Ethio Press

Ethio Press Media-ሚዲያ
ዜና - መዝናኛ -ታሪክ - ጤና - ማህበራዊ ጉዳይ
ወ. ዘ. ተ.
ታማኝ እና ፈጣን-የሁሉም ለሁሉም
(2)

ጳጉሜን አስወግዱ:-አይኤምኤፍ‼️አይ ኤም ኤፍ ኢትዮጵያ የጳጉሜን ወር እንድታስወግድ ምክረሀሳብ ማቅረቡ ተሰማ13ኛውን ወር - ጳጉሜን ሙሉ በሙሉ ስለማያስፈልግ እንድታስወግድ አይኤምኤፍ አሳስቧ...
23/07/2025

ጳጉሜን አስወግዱ:-አይኤምኤፍ‼️

አይ ኤም ኤፍ ኢትዮጵያ የጳጉሜን ወር እንድታስወግድ ምክረሀሳብ ማቅረቡ ተሰማ

13ኛውን ወር - ጳጉሜን ሙሉ በሙሉ ስለማያስፈልግ እንድታስወግድ አይኤምኤፍ አሳስቧል።

አንድ የአይኤምኤፍ ባለስልጣን “በአመት ውስጥ አስራ ሶስት ወራት ቅንጦት ነው ማንም በማደግ ላይ ያለ ኢኮኖሚ አቅም የለውም። ብለዋል

የአይኤምኤፍ የማክሮ ኢኮኖሚ ሞዴል ጳጉሜን "በቀን መቁጠሪያ ላይ የተመሰረተ የዋጋ ግሽበት ከባህል ጋር የተቆራኘች ናት" በማለት ተናግረዋል።

 #ሐዋሳ #ማሳሰቢያ‌‎የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላለፈ።‎‎ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል ቅዳሜ ይከበራል።በዓሉን አስታኮ ግን አንዳን...
23/07/2025

#ሐዋሳ
#ማሳሰቢያ

‌‎የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ጥብቅ ማሳሰቢያ አስተላለፈ።

‎ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል ቅዳሜ ይከበራል።

በዓሉን አስታኮ ግን አንዳንድ አገልግሎት ሰጪዎች ከፍ ያለ የዋጋ ጭማሪ እያደረጉ እንደሆነ በግልጽ ታይተዋል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያም " ጥቂት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በዓሉን አስታከው በአንዳንድ አገልግሎቶችና በማረፊያ ቦታዎች ላይ ከወትሮው ውጭ የዋጋ ጭማሬ የሚመስሉ አዝማሚያዎችን እያደረጉ ስለመገኘታቸው ጥቆማዎች ቀርበውልኛል " ብሏል።

" የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በእነዚህ አብዛኛው አገልግሎት ሰጪ ተቋማትን በማይወክሉ ላይ እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ቀደም ብለው እንዲታረሙ በጥብቅ ያሳስባል " ሲል ገልጿል።

" ‎ይህ አይነቱ ድርጊት በተለይም ሁላችንም የአይን ብሌን አድርገን የምናያትን ከተማችን የሀዋሳን ስም የሚያጠለሽ ሆኖ እንዳይገኝ ከወዲሁ በመሰል ድርጊት ላይ የተሰማሩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ማስገንዘብ እንወዳለን " ሲል መምሪያው አሳስቧል።

" ‎በጥቆማው መሰረት በተጨባጭ መልኩ በዓሉን አስታከው ያልተገባ የዋጋ ጭማሬ በማንኛውም አገልግሎት ላይ በሚያደርጉ አካላት ላይ አስተዳደሩ የማያዳግም እርምጃ ይወስዳል " ብሏል።

ስግብግብነትም ልክ አለው !" የአንድ አልጋ ዋጋ 800 ብር ከነበረበት 2500 እና 3000 ብር ብለው አስደነገጡኝ ! "(ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ታከለ)በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮ...
23/07/2025

ስግብግብነትም ልክ አለው !

