Addis Standard Amharic

Addis Standard Amharic Addis Standard Amharic is an independent online media outlet providing news and in-depth analysis in the Amharic language.
(1)

Its contents mainly focus on current social and political affairs.
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4 Its contents mainly focus on current social and political affairs.

10/09/2025

#ኢትዮጵያ: የ ህትመት አሳታሚ ኃ.የተ.የግ.ማ ለመላው ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ2018 ዓ.ም በሰላም አደረሳችሁ እያለ አዲሱ ዓመት የጤናና የሰላም እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞቱን ይገልጻል።

መልካም አዲስ ዓመት!

Ayyaana Qaammee Garii!

ርሑስ ሓድሽ ዓመት!

ዜና: ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ለታዳሽ ሀይል እና የዲጂታል ሽግግርን የሚያግዝ የ120 ሚሊዮን ዩሮ ስምምነት ተፈራረሙየአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ በመካሄድ ላይ ላሉ የታዳሽ ሀይል እና ...
10/09/2025

ዜና: ኢትዮጵያ እና የአውሮፓ ህብረት ለታዳሽ ሀይል እና የዲጂታል ሽግግርን የሚያግዝ የ120 ሚሊዮን ዩሮ ስምምነት ተፈራረሙ

የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ በመካሄድ ላይ ላሉ የታዳሽ ሀይል እና የዲጂታል ሽግግርን የሚያሳልጡ ፕሮጀክቶችን የሚያግዝ የ120 ሚሊዮን ዩሮ ስምምነት መፈጸሙን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ። በአለም አቀፉ ታዳሽ፣ የተቀናጀ፣ ዘላቂ ኃይል እና ዲጂታላይዜሽን (RISED) ተነሳሽነት ስር የተፈጸመው ስምምነቱ በአዲስ አበባ ከተካሄደው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ ጎን ለጎን መካሄዱን ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል።

በአውሮፓ ህብረት፣ በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ (AFD) እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጋራ የገንዘብ ድጋፍ የተደረገው ፕሮግራሙ የኢትዮጵያን የኤሌክትሪክ ኃይል አውታር ለማዘመንና ለማጠናከር፣ ታዳሽ ኃይልን በስፋት ለማቀናጀትና የዲጂታል ትስስርን ለማሻሻል ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ፕሮግራሙ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2030 ድረስ ለ4 ሚሊዮን ሰዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለ12 ሚሊዮን ሰዎች ደግሞ የሞባይል ብሮድባንድ አገልግሎትን ተደራሽ ያደርጋል የተባለ ሲሆን፣ የኃይል መቆራረጥን በግማሽ መቀነስ እና በየዓመቱ 150,000 ቶን የካርቦን ዳይኦክሳይድ ልቀትን መከላከል ያስችላል ተብሎ ይጠበቃል።

ተጨማሪ ያንብቡ:
https://addisstandard.com/Amharic/?p=9198

አቶ   "ህዳሴ ግድቡ አትዮጵያውያን ስንከፋፈል ሳይሆን ስንተባበርና አንድ ስንሆን  የማንሠራው ድንቅና ደማቅ ታሪክ እንደሌለ አመላካች ነው" አሉ #ይህ በእንዲህ እንዳለ "በየቀኑ ስለሚጠፋው ...
10/09/2025

አቶ "ህዳሴ ግድቡ አትዮጵያውያን ስንከፋፈል ሳይሆን ስንተባበርና አንድ ስንሆን የማንሠራው ድንቅና ደማቅ ታሪክ እንደሌለ አመላካች ነው" አሉ

#ይህ በእንዲህ እንዳለ "በየቀኑ ስለሚጠፋው የዜጎቻችን ህይወት መቋጫ ልናበጅለት ይገባል" ብለዋል

የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር እና የመከላከያ ሚንስትር የነበሩት አቶ ለማ መገርሣ "ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት አትዮጵያውን ስንከፋፈል ሳይሆን ስንተባበርና አንድ ስንሆን የማንሠራው ድንቅና ደማቅ ታሪክ እንደሌለ አመላካች ነው" ሲሉ የፕሮጀክቱን ምርቃት ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት ገለፁ።

"እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ከትንሽ እስከ ትልቅ፣ ከደሃ እሰከ ሀብታም ይህንን ግድብ ለመገንባት የአቅሙን ያህል ሀብት በማዋጣት አሻራውን ያሳረፈበት ታሪካዊ ግድብ ነው" ያሉት አቶ ለማ አክለውም በመላው የኢትዮጵያውያን ተሳትፎና ጥረት የተገነባው ታላቁ የህዳሴ ግድብ በመጠናቀቁ የተሰማቸውን ደስታ ገልጠዋል።

"ይህም የሚያሳየው ስንከፋፈል ሳይሆን ስንተባበርና አንድ ስንሆን አትዮጵያውያን የማንሠራው ድንቅና ደማቅ ታሪክ እንደሌለ ይህ የህዳሴ ግድብ የክፍለ ዘመኑ ህያው ምስክር ነው" ሲሉ በመግለጽ፣ "መላው ኢትዮጵያውያን ምንግዜም አንድነታችን የድላችን መሠረት መሆኑን በመገንዘብ ለነገይቱ የተሻለች ኢትዮጵያ አንድነታችንን መጠበቅና ማጠናከር የግድ ይለናል" ሲሉ አበክረዋል።

ከህዳሴ ግድብ ምርቃት ጎን ለጎንም "በየቀኑ ስለሚጠፋው የዜጎቻችን ህይወት፣ ስለሚፈሰው ደምና ስለምታነባው ኢትዮጵያዊ እናት፣ በጥቅሉ ስለአገራችን ሠላምና ደህንነት ቆም ብለን ልናስብበትና በጋራ መቋጫ ልናበጅለት ግድ ይለናል" ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

አቶ ለማ በመልዕክታቸውም የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክቱን አስጀምረው በማጠናቀቅ ሂደት ውስጥ አስተዋጽኦ የነበራቸው የአገራችን መሪዎችና ባለሙያዎች ሁሉ እንደየድርሻቸውና አስተዋጽኦአቸው መጠን ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

መጋቢት 24/2003 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ከ14 ዓመታት በኋላ ትናንት ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የቀጠናው ሀገራት መሪዎች እና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት በይፋ ተመርቋል።

ይህን ተከትሎ የሀገራት መሪዎች፣ የተቋማት የስራ ሀላፊዎች እና በርካታ ወገኖች የተሰማቸውን ደስታ በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።

 #ኬንያ እና   ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን አወድሰው ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ስምምነት እንደሚያደርጉ ገለፁኢትዮጵያ በአፍሪካ ትልቁን የኃይል ማመንጫ የሆነውን ታ...
10/09/2025

#ኬንያ እና ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቁን አወድሰው ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ስምምነት እንደሚያደርጉ ገለፁ

ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትልቁን የኃይል ማመንጫ የሆነውን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ማስመረቋን ተከትሎ ኬንያ እና ደቡብ ሱዳን ፕሮጀክቱን በማወደስ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ስምምነት እንደሚያደርጉ ገለፁ።

የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኪር፣ መንግስታቸው ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሚመነጨውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት የሚያስችለውን ስምምነት በማጠናቀቅ ላይ መሆኑን አስታውቀዋል።

ኪር “ለሆስፒታሎቻችን እና ትምህርት ቤቶቻችንን የሚሆን የኤሌክትሪክ ኃይል ከግድቡ ለማግኘት በቅርቡ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ስምምነት እንፈርማለን” ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የምታገኘው ኬንያም ተጨማሪ ኃይል ለመግዛት ፍላጎት አሳይታለች ተብሏል፡፡ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክቱን “የመላው አፍሪካውያን መገለጫ” ሲሉ አሞካሽተውት፣ ሀገራቸው ተጨማሪ የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ዕቅድ እንዳላት አረጋግጠዋል።

