DAILY News Ethiopia

DAILY News Ethiopia ሁሌም ትኩስ እና አዳዲስ መረጃዎችን ያገኛሉ ። ስለተከታተሉን ከልብ እናመሰግናለን !!!

ድምፃዊ አሊ ቢራ ከዚህ አለም በሞት ተለየ!እዉቁ እና ተወዳጁ የኦሮምኛ ሙዚቃ አቀንቃኝ ድምፃዊ አሊ ቢራ ከዚህ አለም በሞት መለየቱን የኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ባወጣዉ የሀዘን ...
06/11/2022

ድምፃዊ አሊ ቢራ ከዚህ አለም በሞት ተለየ!

እዉቁ እና ተወዳጁ የኦሮምኛ ሙዚቃ አቀንቃኝ ድምፃዊ አሊ ቢራ ከዚህ አለም በሞት መለየቱን የኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ቢሮ ባወጣዉ የሀዘን መግለጫ አስታዉቋል።

እኔ እና አንቺ ለወዳጅ ዘመድ እንዲሁም ለመላው አድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል።

DAILY News Ethiopia

 #መልዕክት🕊የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የፕሪቶሪያውን የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ስምምነት አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ መላው ህዝብ በጦርነቱ ሳቢያ የ...
06/11/2022

#መልዕክት🕊

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል የፕሪቶሪያውን የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ስምምነት አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ መላው ህዝብ በጦርነቱ ሳቢያ የተጎዱ ወገኖችን ለመደገፍ እና ለዘላቂ ሰላም እንዲነሳ ጥሪ አቅርቧል።

የካውንስሉ ፀሀፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ ካስተላለፉት መልዕክት ፦

" የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊ እንዲሆንና ሕዝባችን ከፍርሃት፣ ከጭንቀት፣ ከስድትና መከራ ያርፍ ዘንድ የሁሉንም ወገኖች ጥረት ይጠይቃል።

መላው ሕዝባችን አፍራሽ ከሆነ ተግባር በመራቅ እና ባለፉት ሁለት ዓመታት በደረሰባቸው ጉዳት ያዘኑትን ወገኖች በማጽናናት፣ ቤታቸውና ንብረታቸው የወደመባቸውን መልሶ በማቋቋም፤ የአካል ጉዳት የደረሰባቸውን በመደገፍ እና በማበርታት ለዘላቂ ሰላም በአንድነት እንድንነሳ ጥሪያችን እናስተላልፋለን።

ስምምነቱ እውን እንዳይሆንና ተመልሰን ወደ ግጭት እንድንገባ የሚያደርጉ ቅስቀሳዎች ሊኖሩ ይችላሉ ፤ በልዩ ልዩ የመገናኛ ዘዴዎች የሚተላለፉ አፍራሽ መልዕክቶችን ቸል በማለት ለስምምነቱ ተግባራዊ መሆን ተግተን ልንሰራ ይገባል።

ከዚህ በተጨማሪም በጦርነቱ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው የትግራይ፣ የአማራና የአፋር ሕዝቦች ለጋራ ሰላምና ዕድገት በይቅርታ ተቀራርበው እውተኛ እርቅ እንዲያከናውኑ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች በአንድነት በመቆም መስራት ይገባል።
.. የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስል አቅም በፈቀደው ሁሉ ለሀገር ሰላምና ለሕዝቦችዋ ዕድገት አስፈላጊውን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኋላ አይልም። "

DDAILY News EthiopiaNDAILY News EthiopiaEDAILY News Ethiopia

ከሰላም ስምምነቱ ማግስት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦንድ ሽያጭ በዓለም ደረጃ በፍጥነት ጨምሯል *********************** በፌዴራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል ከተደረገው የሰላ...
06/11/2022

ከሰላም ስምምነቱ ማግስት የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦንድ ሽያጭ በዓለም ደረጃ በፍጥነት ጨምሯል
***********************

በፌዴራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል ከተደረገው የሰላም ስምምነት ጋር ተያይዞ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የኢትዮጵያ ‘ዩሮ ቦንድ’ ገዢ ኢንቨስተሮች ቁጥር በአንዴ በዓለም ደረጃ መጨመሩን የምጣኔ ሀብት ባለሙያው አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ አመለከቱ።

