Nahoo Television

Nahoo Television Nahoo TV Nahoo TV is a private Infotainment TV station with a motto of promoting Ethiopian Culture.

Nahoo Tv is a privately held media company established in 2016 in Ethipia with a motto of promoting Ethiopian Culture, History & general well being of the society. Main Office
Rosetta Bldg. 2nd Floor # 14/2010, Addis Ababa, Ethiopia

በኬንያ ዋና ከተማ አቅራቢያ የህክምና አውሮፕላን ተከስክሶ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ።በኬኒያ ርዕሰ መዲና ናይሮቢ አቅራቢያ በሚገኝ ህዝብ በሚበዛበት አካባቢ የህክምና ቡድኖችን ያሳፈረ አነስተኛ...
08/08/2025

በኬንያ ዋና ከተማ አቅራቢያ የህክምና አውሮፕላን ተከስክሶ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ።

በኬኒያ ርዕሰ መዲና ናይሮቢ አቅራቢያ በሚገኝ ህዝብ በሚበዛበት አካባቢ የህክምና ቡድኖችን ያሳፈረ አነስተኛ አውሮፕላን ተከስክሶ የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የአካባቢው ባለስልጣናት ገልጸዋል፡፡

የአየር አምቡላንስ አገልግሎት ሰጭ የሆነ አውሮፕላን ከኬንያ ዋና ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኝ የመኖሪያ መንደር ላይ ሐሙስ እለት መከስከሱን ግብረ ሰናይ ድርጅቱ በሰጠው መግለጫ አመልክቷል።

በአደጋው በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ አራት ሰዎች እና ምድር ላይ የነበሩ 2 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን በአካባቢው ኪያምቡ የተሰኘችው ግዛት ኮሚሽነር ሄነሪ ዋፉላ ተናግረዋል፡፡

አውሮፕላኑ ከዊልሰን አየር ማረፊያ ከተነሳ ከሦስት ደቂቃዎች በኋላ ከአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ጋር ያለው ግንኙነት መቋረጡን የኬኒያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣናቴ ገልጸዋል።

የኬንያ ቀይ መስቀል የነፍስ አድን ቡድኖቹ ከናይሮቢ ጋር በሚያዋስነው አውራጃ ኪያምቡ ወደሚገኘው የአደጋው ቦታ ማቅናታቸውን ገልጿል።

የአካባቢው ስታር ጋዜጣ የኬንያ መንግስት ባለስልጣናት ምንም አይነት ዝርዝር መረጃ አልሰጡም ሲል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል።

በኤልዳና ታደሰ

የምርጫ ሂደትን በተመለከተ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ መሆኑን ቦርዱ አስታወቀ።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ የምርጫ ሂደትን በተመለከተ ግንዛቤ የመፍጠር ...
08/08/2025

የምርጫ ሂደትን በተመለከተ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ መሆኑን ቦርዱ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ የምርጫ ሂደትን በተመለከተ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ መሆኑን ገለጸዋል።
ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ፤ ቀጣዩን ሀገራዊ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ለማካሄድ ቦርዱ ዝግጁ መሆኑንም አክለዋል። ቦርዱ በ2011 ዓ.ም በአዲስ መንገድ ከተደራጀ በኋላ አንድ ሀገራዊ ምርጫ እና ሶስት ህዝበ ውሳኔ አካሂዷል ሲሉ አስታውሰዋል።
ይህ ሂደት በተቋሙ ላይ የፈጠረው አቅም ቦርዱ መስራት የሚችልበት ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ተናግረዋል።
የቦርዱ አባላትን ጨምሮ የተቋሙን የሰው ሃይል አቅም የማጠናከር እና ወደ 20 ሺህ የምርጫ ጣቢያዎችን በጂአይኤስ የማስተሳሰር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል። በዚህም የምርጫ ታዛቢዎች ምርጫ ጣቢያዎችን በቀላሉ ማግኘት የሚችሉበትን ያካተተ መረጃ ሰብስበናል ነው ያሉት።
የምርጫ ቁሳቁሶች ስርጭት በሚከናወንበት ወቅት ምን ሊያጋጥም እንደሚችል የተነተነ የመረጃ ዝግጅት እንዳለ ገልጸው፤ ቦርዱ ቀጣዩን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችል ቁመና ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።
የምርጫ ሂደትን በተመለከተ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ በተለያዩ አካባቢዎች ግንዛቤ የመፍጠር ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።
ተደራሽነታቸው ውስን በሆኑ አካባቢዎች የማህበረሰብ ሬዲዮ አማራጭን በመጠቀም ግንዛቤ የማስጨበጥ ተግባር እየተከናወነ እንደሆነ አመልክተዋል።
ቦርዱ በራሱ ከሚሰራው የግንዛቤ ማስጨበጥ ተግባር በተጨማሪ ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በመተባበር እየሰራ እንደሆነም ጠቁመዋል።