ፕሮጀክቱ በአፍሪካውያን የሚመሩ የመሠረተ ልማት ዝርጋታዎችን ስፋት ያሳያል ያሉት ሩቶ አክለውም ዓላማው አፍሪካውያንን በኃይል ማስተሳሰር ከሆነው የአፍሪካ ሕብረት መርህ ጋር የሚጣጣም እንደሆነ መግለጻቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማጠናከር፣ ተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥን ለማቃለል እና ኢትዮጵያ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የምታደርገውን ሽግግር ለማፋጠን አይነተኛ ሚና እንደሚጫወት ተመላክቷል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክቱን “አፍሪካውያን ማጠናቀቅ እና ማሳካት እንደሚችሉ ማሳያ ነው” ሲሉ ገልጸው የፕሮጀክቱን ፍጻሜ “ታሪካዊ ስኬት” ሲሉ አወድሰውታል። በደርዘን የሚቆጠሩ የአፍሪካ ሀገራት እና የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች በተገኙበት የተካሄደው የፕሮጀክቱ የምረቃ ስነ ስርዓት፣ የቀጠናው ሀገራት ኢትዮጵያ በኃይል ኤክስፖርት እያደገ የመጣውን ሚናዋ ላይ ያላቸውን ፍላጎት የሚያንጸባርቅ መሆኑ ተጠቁሟል።

 #ግብፅ በ  #ሶማሊያ ለምታሰማራቸው ወታደሮቿ የጦር ሰፈር ለይታለች ተባለየግብፅ መከላከያ ሠራዊት በአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የድጋፍና ማረጋጋት ተልዕኮ (AUSSOM) ስር ለሚያሰማራቸው ወታ...
10/09/2025

#ግብፅ በ #ሶማሊያ ለምታሰማራቸው ወታደሮቿ የጦር ሰፈር ለይታለች ተባለ

የግብፅ መከላከያ ሠራዊት በአፍሪካ ህብረት የሶማሊያ የድጋፍና ማረጋጋት ተልዕኮ (AUSSOM) ስር ለሚያሰማራቸው ወታደሮቹ መስፈሪያ የሚሆን የጦር ሰፈር መለየቱ ተገለፀ።

የግብፅ ጦር የቴክኒክ ኮሚቴ ባሳለፍነው ሳምንት በአፍሪካ ቀንድ አገራት ባደረገው ጉብኝት ወቅት፣ ለግብፅ ጦር ኃይል የአካባቢ፣ የአየር ንብረትና የማህበረሰብ መስተጋብሮችን ገምግሞ ቁልፍ የሆኑ ከተሞችን ለይቷል ተብሏል።

የግብፅ የጦር ኃይል በቅርቡ በመካከለኛው ሸበሌ ክልል የሚገኙትንና የብሩንዲ ሰላም አስከባሪዎች የሰፈሩባቸውን የባላድ፣ የጆውሃር፣ የቡራኔ እና የመሃዳይ ከተሞች ላይ ይሰፍራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጋርዌ ኦንላይን በዘገባው አመልክቷል።

በቅርቡ የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስቴር የመጀመሪያው የግብፅ ጦር ኃይሎች ሥልጠና መጠናቀቁን ተከትሎ የግብፅ ወታደሮች በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ እና ማረጋጋት ተልዕኮ (አውሶም) ሊሰማሩ መቃረባቸውን በአዎንታ መቀበሉን መዘገቡ አይዘነጋም፡፡

ሁኔታውንም “ግብፅ ለሶማሊያ ደህንነት ያላትን ቁርጠኝነት እና በአዲሱ የአፍሪካ ህብረት ተልዕኮ ማዕቀፍ ስር የሶማሊያ ብሔራዊ ጦርን አቅም ለማጎልበት የምታደርገውን ድጋፍ የሚያሳይ ነው” ሲል መግለጹ ይታወሳል።

ይህን የግብጽ ወታደሮች በሶማሊያ መገኘት በተመለከተ ኢትዮጵያ "ምቾት የሚሰጥ ባይሆንም ለስጋት የሚዳርገኝ ግን አይደለም" ስትል በቅርቡ መግለጿ ይታወቃል።

በወቅቱ በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ ከሶማሊያ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቆይታ የግብፅ ጦር ሀይል በሶማሊያ ውስጥ መኖሩ "ኢትዮጰያን እንደማያስፈራት እና እንደማያሳስባት" ገልጸዋል።

አክለውም "የግብፅ ወታደሮች ሀይሎቻችንን ለመገዳደር እስካልሞከሩ ድረስ በሶማሊያ ውስጥ መገኘታቸውን ኢትዮጵያ እንደ ቀጥተኛ ስጋት እንደማትመለከተው"ም አጽንኦት ሠጥተዋል።

