Roha Media ሮሃ ሚዲያ

Roha Media ሮሃ ሚዲያ "ሮሃ ሚዲያ " መልዕክት ፡ሀሳብ ፡መረጃ፡የሚተላለፍበት መንገድ ነው።

አምባገነኖች ከአንድ ወንዝ ይቀዳሉ ! "  ቁርጥ'ሷን ''ከሰሞኑ ሊዊስ ናኒ አዲስ አበባ መጥቶ ነበር። ለምን እንደመጣ ራሴን ስጠይቅ ሰነበትኩ ፡ የካኑ እንኳን ብዙም ግድ አልሰጠኝም ። ልጅነ...
21/07/2024

አምባገነኖች ከአንድ ወንዝ ይቀዳሉ !

" ቁርጥ'ሷን ''

ከሰሞኑ ሊዊስ ናኒ አዲስ አበባ መጥቶ ነበር። ለምን እንደመጣ ራሴን ስጠይቅ ሰነበትኩ ፡ የካኑ እንኳን ብዙም ግድ አልሰጠኝም ።

ልጅነቴን የጨረስኩት ማንቸስተር ዩናይትድን ከልቤ በመደገፍ ነበር ለዛም ነው ናኒ ለምን መጣ ያልኩት።

(የኳስ ነገር ምንም ለማይገባችሁ ናኒ የማንቸስተር ዩናይትድ የአንድ ወቅት ፈርጥ ነው)

እናም በውስጤ ይብሰለሰል የነበረው ጥያቄ ድንገት መልሱ ፊቴ ላይ ድግን አለ።

ስሎቦዳን ሚሊሶቪች የሚሉት ዩጎዝላቪያን 1989-1997 G.C የመራ አምባገነንና ቦስኒያዎችን በዘር መርጦ ሲጨፈጭፍና በጅምላ ሲያስር የነበረ "ቡቸር" መሪ ድንገት ትዝ አለኝ።

ይህ አምባገነን በጊዜው እየፈረሰች ያለችውን ዩጎዝላቪያ ፡ዓለም በሌላ መልክ ይይልኝ ብሎ (ገፅታ ግንባታ መሆኑ ነው) የዓለማችን ምርጥ የእግር ኳስ ተጨዋች የሆነውን አርጀንቲናዊ ተጫዋች ዲያጎ አርማንዶ ማራዶናን …ና !ሀገሬን ጎብኛት ፡በዛውም አድንቃት ብሎ ጋበዘው ።

ማራዶናም 150 ሺ $ ተከፍሎት ወጭው ተሸፍኖለት ፡ዩጎዝላቪያ ገባ። ያየውን ፡የሰማውን አደነቀ ። በርታ ሚሊሎሶቪች አለ ። (ምን'ኳ የማራዶና አድናቆት ኃላ ላይ ሚሎሶቪችን ህግ ፊት ከመቆም ባያስጥለውም ቅሉ)

የኛም ነገር ይሄው ነው ። ሊዊስ ናኒ በርቱ ብሎ ይሆናል ፡፡ ነገር ግን በዘራችንና በማንነታችን ብቻ ያለምንም ወንጀላችን ግድያ'ና ጅምላ እስር የሚፈፅሙብንን መጨረሻ ላይ ህግ ፊት ቀርበው መልስ ይሰጡበታል።

አዎ። ማራዶና ሚሎሶቪችን ካላዳነው ሊዊስ ናኒ ማንን ከህግ ሊያስጥል ነው ?

ኤርሚያስ አለባቸው

ጀግናው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አፍሪካዊ ስፖርተኛ ተባለRoha Media |ኢኤስፒኤን (ESPN) የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ 10 ታላላቅ አፍሪካውያን ስፖርተኞችን ...
20/07/2024

ጀግናው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ አፍሪካዊ ስፖርተኛ ተባለ

Roha Media |ኢኤስፒኤን (ESPN) የ21ኛው ክፍለ ዘመን ምርጥ 10 ታላላቅ አፍሪካውያን ስፖርተኞችን ይፋ ማድረጉን ተከትሎ ኢትዮጵያ እና ኬኒያ ሁለት አትሌቶችን በማስመረጥ ቀዳሚውን ደረጃ ይዘዋል።