በየሶስት ወሩ የሚደረገው የኤሌክትሪክ ዋጋ ማሻሻያ ተርፍን ታሳቢ ያደረገ አለመሆኑን ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2017 ዓ.ም አመታዊ ጋዜጣዊ መግለጫውን በትላንት...
08/08/2025

በየሶስት ወሩ የሚደረገው የኤሌክትሪክ ዋጋ ማሻሻያ ተርፍን ታሳቢ ያደረገ አለመሆኑን ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2017 ዓ.ም አመታዊ ጋዜጣዊ መግለጫውን በትላንትናው እለት ነሀሴ 01 ቀን 2017 ዓ.ም ሰጥቷል።
በዚህም አመታውዊ መግለጫው ኢትዮጵያ ውስጥ ለአራት ዓመታት በየሦስት ወሩ እየጨመረ የሚሄደው የኤሌክትሪክ ኃይል የመሸጫ ዋጋ ማሻሻያ "ትርፍን ታሳቢ ያደረገ አይደለም" ሲል ገልጿል። የኤሌክትሪክ ሽያጭ ተመን "አሁንም ከዋጋው በታች ነው" ያለው ተቋሙ፤ "ዝቅተኛ ገቢ ያለውን ሕዝብ በማይጎዳ መልኩ" የተሻሻለ ነው ሲል አክሏል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የሕዳሴ ግድብ ካለምንም የውጭ ብድር በመንግሥት እና ሕዝብ ተሰርቶ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን በመግለጫቸው ተናግረዋል።
ኃላፊው አክለውም ግድቡ የሚመረቅበት ጊዜ ይፋ ከሆነ ወዲህ በግብጽ በኩል በምርቃቱ ላይ እክል ለመፍጠር "ከፍተኛ ሩጫ አለ" ሆኖም "ውጤቱን ሊቀይሩት አይችሉም" ብለዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በቅርቡ ይፋ ያደረገው የኃይል መሸጫ ዋጋ ተቋሙ የኃይል ማመንጫዎችን፣ ማስተላለፊያ እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ለመገንባት፣ ጥገናዎችን ለማከናወን የሚያወጣውን ወጪ ለመሸፈን የሚያስችል አለመሆኑን ገልጿል። እንደ ማሳያም ተቋሙ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ተበድሮት የነበረው የ260 ቢሊዮን ብር ዕዳ በመንግሥት መዞሩን ጠቅሷል። የተቋሙ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንዳሉት የኤሌክትሪክ ኃይል ለሕዝብ ይቀርብ የነበረው በኪሳራ ነው።
አሁን የተደረገው ጭማሪ ምንም ትርፍ ሳይታሰብበት ዋጋን ብቻ እንዲመልስ ታሳቢ በማድረግ መሆኑንም ተቋሙ አስታውቋል። የሕዳሴ ግድብን ጨምሮ 20 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃላይ የማምረት አቅሙ 7 ሺህ 910 ሜጋ ዋት መሆኑን ገልጿል። በዚህ ምክንያት 46 በመቶው የኢትዮጵያ ሕዝብ ኤሌክትሪክ የማያገኝ ከመሆኑም በላይ መቆራረጡ አሁንም ከኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር ያለ የጋራ ችግር ነው ብለዋል ኃላፊው።

