ALL IN ONE Ethiopia

ALL IN ONE Ethiopia The main aim of this Page is to provide timely information to the community, in order to rescue from

ከ15 አመታት በፊት የኢትዮጵያ ቁንጅና ውድድር አሸናፊ የነበረችዉ ሀያት አህመድ ትምህርቷን አጠናቅቃ ዋና አብራሪ(Pilot) በመሆን ተከስታለች።ለበረታ ህልሙ ቅርብ ነዉ‼️
18/01/2025

ከ15 አመታት በፊት የኢትዮጵያ ቁንጅና ውድድር አሸናፊ የነበረችዉ ሀያት አህመድ ትምህርቷን አጠናቅቃ ዋና አብራሪ(Pilot) በመሆን ተከስታለች።
ለበረታ ህልሙ ቅርብ ነዉ‼️

የተሰረቁ የመኪና እቃዎችን የሚገዙና የሚያሻሽጡ 89 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊሰ አሰታወቀ***********************(ኢ ፕ ድ) የተሰረቁ የመኪና እቃዎችን የሚገዙ እና...
03/05/2024

የተሰረቁ የመኪና እቃዎችን የሚገዙና የሚያሻሽጡ 89 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊሰ አሰታወቀ
***********************
(ኢ ፕ ድ)

የተሰረቁ የመኪና እቃዎችን የሚገዙ እና የሚያሻሽጡ 89 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። በተለያዩ ጊዜ የተሰረቁ በርካታ የመኪና እቃዎችን ማስመለሱን ገልጿል፡፡

በህገወጦች ላይ የሚደረገው ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡ የወንጀሉን ስጋት ለመቀነስ ጥናትና ክትትልን መሰረት በማድረግ አዲስ አበባ ፖሊስ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል፡፡

በልደታ ፤በአራዳና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ አዋሳኝ ወረዳዎች የመኪና እቃ በሚሰርቁ ፣ ህጋዊ የንግድ ፈቃድን ሽፋን በማድረግ የተሰረቀውን የመኪና እቃ በሚቀበሉ በአጠቃላይ ወንጀሉን ተደራጅተው ሲፈፅሙ በነበሩ ህገወጦች ላይ በተወሰደ እርምጃ 89 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል በልዩ ልዩ ጊዜ የተሰረቁ ከ1ሺ በላይ 33 አይነት የመኪና እቃዎችን አስመልሷል፡፡

ፖሊስ የመኪና እቃ ስርቆትን ለመከለከልና ህገወጦችን ህግ ፊት ለማቅረብ ልዩ ልዩ ማስረጃዎችን በማሰባሰብ በተቀናጀ ኦፕሬሽንና ህግን መሰረት አድርጎ በወሰደው እርምጃ 528 ልዩ ልዩ ፍሬቻዎችን ፣ 187 ስፖኪዮችን፣ 113 የመኪና መብራቶች ፣ 172 የዝናብ መጥረጊያ በአጠቃላይ 33 ልዩ ልዩ 1ሺ 269 አይነት የመኪና እቃዎችን መያዙን አስታውቋል፡፡

የተሰረቁ የመኪና እቃዎችን የሚገዙ ህገ-ወጦች ለወንጀሉ መስፋፋት ዋና መንስኤ በመሆናቸው ፖሊስ የሚያደርገውን ቁጥጥር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል፡፡ የተሰረቀባቸውን እቃ ከወንጀለኞች የሚገዙ ግለሰቦችም በተዘዋዋሪ ለወንጀል ፈፃሚዎች ምቹን ሆኔታ እየፈጠሩ መሆኑን ተገንዝበው ከዚህ ድርጊታቸው ሊታቀቡ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልእክቱን አስተላልፏል፡፡

በተለያየ ጊዜ የመኪና እቃ የተሰረቀባቸው ግለሰቦች በልደታ፣ በአራዳና በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያዎቸው በመቅረብ ንብረታቸውን መውሰድ እንደሚችሉም ፖሊስ አስታውቋል፡፡

ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓም

03/05/2024
03/05/2024

እንዳያመልጦ👐

ኢሳ 53:5 ነገር ግን እሱ ስለ መተላለፋችን ተወጋ ፤ ስለ በደላችንም ደቀቀ ፤ በእርሱ ላይ የወደቀው ቅጣት ለእኛ ሰላም አመጣልን ፤ በእርሱም ቑስል እኛ ተፈወስን።ለመላው የክርስትና እምነት...
03/05/2024

ኢሳ 53:5 ነገር ግን እሱ ስለ መተላለፋችን ተወጋ ፤ ስለ በደላችንም ደቀቀ ፤ በእርሱ ላይ የወደቀው ቅጣት ለእኛ ሰላም አመጣልን ፤ በእርሱም ቑስል እኛ ተፈወስን።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን የጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

መልካም ቀን!

