Ethio Press

Ethio Press Media-ሚዲያ
ዜና - መዝናኛ -ታሪክ - ጤና - ማህበራዊ ጉዳይ
ወ. ዘ. ተ.
ታማኝ እና ፈጣን-የሁሉም ለሁሉም
(9)

31/05/2026

አርሴናል ከደጋፊዎቹ ጋር በመሆን የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮንነቱን እያከበረ ነው::
በመጪው ዓመት ለተጨማሪ ድል እንመጣለን:: ዴክላን ራይስ

31/05/2026

ፍልቅልቋ አትሌት ደራርቱ ቱሉ ልጇን ዳረች::

ነገ  በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ያለተቀናቃኝ ለፓርላማ የሚያልፉት እጮዎች ታወቁ !-----------------------------------------------ለፓርላማ ምርጫ የሚካ...
31/05/2026

ነገ በሚካሄደው 7ኛው ጠቅላላ አገራዊ ምርጫ ያለተቀናቃኝ ለፓርላማ የሚያልፉት እጮዎች ታወቁ !
-----------------------------------------------

ለፓርላማ ምርጫ የሚካሄድባቸው የፓርላማ ወንበሮች 501 መሆናቸው ታውቋል፤ ይህም የሆነው የትግራይ 38 እና የአማራ 8 ወንበሮች ምርጫ ስለማይካሄድባቸው ነው። ብልፅግና ፓርቲ ለፓርላማ ያቀረባቸው ዕጩዎች ብዛት 461 ነው፤ ሆኖም፣ በአማራ ክልል ምርጫ አይካሄድባቸውም የተባሉት 8 የምርጫ ክልሎች ከመታወቃቸው በፊት የተመዘገበ የዕጩዎች ቁጥር ስለሆነ ከምርጫው ጋር አብረው የተሰረዙ ዕጩዎች መኖራቸውን ለጊዜው ማረጋገጥ አልተቻለም።
ይሁን እንጂ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በአማራ ክልል ምርጫ ከማይካሄድባቸው አካባቢዎች መካከል ደቡብ እና ምዕራብ ጎንደር፣ አምባሰል እና ደጋ ዳሞት እንደሚገኙበት ተናግረዋል።
በዚህ መሠረት ሲሰላ፣ ከ40 እስከ 48 የሚሆኑ የፓርላማ ወንበሮች በተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ወይም በግል ተወዳደሪዎች ሊወሰዱ እንደሚችሉ ይገመታል። በሌላ በኩል 75 ዕጩዎች ያለተፎካካሪ እንደሚወዳደሩ ሲታወቅ፣ ከነዚህ ውስጥ 65ቱ የብልፅግና ተወዳዳሪዎች ናቸው። ከቀሪዎቹ 10 ዕጩዎች መከካከል ሁለት የግል ተወዳዳሪዎች እና ስምንት የተቃዋሚ ፓርቲ ወኪሎች ከወዲሁ ያለተፎካካሪ ወደ ፓርላማ እንደሚገቡ ተገምቶ ነበር። ሆኖም ደጋ ዳሞት የምርጫ ክልል ውስጥ ነገ ምርጫ እንደማይካሄድ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስለተገለጸ፣ የትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ዕጩ የሆኑት በአማራ ክልል ደጋ ዳሞት የምርጫ ክልል የቀረቡት ይልቃል አስቻለ፣ ብቻቸውን ተወዳድረው ፓርላማ የመግባት ዕድላቸው ተስተጓጉሏል።
እነዚህ በምርጫ ክልላቸው ሌላ ተወዳዳሪ ዕጩ ባለመኖሩ፣ በእነዚህ አካባቢዎች ምርጫው ካልተደናቀፈ በቀር በመጪው ፓርላማ ያለተቀናቃኝ የሚገቡት ዕጩዎች የሚከተሉት ናቸው፤

* ቀጄላ መርዳሳ፣ በኦሮሚያ መንዲ የምርጫ ክልል፣ የግል ዕጩ

* አራርሶ ቢቂላ፣ በኦሮሚያ ደደር 2 የምርጫ ክልል፣ የግል ዕጩ

* ሰለሞን ታፈሰ፣ በኦሮሚያ ኮፈሌ 2 የምርጫ ክልል፣ የአዲስ ትውልድ ፓርቲ ዕጩ

* ዮሐንስ ጥላሁን፣ በአማራ ክልል አማኑኤል የምርጫ ክልል፣ የትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት ዕጩ