" የአንድ አልጋ ዋጋ 800 ብር ከነበረበት 2500 እና 3000 ብር ብለው አስደነገጡኝ ! "

(ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ታከለ)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ አመታዊው የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ ከሚከበርባቸው ከተሞች መካከል የፍቅር ከተማዋ ሀዋሳ አንዷ ናት።

በርካቶች ከተለያዩ የአለም እና የሀገሪቱ አካባቢዎች ለዚህ መንፈሳዊ በዓል ወደ ከተማዋ በመምጣት በደመቀ መልኩ ያከብራሉ።

የእንግዶቹን መምጣት ተከትሎም የእንግዳ ማረፊያዎች ፣ ሆቴሎች እና ምግብ ቤቶች አለፍ ሲልም ከሊስትሮ እስከ ቡና መሸጫ ቦታዎች እንዲሁም ሌሎች በንግድ የሚተዳደሩ የከተማይቱ ግለሰቦች በዚህ በአል ተጠቃሚ በመሆን ገቢ ያገኛሉ።

ነገር ግን አንዳንድ ስግብግቦች በእጅጉ እንግዶችን የሚያሳቅቁ የዋጋ ጭማሪዎችን በማድረግ ከተማው ላይ ሰዎች ቆይታቸውን እንዳያራዝሙ በአጭሩም እንዲያጥር እያደረጉ ናቸው።

ትዝብቴ እዚህ ጋር ነው አንድ የቅርብ ወዳጄ ወደ ከተማይቱ ለመምጣት የአልጋ አገልግሎትን ፈልጎ እንዳመቻችለት ስለነገረኝ ወደ አንድ የእንግዳ ማረፊያ ሆቴል / በቅርበት ወደማውቀው ቦታ ሄድኩኝ።

ወደ ቦታው የሄድኩት የአልጋ ዋጋ በቅርብ እንኳን ስምንት መቶ ብር እንደሆነ ስለማውቅ ነው።

የአልጋ ዋጋ በዚሁ በዓል ምክንያት ብቻ ከእጥፍ በላይ በመጨመር ሁለት ሺህ አምስት መቶ እና ሦስት ሺህ ብር ነው ብለው በእጅጉ አስደንግጠውኛል።

ስለሆነም የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከተማዋ ከፍተኛ ገቢ ከምታገኝበት በዓል መካከል አንዱ የሆነውን የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በአልን አክብረው ከተማዋን ጎብኝተው እንግዶች ቀናቸውን አራዝመው ይቆዩ ዘንድ እንዲህ አይነት ራስ ወዳድ የሆኑ ስግብግብ የአልጋ ፣ የሆቴል ፣ የምግብ እና መሰል ነጋዴዎች ላይ በአፋጣኝ ክትትል በማድረግ እልባት ሊሰጠው ይገባል ስል በትዕትና እጠይቃለሁ። "

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከተናገሩት....“ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው ፤ ከእኛ በንስሐ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከ...
23/07/2025

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከተናገሩት....
“ለችግሮች ሁሉ መፍትሔ አላቸው መፍትሔውም የሚገኘው ከእግዚአብሔርና ከእኛ ነው ፤ ከእኛ በንስሐ ተመልሰን ከልብ እግዚአብሔርን ይቅርታ መጠየቅና ከክፉ ተግባራችን በእውነት መጸጸት ይጠበቃል እግዚአብሔር ደግሞ ይህን አይነቱን ንስሐ ከእኛ መኖሩ ሲመለከት ምሕረትና ይቅርታን ይለግሰናል
በዚህም መፍትሔና ፈውስ ይገኛል”

ከ28 ሺህ በላይ የህብረት ሥራ ማህበራት ደብዛቸው ጠፍቷል ተባለ ----------------------------------------------- አቶ ሺሰማ ገብረሥላሴ የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚ...
23/07/2025

ከ28 ሺህ በላይ የህብረት ሥራ ማህበራት ደብዛቸው ጠፍቷል ተባለ
-----------------------------------------------

አቶ ሺሰማ ገብረሥላሴ የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽ36 ሺህ 292 መሠረታዊ የህብረት ሥራ ማህበራት እና 19 ዩኒየኖች መሰረዛቸው ተነገረ

የኢትዮጵያ ህብረት ሥራ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር አቶ ሺሰማ ገብረሥላሴ እንደገለጹት ላለፉት አንድ ዓመት ተኩል በህብረት ሥራ ማህበራት ላይ በተሠራው የሪፎርም ሥራ 28 ሺህ 212 መሠረታዊ የህብረት ሥራ ማህበራት በሰነድም ሆነ በአድራሻም አልተገኙም፡፡ ከዚህ በፊት ይህን ያህል ቁጥር እየተባለ ሲነገር የቆየው በስም ደረጃ ብቻ ነው ብለዋል፡፡