በአርጀንቲና የሀሞት ፊኛ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ወደ ሆስፒታል የገባው ታካሚ በስህተት የወንድ የዘር ፍሬ ቱቦ ተቆረጠበት 👉 በስህተት ምክንያት በተፈጥሯዊ መንገድ ልጅ መውለድ አይችልም አንድ ...
04/03/2024

በአርጀንቲና የሀሞት ፊኛ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ወደ ሆስፒታል የገባው ታካሚ በስህተት የወንድ የዘር ፍሬ ቱቦ ተቆረጠበት

👉 በስህተት ምክንያት በተፈጥሯዊ መንገድ ልጅ መውለድ አይችልም

አንድ አርጀንቲናዊ በሐሞት ከረጢቱ ላይ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ወደ ሆስፒታል ቢገባም ዶክተሮቹ በምትኩ በስህተት የወንድ የዘር ፍሬ ቱቦውን ቆርጠዋል።

ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ የ41 አመቱ ጆርጅ ባሴቶ ለሀሞት የፊኛ ቀዶ ህክምና በአርጀንቲና ኮርዶባ ወደሚገኘው ፍሎሬንሲዮ ዲያዝ ግዛት ሆስፒታል አምርቶ ነበር። ቀዶ ህክምናውን ለማክሰኞ ለመስጠት ቀን ተቆርጦለት የነበረ ቢሆንም በአንዳንድ ከቁጥጥር ውጪ በሆኑ ሁኔታዎች ምክንያት የጆርጅ ህክምና ወደ እሮብ ተላልፏል። ግን ይህ የቀን ለውጥ ብልሹ የአሰራር ቅሌትን ያስከተለና በመላው አገሪቱ ቁጣን የፈጠረ ድርጊት ተፈፅሟል።

በቀዶ ህክምናው ቀን የሆስፒታሉ ሰራተኞች ወደ ታካሚው ክፍል ገብተው በቀዶ ህክምና አልጋ ላይ ጆርጅና ካስቀመጡት በኃላ ምንም ሳይጠይቁት እንዲሁም የህክምና ክትትል ቻርቱን እንኳን ሳይፈትሹ ወደ ቀዶ ህክምና ክፍል ይወስዱታል። ዶክተሮቹ ለእለቱ ያቀዱትን የቀዶ ህክምና የወንድ የዘር ፍሬ ቱቦ መቁረጥ ስለነበር ስም እና የታካሚውን ማንነት ሳያጣሩ መቁረጣቸው ተሰምቷል። ጆርጅ ከቀዶ ህክምናው በኃላ ከእንቅልፉ ሲነቃ ምን እንደተፈጠረ ምንም አላወቀም ነበር።

ነገር ግን አንድ ዶክተር ሁኔታውን ሊያጣራ ሲገባ እና ቻርቱን ካየ በኋላ አስደንጋጭ ዜናው ለታካሚው ነግሮታል። ከተያዘለት የሐሞት ፊኛ የቀዶ ህክምና ቀጠሮ ይልቅ የቱቦ መቆረጥ እንደተደረገለት ይነግረዋል። ይህው አርጀንቲናዊ ታካሚ ለጥቂት ጊዜ ዝምታ ውስጥ የነበረ ሲሆን ከዚያም መደናገጥ ይጀምራል ሆኖም ብዙም ሳይቆይ ግን መጀመሪያ ላይ ሊያደርገው የሚገባውን ቀዶ ህክምና ማድረግ ስለነበረበት በድጋሚ ወደ ህክምናው ያመራል።

ከሁለተኛው ቀዶ ህክምና በኋላ ጆርጅ ባሴቶ ስህተቱ እንዴት እንደተከሰተ እና የዘር ፍሬው ቱቦ ለምን እንደተቆረጠ ይጠይቃል።ዶክተሮቹ ለተፈጠረው ስህተት እርስ በእርሳቸው መወነጃጀላቸውን ይቀጥላሉ። ታካሚው ጉዳት ከደረሰበት በኃላ በሰው ሰራሽ የማዳቀል ሂደት ልጅ መውለድ ስለሚችል በሁኔታው እንዳይደናገጥ ነግረውት ነበር። በእድሜው እና በተቆራረጡት ቱቦዎች ምክንያት ልጅ የመውለድ የስኬት እድሉ በጣም አነስተኛ መሆኑ ግልፅ ነው።

