ሃቅ ሚዲያ - Haq Media

ሃቅ ሚዲያ - Haq Media ለእውነተኛ እና ፈጣን የመረጃ ፍላጎትዎ እንተጋለን

አስፋው “ተሽሎኛል!” አለ!አስፋው “ተሽሎኛል” የሚል መለዕክቱን አስተላልፏል። አስፋው ለውጥ አለው። ዛሬ ከወትሮው በተሻለ ጠንካራ መንፈስ ላይ ይገኛል። አሁንም ህክምናውን በጥሩ ሁኔታ እየተ...
25/10/2023

አስፋው “ተሽሎኛል!” አለ!
አስፋው “ተሽሎኛል” የሚል መለዕክቱን አስተላልፏል። አስፋው ለውጥ አለው። ዛሬ ከወትሮው በተሻለ ጠንካራ መንፈስ ላይ ይገኛል። አሁንም ህክምናውን በጥሩ ሁኔታ እየተከታተለ ነው።
የህመሙን መሰረታዊ መንስኤወች ለማወቅና ተጓዳኝ ህመሞችን በሚገባ ለመለየት፣ ብሎም ተገቢውን የህክምና መፍትሄ ተፈጻሚ ለማድረግ ናሙናወች ተወስደው ተከታታይ ምርመራወች እየተደረጉለት ነው። በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ብቃት ባላቸው የህክምና ባለሞያወች ጥሩ ህክምናን እያገኘ ነው።
ህክምናው እረፍትና ቋሚ ክትትል ስለሚያስፈልገው፤ እንደልብ ለመጠየቅና ለማየት አይቻልም። በጣም በርካታ የዲሲ፣ የቨርጂኒያና የሜሪላንድ ነዋሪወች፣ እንዲሁም ኢትዮጵያውያን የህክምና ባለሞያወች እንክብካቤ እናድርግለት ብለው ሆስፒታል መጥተው ከበር ተመልሰዋል። አስፋው ለሁሉም፤ በአካልም፣ በመንፈስም፣ በጸሎትም አብረውት ላሉት ምስጋና ይድረስ ብሏል።
አሁንም ለጊዜው ሆስፒታል ውስጥ ለመጎብኘት ስለማይፈቀድ ሁላችሁም በያላችሁበት በጸሎት አስቡኝ ብሏል። የበለጠ ሲያገግም እና ህክምናውን በማያስተጓጉል መልኩ መጠየቅ ሲቻል፣ እናሳውቃለን።
በአበበ ፈለቀ

እህታችን አርቲስት ኤሊያና ብርሃኑ መልካም ልደት እንኳን ተወለድሽልን 😍
25/10/2023

እህታችን አርቲስት ኤሊያና ብርሃኑ መልካም ልደት እንኳን ተወለድሽልን 😍

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና በአቻ ውጤት ተለያዩ በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ በአንድ አቻ ውጤት ተለያዩ፡፡በአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲ...
25/06/2023

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና በአቻ ውጤት ተለያዩ

በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ በአንድ አቻ ውጤት ተለያዩ፡፡

በአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደውየ28ኛ ሣምንት መርሐ ግብር÷ 9 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ ቡና ከቅዱስ ጊዮርጊስ ተጫውተዋል፡፡

በተጠባቂው ደርቢ ጨዋታም ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡

የቅዱስ ጊዮርጊስን ግብ እስማኤል ኦሮ አጎሮ 66ኛው ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር÷ የኢትዮጵያ ቡናን ደግሞ ብሩክ በየነ በ72ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡

እስማኤል ኦሮ አጎሮ ዛሬ ግብ ማስቆጠሩን ተከትሎ በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን ግቦች 24 አድርሷል፡፡



ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ይከተሉን

25/06/2023
የዘመናችን ምርጥ ወጣት! ሳያት ደምሴ! ውበት+ አስተሳሰብ= ሳያት ደምሴ!
13/01/2023

የዘመናችን ምርጥ ወጣት! ሳያት ደምሴ!
ውበት+ አስተሳሰብ= ሳያት ደምሴ!