08/08/2025

ባሳለፍነው ማክሰኞ ነፋስ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ በሰሜን ወሎ ዞን በጃራ መጠለያ የሚገኙ ተፈናቃዮች ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገለጸ።
በሰሜን ወሎ ዞን ሀብሩ ወረዳ ስር በሚገኘው ጃራ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ ሀምሌ 29 ቀን 2017 ዓ.ም ለ40 ደቂቃ ያህል ነፋስ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ 23 ሰዎች ሲቆስሉ በ61 መጠለያ ጣቢያ በሚኖሩ 366 አባወራዎችን ደግሞ መጠለያ አልባ ማድረጉ በመጠለያው የሚኖሩ ተፈናቃዮች ገልጸዋል።
ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በአቅራቢያው ወደ ሚገኝ የጤና ተቋማት ታክመው መመለሳቸውን የተናገሩት በመጠለያው ያሉ ተፈናቃዮች "መጠለያቸው የፈረሰባቸው ሰዎች ከሌሎች ተፈናቃዮች ጋር ተቀላቅለው ይገኛሉ" ብለዋል። ተፈናቃዮቹ አሁንም በከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንደሚገኙ ነው የተናገሩት።
በመጠለያ ጣቢያዉ ዉስጥ ያለ ትምህርት ቤት መፍረስሱም ተመላክቷል። አሁን ላይ የቀሩት የመጠለያ ቤቶች ለአደጋ የተጋለጡ በመሆናቸው ዝናብ ሲመጣና ሌሊቱን ከቤት ውጭ እንደሚያሳልፉ የሚገልጹት የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮቹ ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት ስጋት ላይ ነን ብለዋል፡፡
በጉዳዩ ዙሪያ የአማራ ክልል አደጋ ስጋት እና ስራ አመራር ኮሚሽን የደረሰው ጉዳት የተባለውን ያህል አለመሆኑን ገልጿል።
ጉዳቱ ከደረሰ በኃላ ከፌደራል፣ ከክልል እና ከዞን የተውጣጣ የባለሙያዎች ቡድን ወደ ስፍራው ተጉዞ ጉብኝት ማድረጉን የገለጸው የክልሉ አደጋ ስጋት እና ስራ አመራር ኮምሽኑ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለው ዝናብ የ61 አባወራዎች መጠለያ መጎዳቱን እና በፍጥነት መልሶ ለመጠገን የሚያስችል ቁሳቁስ ወደ ስፍራው እየተጏጏዘ እንደሆነ አክሏል።
እንደ መፀዳጃና ማብሰያ ክፍሎችም በዛው ጥገና እንደሚደረግላቸው የክልሉ አደጋ ስጋት እና ስራ አመራር ኮምሽን አስታውቋል። በሰሜን ወሎ ዞን በሚገኘው ጃራ መጠለያ ጣቢያ ከ8 ሺ በላይ ተፈናቃዮች እንደሚገኙ አስቀድሞ የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

https://youtu.be/AieXmYwQxV8?si=eM-IWalw2y4hekDe
07/08/2025

https://youtu.be/AieXmYwQxV8?si=eM-IWalw2y4hekDe

ማሳሰቢያ ተሰጠ! - የመንግስታ ባለስልጣናቱ ታሰሩ/የዜግነት አገልግሎት የቀድሞ ከፍተኛ አመራሮች/ የብሔራዊ ባንክ ገዢው ማሳሰቢያ/ “ከእውቅና ውጪ” የተባለው ከናይሮቢ አዲስ አበባ ጉዞ ...

የተባበሩት መንግስታት የኤም 23 ታጣቂ ቡድን በሰላማዊ ዜጎች ላይ የፈጸመውን ጥቃት አወገዘ።በቅርቡ በኳታር ዶሃ የተፈረመውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመተላለፍ በሩዋንዳ የሚደገፈው ኤም 23 ...
07/08/2025

የተባበሩት መንግስታት የኤም 23 ታጣቂ ቡድን በሰላማዊ ዜጎች ላይ የፈጸመውን ጥቃት አወገዘ።
በቅርቡ በኳታር ዶሃ የተፈረመውን የተኩስ አቁም ስምምነት በመተላለፍ በሩዋንዳ የሚደገፈው ኤም 23 ታጣቂ ቡድን በምስራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በቀጠለው ውጊያ በሰላማዊ ዜጎች ላይ እየፈጸመ ያለውን አስከፊ ጥቃት የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ቢሮ አውግዟል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፅህፈት ቤት ቃል አቀባይ ጄረሚ ሎሬንስ እንዳስታወቁት M23 በሩዋንዳ የመከላከያ ሃይል አባላት የተደገፈ ቢያንስ 319 ንፁሀን ዜጎችን በሰሜን ኪቩ ግዛት ውስጥ በሚገኙ አራት መንደሮች ውስጥ ገድሏል።
ቢያንስ 48 ሴቶች እና 19 ህጻናትን ጨምሮ አብዛኛዎቹ ተጎጂዎች ለእርሻ ስራ የተሰማሩ ገበሬዎች መሆናቸውም ተመላክቷል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር ቮልከር ተርክ በምስራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ግጭቶች ውስጥ ሁሉም ወገኖች ሰላማዊ ሰዎችን ከጉዳት እንዲከላከሉ እና በአለም አቀፍ የሰብአዊ ህግ እና በአለም አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ህግ መሰረት ሁሉንም ግዴታዎች እንዲወጡ ጥሪ አቅርቦል።
የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጦር ከአማፂ ቡድኑ ጋር ለረጅም ጊዜ ሲታገል የቆየ መሆኑም ተገልጿል።