ጆርጅ እንደተናገረው "በጣም የሚገርመው ነገር በተኛሁበት አልጋ ላይ የ'ሀሞት ፊኛ' ታካሚ ተብሎ ተፅፎ ነበር ማድረግ ያለባቸው ትንሹ ነገር ማንበብ ብቻ ነበር፣ ይህንን ለማወቅ ሳይንቲስት መሆን አይጠበቅብህም' ሲል ጆርጅ ለአርጀንቲና የዜና አውታር ኤል ዶሴ ተናግሯል። "ጣቴን በማንም ላይ መቀሰር አልፈልግም ፣ ግን ለደረሰብኝ ነገር ማንም ሀላፊነቱን አይወስድም። ‘ደህና፣ ነህ ያን ያህል ድራማ አትስራ ምክንያቱም በማዳቀል ሰው ሰራች ሂደት አሁንም ልጅ መውለድ ትችለህ" ሲሉ ብቻ ነግረውኛል ሲል አክሏል።

የጆርጅ ጠበቃ ዲዬጎ ላሬይ ደንበኛዬ ላይ በደረሰበት ስህተት በጣም አዝኗል ሲል ተደምጧል። ምንም እንኳን የሁለት ወንድ ልጆች አባት ቢሆንም አዲስ የፍቅር ግንኙነት የጀመረ ሲሆን ወደፊት ከአዲሱ የትዳር ጓደኛው ጋር ልጅን ለመውለድ እቅድ ነበረው። በተፈጥሯዊ መንገድ ለመውለድ እንደሚፈልግ ግልጽ ቢሆንም አሁን ግን አማራጭ ስለሌለው ሰው ሰራሽ ማዳቀል መጠቀም ብቸኛ ምርጫው ሆኗል።

ይህ የቸልተኝነት ደረጃ የሚያሳይ ነው፤ እንዴት እንዲህ አይነት ትልቅ ስህተት ይሰራል ሲሉ ጠበቃው ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።ጆርጅ ዶክተሮችን እና ሆስፒታሉን በቸልተኝነት ለመክሰስ እንደሚፈልግ አስታውቋል።

በሃያዎቹ መጀመሪያ ዕድሜ ላይ የሚገኘው ወጣት ኢዘዲን ካሚል፤እስካሁን ከ30 በላይ የፈጠራ ስራዎችን ሰርቷል። እነዚህን ስራዎቹን ወደ ምርት እና አገልግሎት ለመቀየር ተቸግሮ የቆየ ቢሆንም፤ በ...
14/01/2024

በሃያዎቹ መጀመሪያ ዕድሜ ላይ የሚገኘው ወጣት ኢዘዲን ካሚል፤እስካሁን ከ30 በላይ የፈጠራ ስራዎችን ሰርቷል። እነዚህን ስራዎቹን ወደ ምርት እና አገልግሎት ለመቀየር ተቸግሮ የቆየ ቢሆንም፤ በቅርቡ ግን ሄክስ ላብ /Hex Labs./የተሰኘ የራሱን ኩባንያ በማቋቋም በፈጠራ ስራዎቹ ሚሌነር መሆን ችሏል።

የ22 ዓመቱ ወጣት ኢዘዲን ካሚል፤ ከፈጠራ ስራው ባሻገር በቱርክ ሀገር በሶፍትዌር ምህንድስና የመጀመሪያ ዲግሪውን ይዟል። ወጣቱ አብዛኛዎቹን የፈጠራ ስራዎቹን የሰራቸው የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪ እያለ ተወልዶ ባደገባት ውልቂጤ ከተማ ሲሆን፤ አሁን ያገኘው ስኬት ላይ ለመድረስም በርካታ ውጣ ውረዶችን አይቷል።እናም ካጋጠመው በመነሳት ወጣቶች ተስፋ ሳይቆርጡ ደጋግመው እንዲሞክሩ ይመክራል።