አሜሪካ ዩክሬን ራሷን ለመከላከል የሚያስችላትን ዘመናዊ እና ረዥም ርቀት የሚወነጨፉ ሮኬቶችን ልትልክ መሆኑን ፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስታወቁ።ዩክሬን የሩሲያ ኃይሎችን ከርቀት መምታት የሚያስች...
01/06/2022

አሜሪካ ዩክሬን ራሷን ለመከላከል የሚያስችላትን ዘመናዊ እና ረዥም ርቀት የሚወነጨፉ ሮኬቶችን ልትልክ መሆኑን ፕሬዝደንት ጆ ባይደን አስታወቁ።

ዩክሬን የሩሲያ ኃይሎችን ከርቀት መምታት የሚያስችላት ይህ መሳሪያ እንዲሰጣት ለረዥም ጊዜ ስትጠይቅ ቆይታለች።

የጦር መሣሪያው በሩሲያ ውስጥ ያሉ ነገሮች ኢላማ ሊያደርግ ይችላል በሚል ስጋት አሜሪካ እስካሁን ድረስ የዩክሬንን ጥያቄ አልተቀበለችውም ነበር።

ይሁን እንጂ ረቡዕ ዕለት ፕሬዝደንት ባይደን፣ የጦር መሣሪያው ድጋፍ ኪዬቭ ከሩሲያ ጋር የሚኖራትን የድርድር አቅም ለማጠናከር እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ግጭቱን ለመፍታት ያስችላል ብለዋል።

“ዩክሬን በጦርነት ቀጠና ውስጥ ወሳኝ ኢላማዎችን ለመምታት የሚያስችላትን ይህንን ዘመናዊ የሆነ ሮኬት እና ተተኳሾች ለመስጠት የወሰነውም በዚህ ምክንያት ነው” ሲሉ ኒው ዮርክ ታይምስ ላይ ጽፈዋል።

አዲሱ የጦር መሣሪያ ድጋፍ መካከል ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ የሚችል ረዥም ርቀት መጓዝ የሚችል የሮኬት ሥርዓት እንደሚገኝበት አንድ የዋይት ሃውስ ከፍተኛ ባለሥልጣን የተናገሩ ሲሆን የጦር መሳሪያ ድጋፎች ግን በአሃዝ ምን ያክል እንደሆኑ ግን በቁጥር አልገለጹም።

ይህ የሮኬት ሥርዓት ዩክሬን አሁን ላይ ካላት ከባድ የጦር መሣሪያ በተሻለ በ70 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኝ ኢላማ ላይ ጥቃት መፈፀም ይችላል።

ከዚህ ባሻገር ሩሲያ ካላት ሮኬቶች በተሻለ ኢላማቸውን በትክክል ይመታሉ ተብሎም ይታመናል።

ሃቅ ሚዲያ

የፈረንሳይ እና የጀርመን መሪዎች፣ ከዜለንስኪ ጋር 'ቀጥተኛ' እና 'ወሳኝ' የሆነ ድርድር እንዲያደርጉ የሩሲያውን ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲንን ማሳሰባቸውን የጀርመን መራሔ መንግሥት ጽ/ቤት አ...
29/05/2022

የፈረንሳይ እና የጀርመን መሪዎች፣ ከዜለንስኪ ጋር 'ቀጥተኛ' እና 'ወሳኝ' የሆነ ድርድር እንዲያደርጉ የሩሲያውን ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲንን ማሳሰባቸውን የጀርመን መራሔ መንግሥት ጽ/ቤት አስታወቀ።