ማህበራቱን በሰነድም በአድራሻ ማግኘት ስላልተቻለ ጥሪ ተደርጎላቸው እንዲቀርቡ ቢጠየቁም አልተገኙም ሲሉ ለኢፕድ ተናግረዋል ፡፡

ማህበራቱ ጥሪ ሲደረግላቸው ያለመገኘታቸው ምክንያት የሚገመተው በሆነ ወቅት ለሥራ እድል ፈጠራ ለማገዝ ተብሎ እንዲደራጁ የተደረጉ እንደነበር ነው፡፡ ከእዚህ በተጨማሪ አልፎ አልፎም የሀሰት ሪፖርቶች ሊኖሩ ይችላሉ ብለዋል ፡፡

በሪፎርሙ መረጃ የማጥራት ሥራ ተሠርቶ 36 ሺህ 292 መሠረታዊ የህብረት ሥራ ማህበራት እና 19 ዩኒየኖች መሰረዛቸውን የገለጹት አቶ ሺሰማ፤ ምክንያቱም ሕጋዊ ሥርዓት ተከትለው የህብረት ሥራ ማህበራት በራሳቸው ፈርሰው የምስክር ወረቀት መልሰው መሆኑን ገልጸዋል፡፡

#ቅዳሜ ገበያ

በአዲስ አበባ ብዙ ሰዎች 'የቫይታሚን ዲ' እጥረት አለባችሁ የሚባሉት በስህተት ነው?-------------------------------ኸዲጃ እና ሪሐና እህትማማቾች ናቸው። ሁለቱም በተለያየ ም...
23/07/2025

በአዲስ አበባ ብዙ ሰዎች 'የቫይታሚን ዲ' እጥረት አለባችሁ የሚባሉት በስህተት ነው?
-------------------------------

ኸዲጃ እና ሪሐና እህትማማቾች ናቸው። ሁለቱም በተለያየ ምክንያት፣ በተለያዩ ቀናት ሐኪም ጎብኝተው ሁለቱም የቫይታሚን-ዲ እጥረት አላባችሁት ተባሉ።

በሥራ ቦታ የሚያውቋቸው ሌሎች በርካታ ሰዎችም እንዲያ መባላቸውን ስለሚያውቁ ተገረሙ።

ኸዲጃ እና ሪሐና በሳምንት ዐርብ ከጁምዓ ስግደት በኋላ የቤተሰብ ፕሮግራም አላቸው። እየተገናኙ ይበላሉ፤ ይጨወታሉ።

በዚህ የቤተሰብ ጉባኤ የቫይቲምን-ዲ ነገር እንደ ዋዛ ተነሳ። "አለብሽ ተባልኩ" የሚለውን ተከትሎ "እኔም-እኔም-እኔም'' መባባል ሆነ።
"ከተሰበሰብነው ውስጥ ግማሻችን ቫይታሚን-ዲ አለባችሁ ተብለናል። ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል?" ትላለች ሪሐና።
"የእኛን አገር ሐኪሞች ብዙ አላምናቸውም። ድሮ ታይፎይድ አለባችሁ ይሉን ነበር፤ አሁን ደግሞ ቫይታሚን-ዲ እጥረት አለባችሁ ማለትን ፋሽን አድርገውታል" ትላለች ታላቅ እህቷ ኸዲጃ።

የጤና ባለሙያዎች ግን ነገሩ ወዲህ ነው ይላሉ።
"የአዲስ አበባ ሕዝብ 75% እጥረት አለበት"
ዓለም አቀፉ የምግብ ፖሊሲ ምርምር ኢንስቲትዩት፣ ከጤና ሚኒስቴር ጋር ተባብሮ የሠራው ጥናት ውጤት አስደንጋጭ ነው።

ከኢትዮጵያ ሕዝብ ግማሹ እጥረት አለበት። ከአዲስ አበባ ሕዝብ ደግሞ ሦስት አራተኛው (¾) ቫይታሚን-ዲ አጥሮታል።
ይህ ነገር ከኑሮ ውድነቱ ጋር የተያያዘ ይሆን? አይደለም።

