Ethiopian Radio /የኢትዮጵያ ሬድዮ/

Ethiopian Radio /የኢትዮጵያ ሬድዮ/ Ethiopian Broadcasting Corporation is a 24 hour working public media.
(3)

Ethiopian Broadcasting Corporation is a national media which disseminates its news and programs world wide via Television,Radio and Website.

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 2ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መርሃግብር!
22/08/2025

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 2ኛ ሳምንት ጨዋታዎች መርሃግብር!

22/08/2025

የኢትዮጵያ ድምጽ በኢትዮጵያ ሬዲዮ
Voice of Ethiopia on Ethiopian radio
ነሐሴ 16/2017 ዓ.ም

21/08/2025

እሑድ ቤት - የእልፍኝ ገበታ
እሑድ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በኢቲቪ መዝናኛ
#እሑድቤት #ሙሉዓለምታደሰ #ሚካኤልታምሬ #ቤትለእንግዳ #እንግዳ

አዲሱን ዓመት በጋራ እንቀበል! 🔥ምርትና አግልገሎትዎን ያስተዋወቁየኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን☎️  011 5 17 25 10  ☎️ 011 5 17 25 38
21/08/2025

አዲሱን ዓመት በጋራ እንቀበል! 🔥

ምርትና አግልገሎትዎን ያስተዋወቁ

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
☎️ 011 5 17 25 10 ☎️ 011 5 17 25 38

አርሰናል ፈጥኖ የወሰነበት ኤቤሬቺ ኤዜ **************አርሰናል ወደ ጎረቤቱ እና የምንጊዜም ተቀናቃኙ ቶተንሀም ሆትስፐር ሊያመራ ጫፍ የደረሰውን ኤቤሪቺ ኤዜን ለማስፈረም ከስምምነት መ...
21/08/2025

አርሰናል ፈጥኖ የወሰነበት ኤቤሬቺ ኤዜ
**************

አርሰናል ወደ ጎረቤቱ እና የምንጊዜም ተቀናቃኙ ቶተንሀም ሆትስፐር ሊያመራ ጫፍ የደረሰውን ኤቤሪቺ ኤዜን ለማስፈረም ከስምምነት መድረሱ ከሰዓታት በፊት የዓለም መገናኛ ብዙሀን እየዘገቡት ይገኛሉ፡፡

ከሁለት ቀን በፊት የክሪስታል ፓላስ ሊቀመንበር ስቴቭ ፓሪሽ እና የቶተንሀሙ አቻቸው ዳንኤል ሌቪ በዝውውሩ ጉዳይ በቀጥታ ከመከሩ በኋላ የኤዜ መዳረሻ ቶተንሀም ይሆናል ተብሎ ሲጠበቅ ነገሮች በፍጥነት ተቀይረዋል፡፡

የጀርመናዊው አጥቂ ካይ ሀቨርዝ ድንገተኛ ጉዳት ሚካኤል አርቴታ የዝውውር መስኮቱ ሳይጠናቀቅ ሌላ መውጫ ቀዳዳ እንዲፈልግም አስገድዶታል፡፡

እግር ኳስን በአርሰናል ቤት ጀመረው የ27 አመቱ ኤቤሪች ኤዜ ዳግም ወደ አርሰናል በመመለስ መጫወት እንደሚፈልግ በተደጋጋሚ ሲናገር ቆይቷል፡፡

የጊዮኬሬሽን ዝውውር ጨምሮ ተጫዋችን ለማስፈረም ረጅም የድርድር ጊዜ የሚወስደው አርሰናል ኤቤሪቺ ኤዜን ወደ ሰሜን ለንደን ለማምጣት ግን 24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ለክሪስታል ፓላስ ያቀረበው 60 ሚሊዮን ፓውንድ ተቀባይነት ስለማገኘቱ ይፋ ሆኗል፡፡