መሪዎቹ ኢማኑኤል ማክሮን እና ኦላፍ ስኮልዝ ከፕሬዚደንት ፑቲን ጋር የ80 ደቂቃ የስልክ ንግግር አድርገዋል።

የመራሔ መንግሥቱ ጽ/ቤት እንዳለው መሪዎቹ በንግግራቸው አስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግና ሩሲያ ወታደሮቿን ከዩክሬን እንድታስወጣ ገፋፍተዋል።

እንደ ክሬሚሊን ከሆነ የሩሲያ መሪ፣ ሞስኮ ከኪዬቭ ጋር እንደገና ንግግር ለመጀመር ፈቃደኛ መሆኗን ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ በፑቲን እና በዩክሬን አቻቸው ቮሎድሚር ዘሌንስኪ ጋር ቀጥተኛ የሆነ ንግግር ሊኖር ይችል እንደሆነ አልጠቀሰም።

ቀደም ብሎ የዩክሬን ፕሬዚደንት ለውይይቱ ጉጉት እንደሌላቸው ገልጸው፣ ነገር ግን ግጭቱን ለማስቆም ውይይቱ አስፈላጊ ሊሆን እንደሚችል ተናግረው ነበር።

ሩሲያ በዩክሬን ላይ ወረራ ከፈፀመችበት እአአ የካቲት 24 ቀን ጀምሮ የሩሲያ እና የዩክሬን ልዑካን በርቀት እና በአካል በመገናኘት ለበርካታ ጊዜ ውይይት አድርገዋል።

ሃቅ ሚዲያ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤትን ተቋማዊ ማድረግ የሁለት ትውልድን አማና መወጣት ነው!ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በየዘመናቱ የተለያዩ ጥያቄዎች የነበሯቸውና የተለያዩ ትግሎች ያደረጉ...
29/05/2022

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤትን ተቋማዊ ማድረግ የሁለት ትውልድን አማና መወጣት ነው!

ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች በየዘመናቱ የተለያዩ ጥያቄዎች የነበሯቸውና የተለያዩ ትግሎች ያደረጉ ቢሆንም ሁለት ተከታታይ ትውልድ ግን መቋጫ ባላገኘው የመጅሊስ ጉዳይ ተወጥሮ እስከዛሬ ዘልቋል፡፡

በመጅሊስ የትግል ታሪክ ትልቁ የሚባለው ስኬት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ለህዝቡ በሚመጥን ቁመና በአዋጅ እንዲቋቋም በማድረግ የተገኘው ድል ወሳኙ ምእራፍ ነው፡፡ የአዋጁ መውጣትን የህዝብ ተከታታይ ትግሎች፣ የመንግስት ቁርጠኝነት እና የልሂቃን ሚና በጋራ በመሆን እውን ያደረጉት የዚህ ትውልድ ስኬት ሲሆን የቀደመው ትውልድ ደግሞ ላደረገው ትግል ህጋዊ እውቅና የሰጠ አንኳር ውጤት ነው፡፡

የአዋጁ መውጣት ጠቅላይ ምክር ቤቱ እንደ አንድ ትልቅ ህዝብን እንደሚወክል፣ ከዚያም አልፎ ሀገርን እንደሚወክል የሀይማኖት ተቋም እንዲወጣቸው ለሚጠበቅበት ኃላፊነቶች ህጋዊ መሰረት የጣለ ቢሆንም አዋጁን ለመተግበር አስፈላጊ የሆኑ ደንቦች፣ መመሪያዎች እና መዋቅሮችን ወደመሬት ማውረድ ግን ግለሰባዊ መሰረት ያላቸው የአቅም ማነስና ለመርህ እምቢተኝነት ይህን ታሪካዊ እድል እያደበዘዙት ነው፡፡