 #ግብፅ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን ተከትሎ ለፀጥታው ምክር ቤት አቤቱታ አሰማችግብፅ በትናንትናው ዕለት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን ተከትሎ ኢትዮጵያ  “ዓለም አቀፍ ...
10/09/2025

#ግብፅ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን ተከትሎ ለፀጥታው ምክር ቤት አቤቱታ አሰማች

ግብፅ በትናንትናው ዕለት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መመረቁን ተከትሎ ኢትዮጵያ “ዓለም አቀፍ ሕግን ጥሳለች” ስትል ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ባስገባችው ደብዳቤ አቤቱታዋን አሰምታለች።

በደብዳቤው የግብጽ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደላቲ የህዳሴው ግድብ ምርቃት “በሕግ ሊደገፍ የማይችል ሕገወጥ የአንድ ወገን ተግባር” ነው ብለዋል።

አያይዞም “ግብጽ በአባይ ወንዝ ላይ ያላትን የህልውና ጥቅም በቀላሉ ትተዋለች ማለት ከንቱ ምኞት ነው” ሲል ገልጾ፣ “ኢትዮጵያ የጋራ በሆነው የውሃ ሃብት ላይ በብቸኝነት ቁጥጥር እንድታደርግ ግብጽ አትፈቅድም” ሲል አጽንኦት ሰጥቷል።

ካይሮ የህልውና ጥቅሟን ለማስከበር እንዲሁም በአለም አቀፍ ህግ እና በተባበሩት መንግስታት ቻርተር ስር የተፈቀዱትን ማናቸውም እርምጃዎች ለመውሰድ እንደምትችል መግለጿን የቱርኩ አናዶሉ ኤጀንሲ ዘግቧል።

ግብጽ አቤቱታዋን ያቀረበችው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ትናንት ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የቀጠናው ሀገራት መሪዎች እና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት በይፋ መመረቁን ተከትሎ ነው።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከተገኙ የቀጠናው ሀገራት መሪዎች መካከልም የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ፣ የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦመር ጊሌህ እና የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት ይገኙበታል።

የ   የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአየር ክልል በአስተማማኝ ሁኔታ እየተጠበቀ ነው አለየታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአየር ክልል በአስተማማኝ ሁኔታ እየተጠበቀ ነው ሲሉ የኢፌዴሪ አየር ሀይል ዋና...
09/09/2025

የ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ የአየር ክልል በአስተማማኝ ሁኔታ እየተጠበቀ ነው አለ

የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአየር ክልል በአስተማማኝ ሁኔታ እየተጠበቀ ነው ሲሉ የኢፌዴሪ አየር ሀይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ አስታወቁ፡፡

የህዳሴ ግድቡ ተጠናቅቆ ለምረቃ በመብቃቱ ለመላው ኢትዮጵያውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ዋና አዛዡ አክለውም ግድቡንና የኢትዮጵያን አየር ክልል የማያስደፍር የአየር ሀይል ተገንብቷል ሲሉ ገልጸዋል፡፡

አያይዘውም የኢትዮጵያ አየር ኃይል የግድቡ መሠረተ ድንጋይ ከተቀመጠበት ጊዜ አንስቶ ለምርቃት እስከበቃበት ግዜ ድረስ የቀጠናውን የአየር ክልል በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ ላይ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ተቋሙ ካለፉት አመታት በተለየ ሁኔታ የምድር አየር መከላከል አቅም ማሳደጉን ጠቅሰው፥ በሰማይ የጠላትን ኢላማ ገና ከመነሻቸው ማውደም የሚችሉ ተዋጊ የጦር ጄቶችን መታጠቁን መግለጻቸውን የዘገበው ኤፍ ኤም ሲ ነው፡፡

================
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ቲክቶክ፡ https://rb.gy/jgdsjm

 #ኢትዮጵያ ለሰላማዊ አገልግሎት የሚውል የ  #ኒውክሌር ማበልጸጊያ ግንባታ በቅርቡ ትጀምራለች ሲሉ ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ አስታወቁጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ኢትዮጵያ ከሕዳሴ ግ...
09/09/2025