ባለፉት ሦስት ተከታታይ አመታት በሊጉ 2ኛ ደረጃን ይዞ ያጠናቀቀው አርሰናል የተሟላ ቡድን ሆኖ ለመቅረብ በዝውውሩ በንቃት እየተሳተፈ ሲሆን ለኤዜ ጥያቄውን ከማቅረቡ ተጫዋቹ ወደ አደገበት ክለብ መመለስ እንደሚፈልግ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ቀደም ብሎ ወደ ቶተንሀም ለማምራት በግል ጉዳይ ጭምር ስለመስማማቱ ቢዘገብም አሁን ግን ወደ ሌላኛ የሰሜን ለንደን ክለብ ለማምራት ከመድፈኞቹ ጋር በሁሉም የግል ጉዳዮች ተስማምቷል ተብሏል፡፡

አርሰናል ኤቤሬቺ ኤዜን የሚያግኘ ከሆን ምን አልባትም ጥያቄ እየተነሳበት ለሚገኘው የማርቲኔሊ ቦታ በቂ ምላሽ የሚያገኘ ሲሆን ሁለገቡ ተጫዋችም የሚፈልገውን ክለብ መለያ ዳግም የሚለብስበትን ዕድል ያገኛል፡፡

የትኛውም ዝውውር እስካልተጠናቀቅ ድረስ እርግጠኛ መሆን ባይቻልም ጀምስ ማዲሰንን በጉልበት ጅማት መበጠስ ጉዳት ለረጅም ጊዜ ያጣው ቶተንሀም ሌሎች አማራጮችን ይመለከታል ወይስ ደግሞ በዝውውሩ ፉክክር ውስጥ ይቆያል የሚለው በጥቂት ጊዜ ውስጥ መልስ የሚያገኝ ይሆናል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

20/08/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) | መደመር | አራተኛው "የመደመር መንግሥት" | አዲስ መጽሐፍ | ቃለ መጠይቅ |medemer
#አዲስመጽሐፍ #ቃለመጠይቅ

ሙሀመድ ሳላ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሆኖ ተመረጠ**************የሊቨርፑሉ አጥቂ ሙሀመድ ሳላ  የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች  ማህበር የዓመቱ ምርጥ  ተጫዋች ሆኖ ተመርጧል፡፡ግብጻዊው...
20/08/2025

ሙሀመድ ሳላ የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሆኖ ተመረጠ

**************

የሊቨርፑሉ አጥቂ ሙሀመድ ሳላ የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር የዓመቱ ምርጥ ተጫዋች ሆኖ ተመርጧል፡፡

ግብጻዊው አጥቂ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ሊቨርፑል የሊጉን ዋንጫ ለ20ኛ ጊዜ ሲያነሳ ትልቁን ሃላፊነት የተወጣ ሲሆን ይሄንን ክብርም ለ3ኛ ጊዜ አሸንፏል፡፡

በግሉም ምርጥ የውድድር ዓመት ያሳለፈው ሳላ በሊጉ 29 ግቦችን ሲያስቆጥር 18 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችንም አመቻችቶ አቀብሏል፡፡

ለ52ኛ ጊዜ በተደረገው ሽልማት ደክለረን ራይስ፣ ቡሩኖ ፈርናዴዝ፣ አሌክሳንደር ይሳቅ፣ አሌክሲስ ማክ አሊስተር እና ኮል ፓልመር የመጨረሻ ዕጩዎች ሆነው የቀረቡ ተፎካካሪዎቹም ነበሩ፡፡

የማንችስተር ሲቲው አማካይ ፊል ፎደን የባለፈው ዓመት አሸናፊ እንደነበር ይታወሳል፡፡

የእንግሊዝ እግር ኳስ ተጫዋቾች ማህበር ሽልማት በ50 ዓመታት ጉዞው ማንችስተር ዩናይትድ 11 ተጫዋቾችን በማስመረጥ ቀዳሚው ክለብ ነው፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