ባለፉት ሁለት አመታት መጅሊሱን መዋቅራዊ ቅርፅ እንዳይዝና የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የጋራ ቤት ሆኖ ለህዝቡም ለሀገርም ሀብት እንዳይሆን ያገደው ጉዳይ እሳቢያዊም ሆነ ህጋዊ ጉዳይ ሳይሆን ግለሰባዊ መሰረት ያለው ለሁለት ትውልዶች የህዝብ ጥያቄ ደንታ ቢስነትና ለመርህ ተገዥ አለመሆን፣ አለፍ ሲልም ለሀገር መረጋጋትና አንድነት ሚና ለመወጣት አለመፈለግ ነው፡፡

ላለፉት ጥቂት ወራት ይህንን ችግር ለመቅረፍ በዋነኛነት አዋጁን መሬት የሚያስነካውን በሊቃውንት የተዘጋጀውን የመጀረመሪያውን ደንብ ለማፅደቅ ከፍተኛ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በደንቡ ላይ አሉ የሚባሉ የመወያያ ነጥቦች በሙሉ አግባብነት ባላቸው ተወያዮች በዝርዝር ተወያይተውበት እና ግብዓት ተወስዶበት በህጋዊ አካል እና አካሄድ ፀደቀው ቀጣይ ስራዎችን ማቀድ በሚያስችልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል፡፡ ይህ ትልቅ ስኬት ቢሆንም ደንቡን ተቀብሎ ሂደቱን ለማሳረግ ግን አሁንም ግለሰባዊ መሰረት ያላቸው እምቢተኝነቶችና ለመርህ አልገዛም ባይነት እንደአዲስ ሲያገረሽ አስተውለናል፡፡ ይህ ተቀባይነት የሌለውና በህግም፣ በሞራልም ግለሰቦቹን የሚያሳጣ ደካማ አቋም ሊቀየርና በደንቡ ውይይት ላይ በተደረሰባቸው ስምምነቶች መሰረት ወደቀጣዩ ምእራፍ ለመግባት መነሳት ያስፈልጋል፡፡ ደንቡን ወደ ተግባር እንዲወርድ ማድረግ ከምንም በላይ ለሁለት ትውልዶች ውጤት ለሆነው ለአዋጁ ያለንን ቁርጠኝነት የምናሳይበት በመሆኑ የትኛውም ግለሰባዊ ጥቅምና ፍላጎታችን ከህዝብ ጥቅምና ፍላጎት ስለማይበልጥ እራሳቸችንን ልንገራ ይገባል::

የህዝቡንና የተለያዩ ክልሎች የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት እየጠበቁት የሚገኘውን ተቋማዊ ለውጥ ለመቀልበስ መሞከር የሚፈጥረውን ቀውስ ከአሁኑ በመረዳት ከዚህ ጥፋት መመለስ ያስፈልጋል፡፡

ደንቡን ለማፅደቅ የነበረውን ጥረት እና ልፋት ከግንዛቤ በማስገባት ሙስሊሙ ማህበረሰብ፣ መንግስት እና የሌላ እምነት ተከታዮችም የተለያየ ድርሻ አላቸው፡፡ ሙስሊሙ ማህበረሰብ ተቋሙ የሁለት ትውልድ ትግል ውጤት መሆኑን በሚመጥን መልኩ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የጋራ ቤት መሆኑን በሚያረጋግጡ ህጋዊና መዋቅራዊ የለውጥ ሂደቶች ላይ በንቃት እንዲሳተፍና ጅምር ትግሉን ወቅቱ በሚጠይቀው ብልሃት በተሞላበት አካሄድ ዳር እንዲያደርስ ማስቀጠል ይጠበቃል፡፡

መንግስት ለአዋጁ መውጣት የተወጣውን ታሪካዊ ኃላፊነት ከግብ እንዲደርስ እንደ መንግስት የሚጠበቅበትን አስፈላጊ የሆኑ መደላድሎችን በመፍጠር እንዲሁም አልፎ አልፎ የሚታዩ ግልፅም ድብቅም ፍላጎት በያዙ ግለሰቦች የሚያጋጥሙ ሂደቱን የማሰናከልና የሰላም መታወክ ወደሚያመጣ አካሄድ የመምራት አዝማሚያዎችን ቀድሞ መከላከል ይጠበቅበታል፡፡