* ዳምጠው ተሰማ፣ በአማራ ክልል መሐል ሜዳ የምርጫ ክልል፣ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ ዕጩ

* ሙሐመድ ቡሽራ፣ በአማራ ክልል ሳይንት 2 የምርጫ ክልል፣ የነፃነት እና እኩልነት ፓርቲ ዕጩ
እንደግ አዳነ፣ በአማራ ክልል ግንደ ወይን የምርጫ ክልል፣ የኢዜማ ዕጩ

* መኮንን ጎለሣ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ካማሺ የምርጫ ክልል፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የጉሙዝ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ዕጩ

* ዘካሪያስ አንበሴ፣ በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ዳሰነች የምርጫ ክልል፣ የኢዜማ ዕጩ

# ኢትዮጵያን ኢንሳይደር

ኡስታዝ ጀማል በሽር በአረቡ ዓለም ለረጅም ጊዜ የነበረውን የአንድ ወገን ትረካ ተግቶ እየሰባበረው ነው !-----------------------------------------------------ለ...
31/05/2026

ኡስታዝ ጀማል በሽር በአረቡ ዓለም ለረጅም ጊዜ የነበረውን የአንድ ወገን ትረካ ተግቶ እየሰባበረው ነው !
-----------------------------------------------------
ለዘመናት ያህል ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ ስታራምደው የነበረውን ዲፕሎማሲያዊ እና ስውር ጫናዎች ለዓረብኛ ተናጋሪው ማህበረሰብ በግልጽ ቋንቋ ማድረሱ፣አዲስ ግንዛቤ እንዲፈጠር አድርጓል።
ኢትዮጵያ በቀጣይ ልትገነባ ባሰበቻቸው ሦስቱ ታላላቅ ግድቦች ላይም መደናገር እንዳይፈጠር ከወዲሁ ደህና መደላድል እያኖረ ነው።
የግብፅንየህልውና ስጋት ትረካ እያፈረሰ፣ ትክክል፣ ተገቢና ፍትሃዊ በሆነ የኢትዮጵያ አቋም ላይ መረጃዎችን እያቀረበ ነው።
ግብፅ በህዳሴው ግድብ የውሃ ፍሰት ላይ አለብኝ የምትለውን ተፅዕኖ ገና ሳትወጣው፣ በቀጣይ የሚመጡት ሦስት ግድቦች ውሃ የማከማቸት አቅም ጩኸቷን ሊያበረታው ይችላል፣ ይሁንና ጩኸቷ በእውነተኛ መረጃ የሚጣራበት ግዜ ላይ ተደርሷል።
እነዚህ ተጨማሪ ግድቦች ፣ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷን የመጠቀም መብቷ የህዳሴው ግድብ ላይ ብቻ የማያበቃ መሆኑን የሚናገሩ ናቸው። ግብፅ በኢትዮጵያ ላይ ላላት ማናቸውም አቋምና የድርድር ስልትም ግልጽ መልዕክት ያስተላልፋሉ።
እንደ ኡስታዝ ጀማል ያሉ ተንታኞች ይህንን እውነት ለአረቡ ዓለም እያስረዱ፣ ጉዳዩ የ"ደባ" ወይም የ"ጥቃት" ሳይሆን የፍትሃዊ አጠቃቀም እና የልማት ጥያቄ መሆኑን አለም እየገባው መጥቷል።
ይህ ሂደት ፍጥጫውን ማናር ሳይሆን እውነታውን እየገለጠ የሚቀጥል ሆኗል።
ውጥረቱን የሚያንረው ቢመስል እንኳ ግብፅ ለዘመናት የያዘችው የብቻ ተጠቃሚነት ስነ-ልቦና ሙሉ በሙሉ እየተናጋ ስለሆነ ነው።
ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ በተሳካ ሁኔታ መገንባቷ በቀጣይ ለሚሰሩት ፕሮጀክቶች ትልቅ የልምድ እና የፖለቲካ ካፒታል ሰጥቷታል።
ስለዚህ የኡስታዝ ጀማልና መሰል ድምጾች መበርከት ውጥረቱን ከመጨመር ይልቅ፣ የአረቡ ዓለም የግብፅን የካርቱም እና የካይሮ ስምምነቶችን ትረካ ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያንም የልማት መብት እኩል እንዲረዳ ያደርገዋል።
ወደፊት ለሚመጣው የማይቀረው እውነታም አእምሮአቸውን እንዲያዘጋጁ እያደረገ ነው ።
ያለ ጥርጥር፣ ቀጣዮቹ ሦስት ግድቦች ቀይ ባህርን ጨምሮ አዲስ እየመጣ ላለው ዲፕሎማሲያዊ ትግል ጉልበት መሆናቸው የማይቀር ነው።