#ኢትዮጵያ ለሰላማዊ አገልግሎት የሚውል የ #ኒውክሌር ማበልጸጊያ ግንባታ በቅርቡ ትጀምራለች ሲሉ ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ አስታወቁ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) "ኢትዮጵያ ከሕዳሴ ግድብ የሚስተካከል ለሰላማዊ አገልግሎት የሚውል የኒውክሌር ማበልጸጊያ ግንባታ በቅርቡ ትጀምራለች" ሲሉ አስታወቁ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያስታወቁት ዛሬ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የቀጠናው ሀገራት መሪዎች እና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት በይፋ በተመረቀበት ወቅት ነው።

በይፋዊ የምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ጠ/ሚ ዐብይ "ኢትዮጵያ ከሕዳሴ ግድብ የሚስተካከል ለሰላማዊ አገልግሎት የሚውል የኒውክሌር ማበልጸጊያ ግንባታ በቅርቡ ትጀምራለች" ሲሉ ተናግረዋል።

እንዲሁም በአፍሪካ ግዙፍ የሆነውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ አክለውም በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ደግሞ የመጀመሪያው የጋዝ ፋብሪካ ይመረቃል፤ በዛው ዕለት ሁለተኛው እና ከመጀመሪያው በ10 እጥፍ የሚበልጠው ሁለተኛው የጋዝ ፋብሪካ ግንባታ ይጀመራልም ብለዋል።

በተጨማሪም የኢትዮጵያን የረጅም ዘመን ነዳጅ የማውጣት ፍላጎት እውን የሚያደርገው የንዳጅ ማጣሪያ እውን ይሆናል ሲሉ ጠቅሰው በቅርቡ የተፈረመው የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታም በቀጣይ ጥቂት ጊዜያት እውን እንደሚሆን አመላክተዋል።

በሚቀጥሉት 5 እና 6 ዓመታት በትንሹ 1.5 ሚሊየን በላይ ቤቶች ይገነባሉም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ በአጠቃላይ ከ30 ቢሊየን ዶላር በላይ ሃብት የሚፈስስባቸው ሜጋ ፕሮጀክቶች እንደሚከናወኑ ገልጸዋል።

በማዕከላዊ ትግራይ ዕዳጋ ዓርቢ ከተማ ከ300 በላይ ቤቶች በከባድ አውሎ ንፋስ ጉዳት ደረሰባቸውበማዕከላዊ ትግራይ ዕዳጋ ዓርቢ ከተማ ከባድ አውሎ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ከባድ ዝናብ  ከ300 በ...
09/09/2025

በማዕከላዊ ትግራይ ዕዳጋ ዓርቢ ከተማ ከ300 በላይ ቤቶች በከባድ አውሎ ንፋስ ጉዳት ደረሰባቸው

በማዕከላዊ ትግራይ ዕዳጋ ዓርቢ ከተማ ከባድ አውሎ ንፋስ ቀላቅሎ በጣለ ከባድ ዝናብ ከ300 በላይ ቤቶች ለጉዳት መዳረጋቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት ገለጹ።

የከተማው አስተዳደር ለአካባቢው መገናኛ ብዙኃን እንደገለጸው፣ ንፋሱ ትናንት ሰኞ ከተማዋን በመምታት በግል እና በመንግስት ንብረት ላይ ከፍተኛ ውድመት አድርሷል። በርካታ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎችም የወደቁ ሲሆን፣ አንዳንዶቹም በእሳት ተያይዘዋል ተብሏል።

የደረሰውን ጉዳት መጠን ለመገምገም አንድ ኮሚቴ ተቋቁሟል የተባለ ሲሆን፣የአከባቢው የስራ ሃላፊዎች ለተጎጂ ነዋሪዎች አስቸኳይ ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጥሪ አቅርበዋል። በአደጋው እስካሁን የሰው ህይወት ስለመጥፋቱ ሪፖርት አልተደረገም።

================
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ቲክቶክ፡ https://rb.gy/jgdsjm

09/09/2025

#ኢትዮጵያ ታላቁን የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የቀጠናው ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት በማስመረቅ ላይ ትገኛለች