ኢትዮጵያዊው የረጅም ርቀት ሯጭ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ቀዳሚውን ደርጃ ሲይዝ ኬንያዊው የረጅም ርቀት ሯጭ ኤሉድ ኪፕቾጌ ሁለተኛ ደረጃን ይዘዋል።

በሴቶች የዚምቧብዌዋ የዋና ስፖርት ተወዳዳሪ ክርስቲ ኮቨንትሪ ቀዳሚውን ደረጃ ስትይዝ ኢትዮጵያዊቷ የረጅም ርቀት ሯጭ አትሌት ጥሩነሽ ዲባባ በሴቶች ሁለተኛ በሁለቱም ጾታ ደግሞ አምስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችላለች።

13-11-2016

 #ኢትዮጵያ በረሃብ ተጠቂ ከሆኑ ሀገራት ተርታ ተመደበች፤ 13 ሚሊዮን ዜጎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ይሻሉ ተባለ።Roha Media |የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት እና ...
19/07/2024

#ኢትዮጵያ በረሃብ ተጠቂ ከሆኑ ሀገራት ተርታ ተመደበች፤ 13 ሚሊዮን ዜጎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ ይሻሉ ተባለ።

Roha Media |የተባበሩት መንግስታት የምግብ እና የእርሻ ድርጅት እና የአለም የምግብ ፕሮግራም (FAO-WFP) አዲስ ባወጡት ሪፖርት፤ ኢትዮጵያ ከተወሰኑ የአፍሪካ አገራት ጋር፤ በዓለም ላይ በረሃብ ተጠቂ ከሆኑ ሀገራት ተርታ ተመደበች።

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በግጭት፣ በድርቅ፣ በከፍተኛ የኑሮ ውድነት እና በተፈጥሮ አደጋዎች ምክንያት በተከሰተ ከፍተኛ የምግብ ችግር ውስጥ እንደምትገኝ ሪፖርቱ ገልጿል።

በኢትዮጵያ የእርስ በእርስ ጦርነት እና ድርቅ ባስከተለው ረሃብ ከሐምሌ 2016 እስከ መስከረም 2017፤ 13 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ሪፖርቱ አመላክቷል።

ከእነዚህም መካከል ወደ አራት ሚሊዮን የሚጠጉት በዋናነት በ #ሶማሌ፣ በ #ትግራይ እና በ #ኦሮሚያ ክልሎች የሚገኙ ተፈናቃዮች መሆናቸው ተገልጿል።

ሪፖርቱ አክሎም ከአምስት አመት በታች ለሆኑ ህጻናት እና ነፍሰ ጡር ለሆኑ እንዲሁም ጡት ለሚያጠቡ ሴቶች የሚውል ከፍተኛ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት ማጋጠሙን አመልክቷል።

12-11-2016

ምሽት በረንዳ ላይ (በእውቀቱ ስዩም)አገር ምድሩ መሽቶሌቱ ምጣድ ሆኖ ፥ በኮከብ ተሟሽቶ  የጎዳናው መብራት ፥ጨለማው ላይ ሲገን  ከመስኮት አምልጦ ፥የወጣ ወጋንን ሳር ቅጠሉን ሲያሳይ አጥብቄ...
19/07/2024

ምሽት በረንዳ ላይ
(በእውቀቱ ስዩም)

አገር ምድሩ መሽቶ
ሌቱ ምጣድ ሆኖ ፥ በኮከብ ተሟሽቶ
የጎዳናው መብራት ፥ጨለማው ላይ ሲገን
ከመስኮት አምልጦ ፥የወጣ ወጋንን
ሳር ቅጠሉን ሲያሳይ
አጥብቄ ስፈልግ ፥የእለት ያይኔን ሲሳይ
የሌት አይኔን ሲሳይ

በኩርማን ገላዋ፤ እራፊ ደርባ
የራሷ ሻጭ ሆና ፤ለሸመታ ቀርባ
በሌት ይፋ ሆና፥ በቀን ልትደበቅ
ያልቀጠረችውን ፥የምትጠባበቅ
አንዲት ሴት እያየሁ
አሰላስላለሁ ፤