07/08/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ የንግዱ ማህበረሰብ ኢ-መደበኛ የውጭ ምንዛሪ ገበያን ከመጠቀም እንዲቆጠብ አሳሰቡ።
ከውጭ ምንዛሪ ጋር ተያይዞ የመደበኛ ባንክ ሥርዓት በማይጠቀሙ አካላት ላይ እስከ መውረስ የሚደርስ ርምጃ እንደሚወሰድም አስጠንቅቀዋል።
የብሔራዊ ባንክ ገዢው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንደ አስፈላጊነቱ የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ማካሄዱን እንደሚቀጥል አስታውቀዋል። ይህ የሚሆነውም ባለፈው ዓመት የባንኩ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት መጠን በሶስት እጥፍ በጨመሩ ምክንያት መሆኑን አስረድተዋል።
ከውጭ ምንዛሪ ገቢ ከፊሉን ለባንኮች በጨረታ መቅረቡ በባንኮች ዘንድ የሚኖረውን የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት ከማሳደግ ባለፈ የዋጋንና የውጭ ምንዛሪ ለማረጋጋት ያስችላል ብለዋል። ባንኮቹ በሚቀጥለው ሳምንት የውጭ ምንዛሪን በበቂ ሁኔታ ለደንበኞቻቸው እንደሚያቀርቡም አክለዋል።
አያይዘውም አነስተኛ የውጭ ምንዛሪ ለሚፈልጉ የውጭ መንገደኞች ደግሞ ፍላጎታቸውን የሚያሟሉ የውጭ ምንዛሪ ቢሮዎች እና ንግድ ባንክ ጋር በመሄድ ያለ ምንም ችግር የውጭ ምንዛሬ ማግኘት እንደሚችሉ ገልጸዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ ለውጭ ምንዛሪ ፋላጎት መደበኛውን የባንክ ሥርዓት መጠቀም እንዳለበትም አሳስበዋል። በህገ ወጥ ምንዛሪ ላይ የሚሳተፉ ነጋዴዎች ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
ነጋዴዎች ወደ ትይዩ የውጭ ምንዛሪ ገበያ የሚሄዱት ከባንኮች በቂ ምንዛሪ ያለማግኘት ቅሬታ፤ አሁን ላይ መፍትሄ እንደተሰጠው ገልጸዋል።
ሌላው የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት ታማኝነት ለመሸርሸርና የገበያ ዋጋን ለማዛበት በሚሰሩ መቀመጫቸውን ውጭ ሀገራት ያደረጉ ህገ-ወጥ ገንዘብ አስተላላፊዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ ሲሆን ይህም እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል።

ከናይሮቢ አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ስለመጀመሩ የተሰራጨው መረጃ ከእውቅናው ውጭ መሆኑን  የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።የትራንስፖርት እና ሎጂ...
07/08/2025

