሰግናለሁ " ብለዋል።

" የሚቀጥሉት አምስት አመታት ሰፊ እና ታላቅ ናቸው። አመራሮች ታውቁታላችሁ ዝርዝር አያስፈልግም፣ ሚድሮክ ይዞት የነበረው አላማ ይህ ብቻ አይደለም ይቀጥላል " ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ

ጉዳፍ ፀጋዬ ቅሬታዋን ገለፀች-------------------------------------"....ተነጋግረን ገብተን አለመተግበር አለ ። ዝምብለን የራሳችን ነው የምንሮጠው ...ውሸት ምን ያደር...
13/09/2025

ጉዳፍ ፀጋዬ ቅሬታዋን ገለፀች
-------------------------------------

"....ተነጋግረን ገብተን አለመተግበር አለ ። ዝምብለን የራሳችን ነው የምንሮጠው ...ውሸት ምን ያደርጋል ...የቡድን ስራ ይቀረናል ..."
ጉዳፍ ጸጋዬ ከውድድሩ በኋላ ቶኪዮ ለሚገኙ ጋዜጠኞች የተናገረችው ...

ምንጭ : - ኤርሚያስ በጋሻው

Address

Addis Ababa

Telephone

+251712187717

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Press:

Share

Category