Ethio Press

Ethio Press Media-ሚዲያ
ዜና - መዝናኛ -ታሪክ - ጤና - ማህበራዊ ጉዳይ
ወ. ዘ. ተ.
ታማኝ እና ፈጣን-የሁሉም ለሁሉም
(8)

ብራዚላዊው የኒውካስትል ዩናይትድ የመሃል ሜዳ ተጫዋች አርሴናልን በ80 ሚሊዮን ፓወንድ ለመቀላልቀል ተስማማ::
01/08/2026

ብራዚላዊው የኒውካስትል ዩናይትድ የመሃል ሜዳ ተጫዋች አርሴናልን በ80 ሚሊዮን ፓወንድ ለመቀላልቀል ተስማማ::

አብዱ ኪያር...?
01/08/2026

አብዱ ኪያር...?

01/08/2026

🫢

አባይ ሆምስ ሪል ስቴት ሁለተኛ  የመኖሪያ ፕሮጀክቱን ለገበያ አቀረበ ❗----------‎አባይ ሆምስ ሪል ስቴት፣ ሁለተኛውን ታላቅ የመኖሪያ ፕሮጀክቱን "ኪንግስ ሬዚደንስ (Kings Resid...
01/08/2026

አባይ ሆምስ ሪል ስቴት ሁለተኛ የመኖሪያ ፕሮጀክቱን ለገበያ አቀረበ ❗
----------
‎አባይ ሆምስ ሪል ስቴት፣ ሁለተኛውን ታላቅ የመኖሪያ ፕሮጀክቱን "ኪንግስ ሬዚደንስ (Kings Residence)" ይፋ አድርጎ ለገበያ ሲያቀርብ ፣‎በሌላ በኩል የመጀመሪያው ፕሮጀክት የግንባታ ሂደት ያለበት ደረጃን ለታዳሚዎች አሳይቷል ።

‎አባይ ሆምስ ሪል ስቴትን ያቋቋመው አባይ ቴክኒክ እና ንግድ አ.ማ. በተሽከርካሪ ንግድ ዘርፍ ከ20 ዓመታት በላይ ልምድ ያካበተ ተቋም ሲሆን፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት ወደ ሪል ስቴት ዘርፍ በመግባት በከተማው ማዕከል 3B+G+25 ያለውን ዘመናዊ የንግድና የመኖሪያ ሕንፃ ግንባታ በማስጀመር መሠረቱን ማጠናቀቁ ይታወሳል።

‎አሁን ደግሞ "ኪንግስ ሬዚደንስ" በተሰኘው አዲስ ፕሮጀክት 668 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ 2B+G+22 የሆነ ዘመናዊ የመኖሪያ ሕንፃ ለመገንባት ዝግጅቱን አጠናቋል።

‎ፕሮጀክቱ ባለ 6 ወለል ፓርኪንግ፣ ዘመናዊ የፓርኪንግ ሊፍት፣ ለኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የቻርጅ ማድረጊያ፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ሥርዓት፣ የጋራ መዝናኛ ቦታዎች እና ሌሎች ዘመናዊ አገልግሎቶችን ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።

‎ግንባታው ሲጠናቀቅ ባለ አንድ፣ ባለ ሁለት እና ባለ ሶስት መኝታ ቤት ያላቸው ዘመናዊ አፓርታማዎች ለገበያ የሚቀርቡ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ከ200 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች አዳዲስ የሥራ እድሎችን እንደሚፈጥርም ተጠቁሟል።

‎ድርጅቱ የመጀመሪያ ፕሮጀክቱን ቀደም ብሎ ለማስጀመር ቢያቅድም፣ በከተማዋ የልማት ሥራዎችና በአሠራር ለውጦች ምክንያት መዘግየቱ ተገልጿል። ይሁን እንጂ እነዚህን ተግዳሮቶች በመሻገር የፕሮጀክቱን ዲዛይን በማሻሻልና ተጨማሪ ግብአቶችን በመጨመር ከከተማዋ የልማት እቅድ ጋር በሚጣጣም መልኩ እንደገና ማስጀመሩን ገልጿል።

‎በሌላ በኩል፣ የፕሮጀክቱን ይፋዊ ማስጀመር አስመልክቶ አባይ ሆምስ ሪል ስቴት ለደንበኞቹ ልዩ የሽያጭ ማበረታቻ ማቅረቡን አስታውቋል። በዚህም በ5 በመቶ ብቻ ቅድመ ክፍያ ቤት መግዛት የሚያስችል ልዩ እድል ለገዥዎች መዘጋጀቱ ተገልጿል።

ፊፋ የዓለም ዋንጫ ሽያጭ  እቅዱን ሰረዘ !--------------------------------------------------ፊፋ የዓለም ዋንጫ እና ሌሎች ዉድድሮቹን የተወሰነ ድርሻ ለግል ባለሀ...
01/08/2026