በጦርነት የወደሙ አካባቢዎችን ለመገንባት የሚፈሰው መዋዕለ ንዋይ በተገቢው ከተተገበረ ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥርም አክለው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ የኢንቨስተሮች ፍሰትን ለመጨመር ከዓለም ኢንቨስተሮች የተበደረችው የአንድ ቢሊዮን ዶላር ‘ዩሮ ቦንድ’ በጦርነቱ ምክንያት ኢንቨስተሮች ወደ አገሪቱ የመሄድ ፍላጎት በማጣታቸው የቦንዱ ዋጋ በዓለም ገበያ በጣም ወርዶ እንደነበር አቶ ዘመዴነህ ለኢፕድ ገልጸዋል። ነገር ግን ከስምምነቱ ማግስት ጀምሮ ዋጋው በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል።

DAILY News Ethiopia

06/11/2022

የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ በሚፈቱበት ሁኔታ ላይ ለመወያየት የሁለቱ ወታደራዊ አመራሮች የፊታችን ሰኞ በኬኒያ ሊገኛኙ ነዉ

በደቡብ አፍሪካዋ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ እንቅስቃሴ መጀመሩን የጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሚኒስትር አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን አስታወቁ።

አምባሳደሩ ሬድዋን ሁሴን የስምምነት ሂደቱን አስመልክቶ መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ላደረጉ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላት ማብራሪያ እየሰጡ ይገኛሉ ሲል አል አይን ዘግቧል።

በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል በደቡብ አፍሪካ ሲካሄድ የነበረው የድርድር ውጤት በሳለፍነው ረቡዕ ምሽት ይፋ መደረጉ የሚታወስ ሲሆን፤ በድርድሩ ስምምነት ከተደረሰባቸው ጉዳዮች ውስጥም ግጭትን በዘላቂነት ማቆም፣ ሰብዓዊ እርዳታን ያለገደብ ማድረስ፣ በሀገሪቱ ህገ መንግስት መሰረት ህግና ስርዓትን ማስከበር አንዲሁም የህወሓት ታጣቂዎችን ትጥቅ ማስፈታትየሚሉት ተጠቃሾች ናቸው።

አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን በማብራሪያቸው ፤ በስምምነቱ መሠረት የህወሓት ታጣቂዎች ትጥቅ በሚፈቱበት ሁኔታ ላይ ለመወያየት የሁለቱ ወታደራዊ አመራሮች የስልክ ልውውጥ ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

በዚህም የሁለቱ ወታደራዊ አመራሮች የፊታችን ሰኞ በኬንያ ናይሮቢ እንደሚገናኙ እና ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ ውይይት እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።

በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የደህንነት ጉዳዮች አማካሪ የሆኑት አምባሳደር ሬድዋን እና በህወሓት በኩል ቃል አቀባዩ አቶ ጌታቸው ረዳ 10 ገፆችና 15 አንቀፆች ባሉት የሰላም ስምምነት ሰነድ ላይ ፊርማቸውን አኑረዋል፡፡ የህወሓቱ ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ የተደረሰው ስምምነት ትልቅ ብስራት ነው ማለታቸዉ ይታወሳል።

የሰላም ስምምነቱን ቀዳሚ የሆነዉን ህወሓት ትጥቅ በሚፈታበት ዙሪያ ለመናገገር እና ተግባራዊ ለማድረግ የሁለቱ ከፍተኛ ወታደራዊ አዛዦች የፊታችን ሰኞ በኬኒያ ሊገናኙ መሆኑ ተገልጿል።

DAILY News Ethiopia

ኢኤምኤስ የመከላከያ ምንጭ ጠቅሶ እንደዘገበው የኢኤፍድሪ ጠቅላይ ኢታማዦር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላና የትህነግ ማዕከላዊ ኮማንድ ፖስት አዛዥ ታደሰ ወረደ (ወዲ ወረደ) ዛሬ በስልክ ተገናኝተ...
06/11/2022

