Ethiopian Radio /የኢትዮጵያ ሬድዮ/

Ethiopian Radio /የኢትዮጵያ ሬድዮ/ Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.
(3)

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.

24/07/2025

"እኔን የሰራኝ"
#የኢትዮጵያሬድዮ #እኔንየሰራኝ #ሃያአምስት #ስልሳ #ዘጠና

ዘመን ተሻጋሪ በዚህ ሳምንት!
24/07/2025

ዘመን ተሻጋሪ በዚህ ሳምንት!

ሐምሌ 24 በአንድ ጀንበር 700 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ቀጠሮ ተይዟል።
24/07/2025

ሐምሌ 24 በአንድ ጀንበር 700 ሚሊየን ችግኝ ለመትከል ቀጠሮ ተይዟል።

ታርጫ ስቱዲዮ - የኢቢሲ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት - (በምሥል) 📸ሳሙኤል ተወልደ     #ኢቢሲወደይዘት
24/07/2025

ታርጫ ስቱዲዮ - የኢቢሲ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት - (በምሥል)
📸ሳሙኤል ተወልደ
#ኢቢሲወደይዘት

24/07/2025

ታርጫ ስቱዲዮ - የኢቢሲ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ የምረቃ ሥነ-ሥርዓት

#ኢቢሲወደይዘት

24/07/2025

የኢትዮጵያ ድምጽ በኢትዮጵያ ሬዲዮ
Voice of Ethiopia on Ethiopian radio
ሐምሌ 17/2017 ዓ.ም

ታርጫ ስቱዲዮ - የኢቢሲ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ 🔥*******************ኢቢሲ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ የሆነውን አዲስ ስቱዲዮ በ...
24/07/2025

ታርጫ ስቱዲዮ - የኢቢሲ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ 🔥
*******************

ኢቢሲ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ የሆነውን አዲስ ስቱዲዮ በዛሬው ዕለት ያስመርቃል።

#ኢቢሲወደይዘት

የኢቢሲ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ - ታርጫ ስቱዲዮ ነገ ሥራ ይጀምራል 🔥 ****************የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን “ኢቢሲ ወደ ይዘት” ብሎ ኢትዮጵያን የመድረስ፣ የመሆን እና...
23/07/2025

የኢቢሲ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ - ታርጫ ስቱዲዮ ነገ ሥራ ይጀምራል 🔥
****************

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን “ኢቢሲ ወደ ይዘት” ብሎ ኢትዮጵያን የመድረስ፣ የመሆን እና የማገልገል የለውጥ ጉዞውን በሙሉ አቅሙ ዛሬም ቀጥሏል።

ኢቢሲ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ የሆነውን አዲስ ስቱዲዮ በነገው ዕለት ያስመርቃል።

የምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ከተለያየ የክልሉ ዞኖች እና ከተሞች የተውጣጡ የኅብረተሰብ ተወካዮች በተገኙበት ይካሄዳል።

ኢቢሲ ወደ ይዘት በሚል እያከናወናቸው ካሉ የይዘት እና የአቀራረብ ማሻሻያ ሥራዎች አንዱ ኅብረተሰቡን በቅርበት ሆኖ ለማገልገል አስቻይ ሁኔታ መፍጠር ነው።

በዚህም ሕዝቡ ድምፁን የሚያሰማባቸው፣ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ችግሮቹን የሚያስተጋባባቸው እንዲሁም ባህሉን፣ ወጉን፣ እሴቱን፣ ሀብቱን የሚያስተዋውቅባቸው ዘመናዊ ስቱዲዮዎችን በየአካባቢው በመገንባት ወደ ኅብረተሰቡ ይበልጥ እየቀረበ፣ የይዘት ምንጮቹን እያሰፋ ይገኛል።

አዲሱ የይዘት ምንጭ የታርጫ ስቱዲዮም በክልሉ ያሉ ሀብቶችን በማስተዋወቅ፣ ኅብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች በማስተናገድ ሁለንተናዊ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።

ኤፍኤም አዲስ 97.1 ስርጭት የጀመረበትን 25ኛ ዓመት፣ የቴሌቪዥን ስርጭት ጅማሮ 60ኛ ዓመት እና በሬዲዮ ሞገድ ለአድማጩ መድረስ የጀመረበትን 90ኛ ዓመት - 25 60 90 - እያከበረ የሚገኘው አንጋፋው የኢትዮጵያ ብርድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በቀጣይም ተጨማሪ የይዘት ምንጮችን በሌሎች የሀገራችን ክፍሎች ማስመረቁን ይቀጥላል።

በተለያዩ ሀገራትም ቋሚ ዘጋቢዎችን በመመደብ መረጃን በቀጥታ ለማድረስ የሚያስችሉ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የብሔራዊነት ትርክት ማፅኛ፣ የኅብራዊ አንድነት መተረኪያ እና የተደራሽነት ማረጋገጫ አዳዲስ የይዘት ምንጮችን ማስፋቱን ይቀጥላል።

ኢቢሲ - ለኢትዮጵያ ልዕልና!