“ አብረዋት ያደጉ፤ ብጤዎቿ ሁሉ
በድሜና በውበት እሷን የሚያክሉ
ተድረው እንደ ሴት፥ ተከብረው እንደ ሰው
የባሎቻቸውን ደረት ተንተርሰው
ፍቅር ሲያጣጥሙ
ወይ በንቅልፍ ሲሰጥሙ
ይች ወገን አልባ
የሌሊት አበባ
በቀትር ተኝታ ለውድቅት የነቃች
የቱን ፍሬ በልታ ለዚህ ፍዳ በቃች ?”

እያልሁ አስባለሁ፥



ደሞ ከደጃፌ ትንሽ ማዶ ርቆ
የመሸበት ለማኝ ፤ መንገዱ ዳር ወድቆ

በግልጥ ይታየኛል
“ ረፍትን ላክልኝ ፥ወይ እንጎቻህን ጣል
በራብ እና በንቅልፍ ሰው እንዴት ይቀጣል"
የሚል ይመስለኛል ፤

በረንዳ ላይ ቆሜ፥ በሌሊት ስምሪት
ከመስኮት በወጣ፥ የብርሀን ቅሪት
አይቼ ማልዘልቀው
ያገሬ ጎዳና የት ላይ ነው የሚያልቀው
መከራና ውበት የሚያፈራርቀው::

መልካም ልደት Bewketu Seyoum ‼️

አንጋፋዎቹ አዋሽ ባንክ እና ዳሸን ባንክ በታሪካቸው ከፍተኛ የሆነውን ትርፍ አተረፉ  | የ12 ወራት የበጀት አመት መጠናቀቁን ተከትሎ አዋሽ ባንክ 14 ቢሊዮን ብር እንዲሁም ዳሽን ባንክ 6....
17/07/2024

አንጋፋዎቹ አዋሽ ባንክ እና ዳሸን ባንክ በታሪካቸው ከፍተኛ የሆነውን ትርፍ አተረፉ

| የ12 ወራት የበጀት አመት መጠናቀቁን ተከትሎ አዋሽ ባንክ 14 ቢሊዮን ብር እንዲሁም ዳሽን ባንክ 6.6 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘታቸውን ገልጸዋል፡፡

በግል የባንክ ዘርፍ አንጋፋ እና ቀዳሚ የሆኑት አዋሽ እና ዳሽን ባንክ በታሪካቸው ከፍተኛውን ትርፍ ማስመዝገባቸውን አዲስ ማለዳ ያገኘችው መረጃ ያመላክታል፡፡

የአዋሽ ባንክ ትርፍ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር 4.2 ቢሊዮን ብር ብልጫ አሳይቷል ተብሏል።

ደሸን ባንክ በበኩሉ በ2015 በጀት አመት ከግብር በፊት 5 ቢሊዮን ብር ትርፍ ማግኘቱን አዲስ ማለዳ መዘገቧ አይዘነጋም።

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ 41 ሚሊዮን ህፃናት ከ18 አመት በታች ሲሆኑ ከነዚህም ውስጥ 7 ሚሊዮን የሚሆኑት ወላጆቻቸውን ያጡ እና ለአደጋ የተጋለጡ ናቸዉ።ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵ...
17/07/2024

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ 41 ሚሊዮን ህፃናት ከ18 አመት በታች ሲሆኑ ከነዚህም ውስጥ 7 ሚሊዮን የሚሆኑት ወላጆቻቸውን ያጡ እና ለአደጋ የተጋለጡ ናቸዉ።

ኤስ ኦ ኤስ የህጻናት መንደሮች በኢትዮጵያ ባለፉት ሃምሳ ዓመታት በአሰቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ከ 8.1ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ህጻናትንና ቤተሰባቸውን እንዲሁም የሚኖሩበትን ማህበረሰብ ህይወት ወደተሻለ ደረጃ ለውጧል።