ኢኤምኤስ የመከላከያ ምንጭ ጠቅሶ እንደዘገበው የኢኤፍድሪ ጠቅላይ ኢታማዦር ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላና የትህነግ ማዕከላዊ ኮማንድ ፖስት አዛዥ ታደሰ ወረደ (ወዲ ወረደ) ዛሬ በስልክ ተገናኝተው የትህነግ ወታደሮች ትጥቅ የሚፈቱበት አካሄድ ላይ የመጀመሪያውን ውይይት አድርገዋል። በስምምነቱ መሰረት በቀጣይ አስር ቀናት የትህነግ TDF የተሰኘው ታጣቂ ትጥቅ ይፈታል።

ዝርዝር እቅዶች ላይ የኢትዮጰያ መከላከያ መኮንኖችና የትህነግ የጦር መሪዎች በአካል ተገናኝተው ይመክራለሁ። በስምምነቱ መሰረት ታጣቆዎች ትጥቅ ፈተው ወደ መደበኛ ህይወታቸው የሚመለሱበት መርሀግብር ይከተላል። ለዚህም የመጀመሪያውን ግኑኝነት ብርሃኑ ጁላ እና ወዲ ወረደ በስልክ ዛሬ መነጋገራቸው ተሰምቷል።

DAILY News Ethiopia

 #ተስፋ በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከምንም በላይ ለበርካታ ወራት የእናት አባቶቻቸውን ፤ የእህት ወንድሞቻቸውን ፣ የወዳጆቻቸውን ድምፅ ያልሰሙ እጅግ በርካቶች ስምምነቱ በፍጥነት  #ወደተግ...
05/11/2022

#ተስፋ

በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከምንም በላይ ለበርካታ ወራት የእናት አባቶቻቸውን ፤ የእህት ወንድሞቻቸውን ፣ የወዳጆቻቸውን ድምፅ ያልሰሙ እጅግ በርካቶች ስምምነቱ በፍጥነት #ወደተግባር ገብቶ ያናፈቋቸውን ሁሉ ድምፃቸውን ሊሰሙ ጓግተዋል።

ከዚህ ቀደም የባንክ አገልግሎት በመኖሩ እያገዟቸው የነበሩ መላ ቤተሰቦቻቸውን ዳግም አግኝተዋቸው የየትኛውም የእርዳታ ድርጅት እና ተቋም /አካል ደጅ እንዳይጠኑ ለማድረግና ያለባቸውን ችግር ለመቅረፍ እየተጠባበቁ ነው።

ቤተሰቦቻቸው " በህይወት ይኑሩ አይኑሩ " እርግጠኛ ያልሆኑ ሚሊዮኖች የሰላም ስምምነቱ እጅግ በፍጥነት ተተግብሮ ፣ መሰረታዊ አገልግሎት ጀምሮ ለማየት ተስፋን ሰንቀዋል።

ከማንም ከምንም በላይ የጦርነቱ ቀጥተኛ ተጎጂዎች ህመማቸው ፣ ናፍቆታቸው ፣ ሀዘናቸው የከፋ ነውና ይህ የሰላም ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን እና እፎይ እንዲሉ በተለይ አፍራሽ ስራ የሚሰሩ ፣ የበለጠ ጥላቻን የሚዘሩ ፤ ሰላም በመሆኑ ጥቅማቸው የሚጎድልባቸው አካላት ከድርጊታቸው ቢታቀቡ መልካም ነው።

የሰላም ስምምነት መፈረሙ " የመጀመሪያው እርምጃ " እንጂ የመጨረሻ አይደለምና በተለይ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ለስኬቱ የራሳቸውን በጎ ድርሻ መጫወት ይጠበቅባቸዋል። በሰላም ሁሉም አሸናፊ ነውና ከብሽሽቅ ፣ ከጥላቻ ከአጉል የአሸናፊነት ስሜት መራቅ ይገባል።

#ሰላም

DAILY News Ethiopia

የ ' ሰላም ስምምነቱ '  #ስኬታማ እንዲሆን ምን ይደረግ ?የፕሪቶሪያው የ "ሰላም ስምምነት" ስኬታማ ሊሆን የሚችለው ስምምነት የተደረሰባቸው ነጥቦች በአግባቡ መሬት ይዘው፤ ሲፈጸሙና የጦርነ...
05/11/2022

የ ' ሰላም ስምምነቱ ' #ስኬታማ እንዲሆን ምን ይደረግ ?