ይህ አሐዝ በተለይ 13 ወር ፀሐይ ለሚጠጣ ሕዝብ ስላቅ ይመስላል። ምክንያቱም የቫይታሚን-ዲ ዋና አከፋፋይ ፀሐይ ስለሆነች።
ዶክተር ፍጹም ጥላሁን በአሜሪካን አገር በሕክምና ሙያ ላይ ተሠማርተው ይገኛሉ።

ውስብስብ የሕክምና መረጃዎችን በሕዝብ ቋንቋ አውርዶ ማኅበረሰባዊ ግንዛቤ በመፍጠር ብዙ ሥራ በመሥራት ይታወቃሉ።

'ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሐኪም ቤት የሄደ አዲስ አበቤ ሁሉ ቫይታሚን-ዲ እጥረት አለብህ የሚባለው ለምንድነው?' ለሚለው ቁልፍ ጥያቄ ምላሽ ሰጥተውናል።

አኗኗራችን ተለውጧል- ምርመራው ዘምኗል"
የሕክምና ባለሙያዎች የኑሮ ዘይቤያችን መቀየሩን አብዝተው ያወሳሉ። ከኮምፒውተር መምጣት ወዲህ እየጎበጥን ነው፤ ከዘመናይ ስልክ ወዲህ እየፈጠጥን ነው።
ይህ ነገር ጣጣ ይዞብን እየመጣ ነው። አያት ቅድመ አያቶቻችን ንቁ ነበሩ። የእኛ አኗኗር ፍዝ ሆኗል።የጤና ጣጣ ይዞብን ይመጣል።

ብዙ ሰው ጠዋት ተንደርድሮ ቢሮ ይገባል።ምሳ እዚያው ክበብ ውስጥ ይበላል። ሲመሽ ወደ ቤት ይነጉዳል።
ታዲያ ከፀሐይ ጋር በየት ይገናኛል? አኗኗራችን ተቀይሯል።

ተማሪ ትምህርት ቤት ይውላል፣ ካድሬ ቀኑን ሙሉ ስብሰባ ነው። ነጋዴው ሱቁ ቆሞ ይሸጣል። ከፀሐይ ጋር በየት በኩል ይገናኛል?

ለመሆኑ አዲስ አበቤ በሺህ በመቶ ሺዎች ለቫይታሚን ዲ የተጋለጠው ለዚህ ይሆን?
ዶክተር ፍጹም አንድ ቁልፍ ምክንያት ያነሳሉ።
"በፊት ምርመራ አልነበረም። ስለዚህ ቫይታሚን-ዲ እጥረት እምብዛም አይታወቅም ነበር ።አሁን ብዙ ሰው ለአጠቃላይ ጤና ምርመራ ሲሄድ እጥረት እንዳለበት ይነገረዋል . . . ።"...

(BBC)

በራሱና በደህንት ሰራተኞ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ የተጭበረበረው ንግድ ባንክ ክስ መመስረቱ ተሰምቷል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ አጭበርብረውኛል ባላቸው አስራ አራት ግለሰቦ...
23/07/2025

በራሱና በደህንት ሰራተኞ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ የተጭበረበረው ንግድ ባንክ ክስ መመስረቱ ተሰምቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከ7 ቢሊዮን ብር በላይ አጭበርብረውኛል ባላቸው አስራ አራት ግለሰቦች ላይ ክስ መመስረቱ ታውቋል።

ሁለቱ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ሰራተኞች መሆናቸው የተገለፀ ሲሆን ሦስቱ የባንኩ ሰራተኞች ናቸው ተብሏል።

በዚህ ሩብ ሚሊዮን የሚጠጋ ተከታይ ባለው የፌስቡክ ገፃችን ንግድና አገልግሎትዎን   በሆነ ክፍያ ያስተዋውቁ🙏°°°°°°°°°°        ብዙ ፈላጊ እንዳሎት ያውቃሉ ❓️ነገርግን አድራሻዎን እ...
22/07/2025