ፊፋ የዓለም ዋንጫ ሽያጭ እቅዱን ሰረዘ !
--------------------------------------------------

ፊፋ የዓለም ዋንጫ እና ሌሎች ዉድድሮቹን የተወሰነ ድርሻ ለግል ባለሀብቶች ለመሸጥ ያሰበዉን እቅድ መሰረዙን ጂያኒ ኢንፋንቲኖ አስታውቀዋል።

ከአውሮፓ፣ ኮንካካፍ እና ከእሲያ እግር ኳስ ፌዴሬሽኖች ከፍተኛ ተቃውሞ የገጠመው ፊፋ እቅዱን ሰርዟል።

ይህም ከፊፋ ዋና ዓላማ ዉጪ አንድነትን ከመፍጠር ይልቅ መከፋፈልን በማምጣቱ እንደሆነ ፕሬዚዳንቱ ገልፀዋል።

ይሁንና የሽያጩ እቅድ ፌዴሬሽኖችን ለመደገፍ ያለመ እንደነበር ጠቁመዋል።

የዓለም ዋንጫውን አነስተኛ ድርሻ ለመግዛት ንግግር ላይ የነበሩት ባለሀብቶችም ራሳቸውን ስለ ማግለላቸዉ ተሰምቷል።

# EBC

01/08/2026

ጠላት እንኳን የማያደርገውን ድርጊት ፈጸሙባት"- ሩት ይርጋለም

ሰላም፤ እንዴት ናችሁ? ሩት ይርጋለም ነኝ፤ የቅዱሳን ይርጋለም ታናሽ እህት።

ሰሞኑን በሚዲያ ሲተላለፍ እንደሰማችሁት ወይም እንዳያችሁት ከሆነ... እህቴ ቅዱሳን የቅርብ ጓደኛዋ በምትላት ከፍቅረኛዋ ጋር በመሆን... እህቴ ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ... የቅርብ ሰው ይቅርና ጠላት የማያደርገውን ድርጊት ፈጽመውባታል።

ሆኖም የአዲስ አበባ ፖሊስ ባደረገው የተጠናከረ ሥራ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል።

ሌሊትና ቀን ልብስ ሳይቀይሩ ከእኛ ጋር አብረው 'አይዟችሁ' እያሉ ይህንን ድርጊት የፈጸሙትን ሰዎች በመያዛቸው የአዲስ አበባ ፖሊስን በጣም አመሰግናለሁ ማለት እፈልጋለሁ።

እቤት ድረስ መጥታችሁ ላጽናናችሁን፣ 'በርቱ፤ አይዟችሁ' ላላችሁን ሁሉ እናመሰግናለን፤ አብዛኞቻችሁ ከጎናችን ነበራችሁ።

ይህ የአንድ ሰው ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ የሀገር ጉዳይ ነው። ዛሬ እኔ ቤት የመጣው ክፉ ሀዘን ነገ የእናንተም ቤት ወይም የማንኛውም ሰው ቤት እንዳያንኳኳ፣ ትክክለኛው ፍትህ እንዲሰጥ "Justice for Kidusan" እያልን፤ ተገቢው ቅጣትና ፍትህ እንዲሰጥ አብራችሁን ሁኑ እላለሁ።

አመሰግናለሁ!"

ቪኒሲየስ ጁኒየር ወደ አርሰናል ለመቀላቀል በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መደረሱ ተነገረ ❗--------------------------------------አርሰናል ከሪያል ማድሪዱ ኮከብ ቪኒሲየስ ...
01/08/2026

ቪኒሲየስ ጁኒየር ወደ አርሰናል ለመቀላቀል በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መደረሱ ተነገረ ❗
--------------------------------------
አርሰናል ከሪያል ማድሪዱ ኮከብ ቪኒሲየስ ጁኒየር ጋር በግል ጥቅማጥቅሞች ዙሪያ በመርህ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሱ ተገለጸ። የቪኒሲየስ ወኪል የሆነው ሮክ ኔሽን ፣ ከአዲሶቹ የኢንግሊዝ ሻምፒዮኖች አርሰናል የቀረበውን እጅግ ከፍተኛ የዝውውር ጥያቄ ይዞ ከሪያል ማድሪድ አመራሮች ጋር ለድርድር እንደሚቀመጥ ተጠቅሷል።(Handofarsenal)

የኢራን አብዮታዊ ዘብ ነዳጅ ጫኝ መርከቦችን ሆርሙዝ ላይ መምታቱን ገለፀ !----------------------የኢራን አብዮታዊ ዘብ የተቀመጠውን መመሪያ “ጥሰዋል” ያላቸው ሁለት በሆርሙዝ ወሽ...
31/07/2026

የኢራን አብዮታዊ ዘብ ነዳጅ ጫኝ መርከቦችን ሆርሙዝ ላይ መምታቱን ገለፀ !
----------------------
የኢራን አብዮታዊ ዘብ የተቀመጠውን መመሪያ “ጥሰዋል” ያላቸው ሁለት በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ሊያልፉ የሞከሩ ነዳጅ ጫኝ መርከቦችን መምታቱን አስታወቀ።