ከናይሮቢ አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ስለመጀመሩ የተሰራጨው መረጃ ከእውቅናው ውጭ መሆኑን የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር፤ "ከናይሮቢ - አዲስ አበባ በአውቶብስ የሕዝብ ትራንስፖርት ተጀመረ" በሚል በሀገር ውስጥና በአለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የተሰራጨው ዘገባ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እውቅና ውጪ መሆኑን አስታውቋል።
“አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች” የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት ከኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ በአውቶብስ ተጓዦችን ማመላለስ መጀመሩን በትናንትናው ዕለት ቢቢሲ አማርኛ መዘገቡን ናሁ ቲይሌቭዥን ለመመልከት ችሏል።
ድርጅቱ ባለፈው ሳምንት እሁድ በይፋ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የድርጅቱ ዳይሬክተር ሚካኤል ጄምስ ማቺዮ መናገራቸውን ዘገባው አክሏል።
ይሁን እንጂ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ጉዳዩን አስመልክቶ፥ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ትናንት ባወጣው አጭር መግለጫ፤ ቢቢሲ አማርኛ በድረገጹ "አቢሲኒያ ሌግዠሪ ኮች” የተሰኘ የትራንስፖርት አገልግሎት አቅራቢ ድርጅት ከኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ ወደ አዲስ አበባ በአውቶብስ ተጓዦችን ማመላለስ መጀመሩን ሰለማሳወቁ መዘገቡን መመልከቱን አስታውቋል።
ይህንን መረጃ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ህጋዊነቱን ሳያረጋግጡ ሌሎችም ሚዲያዎች ማሰራጨታቸውንም የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር በይፋዊ የማህበራዊ ትስስስር ገጹ አስፍሯል። ሆኖም “ይህንን ጉዳይ በሀገሪቱ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ጉዳዮች ላይ በአዋጅ ሀላፊነት የተሰጠው ሚኒስቴር መስሪያቤታችን የማያውቀው ነው” ማለቱን ናሁ ቴሌቭዥን ከሚንስቴሩ ያገኘው መረጃ ይጠቁማል።
እንደሀገር በ 2018 በጀት አመት በሁለቱ ሀገራት መካከል ትስስር ለመፍጠር ይህንን አገልግሎት ለመጀመር እቅድ የተያዘ ቢሆንም ሂደቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል የትብብር ስምምነት መፈራረም፣ ታሪፍ በጋራ መወሰን እና ሌሎች የዲፒሎማሲ ጉዳዮች የሚፈልግ በመሆኑ ከሚመለከተው መንግስታዊ መስሪያቤት ጋር በመተባበር የሚሰራበት መሆኑንም ሚንስቴሩ ገልጿል።

https://youtu.be/mxQUK3rWBR4?si=FuqErew7OzvXdD2k
06/08/2025

https://youtu.be/mxQUK3rWBR4?si=FuqErew7OzvXdD2k

በኤርትራ የተወረሰው የኢትዮጵያ ገንዘብ - “ማስመለስ አልቻልኩም” - በነዋሪዎች ቅሬታ የቀረበበት የቆሻሻ ክምር/ በኤርትራ መንግስት የተያዘው የአየር መንገዱ ገንዘብ/ በትግራይ ክልል .....

https://youtu.be/BPcHX5RxQeM?si=KODiN8KNVtfP5nvz
06/08/2025

https://youtu.be/BPcHX5RxQeM?si=KODiN8KNVtfP5nvz

አወዛጋቢው የበቴ ኡርጌሳ ግድያ - ስራቸውን የለቀቁት የመንግስት ባለስልጣናት/ የኢትዮጵያ አምባሳደር በሶማሊያ/ ሀገራዊ ሰላምና የሃይማኖት ተቋማት/ የስራ መልቀቂያ ያስገቡት የኢሰመኮ ...

06/08/2025

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን “አካባቢን በክለዋል” ባላቸው ከ3 ሺህ በላይ ተቋማት ላይ እርምጃ መዉሰዱን አስታወቀ፡፡

ባለስልጣኑ በ2017 ዓ.ም አቅዶ የከወናቸውን ስራዎችን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን ሀምሌ 30 ቀን 2017 ዓ.ም መግለጫ ሰጥቶል፡፡
በ2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማና አካባቢዋ ባሉ 14 ሺህ 872 አገልግሎት ሰጪና አምራች ተቋማት ላይ ክትትልና ቁጥጥር ማድረጉንም ባለስልጣኑ አብራርቷል፡፡
በዚህም ክትትልና ቁጥጥር ካደረገባቸው ተቋማት ውስጥ 3 ሺህ 249 አገልግሎት ሰጪና አምራች ተቋማት አካባቢ ሲበክሉ ተገኝተዋል ብለዋል፡፡
ባለስልጣኑ በእነዚህ ተቋማት ላይ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያና የማሸግ እርምጃ እንደወሰደባቸውም ገልጻል፡፡
የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዲዳ ድሪባ እንደገለጹት የከተማዋን የአካባቢ ብክለት፣ የድምፅና የፍሳሽ ብክለት፣ ከተሽከርካሪ የሚለቀቀውን ጭስ የመከላከልና የመቆጣጠር ሥራ ተሰርቷል ብለዋል ።