በዚህ ሩብ ሚሊዮን የሚጠጋ ተከታይ ባለው የፌስቡክ ገፃችን ንግድና አገልግሎትዎን በሆነ ክፍያ ያስተዋውቁ🙏
°°°°°°°°°°
ብዙ ፈላጊ እንዳሎት ያውቃሉ ❓️ነገርግን አድራሻዎን እና የሚሰጡትን አገልግሎት ብዙዎች ባለማወቃቸው ተቸግረዋል! ስለዚህ ለምን ይዘገያሉ ❓️ የት እንዳሉ እና የሚሰጡትን አገልግሎት በአንድ ጊዜ ለብዙሺዎች ያሳውቁ 🙏
**********
👔 ቡቲኮች
👟የጫማ መሸጫ መደብሮች
🖥️የሞባይል እና ኤሌክትሮኒክስ መሸጫ እና ጥገና ቤቶች
📖ትምህርት ቤቶች እና ኮሌጆች
🩺 ክሊኒኮች - የጥርስ, የጠቅላላ ሕክምና, የቤት ለቤት ሕክማና አገልግሎት ወዘተ.
🫒 የባህል ሕክምና አገልግሎት ስጪዎች
🪟 ፈርኒቸር ቤቶች, ጂምናዝዬሞች
🌐 የጨረታ ማስታወቂያዎች
🌐 የስፔር ፓርት መሸጫ መደብሮች
🌐 የውበት ሳሎኖች
🌐 የስራ ማስታወቂያዎች
🌐 የመፅሐፍት, የፊልም እና የኮንሰርት ማስታወቂያዎች
🌐 የፊኒሺንግ ስራ
🌐 ባዮ መዲካል ኢንጂነሮች - የህክምና መሳሪያ ጥገና
🌐 የባህል አልባሳት መደብሮች
🌐 ማይክሮ ኢንተርፕራይዞች
🌐 አምራቾች
🌐 የቤት ለቤት አስጠኚዎች
🌐 መንፈሳዊ ጉዞ አዘጋጆች
🌐 ትምህርት ቤቶች
🌐 የስራ ማስታወቂያ እና

ሌሎችም
ምርትና አገልግሎትዎን ያስተዋውቁ
ለብዙዎች ይድረሱ❗️

ለተጨማሪ መረጃ - በቴሌግራም አድራሻችን ያናግሩን 👇
https://t.me/Advertinfo

አርቲስት ሠራዊት " ፍቅሬ መኪናው የእኛ አይደለም " አለ !-----------------------------------------" ... ለባለቤቴ፤ ለፊልም ባለሞያዋ ሮማን አየለ Tesla Cyb...
22/07/2025

አርቲስት ሠራዊት " ፍቅሬ መኪናው የእኛ አይደለም " አለ !
-----------------------------------------

" ... ለባለቤቴ፤ ለፊልም ባለሞያዋ ሮማን አየለ Tesla Cybertruck ስጦታ አላበረከትኩም።

እኔ፣ ባለቤቴ እና ልጆቼ ጋር ለእረፍት ሰሜን አሜሪካ ነው ያለነው። የTesla ኩባንያን የመጎበኘት ዕድል አጋጥሞን ነበር።

እግረመንገድ "Test Drive" አድርጊያለሁ። ለማስታወሻ የተነሳነውን ፎቶግራፍ ሮሚ በፌስቡክ ገጻ ለጠፈች።

"የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስለ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ያደረጉት ተደጋጋሚ ንግግር የአሜሪካንን የዳበረ የዲፕሎማሲ ባሕል የማይመጥን ነው"          ኢዜማ----------------...
22/07/2025

"የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስለ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ያደረጉት ተደጋጋሚ ንግግር የአሜሪካንን የዳበረ የዲፕሎማሲ ባሕል የማይመጥን ነው"
ኢዜማ
-----------------------------------------------

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ) የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በአሜሪካ የገንዘብ እርዳታ እንደተሰራ በመግለጽ ያደረጉትን ንግግር እንደማይቀበለው አስታውቋል።

ኢዜማ በዛሬው ዕለት ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ማንኛውም አካል ለሕዳሴው ግድብ የሞራል፣ የፋይናንስ፣ የዲፕሎማሲ ድጋፍ አድርጎም ቢሆን፤ ኢትዮጵያውያን ግድቡን ለመፈፀም ያደረጉትን ያህል እልህ አስጨራሽና ፈታኝ ተጋድሎ በሚመጥን ደረጃ ያደረገ እንደሌለ ገልጿል።

"እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ በተደጋጋሚ እና በአደባባይ ግድቡ በአሜሪካ ገንዘብ እንደተገነባ የሚገልጽ የስህተት ንግግር ማድረጋቸው ስህተት ነው" ብሏል።

የፕሬዝዳንቱ ንግግር ኢትዮጵያ መሥራች አባል በሆነችበት የተባበሩት መንግሥታት ኮንቬንሽን አንቀጽ 2 ቁጥር አንድ የተደነገገውን የሁሉንም አባል ሀገራት ሉዓላዊ እኩልነት ድንጋጌ የሚፃረር እና የአሜሪካንን የዳበረ የዲፕሎማሲ ባሕል የማይመጥን መሆኑንም አመላክቷል።

ከአሜሪካ በተጨማሪም "አንዳንድ የግብጽ ባለሥልጣናት ይህንኑ የፕሬዝዳንቱን አድሏዊ ንግግር እንደ መልካም አጋጣሚ በመውሰድ የሕዳሴው ግድብ ላይ በአዲስ መልክ የጀመሩት አፍራሽ ቅስቀሳ ሀገራችን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሀብቶቿ የመጠቀም ሉዓላዊ መብቷን የሚክድ ብቻ ሳይሆን በመልካም ጉርብትና አብሮ የመልማት እድሎችን የሚያጨልም እንዳይሆን ቆም ብለው እንዲያስቡ እናሳስባለን" ብሏል።

ከመርሆዎቹ ቀዳሚው የኢትዮጵያ እና የሕዝቦቿ ጥቅም ምንጊዜም ቅድሚያ እንደሚኖረው ስለመሆኑ የገለጸው ፓርቲው፤ የኢትዮጵያውያን ጥቅምና ኩራት ማሳያ የሆኑ የልማት ፕሮጀክቶች በዝተው ማየት እንደሚፈልግ አስታውቋል።

"ድህነትና ጉስቁልናን ለመጫው ትውልድ ማውረስ የለብንም፣ ብሔራዊ ሀብታችንን ለዜጎች ጥቅምና ክብር መልማት አለባቸው ብለን፤ በቆራጥነት ወጥነን ከዳር ካደረስናቸው ፕሮጀክቶች ዋነኛው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ እንደሆነ ይታወቃል" ሲልም በመግለጫው አስታውቋል፡፡

ኢዜማ አክሎም፤ "የተለያየ የፖለቲካ አመለካከት ያለን የፖለቲካ ኃይሎች፣ ምሁራን፣ የማኅበረሰብ መሪዎች እና አንቂዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና መላው ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ከጊዜያዊ ልዩነቶቻችን ይልቅ ዘላቂ የሆነ ብሔራዊ ጥቅማችንን፣ ክብራችንን እና የልጆቻችንን መጻኢ እድል በማሰብ ይህንን ዐይን ያወጣ አድሎአዊነት የማንቀበለው ብቻ ሳይሆን በጋራ የምናወግዘው እና የምንመክተው መሆኑን ሁሉም እንዲያውቀው በጋራ እንድንቆም ጥሪ እናቀርባለን" ሲል ገልጿል።

"በድህነታችን ሊከብሩ፤ ባለመተባበራችን የእርዳታቸው ደጅ ጠኚ እና ለማኝ ሊያደርጉን ለሚፈልጉ ሁሉ መልዕክታችን አንድ መሆን አለበት" ሲልም አሳስቧል ሲል አሐዱ ሬዲዮ ዘግቧል።

ተጠናቀቀ ❗አርሰናል እና ስፖርቲንግ በዮኬሬሽ ዝውውር ላይ ሙሉ ለሙሉ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።- አርሰናል ለዮኬሬሽ ዝውውር €63.5M  + €10M add ons. ክፍያ ይፈፅማል ።-ተጫዋቹ በ...
22/07/2025

ተጠናቀቀ ❗

አርሰናል እና ስፖርቲንግ በዮኬሬሽ ዝውውር ላይ ሙሉ ለሙሉ ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

- አርሰናል ለዮኬሬሽ ዝውውር
€63.5M + €10M add ons. ክፍያ ይፈፅማል ።

-ተጫዋቹ በአርሰናል ቤት ለአምስት አመት የውል ሥምምነት ይፈርማል::