የፕሪቶሪያው የ "ሰላም ስምምነት" ስኬታማ ሊሆን የሚችለው ስምምነት የተደረሰባቸው ነጥቦች በአግባቡ መሬት ይዘው፤ ሲፈጸሙና የጦርነቱ ሰለባ የሆነው ሕዝብ እፎይታን ሲያገኝ እና ሲታከም ብቻ መሆኑን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ም/ቤት በላከል መግለጫ አሳውቋል።

ም/ ቤቱ የሰላም ስምምነቱ ፍሬያማ ይሆን ዘንድ ፦

- የኢትዮጵያ መንግሥት እና ሕወሓት በስምምነቱ ማእቀፍ ሊተገብሩ በተስማሙት ሠነድ መሠረት ፦ የአፈጻጸም ሂደቱ አካታች ፣ ተዓማኒ እና ግልጽ ሆኖ በታመለት ጊዜ ውስጥ ማጠናቀቅ እንዲቻል በፍጹም ቁርጠኛነት እንዲሁም በተጠያቂነት መንፈስ እንዲያከናውኑ በአጽንዖት ጠይቋል።

- የፓለቲካ ኃይሎች ስምምነቱ ፍሬ እንዲያፈራና በሀገራችን ዘላቂ ልማትና እድገት እንዲኖር የሰላም ደጋፊ ሊሆኑ ይገባል ብሏል። የእልህ እና የብሽሽቅ ፕሮፖጋንዳዎች ቆመው የአሸናፊነትና ተሸናፊነት ኋላቀር አስተሳሰብ ሊወገዝ እንደሚገባው ገልጾ ሁላችንም ኢትዮጵያውያን #በይቅርታ ሕመማችንን በጋራ እንድናክም ሲል ጥሪ አቅርቧል።

- የተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት እጅግ በጣም ውጤታማ ይሆን ዘንድ በጦርነቱ ሳቢያ የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ ይገባል ብሏል ፤ ለዚህም ሁሉም እንዲረባረብ ጥሪ አቅርቧል።

- በተደረገው የሰላም ስምምነት ስኬታማነት ላይ ስጋት ያላቸው ዜጎች ፣ ፖለቲከኞች ፣ አክቲቪስቶች ፣ ጋዜጠኞች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና ሌሎችም ኢትዮጵያ ከሰላም ውጪ ሌላ አማራጭ እንደሌላት በማወቅ ስለሰላም መልካሙን እንዲያስቡና እንዲያደርጉ አሳስቧል።

(ሙሉ የም/ቤቱ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)

DAILY News Ethiopia

አባታዊ የደስታ መልዕክት !የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በተመለከተ የደስታ መግለጫ አስተላልፈዋል።ከመልዕክታቸው ...
05/11/2022

አባታዊ የደስታ መልዕክት !

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት በተመለከተ የደስታ መግለጫ አስተላልፈዋል።

ከመልዕክታቸው የተወሰደ ፦

" ሰላም በመሸናነፍ መርህ የሚገኝ አይደለም፣ ጠብ የሚባል ነገርንም አያውቅ ይልቁንም #የትህትና እና #የይቅር ባይነትን መንፈስ ያጎናጽፋል እንጂ።

አሁን የተደረሰበት ስምምነት የበርካታ እናቶችን እምባ የሚያብስ፣ የህጻናትን ሰቆቃ የሚያቆም እንዲሁም በወንድማማች ሕዝቦች መካከል የተከሰተውን ደም መፈሰስ ለማቆም መሰረት የሚጥል፣ ሕዝቦችንም ወደ አንድነት እና ሰላም የሚመራ በጎ እርምጃ ነው ብለን እናምናለን።

በመሆኑም የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የመስንግስት የስራ ሃላፊዎች፤ የሚመለከታቸው ሁሉ እና በጎ ፈቃድ ያላችሁ በሙሉ የሀገራችን ሰላሟ በዘላቂነት እንዲረጋገጥ፤ በህዝባችን መካከል የይቅርባይነት እና የእርቅ መንፈስ እንዲሰፍን እና የተፈናቀሉ ወገኖች ወደየቀዬአቸው መመለስ እንዲችሉ እንድንረባረብ አደራ እላችኋለሁ።