የሌሎች እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ደግሞ እንደሀገር በምንጋራቸው አጅንዳዎችና እሴቶች የጋራ ስራ መስራታችን እንደተጠበቀ ሆኖ የመጅሊስ ጉዳይ የናንተን ብሔር ነክ፣ ፖለቲካዊ ነክ እና የእምነታችሁን ቀኖና የሚመለከት ምንም ጉዳይ የሌለው መሆኑን በመረዳት ፅንፍ የያዙ ልሂቃኖች በተወሰነ መልኩ ከሚያሳዩት ያልተገባ ጣልቃ ገብነት በመቆጠብ ፍፁም ሃማኖታዊ እና የውስጥ ተቋማዊ ጉዳይ ከሆነው የመጅሊስ አጀንዳ እጃችሁን በመሰብሰብ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ አደራ እላለሁ፡፡

ኡስታዝ አቡበከር አህመድ

ሃቅ ሚዲያ

አውሮጳ ከሩሲያ በነዳጅና በጋዝ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለማቆም እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። የደቡብ አፍሪቃዊትዋ ሀገር ናሚቢያ በነዳጁ ዘርፍ አዉሮጳን መርዳት እችላለሁ እያለች ነዉ። ናሚቢያ ይህን ...
29/05/2022

አውሮጳ ከሩሲያ በነዳጅና በጋዝ ላይ ያለውን ጥገኝነት ለማቆም እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። የደቡብ አፍሪቃዊትዋ ሀገር ናሚቢያ በነዳጁ ዘርፍ አዉሮጳን መርዳት እችላለሁ እያለች ነዉ። ናሚቢያ ይህን ያሳወቀችዉ ባለፈው ሳምንት ዳቮስ ስዊዘርላንድ ላይ በተካሄደው ዓለም አቀፍ ዓመታዊ የኤኮኖሚ መድረክ ነዉ።

ሃቅ ሚዲያ

የዝንጀሮ ፈንጣጣ ከሰው ወደ ሰው በቀላሉ አይተላለፍም። አሁን ላይ በቫይረሱ የተያዙ በርካታ ሰዎች መገኘታቸው በምን ምክንያት እንደሆነ እስካሁን አልታወቀም። ይሁን እንጂ ቫይረሱ በዚህ ወቅት ...
29/05/2022

የዝንጀሮ ፈንጣጣ ከሰው ወደ ሰው በቀላሉ አይተላለፍም። አሁን ላይ በቫይረሱ የተያዙ በርካታ ሰዎች መገኘታቸው በምን ምክንያት እንደሆነ እስካሁን አልታወቀም። ይሁን እንጂ ቫይረሱ በዚህ ወቅት ለመከሰቱ ሦስት መላ ምቶች ተሰጥተዋል። አንደኛው ቫይረሱ የተለየ ዝርያ ነው የሚል ነው። ተመራማሪዎች የዝንጀሮ ፈንጣጣ በቀላሉ እንዲተላለፍ የሚያስችል የመለወጥ ሂደት እንዳለው ዝርያውን እያጠኑ ነው፤ ነገር ግን እስካሁን ቫይረሱ ራሱን ለውጦ ስለመሆኑ የሚያሳይ መረጃ አልተገኝም።

ሃቅ ሚዲያ

የሸገር አዲስ ገጽታ ፕሮጀክትን ለማበልፀግ በቀረቡት የዲዛይን ሀሳቦች ላይ አስተያየት ለመሰብሰብ ያለመ ኤግዚቢሽን ተከፈተአዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የመሬት ባንክና ልማ...
28/05/2022