# አለምሸት ሞገስ

በጎንደር ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት የአርሴናል እና ፒኤስጂ የቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ በሚተላለፍበት ወቅት በተከሰተ "ፍንዳታ" የተማሪዎች ህይወት አለፈ !--------...
31/05/2026

በጎንደር ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ትላንት ምሽት የአርሴናል እና ፒኤስጂ የቻምፒየንስ ሊግ ፍጻሜ ጨዋታ በሚተላለፍበት ወቅት በተከሰተ "ፍንዳታ" የተማሪዎች ህይወት አለፈ !
--------
ተማሪዎቹ ፍንዳታው "ቦንብ" ነው ሲሉ የገለጹ ሲሆን "ዲ.ኤስ ቲቪ ውስጥ ጭንቅንቅ ብሎ ስለነበር ከቦንቡ በተጨማሪ ተረጋግጦ የተጎዳም አለ ትክክለኛው ጉዳት ምን ያህል እንደሆነ ማወቅ አልቻልንም" ብለዋል።

አደጋው ስለተከሰተበት ሰዓትም ሲያስረዱ ፥ "የአርሰናል ጨዋታ የመጀመሪያው 45 ደቂቃ ሊያልቅ ጥቂት ደቂቃ ሲቀረው ነው ፍንዳታውን የሰማነው" ሲሉ ለቲክቫህ ተናግረዋል።

አንድ ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ የጤና ሳይንስ ተማሪ ፤ " አሁን ላይ በካምፓሱ ፖሊሶች ገብተው የፍንዳታውን መንስኤ እያጣሩ ነው " ያለ ሲሆን " አሁን ካምፓሱ ሰላም ነው፣ ግን ከዚህ በፊት ከነበረው ሁኔታ የተወሰነ ነገር ተቀይሯል። ጠዋት ላይ የሞቱ ልጆችን አስክሬን ወደቤተሰቦቻቸው ሸኝተናል። አሁን የተወሰነ የሀዘን ድባብ አለ። ግን ተረጋግቷል " ብሏል።

" በትክክል የሟቾች ቁጥር ባይታወቅም በእርግጠኝነት ሁለት ተማሪዎች ሞተዋል። ጠዋት የአስክሬን ሽኝት አድርገናል። አሁንም ቢሆን ሌላ የሞተ ተማሪ ይኖራል። ማታ ጉዳት ከደረሰባቸው ውስጥ በርካቶች በአንቡላንስ ወደ ጤና ተቋማት ተወስደዋል። ፍንዳታው ያስከተለው ጉዳት ከባድ ነው " ሲል አክሏል።

አብዛኞቹ ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በካምፓሱ ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑንም ጠቁሟል።

በሰዓቱ ጨዋታውን ከፊት ወንበር ላይ ሁኜ እያየሁ ነበር ያለን አንድ ተማሪ ደግሞ " የመጀመሪያው የጨዋታ ስዓት አልቆ ለእረፍት ልንወጣ ስንል ነው ፍንዳታው የተከሰተው " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

" በጣም ትልቅ አዳራሽ ነው ኳስ የምናይበት፣ ግን በጣም ሰው ሞልቶት ተጨናንቋል፣ መግቢያ መውጫ የለውም። እያየን የነበረው በፕሮጀክተር እና በቴሌቪዥን ነበር " ሲል ገልጿል።

" መጀመሪያ ላይ የሆነ የሮኬት አይነት ድምጽ ተሰማን፣ ከዛ ስንነሳ እንደመብረቅ ድፍን ነው ያደረገን። ከፊታችን ብረት ስለነበር በድንጋይ መተውት ነው ብለን ነበር ያሰብነው። ግን ጭሱ በጣም አፈነን፣ በጣም ብዙ ተማሪ ነበርን እየተረጋገጥን በድንጋጤ ወጣን " ሲል አስረድቷል።