በቀጣይም በአማራጭ የቤተሰብ ክብካቤ፣ በቤተሰብ እና ማህበረሰብ አቅም ግንባታ፣ በአስቸኳይ ጊዜ ሰብዓዊ ድጋፍ፣ በትምህርት፣ ጤና እና በወጣቶች ማብቂያ ፕሮግራሞቻችን ተደራሽነታችንን በማስፋት ለብዙዎች እንድንደርስ ከጎናችን ይቁሙ።

ከስር ያለውን ሊንክ በመጫን ከ 50ብር ጀምሮ በመለገስ ይህንን የጀመርነውን በጎ አላማ ይደግፉ።
https://chapa.link/donation/view/DN-oD3RuyVnMqC8

SOS Children's Villages in Ethiopia

የእስራኤል ወታደሮች በየወሩ ከ2,500 በላይ ፍልስጤማውያንን ይገድሉ እንደነበር ተነገረ  |አለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት (ICJ) እስራኤል የዘር ማጥፋት ወንጀል ስምምነትን የሚጥሱ ድርጊቶ...
17/07/2024

የእስራኤል ወታደሮች በየወሩ ከ2,500 በላይ ፍልስጤማውያንን ይገድሉ እንደነበር ተነገረ

|አለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት (ICJ) እስራኤል የዘር ማጥፋት ወንጀል ስምምነትን የሚጥሱ ድርጊቶችን መፈጸሟ “አሳማኝ” ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል።አለም አቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት (ICJ) እስራኤል በጋዛ የዘር ማጥፋት ድርጊቶችን ለመከላከል እርምጃ እንድትወስድ አዟል።

በጥር ወር በጋዛ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 26,083 ሰዎች ሲሆኑ ከ64,400 በላይ ሰዎች ቆስለዋል።ከዚያን ጊዜ ጀምሮ የእስራኤል ጦር ተጨማሪ 12,630 ሰዎችን ገድሏል፡፡ከ24,600 በላይ ሰዎችን አቁስሏል፡፡ ይህም ማለት ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ በየወሩ ከ2,500 በላይ ፍልስጤማውያን ተገድለዋል።

የእስራኤል ወታደሮች በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሚተዳደሩትን ሲቪሎችን የሚያስጠልሉ ተቋማትን መምታታቸዉን ቀጥለዋል። የተባበሩት መንግስታት የፍልስጤም የስደተኞች ኤጀንሲ በጦርነቱ ወቅት በጋዛ ከሚገኙት ትምህርት ቤቶች 70 በመቶው የቦምብ ጥቃት ደርሶባቸዋ ብሏል፡፡ 95 በመቶዎቹ ጥቃት በተፈፀመበት ጊዜ እንደ መጠለያ ጣቢያ ያገለግሉ እንደነበር ተገልጿል፡፡

በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ በተከሰተው ትራፊክ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት አለፈ Roha Media |ሐምሌ 10-2016 ዓ/ም በጮርሶ ወረዳ ዲባንድቤ አከባቢ በተፈጠረው ትራፊክ አደጋ በሰውና በንብ...
17/07/2024

በጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ በተከሰተው ትራፊክ አደጋ የ5 ሰዎች ህይወት አለፈ

Roha Media |ሐምሌ 10-2016 ዓ/ም በጮርሶ ወረዳ ዲባንድቤ አከባቢ በተፈጠረው ትራፊክ አደጋ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን በአደጋው የ5 ሰዎች ህይወት ማለፉን የጮርሶ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የትራፊክ ፖሊስ አስተባባሪ ረዳት እንስፐክተር ግርማ ሳሊ ገልጸዋል።

የአደጋው መንስኤ ሲኖ ትራክ የተሪጋ ቁጠረ ኢት ከዲ (03)19178 የጎን ጥቁር 85_339 ከዲላ ወደ ሞያሌ ስጓዝ ከነበረው ዶልፈን ምንባሰ ከድ 0322503 በተመሳሳይ ከዲላ ወደ ቡለሆራ ስጓዝ ከነበረው በተቃራኒው ከቡለሆራ ስጓዝ ከነበረው ኤፈሳሪ መክና ተረጋ ጥቁር AA ከድ 03 74596 በመጋጨቱ መሆኑን ተገልጸዋል።