የሸገር አዲስ ገጽታ ፕሮጀክትን ለማበልፀግ በቀረቡት የዲዛይን ሀሳቦች ላይ አስተያየት ለመሰብሰብ ያለመ ኤግዚቢሽን ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የመሬት ባንክና ልማት ኮርፖሬሽን ያዘጋጀው ለሸገር አዲስ ገጽታ ፕሮጀክትን ለማበልፀግ ለውድድር የቀረቡት የዲዛይን ሀሳቦችን አስመልክቶ የህዝብ አስተያየት ለመሰብሰብ ያለመ ኤግዚቢሽን ተከፈተ፡፡

ኤግዚቢሽኑ ለአንድ ወር የሚቆይ ሲሆን ፥ መስቀል አደባባይ በሚገኘው ዳያስፖራ ማዕከል ነው የተከፈተው።

የመሬት ባንክና ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ወ/ሪት ሌንሳ መኮንን እንደተናገሩት ፥ የአዲስ አበባ መንገዶች ዳር የሚገኙ ይዞታዎች ማራኪ ገጽታ እንዲላበሱ ከማድረግ ባሻገር ኢኮኖሚና ማህበራዊ ጥቅማቸው እንዲያጎላ ሁሉን አቀፍ ዲዛይን ለማዘጋጀት ባለሙያዎች በስፋት ለማሳተፍ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል።

በአዲሱ ዲዛይን መሰረተ ልማቶች ተናበው ካለመስራት የሚከሰቱ ችግሮች እንደሚቀርፍም ዋና ዳይሬክተሯ ገልፀዋል ሲል የዘገበው ኢፕድ ነው።

ኮርፖሬሽኑ ቀደም ሲል ከቦሌ ሲቪል አቪዬሽን እስከ እንጦጦ እንዲሁም ከመስቀል አደባባይ እስከ አዲስ አበባ ከተማ መስተደድር ባሉ መንገዶች ላይ የሚገኙ የፌዴራል ይዞታዎችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥቅማቸውን ለማሳደግ አጋዥ የሆኑ የልማት ሀሳቦችን ለማበልፀግ የመጀመሪያ ዙሪ የዲዛይን ጽንስ ሀሳብ ውድደሮችን አጠናቋል።

በመሆኑም በቴክኒካል ዳኞች ጥቅል ውጤት ከመሰጠቱ በፊት ለህዝብ አስተያየት ለመሰብሰብ መክፈት ወስኗል።

ሃቅ ሚዲያ

ሊቨርፑል ከ ማድሪድ፡ ታላቁ የአውሮፓ እግር ኳስ ፍልሚያሳላህ እና ቤንዜማ ዛሬ ምሽት አራት ሰዓት ላይ የፈረንሳይዋ ዋና ከተማ ፓሪስ በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ የኃያላኑን ሪያል ...
28/05/2022

ሊቨርፑል ከ ማድሪድ፡ ታላቁ የአውሮፓ እግር ኳስ ፍልሚያ
ሳላህ እና ቤንዜማ

ዛሬ ምሽት አራት ሰዓት ላይ የፈረንሳይዋ ዋና ከተማ ፓሪስ በአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ የኃያላኑን ሪያል ማድሪድና ሊቨርፑል ፍልሚያ ታስተናግዳለች።

ሁለቱ ቡድኖች ከአራት ዓመታት በፊት በዚሁ መድረክ ለፍጻሜ ተገናኝተው ማድሪዶች ማሸነፋቸው የሚታወስ ነው።

እግር ኳስ የሚወድ ማንኛውም ሰው ይህ ጨዋታ እንዲያመልጠው አይፈልግም። እግር ኳስ ለምኔ የሚሉት እንኳን ስለነዚህ ቡድኖች ፍልሚያ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ ሰምተዋል።