የደቡባዊ ትግራይ ዞን አስተዳደር ለጄኔራል ታደሰ ወረደ ማሳሰቢያ አስተላለፈ❗--------------------------- ‹‹የጄኔራል ታደሰ ወረደ ውሳኔ ህገ ወጥ ነው፣ መቆም አለበት›› ሲል ...
22/07/2025

የደቡባዊ ትግራይ ዞን አስተዳደር ለጄኔራል ታደሰ ወረደ ማሳሰቢያ አስተላለፈ❗
---------------------------

‹‹የጄኔራል ታደሰ ወረደ ውሳኔ ህገ ወጥ ነው፣ መቆም አለበት›› ሲል የደቡባዊ ትግራይ ዞን አስተዳደር ማሳሰቢያ ሰጠ፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት ጄተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በደቡባዊ ዞን የአመራር ለውጥ ሊደረግ መሆኑን መግለፃቸው ይታወቃል፡፡

ይህ የአመራር ለውጥ የሚከናወነውም ‹‹በሰላማዊ መንገድ›› መሆኑን የጠቀሱት ፕሬዝደንቱ ቢሆንም ‹‹የስልጣን ሽግግሩን ተግባራዊ ለማድረግ የፖሊስ አካላት ወደስፍራው ተንቀሳቅሰዋል›› ብለው ነበር፡፡ የአመራር ለውጡ የሚከናወነው በምክክር እንደሆነም ጄኔራል ታደሰ አስረድተዋል፡፡ ነገር ግን የትግራይ ደቡባዊ ዞን አስተዳደር የካቢኔ አባል የሆኑት አቶ ተዘራ ጌታሁን ይህንን የጄኔራሉን እቅድ አጥብቀው ተቃውመዋል፡፡

አቶ ተዘራ ጌታሁን ከላንዳ ሪፖርት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ‹‹በጄኔራል ታደሰ ወረደ የተወጠነው የስልጣን ሽግግር ውሳኔ ህገ ወጥ ነው›› ካሉ በኋላ በአስቸኳይ መቆም እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ የዞኑ አስተዳደር በስልጣን ሽግግሩ ላይ ምንም ምክክር አለማድረጉን ገልፀውም በጄኔራሉ የተላኩት የፖሊስ አካላት የአካባቢውን ባለስልጣናት እያሰሩ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

አቶ ተዘራ ጨምረውም የአመራር ለውጥ የተባለው ‹‹የተወሰኑ ቡድኖችን ለመጥቀም የታሰበ ነው›› ያሉ ሲሆን ውሳኔው ወደግጭት እንደሚያመራና ለትግራይ ሰላምም ስጋት እንደሚሆን አስጠንቅቀዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በትግራይ ደቡባዊ ዞን የአመራር ለውጥ ለማድረግ የታቀደው ከወራት በፊት ሲሆን ይህንን እቅድ የአካባቢው ነዋሪዎች ተቃውመው አደባባይ በመውጣት ድምፃቸውን ማሰማታቸው ይታወሳል፡፡

ሌተና ጄኔራል ታደሰ ወረደ በዛሬ መግለጫቸው ‹‹ሰላማዊ›› ያሉትን የአመራር ሽግግሩን ለማስፈፀም የፀጥታ አካላት ትእዛዝ እንደተሰጣቸው በመግለፅ ሀላፊነት የሰጧቸውን ሰዎች ስም ዝርዝር ጠርተዋል፡፡ በሌላ በኩል ከአካባቢው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚገልፁት የአመራር ለውጡ ከፖሊስ ከፖሊስ አቅም በላይ ሊሆን ስለሚችል ቲዲኤፍ ጣልቃ እንዲገባ ለማድረግ ዝግጅት እየተደረገ ነው፡፡

በጄኔራል ዮሀንስ የሚመራ የቲዲኤፍ ደቡባዊ እዝ ወደራያና ዋጅራት አካባቢ በመዝለቅ በወታደራዊ ጣልቃ ገብነት የስልጣን ሽግግሩን ለማከናወን እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ትግራይ ሄራልድ ዘግቧል፡፡

# ዘሐበሻ

Address


Telephone

+251712187717

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Press:

Shortcuts

  • Address
  • Telephone
  • Alerts
  • Contact The Business
  • Claim ownership or report listing
  • Want your business to be the top-listed Media Company?

Share