በባለስልጣኑ የማሸግ እርምጃ ከተወሰደባቸው ተቋማት መካከል 6 የፕላስቲክ ፋብሪካዎች፣ 23 የብሎኬት ፋብሪካ፣ 1 የሶፍት ፋብሪካ፣ 102 የምሽት ጭፈራ ቤቶች፣ 15 ጋራዥ ቤቶች፣ 1 ዘይት ፋብሪካ፣ 1 ማሽነሪና ብረታ ብረት አምራች ተቋም እንዲሁም 1 የቤትና የቢሮ እቃዎች ማምረቻ ድርጅት የማሸግ እርምጃ እንደተወሰደባቸው ተገልጿል፡፡
ባለስልጣኑ በእነዚህ እና በመሰል የደንብ ጥሰቶች 1.6 ሚሊየን ብር ከቅጣት መሰብሰቡን መግለጹን ናሁ ቴሌቭዥን ሰምቷል፡፡

ዘገባው የባልደረባችን ኤልዳና ታደሰ ነው።

በትግራይ ክልል በተከሰተ ድርቅ የሰዎች እና እንስሳት ሕይወት ማለፉ ተገለጸ።ከጦርነት በኋላ በከፋ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ቀውሶች ውስጥ በሚገኘው የትግራይ ክልል ተፈጥሮአዊ ክስተ...
06/08/2025

በትግራይ ክልል በተከሰተ ድርቅ የሰዎች እና እንስሳት ሕይወት ማለፉ ተገለጸ።
ከጦርነት በኋላ በከፋ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ቀውሶች ውስጥ በሚገኘው የትግራይ ክልል ተፈጥሮአዊ ክስተቶች ተጨማሪ ጫና እየፈጠሩ መሆናቸው ተጠቁሟል። እንደ ክልሉ አስተዳደር ቁጥራዊ መረጃዎች መሰረት በትግራይ ተፈናቃዮችን ጨምሮ 2.4 ሚልዮን ሕዝብ የምግብ እርዳታ የሚፈልግ ሲሆን በአንዳንድ የክልሉ ወረዳዎች በተከሰተ ድርቅ ደግሞ በሰዎችና እንስሳት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት የከፋ ሆኖ እንደሚገኝ ተገልጿል።
በማዕከላዊ ትግራይ ዞን ቆላ ተምቤን ወረዳ በሚገኘው ያቄር የተባለ አካባቢ ለረዥም ጊዜ ዝናብ አለመዝነቡን ተከትሎ ከፍተኛ ድርቅ ተከስቶ እንዳለ የወረዳው የኢኮኖሚ እና ገጠር ልማት ዘርፍ ሐላፊ አቶ ጎይትኦም ገብረ ሐዋርያ፤ በቆላማ ያቄር ቀበሌ ብቻ ካለፈው ግንቦት ወር ወዲህ በረሃብ ምክንያት ሰባት ሕጻናትን ጨምሮ 22 ሰዎች መሞታቸው መረጋገጡን የጀርመን ድምጽ ዘግቧል።
ከዚህ በተጨማሪ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ከብቶች እና ሌሎች እንስሳት በመኖ እጦት ምክንያት መሞታቸውንም አክለው መግለጻቸውን ዘገባው አክሏል።
በአካባቢው ከተከሰተው ድርቅ በተጨማሪ መሠረተ ልማት አለመኖሩ ደግሞ ሁኔታውን የከፋ እንዳደረገው አቶ ጎይትኦሞ ገብረ ሐዋርያ ጨምረው ገልፀዋል።
ሰሞኑን ከረሃብ ጋር በተያያዘ በሰዎች እና እንስሳት የሚደርስ ጉዳት መቀጠሉን የሚያነሱት ሐላፊው፥ እስካሁን በመንግሥትም ይሁን በእርዳታ ድርጅቶች የተደረገ ተጨባጭ ድጋፍ አለመኖሩንም ጠቁመዋል።
ይህን ጉዳይ በተመለከተ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ምላሽ በዘገባው ያልተካተተ ሲሆን ናሁ ቴሌቭዥን ከኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ያደረገው ጥረት ሳይሳካለት ቀርቷል።
ዓለም አቀፍ ተቋማት ያደርጉት የነበረ የምግብ እርዳታ መጠን መቀነሱ እንዲሁም እንዳንዶች እርዳታ ሰጪ ተቋማት አቅርቦት ማቋረጣቸውን ተከትሎ በትግራይ ካለውም የከፋ ሰብአዊ ቀውስ እንዳይከሰት ስጋት መኖሩን የክልሉ ባለሥልጣናት ከዚህ ቀደም ሲገልፁ ቆይተዋል።

Address

Rosetta Bldg. 2nd Floor # 14/2010
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nahoo Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share