በአውሮፓ ቻምፒየንስ ታሪክ ዋንጫውን 13 ጊዜ በማንሳት ተወዳዳሪ የሌላቸው ማድሪዶች ስድስት ጊዜ የውድድሩ አሸናፊ መሆን ከቻሉት ሊቨርፑሎች ጋር ነው የሚፋለሙት።

የስፔን ኃያላኑ ማድሪዶች በዘንድሮው ውድድር ከምድብ ድልድል ጀምሮ አበቃላቸው እየተባለ ነው እዚህ የደረሱት።

ቼልሲን፣ ፒኤስጂን እንዲሁም ለዋንጫው ለማለፍ ደግሞ ማንቸስተር ሲቲን ባለቀ ሰዓት ባስቆጠሯቸው ግቦች በመታገዝ ነው እዚህ የደረሱት።

አጥቂው ካሪም ቤንዜማ ከምን ጊዜው በበለጠ በምርጥ አቋም ላይ ይገኛል። በዘንድሮው የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ 15 ግቦችን በማስቆጠር ተወዳዳሪ ያልተገኘለት ቤንዜማ፣ በስፔን ላሊጋም ቢሆን 27 ግቦችን በማስቆጠር ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ነው የጨረሰው።

ሌላኛው የቡድን አጋሩ ቪኒሺየስ ጁኒየርም ቢሆን እንደ ዘንድሮ ብዙ ግቦችን አስቆጥሮ አያውቅም። በዛሬው ምሽት ጨዋታ እነዚህ ኮከቦች የሊቨርፑልን የተከላካይ መስመር በእጅጉ እንደሚፈትኑ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል የሊቨርፑሉ አምበል ጆርዳን ሄንደርሰን በስታ ዴ ፍራንስ ስታዲየም “ማድሪድን ዝም እናሰኛለን” ሲል ተደምጧል። በዘንድሮው ውድድር ኤፍኤ ካፕ እና ካራባዎ ካፕ ያሸነፉት ሊቨርፑሎች በፕሪምየር ሊጉ ዋንጫውን በማንቸስተር ሲቲ ተነጥቀዋል።

አራት ዋንጫ ለማሸነፍ አልመው የነበሩት አሰልጣኙ የርገን ክሎፕ አሁን ላይ የመጨረሻ ተስፋቸው ቻምፒየንስ ሊግ ሆኗል።

የርገን ክሎፕ ስለቡድናቸው ስብስብ ሲናገሩ ይህ ቡድን በእውነት ልዩ ነው ብለዋል። ዋንጫውን አሸንፈው ደጋፊዎቻቸውን በደስታ ለማስፈንጠዝ መዘጋጀታቸውን አክለዋል።

ስለጨዋታው ተጠይቆ የነበረው የማድሪዱ ቤንዜማ ሊቨርፑሎች ምናልባት ይህንን ዋንጫ ያሸነፉ ያህል ሊያስቡ ይችላሉ። እኛም እሱን ነው የምንፈልገው ብሏል።

አሰልጣኝ ካርሎ አንቸሎቲ በበኩላቸው የዓመታት ልምድ ባላቸው ሞድሪች እና ክሩዝ የሚመራው የመሀል ሜዳው ቤንዜማ እና ቪኒሺየስ ሲጨመሩበት ቡድናቸው አስፈሪ እንደሚሆን ዝተዋል።

ከአራት ዓመት በፊት ሊቨርፑል በማድሪድ በፍጻሜው ሲሸነፍ ተጎድቶ የወጣው ሞሐመድ ሳላህ በዚህ ፍልሚያ ግብ ማስቆጠር እንደሚፈልግ ተናግሯል። ማድሪድ ለዋንጫው ማለፉን ሳያረጋግጥ በፊት እንኳን በፍጻሜው ማድሪድን መግጠም እንደሚፈልግ በተደጋጋሚ ተናግሮ ነበር።

ሃቅ ሚዲያ

Address

Скопје

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሃቅ ሚዲያ - Haq Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሃቅ ሚዲያ - Haq Media:

Share