በጸሎታችሁም በርቱ።

እግዚአብሔር እትዮጵያን እና ሕዝቦቿን ይባርክ "

(የብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሙሉ መልዕክት ከላይ ተያይዟል)

DAILY News Ethiopia

 • ከቀያቸው የተፈናቀሉትን መልሶ በማቋቋሙ ሂደት ላይ ህዝበ ሙስሊሙ በንቃት እንዲሳተፍ ይፋዊ ጥሪ ቀርቧል።ዛሬ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የፕሪቶሪያውን የኢትዮጵያ መንግስት...
05/11/2022



• ከቀያቸው የተፈናቀሉትን መልሶ በማቋቋሙ ሂደት ላይ ህዝበ ሙስሊሙ በንቃት እንዲሳተፍ ይፋዊ ጥሪ ቀርቧል።

ዛሬ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት የፕሪቶሪያውን የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት የሰላም ስምምነት እስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ፤ " በሰሜኑ የሐገራችን ክፍል ተከስቶ የነበረውን የእርስበርስ ጦርነት ለማቆም ሲደረግ የነበው የሰላም ውይይት ስምምነት ላይ በመድረሱ ለመላው ኢትዮጵያዊያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች የእንኳን ደስ አላችሁ " ብለዋል።

ለሐገራችን ዘላቂ ሰላም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ብሔር፣ ዘር፣ ቀለምና ሃይማኖት ሳይለይ በጋራ ጠንክሮ መሥራት እንዳለበት አስገንዝበዋል።

በጦነቱ ሕይወታቸው ላለፈ ወገኖች የአላህን እዝነት ፣ ለቤተሰቦቻቸው ደግሞ መጽናናትን ተመኝተው ከቀያቸው የተፈናቀሉትን መልሶ በማቋቋሙ ሂደት ላይ በተለይ ህዝበ ሙስሊሙ ከጠቅላይ ም/ቤቱ በሚወጡ መርሐ ግብሮች ላይ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

" አፍሪካዊ መፍትሄ ለአፍሪካ ችግሮች " በሚለው መርሕ መሠረት በደቡብ አፍሪካ ሲካሄድ የነበረውን ድርድር ላመቻቹት የአፍሪካ መሪዎች፣ ለተወከሉት ተደራዳሪዎች እንዲሁም ለአፍሪካ ሕብረት የላቀ ምስጋና ማቅረባቸውን ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የደረሰን መረጃ ያሳያል።

DAILY News Ethiopia

 ዛሬ " የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴ " አባላት ፤ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት አጠቃላይ ሂደት እና ቀጣይ ስራዎችን በሚመለከት ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት ለሁለቱ ም/ቤቶች አ...
04/11/2022



ዛሬ " የሰላም አማራጭ አብይ ኮሚቴ " አባላት ፤ የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት አጠቃላይ ሂደት እና ቀጣይ ስራዎችን በሚመለከት ጠ/ሚር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በተገኙበት ለሁለቱ ም/ቤቶች አፈ-ጉባኤዎች ፣ ለክልል ርዕሳነ-መስተዳድሮች ፣ ለከፍተኛ ባለስልጣናት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አምባሳደር ሬድዋን ሀሴን የተናገሩት ፦

- ስምምነቱ በዋናነት የኢትዮጵያን ዘላቂ ሰላም፣ ሉዓላዊነትና የግዛት እንድነትን ማስጠበቅ ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን የኢትዮጵያ ህዝቦችን የጋራ ጥቅም ባስከበረ መልኩ ተጠናቋል።

- በአንድ ሉዓላዊ ሀገር ውስጥ ሁለት የታጠቀ ሀይል ሊኖር እንደማይችልና ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን ማክበር እንደሚገባ ስምምነት ላይ ተደርሷል።

- ከህገ-መንግስት ውጪ ያሉ እንቅስቃሴዎች ቆመው በትግራይ ክልል በህገ-መንግስቱ መሰረት ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ ይቋቋማል።

- ጉዳት የደረሰባቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ከጉዳታቸው አገግመው ወደ ቀደመው ማህበራዊ ትስስር እንዲመለሱ በጋራ ይሰራል።