#ኢቢሲወደይዘት

23/07/2025

"ድምጾቹ ቀለሞች"

#የኢትዮጵያሬድዮ #ድምጾቹቀለሞች #ሃያአምስት #ስልሳ #ዘጠና

ኢቢሲ ወደ ይዘት ኢቢሲ ወደ ይዘት ታርጫ ስቱዲዮ - ተጨማሪ  የይዘት ምንጭ የኢቢሲ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ  - ታርጫ ስቱዲዮ ነገ ስራ ይጀምራል።ኢቢሲ “ኢቢሲ ወደ ይዘት” በሚል የጀመረውን የ...
23/07/2025

ኢቢሲ ወደ ይዘት

ኢቢሲ ወደ ይዘት ታርጫ ስቱዲዮ - ተጨማሪ የይዘት ምንጭ

የኢቢሲ ተጨማሪ የይዘት ምንጭ - ታርጫ ስቱዲዮ ነገ ስራ ይጀምራል።

ኢቢሲ “ኢቢሲ ወደ ይዘት” በሚል የጀመረውን የለውጥ ስራዎችን በየጊዜው እያሰፋና እያጠናከረ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን 2017 ከመጠናቀቁ በፊት ተጨማሪ የይዘት ምንጭ ሊያበረክት ነው። ለሀገራት መልማት እና መበልፀግ፣ ለህዝቦች መቀራረብ እና አንድነት ሚዲያ ከፍተኛውን ሚና ይጫወታል።

ኢቢሲ ይሄን የሚዲያ አላማ እውን ለማድረግ በተፈጥሮ ሀብቱ ፤ በታላላቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦች እና የቱሪስት መዳረሻነት በሚታወቀው ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ተጨማሪ የይዘት ምንጭ የሆነውን የታርጫ ስቱዲዮ ነገ ስራ ያስጀምራል፡፡

ኮርፖሬሽኑ በዘንድሮው 2017 አዲስ ዓመት ዋዜማ ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ አዳዲስ ተጨማሪ የይዘት ምንጮችን ስራ በማስጀመር ኢቢሲን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎችን ከሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች የሚያደርስ፤ ዜጎች የሚናገሩበት አጠገባቸዉ ያለ ሚዲያ እንዲሆን አስችለዉታል።

ይሄን ስራ በማጠናከር የደቡብ ምዕራብ ክልል እና አከባቢው ህዝብን በቅርበት ለማገልገል ህዝቡ ድምጹን የሚያሰማባቸው፣ ወጉ - ባህሉን፣ ታሪኩን ከምንጩ ለመቅዳት የልማትና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን በቅርበት ለመድረስ እንዲያስችለው በዳውሮ ዞን ታርጫ ከተማ ነገ አዲስ የይዘት ምንጭ ይፋ ያደርጋል።

የደቡብ ምዕራብ ክልል እና አካባቢው በእምቅ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ ፀጋውና በምርታማነቱ ይታወቃል። ግልገል ጊቤ እና ኮይሻ ጨምሮ የሀገራችን ታላላቅ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በዚህ ክልል ይገኛሉ፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት የተገነባው የሀላላ ኬላ እና የዝሆን ዳና ሎጅ ፣ የቱሪዝም መስህብ የሆኑት ጨበራ ጩርጩራ ብሄራዊ ፓርክ ፣ ታሪካዊው ታላቅ ግንብ - ካብ ፣ የኦሞና ጎጀብ ወንዞችም የሚገኙት በዚሁ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ነዉ።

ይህ አዲሱ የይዘት ምንጭ የታርጫ ስቱዲዮ በክልሉ ያሉ ሀብቶችን በማስተዋወቅ፣ ህብረተሰቡ የሚያነሳቸዉን ጥያቄዎች በማስተናገድ ሁለንተናዊ አስተዋፅኦ ይኖረዋል ።

ኤፍኤም አዲሲ 97.1 ስርጭት የጀመረበትን 25ኛ ዓመት፤ የቴሌቪዥን ስርጭት ጅማሮ 60ኛ ዓመትና በሬዲዮ ሞገድ ለአድማጩ መድረስ የጀመረበትን 90ኛ ዓመት - 25 60 90 - እያከበረ የሚገኘው አንጋፋው የኢትዮጵያ ብርድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በቀጣይም ተጨማሪ የይዘት ምንጮችን በሌሎች የሀገራችን ክፍሎች ፤ በተለያዩ ሀገራትም ቋሚ ዘጋቢዎችን በመመደብ መረጃን በቀጥታ ለማድረስ የሚያስችሉ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ይገኛል ፡፡

በኢቢሲ አሁን የተጀመሩት የ “ኢቢሲ ወደ ይዘት” የለውጥ ስራ ውጤት የሆኑት በሁሉም ቻናሎቻችን ያሉት አዳዲስ የዜና እና ፕሮግራም ዝግጅቶች መረጃ እያደረስን፣ ወቅታዊና ሀገራዊ ጉዳዮችን በጥልቀት እየተነተንን ጠንካራ፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን ለመገንባት በሚደረገው ሀገራዊ ጥረት ውስጥ የበኩላችንን ለመወጣት ከምንጊዜውም በላይ በይዘት ለዉጥ በትኩረት እየሰራን መሆኑን የሚያሳይ ነዉ።

ለውጥ ላይ ባለችው ሀገራችን ኢትዮጵያ ኮርፖሬሽኑ ይሄንን የለውጥ ስራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ያረጋግጣል።

ለኢትዮጵያ ልዕልና

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን

21/07/2025

የኢትዮጵያ ሬዲዮ / Ethiopian radio … ሐምሌ 14/2017 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ድምጽ በኢትዮጵያ ሬዲዮ
Voice of Ethiopia on Ethiopian radio

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Radio /የኢትዮጵያ ሬድዮ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Radio /የኢትዮጵያ ሬድዮ/:

Share

Category