10-11-2016

ዘገባው የጌዴኦ ዞን የመንግስት ኮሙኒኬሽን

ኮድ 2 በፈረቃ ሊሆን ነውRoha Media |በአዲስ አበባ በስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት፤ የኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ ሊደረግ ነው፡፡በከተማዋ ጠዋትና ማታ የሚታየውን የትራ...
17/07/2024

ኮድ 2 በፈረቃ ሊሆን ነው

Roha Media |በአዲስ አበባ በስራ መግቢያ እና መውጫ ሰዓት፤ የኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ ሊደረግ ነው፡፡

በከተማዋ ጠዋትና ማታ የሚታየውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቀነስ የኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በፈረቃ እንዲቀሳቀሱ ሊደረግ መሆኑን የአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ለሸገር ተናግሯል፡፡

ጎዶሎ ቁጥር እና ሙሉ ቁጥር የኮድ 2 ተሽከርካሪዎችን በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ የሚያደርግ የህግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቷል ያሉት በባለስልጣን መስሪያ ቤቱ የትራፊክ ቁጥጥርና ሁነት አስተዳደር ዳይሬክተር የሆኑት አቶ አያሌው እቴሳ ናቸው፡፡

እቅዱ በ2 እና በ3 ወር ጊዜ ውስጥ፤ በከተማው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኮድ 2 ተሽከርካራች በፈረቃ አንዲንቀሳቀሱ ይደረጋል ተብሏል፡፡

የኦሮሚያንና የፌዴራልን ታርጋ ሳይጨምር የአዲስ አበባ ታርጋ ብቻ ያላቸው ተሽከርካሪዎች ከ755,000 በላይ ናቸው ያሉት አቶ አያሌው ከእነዚህ ውስጥ የበዙት ኮድ 2 ተሽከርካሪዎች በመሆናቸው ነው ጠዋትና ማታ በፈረቃ እንዲንቀሳቀሱ የሚደረገው ሲሉም ለሸገር ተናግረዋል፡፡

10-11-2016

Announcement | ስለ ማሳወቅ ለጠቅላላው ይረዳችሁ ዘንድ አንዳንድ እውነቶችን ስለ ማሳወቅ !ይህ የፌስ ቡክ ገፅ ነዋሪነቷን አሜሪካን ሀገር ያደረገችው የመዓዛ መሐመድ ገፅ አይደለም !ይ...
16/07/2024

Announcement | ስለ ማሳወቅ

ለጠቅላላው ይረዳችሁ ዘንድ አንዳንድ እውነቶችን ስለ ማሳወቅ !

ይህ የፌስ ቡክ ገፅ ነዋሪነቷን አሜሪካን ሀገር ያደረገችው የመዓዛ መሐመድ ገፅ አይደለም !

ይህ ገፅ March 21-2021 G.C የተከፈተ መሆኑን ከታች በ Screenshot ለማመላከት ተሞክሮሃል።

በአንፃሩ ደግሞ መዓዛ የምትገለገልበት የፌስ ቡክ ገፅ "80 plus K " ተከታይ ያለውና በ March 25-2022 የተከፈተ ነው።

ከሱስ የፀዳ በስነ-ምግባር የታነፀ ወጣት ለመፍጠር የሱስ-ማገገሚያ እና የስልጠና ማዕከል እየተገነባ ነው።Roha Media |  ትኩረቱን በወጣቶች እና ታዳጊዎች ላይ ያደረገው መልካም ወጣት የ...
16/07/2024

ከሱስ የፀዳ በስነ-ምግባር የታነፀ ወጣት ለመፍጠር የሱስ-ማገገሚያ እና የስልጠና ማዕከል እየተገነባ ነው።

Roha Media | ትኩረቱን በወጣቶች እና ታዳጊዎች ላይ ያደረገው መልካም ወጣት የተሰኘው የስልጠና መርዓ-ግብር ከሐምሌ 21 እስከ ጳጉሜ 2 በሐዋሳ ከተማ ይካሄዳል ተባለ።

የአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተ-ክርስቲያን መስራችና መጋቢ ወንጌል ፓስተር ዮናታን አክሊሉ ከሰባት ዓመት በፊት የተጀመረው የመልካም ወጣት ፕሮጀክት 180 ሺ የሚሆኑ ወጣቶችን ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን ፤በዘንድሮ ዓመት ደግሞ "መልካም ወጣት ወደ ብርታት" በሚል መሪ ቃል ለ 30 ሺ ሰዎች ተደራሽ ይሆናል ተብሏል።

ከዚህም ሌላ በሀገራችን ከቅርብ ጊዜ ወዲ እየተስፋፋ የመጣውን የወጣቶች የአዕምሮ መታወክ በሽታ ሊያክም የሚችል ሜንታል ሄልዝ ሴንተር በወላይታ ከተማ ፡በ500 ሚሊዮን ብር ወጭ አንድ ሺ ካሬ በሚሆን ቦታ ላይ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑንና በሶስት ዓመት ውስጥም እንደሚጠናቀቅ የፕሮጀክቱ ባለቤት ፓስተር ዮናታን ለሚዲያዎች እወቁልኝ ብሏል።

በተጨማሪም የታዳጊ እና ወጣቶች በጎ ስብዕና ማሰልጠኛ ማዕከል በሐዋሳ ከተማ በ 1.2 ቢሊዮን ብር ወጭ እየተሰራ የሚገኝ ሲሆን ፤ግንባታውም አሁን ላይ ሰባ ከመቶ መገባደዱ ተገልፃል።

የመልካም ወጣትን የስልጠና ዓላማ ሁሉም ሊደግፈው ይገባል ያለው ፓስተር ዮናታን በቀጣይም ከተለያዩ የዕምነት ተቋማት ጋር በጋራ አብሮ ለመስራት እንደታሰበ ተናግሯል።

ለዘንድሮው የመልካም ወጣት ስልጠና ምዝገባ ከነገ ጀምሮ እንደሚሆን የተገለፀ ሲሆን ማንኛውም ሰው በሐዋሳ የስድስት ቀናት ቆይታ ወጭ መሸፈኛ እንዲሆን አንድ ሺ አምስት መቶ ብር የመመዝገቢያ ይከፈላል ተብሏው።

09-11-2016 ዓ.ም

ኤርሚያስ አለባቸው

ከድሬዳዋ ወደ ሀረር ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አፈጋ የ11 ሰዎች ህይወት አለፈ👉🏼በሌሎች 10 ሰዎች ላይም ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷልበትናንትናው እለት ከሌሊቱ 6 ሰዓት...
16/07/2024

ከድሬዳዋ ወደ ሀረር ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ የትራፊክ አፈጋ የ11 ሰዎች ህይወት አለፈ

👉🏼በሌሎች 10 ሰዎች ላይም ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል

በትናንትናው እለት ከሌሊቱ 6 ሰዓት ከ 30 ላይ ሲሆን ከድሬዳዋ ወደ ሀረር 21 ሰዎችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ዶልፊን ተሽከርካሪ 75601 ኢቲ ከሆነ ሲኖትራክ ተሽከርካሪ ጋር ተጋጭቶ የ 11 ሰዎች ህይወት ወዲያዉኑ ማለፉን የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታዉቋል።

በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ደሊና ገበሬ ማህበር ቢርካ በተሰኘዉ አካባቢ ነዉ አደጋዉ ሌሊቱን የደረሰዉ። በአደጋዉ ሌሎች 10 ሰዎች ላይም ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል።

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ አደጋ ምርመራ ዲቪዥን ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ሰዓዳ መሀመድ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት የአደጋዉ መንስዔ በከባድ ፍጥነት ሲጓዝ የነበረዉ የህዝብ ማመላለሻ ዶልፊን ተሽከርካሪ ከከባድ መኪናዉ ጋር በመጋጨታቸው ነዉ ብለዋል።

አደጋዉ በተከሰተበት ወቅትም ከፍተኛ ዝናብ እየጣለ እንደነበርም የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ አደጋ ምርመራ ዲቪዥን ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ሰዓዳ መሀመድ ጨምረዉ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።

Address

Bole
Addis Ababa
71

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Roha Media ሮሃ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Roha Media ሮሃ ሚዲያ:

Share