- የወደሙ ተቋማትን ጨምሮ የመልሶ ግንባታ ስራዎች በጋራ ርብርብ ሊከናወኑ ይገባል። የትስስርና የተግባቦት ስራዎች የህዝቦችን መጻኢ የጋራ ጉዞ ታሳቢ ያደረጉ ሊሆኑ ይገባል።

- በግጭቱ ምክንያት በኢኮኖሚ፣ በዲፕሎማሲ እንዲሁም በሌሎች መስኮች የደረሰውን ጫና በማስተካካል ረገድ በትብብር መስራት ይጠበቃል።

- የመገናኛ ብዙሃን #ቁርሾዎችን ማባባስ ሳይሆን ዜጎች ከችግሩ ተምረው በቀጣይ አብሮነታቸውን አጠናክረው የሚሄዱበትን ሁኔታ መፍጠር ላይ ሊሰሩ ይገባል።

- #በማወቅም ሆነ #ባለማወቅ የሰላም ሂደቱን ለማደናቀፍ የሚሰሩ ኣካላትን በጋራ ማስቆም ይገባል።

- ሁሉም ዜጋ ለሰላም ስምምነቱ #ተግባራዊነት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት ሊወጣ ይገባል።



DAILY News Ethiopia

የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች አስቸኳይ ስብሰባ ተጠሩ።በዛሬው እለት በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ሁሉም ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና ሚኒስትሮች የክልል ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊወች የተወካዮችና የፌደሬ...
04/11/2022

የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች አስቸኳይ ስብሰባ ተጠሩ።

በዛሬው እለት በጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ሁሉም ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና
ሚኒስትሮች የክልል ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊወች የተወካዮችና የፌደሬሽን ምክር ቤት ሀላፊወች የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች የሚሳተፉበት አስቸኳይ ስብሰባ ተጠርቷል።

አስቸኳይ ስብሰባው በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መክሮ የቀጣይ አቅጣጫዎችን ያስቀምጣል ተብሎ ይጠበቃል።

DAILY News Ethiopia

በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የሚመራው ጥምር ፓርቲ አሸነፈ**********************************በቤንያሚን ኔታንያሁ የሚመራው ጥምር የፖለቲካ ፓርቲ ከ120 የ...
04/11/2022

በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የሚመራው ጥምር ፓርቲ አሸነፈ
**********************************

በቤንያሚን ኔታንያሁ የሚመራው ጥምር የፖለቲካ ፓርቲ ከ120 የፓርላማ መቀመጫ 64ቱን በማግኘት ማሸነፍ ችሏል።

በዚህም ቀኝ ዘመሙ የፖለቲካ ፓርቲ ከ120 የእስራዔል ፓርላማ መቀመጫ አብዛኛውን ማግኘት የቻለ ሲሆን፤ በእስራዔል ፖለቲካ ውስጥ ታዋቂ የሆኑት ቤንያን ኔታንያሁ ወደ ፖለቲካው መመለስ የቻለ ሆኗል።

ከ64ቱ መቀመጫዎች ውስጥ የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ፓርቲ የሆነው ሊኩዊድ 32 መቀመጫዎችን ማግኘት መቻሉም ነው የተገለፀው።

በዚህ ምርጫ አብላጫ የምክር ቤት ወንበር ያገኙት ሊኩድ ፓርቲ እና ቀኝ አክራሪ የእስራኤል ፓርቲዎች በጋራ አዲስ መንግሥት እንደሚመሰርቱ ይጠበቃልም ተብሏል።

ቤንያሚን ኔታንያሁ የምርጫ ውጤቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ በሰጡት አስተያየት "የእስራኤላዊያንን እምነት ማግኘት ችለናል፣ የተረጋጋ መንግስትም እንመሰርታለን" ብለዋል።

የምርጫው የመጨረሻ ውጤት ለህዝብ ይፋ መደረጉን ተከትሎም ቤንያሚን ኔታንያሁ ዳግም ወደ ስልጣን እንደሚመጡ ቢቢሲ ዘግቧል።

DAILY News Ethiopia

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DAILY News Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share