#ኢትዮጵያ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በዛሬው ዕለት የቀጠናው ሀገራት መሪዎች እና ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት በደማቅ ሥነ-ሥርዓት በይፋ በማስመረቅ ላይ ትገኛለች።

  ፕሮጀክት በይፋ ተመረቀታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዛሬ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ተመርቋል።በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የኬንያው ፕሬዚዳን...
09/09/2025

ፕሮጀክት በይፋ ተመረቀ

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዛሬ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም በይፋ ተመርቋል።

በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ፣ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼክ ሞሐሙድ፣ የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦመር ጊሌህ እና የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት ተገኝተዋል።

በተጨማሪም የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግሥት የስራ ሀላፊዎች በምረቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተዋል፡፡

መጋቢት 24/2003 ዓ.ም የተጀመረው የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ግንባታ 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ የሚይዝ ሲሆን 5,150 ሜጋ ዋት ሃይል የማመንጨት አቅም አለው።

================
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ቲክቶክ፡ https://rb.gy/jgdsjm

ስማቸው ከግድቡ ጋር ከተጣበቀ ባለታሪኮች መካከል አንዱ የሆኑት ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ሲታወሱየታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሲነሳ በረሃ ባጠየመው ፊታቸው ላይ ጺማቸው የጎፈረ አንድ ጎልማሳ አይዘነጉም።...
09/09/2025

ስማቸው ከግድቡ ጋር ከተጣበቀ ባለታሪኮች መካከል አንዱ የሆኑት ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ሲታወሱ

የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ሲነሳ በረሃ ባጠየመው ፊታቸው ላይ ጺማቸው የጎፈረ አንድ ጎልማሳ አይዘነጉም። ስማቸው ከግድቡ ጋር ከተጣበቀ ባለታሪኮች መካከልም አንዱ ናቸው - ኢንጂነር ስመኘው በቀለ።

ኢንጂነሩ የህዳሴ ግድቡ የመሠረተ ድንጋይ ከተጣለበት መጋቢት 24/2003 ዓ.ም. አንስቶ የግድቡን ፕሮጀክት ለሰባት ዓመታት መርተዋል።

"ስመኘው ልጆቹን፣ ሚስቱን እና ቤተሰቡን ትቶ ያገባው ሕዳሴን ነበር"- የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስዩም መስፍን። የቤተሰብ አባሎቻቸውም የሚያስረግጡት ይህንኑ ነው።

የኢንጂነሩን ሕልፈት ተከትሎ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ አንድ የቤተሰብ አባል "እሱ አገሬን ሥራዬን እያለ ሁሉም ሰው ረስቶታል። እሱ ሁሉ ነገሩ ሥራው ላይ ነበር። ዘመድ አይልም .." ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

እርሳቸው የግድቡን ሥራ እየመሩ በነበረበት ወቅት ባልደረባቸው የነበረችው ኢንጂነር ብሩክታዊት እሸቱ፣ "ኢንጂነሩ እረፍት አልበራቸውም" ስትል ለጣቢያው እማኝነቷን ሰጥታለች።

የግድቡ ግንባታ 24 ሰዓት የሚከናወን ስለነበር ሌሊት ሳይቀር ወደ ግንባታው ሥፍራ በድንገት የመጡበት ቀን ጥቂት እንዳልነበር ትናገራለች።

በዚህ ሁሉ ውስጥ እያለፉ "ትህትናቸው ያስገርመኝ ነበር" የምትለው ብሩክታዊት፣ እውቀታቸው እና አክብሮታቸው የሠራተኛውን ቀልብ የገዛ እንደነበርም ታወሳለች።

ከአፍሪካ በግዝፈቱ ቀዳሚ የሆነው ግድብ ግንባታ የመጀመሪያ መሪ የነበሩት ኢንጂነር ስመኘው ጎንደር፣ ማክሰኝት በተባለች አነስተኛ ከተማ ነው የተወለዱት። የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውንም በእንፍራንዝ፣ በደሴ እና በወልዲያ ከተሞች ተከታትለዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/cdxq9lv57q8o

Address

Opposite CMC
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 12:30

Telephone

+251970048900

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Standard Amharic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Standard Amharic:

Share