20/08/2025

የኢትዮጵያ ድምጽ በኢትዮጵያ ሬዲዮ
Voice of Ethiopia on Ethiopian radio
ነሐሴ 14/2017 ዓ.ም

የተጨማሪ እሴት ታክስ 15 በመቶ ሆኖ ይቀጥላል*******************የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ እንዲቀጥል መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡በገንዘብ ሚኒስቴር ...
19/08/2025

የተጨማሪ እሴት ታክስ 15 በመቶ ሆኖ ይቀጥላል
*******************
የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ እንዲቀጥል መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

በገንዘብ ሚኒስቴር የታክስ ፖሊሲ መመሪያ ኃላፊ አቶ ሙላይ ወልዱ ለኢቢሲ እንደገለጹት፤ የገንዘብ ሚኒስቴር በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ማሻሻያ መሰረት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ እንዲቀጥል ወስኗል፡፡

ነባሩ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ከምጣኔ ውጭ ሌሎች ማሻሻያዎችን በማካተት ከ3 አስርት ዓመታት በኋላ ተሻሽሎ በ2017 በጀት አመት ስራ ላይ መዋሉን አቶ ሙላይ ገልፀዋል፡፡

የታክስ ገቢ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ከነበረው ከ12 በመቶ በላይ ድርሻ በየዓመቱ በተከታታይ እየቀነሰ ከ7 በመቶ በታች መድረሱን የጠቀሱት ኃላፊው፤ ከዚህ ጠቅላላ ቅናሽ 44 በመቶው የተጨማሪ እሴት ታክስ ድርሻ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡

የተጨማሪ እሴት ታክስ ህጉን አሁን ካለው የኢኮኖሚ ሁኔታ የቀጣይ ዓመታት ለውጦች ጋር እንዲጣጣም በማድረግ በመካከለኛ ዘመን የገቢ ስትራቴጂው መሰረት ተሻሽሎ በ2017 በጀት ዓመት ስራ ላይ እንዲውል መደረጉንም አውስተዋል፡፡

መጣኔው አሁን ካለበት 15 በመቶ ከፍ እንዲል ማድረግ ጫናው ተጨማሪ እሴት ታክስ በአግባቡ የሚከፍሉት ላይ እንዲባባስ በማድረግ የታክስ አስተዳደር ወይም የታክስ ህግ ተገዥነት ችግሩ ሊባባስ እንደሚችል በጥናት መረጋገጡን ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡

በዚህም በማሻሻያው መሰረት በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ማሻሻያ መሰረት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ እንዲቀጥል መወሰኑን ነው የገለፁት፡፡

የተጨማሪ እሴት ታክስ ቀጥታ ካልሆኑ ታክሶች ውስጥ የሚመደብ ሆኖ በፍጆታ የሚጣል፣ ቁጠባንና ካፒታልን የሚያበረታታ ከተጠቃሚው የሚሰበሰብ ታክስ ነው፡፡

በጌታቸው ባልቻ

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የደረጃ ሰንጠረዥ፡-
19/08/2025

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የደረጃ ሰንጠረዥ፡-

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አራተኛው "የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ *********************ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመደመር ሐሳብ ላይ የጻፉት አራተኛውንና "...
19/08/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አራተኛው "የመደመር መንግሥት" መጽሐፍ
*********************

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በመደመር ሐሳብ ላይ የጻፉት አራተኛውንና "የመደመር መንግሥት" የተሰኘውን አዲስ መጽሐፍ በተመለከተ ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ነገ ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2:30 ጀምሮ በኢቢሲ ሁሉም አማራጮቻችን ይጠብቁ።

19/08/2025

የኢትዮጵያ ሬዲዮ | Ethiopian Radio ... ነሐሴ 13/2017 ዓ.ም
Ethiopian Radio | Ethiopian Radio

Address

Churchill Road
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Radio /የኢትዮጵያ ሬድዮ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian Radio /የኢትዮጵያ ሬድዮ/:

Share

Category