06/10/2025
ብረዝምም ይነበባል።
በተዋወቅን በሁለተኛው ቀን "ለምን ቤቴ አትመጪም"የሚል ጥያቄ አቀረበልኝ።መጀመርያ ደነገጥኩ...ቀጥሎ ውስጤ ላይ አንዳች ደስ የማይል ስሜት ተፈጠረብኝ።ሳላውቀው "ይኼ ሴሰኛ አልኩኝ...."ሴሰኛ ስል ድሮ እናቴ ጎረቤታችን ያሉትን ሽማግሌ የምትጠራበት ቅፅል ስም ትዝ አለኝ።ለምን እንዲህ እንዳለቻቸው ስጠይቃት አስር ቦታ ይዘላሉ ትለኛለች ነገሩን አለባብሳ።አስር ቦታ ማለት ከብዙ ሴት ጋ ይገናኛሉ ማለቷ እንደሆን ገብቶኝ ወንድ ልጅ ከትውውቃችን ማግስ ስሜቱን ሲያሳየኝ ሴሰኛ ማለት ይቀናኛል
መልካሙ ጋ ስንገናኝ የታክሲ ብር አጥቼ ከኤቲኤም ማሽን ጋ ስታገል ነው ድንገት ከኋላዬ መጣና
"እኔ ልሞክረው"አለኝ ድምፁ ቀጭን ሰውነቱ ግዙፍ ውሀ ውሀ የሚል ንፁህ ወንድ ነው።እኔም ደጋግሜ መሞከሬ አሰልችቶኝ ቦታውን ለቅቄለት ቆምኩ።የትምህርት ሰአት ረፍዶብኝ ማደርገው ጠፍቶኝ እየተንቆራጠጥኩ ማሽኑ ለሱ ገንዘቡን ሲሰጠው ችግሩ ከኔ መሆኑ ገብቶኝ ልሄድ ስል...
"ቆንጆ እኔ ላበድርሻ"አለኝ ሁለት መቶ ብር ነጥሎ እየሰጠኝ።እውነት ለመናገር አልተግደረደርኩም ብሩን ተቀብዬው ስልኬን ሰጥቼው ተለያየን....ያን ቀን ማታ ትንሽ አወራን በነጋታው ረጅም ወሬ እና ሳቅ ተጨምሮበት ተግባባንና ሊዘጋው ሲል እቤቱ እንድሄድ ጠየቀኝ....ይሄኔ ውስጤን ቅር እያለው ቢሆንም"አንድ ቀን"አልኩት ያው እምቢ መሆኑ ይገባው ብዬ ነበር...እሱ ግን ጥያቄውን አላቆመም በመግባባታችን ውስጥ መላመድ ቢጨምርም አምኜው መሔድ አልፈለኩም።እሱም ቢሰለቸው ጭራሽ መደወሉን ተወው። እኔም ለአልጋ አስቦኝ እምቢ ስላልኩት ነው ብዬ ተውኩት።ተረሳሳን።ወር ሆነን....አንድ ቀን ድንገት ስልኬ ጮኸች ክላስ ስለነበርኩ አላነሳሁም ግን ደሞ መደወሉ ደስ ብሎኝ ነበር.....እንደወጣሁ ደወልኩለትና
የጠፋ ሰው ኩራትህ ለቀቀህ አልኩት እየተጀነንኩ
ሜሪ እናቴ አርፋለች ብቻ አለኝ።ድንግጥ ብዬ ቀረሁ የምለው አጥቼ እየተንተባተብኩ እሱ ወሬውን ቀጠለ....
ታቂያለሽ ህርሜን ከቤት ብወጣ ነው ያገኘሁሽ እናቴን ጥዬ ስለማልወጣ ሁሉ ነገሬ ቤት ነበር ድንገት በወጣሁበት ቅፅበት አንቺን አገኘሁሽ ስንገናኝ ለእማ መፍትሔ ያበጀሁ መስሎኝ ነበር።ሚስትህን ሳላይ እያለች ስለምታስጨንቀኝ አንዴ እንድትስቅልኝ ፈልጌ ነበር ቤቴ እንድትመጪ የጠየቅኩሽ ግን አልሆነም በጠቅኩሽ ማታውን እናቴ ሞታ አደረች በቃ አለና ፀጥ አለ
ምገባበት አጣሁ ምናለ እሺ ባልኩትና የእናቱን ሳቅ አይቶ በተለያዩ ብዬ አሰብኩ ከፋኝ ወድያው ሳላስበው
አሁን የት ነህ ልምጣ አልኩት ቤቱን ጠቆመኝ ሄድኩኝ ተመላለስኩኝ እዛው ቤቱ ቀረሁ ሁለት ልጆችን ወለድን መልካሙን ባሌ አደረግኩት
ከመጻሕፍት ማዕድ❤