ዘቡ ባወጣው መግለጫ ላይ ሁለቱ ነዳጅ ጫኝ መርከቦች የጥቃት ዒላማ የሆኑት “ለደኅንነት አስተማማኝ ባልሆነ እና በሕገወጥ መስመር” በአሜሪካ ሠራዊት “በአየር ታጅበው ባልተፈቀደ መስመር” በሆርሙዝ በኩል ሲጓዙ እንደሆነ አመልክቷል።

ጨምሮም ሁለቱ መርከቦች ጥቃት ከደረሰባቸው በኋላ “ሌሎች አራት ነዳጅ ጫኝ መርከቦች በፍጥነት አቅጣጫቸውን” ቀይረው ወደመጡበት መመለሳቸውን አሳውቋል።

አብዮታዊ ዘቡ “ለመርከብ ባለቤቶች እና ለኢንሹራንስ ኩባንያዎች የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ የሚያወጣውን ማስታወቂያ እንዳይሰሙ” ማስጠንቀቁን ገልጿል።

የአሜሪካ ጦር ሠራዊት ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) ሐሙስ ዕለት በሆርሙዝ ላይ ያሉት ነጻ የመርከቦች መተላለፊያ መመስሮች የደኅንነት ስጋት የለባቸውም በማለት፤ ነገር ግን በወሽመጡ ላይ ለንግድ መርከቦች እና ለሠራተኞቻቸው አደጋ የነበረው የኢራን አብዮታዊ ዘብ ነው ብሎ ነበር።

ከኢራን አብዮታዊ ዘብ ባሕር ኃይል ጋር ግንኙነት ያለው የኤክስ ማኅበራዊ ሚዲያ አካውንት በእሳት የተያያዙ በርካታ መርከቦችን የሚያሳይ ምሥል በእንግሊዝኛ እና በፋርስ ቋንቋ “የመመሪያ ጥሰት መጨረሻው” ከሚል ጽሁፍ ጋር አጋርቷል።

# ቢቢሲ

ቼልሲ የተጫዋቾች ዝውውር እገዳ ተጣለበት !--------------------------------------------------ቸልሲ 10 ሚሊየን ፓውንድ እና በቀጣይ ሁለት የዝውውር መስኮቶች ተጫ...
31/07/2026

ቼልሲ የተጫዋቾች ዝውውር እገዳ ተጣለበት !
--------------------------------------------------

ቸልሲ 10 ሚሊየን ፓውንድ እና በቀጣይ ሁለት የዝውውር መስኮቶች ተጫዋች እንዳያዘዋውር እገዳ ተጥሎበታል።

በሮማን አብራሂሞቪች ዘመን ቸልሲዎች በድብቅ ለወኪሎች ያልተገባ ክፍያ መፈፅማቸው በመረጋገጡ ነው ቅጣቱ የተጣለባቸው።

# ሲዲ ስፖርት

የፖሊስ አባሏ በፈራረሠ ቤት ተጥሎ በረሃብ ተዳክሞ የተገኘ ሕፃን አንስታ ጡታን በማጥባት ከሞት ታደገችው !-----------------------------------------------------...
31/07/2026

የፖሊስ አባሏ በፈራረሠ ቤት ተጥሎ በረሃብ ተዳክሞ የተገኘ ሕፃን አንስታ ጡታን በማጥባት ከሞት ታደገችው !
------------------------------------------------------------
በምዕራብ አርሲ ዞን ነገሌ አርሲ ወረዳ ቱሉ ቀበሌ በፈራረሠ ቤት ተጥሎና በረሐብ ምክንያት ተዳክሞ የተገኘን ሕፃን የተመለከቱ የአካባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ጥቆማ ያደርጋሉ።

ጥቆማ ከደረሣቸው የነገሌ አርሲ ወረዳ ፖሊሶች መካከል ኢንስፔክተር ጉደቱ ኡሊ የተባለችው ገና ሕፃኑን ስታይ በረሐብ የተዳከመ መሆኑን አይታ ቶሎ ከመሬት አንስታ ጡታን በማጥባት ከሞት የታደገች መሆኑን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።

ሐምሌ 19 ቀን 2018 ማንነቷ ለጊዜው ባልታወቀች እናት የተጣለው የሑለት ወር ሕፃን በባዶና በፈራረሰ ቤት ሲያለቅስ የሠሙ ሠዎች ለፖሊስ በሠጡት ጥቆማ ሕፃኑ በረሐብ የተዳከመ የነበረ ሲሆን በኢንስፔክተር ጉደቱ ኡሊ መልካም ተግባር ጡቷን በመጥባት ሊያገግም ችሏል።

የፖሊስ መኮንኗ በፈፀመችው መልካም የእናትነት ተግባር ያገገመው የሑለት ወር ሕፃን በጤና ተቋም የተመጣጠነ ምግብ አግኝቶ በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛል።

# ኢትዮጵያ ትረዝ

Address

Addis Ababa

Telephone

+251712187717

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Press posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Press:

Shortcuts

Share

Category