" ውጪ ከወጣን በኋላ ብዙ ተማሪ መመታቱን አየን፣ እኔም መጀመሪያ ደህና ነበርኩ፣ ከወጣሁ በኋላ ሳይ እግሬን ተመትቻለሁ። ምን እንደፈነዳ እንኳ አላውቅም። እኔ ያየሁት የሞቱ ሁለት ናቸው። ሌላ አላየሁም። ግን ለሞት የሚያሰጋቸው አሉ " ሲል አክሏል።

" ሁለቱንም እግሬን ነው የተመታሁት፣ እስካሁን እግሬ ላይ የገባው የፍንዳታው ፍንጥርጣሪ አልወጣልኝም። ግንባሬንም ተመትቻለሁ" ሲል በስዓቱ የተፈጠረውን ገልጿል።

የትላንት ምሽቱን ፍንዳታ ለዩንቭርስቲው ቅርበት ያላቸው የከተማው ነዋሪ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ያረጋገጡ ሲሆን ተማሪዎች መጎዳታቸውንና ህይወታቸው ያለፉ "ተማሪዎች" መኖራቸውንም ገልጸዋል።

የሞቱት ተማሪዎች ቁጥር 3 እንደሆነ፤ 3 ሌሎች ተማሪዎች ከባድ አደጋ እንደደረሰባቸውና ከ30 ያላነሱት ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱን እኚሁ ቅርበት ያላቸው ሰው አረጋግጠዋል።

ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ሌላኛው የጎንደር ነዋሪም " በዩኒቨርሲቲ የምትማር አንድ ልጅ አለች ብዙ ተማሪ መጎዳቱን ገልጻልኛለች እኛም መረጃውን ሰምተናል። ምን ያህል ተማሪዎች እንደተጎዱ እና ስለፍንዳታው አይነት ግን አላውቅም " ሲሉ ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን በተመለከተ የተማሪዎች ህብረት አመራሮችን አነጋግሯል ፤ የቦምብ ፍዳታ መከሰቱንና የተማሪ ህይወት ማለፉን አረጋግጠዋል።

" ፍንዳታው በቦምብ ነው የተከሰተው፤ ተማሪዎች የዲኤስቲቪ ኳስ ጨዋታ እየተከታተሉ ባሉበት ሰዓት ነው የተከሰተው " ሲሉ ነው የገለጹት።

የተጎዱ ተማሪዎችን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸው አመራሮቹ " የተጎዱ ተማሪዎች የህክምና ክትትል እያደረጉ ነው ያሉት፤ በርካታ ተማሪዎች ነበሩ የተጎዱት ግን የተወሰኑ ተማሪዎች ናቸው። ውስጡ ያሉ ተማሪዎች ሙሉ አልተጎዱም " ሲሉ አክለዋል።

ህይወታቸው ያለፉ ተማሪዎች ስለመኖራቸው ጥያቄ ያቀረብንላቸው የተማሪዎች ኅብረት አባላት " ሁለት ተማሪዎች ለህክምና ከገቡ በኋላ ህይወታቸው አልፏል። ሆስፒታል ከገቡ በኋላ ነው ህይወታቸው ያለፈው " ብለዋል።

የተማሪዎቹ አስክሬንም ለቤተሰቦቻቸው መላኩን አክለው ገልጸውልናል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጉዳዩን ከዩኒቨርስቲው አመራሮች ተጨማሪ ቃል ለመቀበል ያደረገው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም።

# ቲክቫህ ኢትዮጵያ

Via Manchester City Manchester United Liverpool FC Fans 🫢
31/05/2026

Via Manchester City Manchester United Liverpool FC Fans 🫢

31/05/2026

Reaction 😪

31/05/2026

ትላንት አመሻሽ
የአርሴናልና የፒ ኤስ ጂ ጨወታ ከመጀመሩ በፊት

31/05/2026

ወንበር እንደ ዝናብ መጠለያ
ትላንት ምሽት አርሴናል ከ ፒ ኤስ ጂ

Address

Addis Ababa

Telephone

+251712187717

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Press:

Share

Category