«ፈጠራ ማለት ዕሴት መፍጠር ነው» የሚለው ኢዘዲን፤ለዚህም የሰዎችን የዕለት ተዕለት ኑሮ የሚያቀሉ እና ችግሮችን ለመፍታት የሚያስችሉ የፈጠራ ስራዎችን በመስራት በተለያዩ ጊዜዎች በመሰረታቸው ጀማሪ የቴክኖሎጅ ኩባንያዎቹ አማካኝነት ሀብት የማመንጨት ስራ ላይ በደንብ እየሰራ መሆኑን ገልጿል።በዓለማችን በቴክኖሎጅ ላይ መዋዕለ ንዋይ ከሚያፈሱ ቱጃሮች መካከል በብዙ ምክንያቶች ኤሎን ማስክን ያደንቃል።ለወደፊቱም በፈጠራ ስራዎቹ እንደ ማስክ ቢሌነር የመሆን ተስፋ ሰንቋል። «የአፍሪቃን ትርክት በፈጠራ ስራ እንቀይራለን» ወጣት ኢዘዲን ካሚል
«የስራ አጦችን ቁጥር ለመቀነስ ሰዎችን ማሳተፍ እንዲሁም ሀብት ማመንጨት ሲችል ነው።ፈጠራ የምለው። ብዙ ጊዜ ከ30 ዓመት በፊት ቢሌነር ሆኘ «አንደር 30» አርቲክል ማፃፍ እፈልጋለሁ።ብዬ አወራለሁ። ይህንን የምልበት ምክንያት «ቫሊዩ ክሬት» ሲደረግ የምለካበት ገንዘብ ነው። ስለዚህ ከ30 ዓመቴ በፊት ጥሩ የሆነ «ቫሊዩ»/እሴት/ ለ«ማርኬቱ ፕሮቫይድ»ማድረግ እፈልጋለሁ።ስለዚህ ለብዙ ስራ አጦች የስራ ዕድል በመፍጠር በጎ ተምሳሌት መሆን እፈልጋለሁ»በማለት ተናግሯል።ይህንን ህልሙን ለማሳካትም በኢ-ኮሜርስ ላይ አተኮሮ እንደሚሰራ ገልጿል።

ምንጭ ዘገባው የዶቸ ቬለ

27/09/2023

(በውስጥ መስመር ከደረሱኝ መልዕክቶች አንደኛውን እንደወረደ ነው ያካፈልኳችሁ)

አቃቂ ቃሊቲ ወረዳ 3 (በተለምዶ ዋናው ንግድ ባንክ) በር ላይ በእግረኛ መንገድ ስር ከተቀበረ ቱቦ ውስጥ የፊጥኝ ታስረው የታገቱ ሰዎች መኖራቸውን አረጋግጠናል። ከንግድ ባንኩ ፊት ለፊት የፖሊስ ጣቢያ ያለ ሲሆን ፖሊሶች ሌሊት ላይ ሰዎችን ከተለያዬ ቦታ እያፈኑ ቱቦው ውስጥ እንደሚከቱ ተረጋግጧል።

ATM የሚጠቀሙ ሰዎች "ውሃ ... ውሃ" የሚል ድምፅ ሰምተው የቱቦውን በር ሲከፍቱ በርካታ ሰዎች የፊጥኝ ታስረው ተመልክተዋል። የዓይን ምስክሩ "የተጎሳቆሉና ለሞት የሚያጣጥሩ እጅና እግራቸው የታሠሩ ሰዎችን አይቻለሁ፤ ውሃ ገዝተን ስናቀብል ፖሊስ መጥቶ አባረረን" ብሎኛል። ATM የሚጠቀሙ እናቶች እያለቀሱ ቢያንስ ምግብ እንስጣቸው ቢሉም ፖሊሶች እየደበደቡ በትነዋቸዋል።

Mesay Mekonnen

መልካም አዲስ አመት እንኳን አደረሳችሁ🌼🌼🌼🌼
12/09/2023

መልካም አዲስ አመት እንኳን አደረሳችሁ🌼🌼🌼🌼

በቀራንዮ አደባባይ ስለፈሰሰው ቅዱስና ክቡር ደሙ ብሎ ይማረን ይቅርም ይበለን 🙏❤
14/04/2023

በቀራንዮ አደባባይ ስለፈሰሰው ቅዱስና ክቡር ደሙ ብሎ ይማረን ይቅርም ይበለን 🙏❤

Stop creating problems that aren't even there.Be aware from this peoples.
29/03/2023

Stop creating problems that aren't even there.
Be aware from this peoples.

ፓስተር ቼሬ እና ፖስተር ቢንያም ሽታዬ  #ተዋህዶ በተጨነቀች ጊዜ አብራችሁን ከጎናችን ስለነበራችሁ እናመሰግናለን ተብለው ሽልማት ከታዋቂው መምህር ምህረተአብ ተረክበዋል!
26/03/2023

ፓስተር ቼሬ እና ፖስተር ቢንያም ሽታዬ #ተዋህዶ በተጨነቀች ጊዜ አብራችሁን ከጎናችን ስለነበራችሁ እናመሰግናለን ተብለው ሽልማት ከታዋቂው መምህር ምህረተአብ ተረክበዋል!

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ALL IN ONE Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share