Addis Standard Amharic

Addis Standard Amharic Addis Standard Amharic is an independent online media outlet providing news and in-depth analysis in the Amharic language.

Its contents mainly focus on current social and political affairs.
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4 Its contents mainly focus on current social and political affairs.

ዜና፡ ፍርድ ቤቱ ለጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ የሰጠውን የዋስትና ትዕዛዝ ቢያጸናም ፖሊስ ለከተማ አስተዳደሩ ሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ ጠየቀ፤  #ሲፒጄና  #አሚነስቲ ተስፋለም ወልደየስ ከእስር...
11/06/2025

ዜና፡ ፍርድ ቤቱ ለጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ የሰጠውን የዋስትና ትዕዛዝ ቢያጸናም ፖሊስ ለከተማ አስተዳደሩ ሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ ጠየቀ፤ #ሲፒጄና #አሚነስቲ ተስፋለም ወልደየስ ከእስር እንዲለቀቅ ጠየቁ

የ ከተማ አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ ችሎት ፍርድቤት ለጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ የሰጠውን የዋስትና ትዕዛዝ ቢያጸናም ፖሊስ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ መጠየቁን የጋዜጠኛው ጠበቃ ቤተማርያም ሀይሉ ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ፖሊስ እሁድ በተካሄደው የ እና የ #ሲዳማ ቡና እግር ኳስ ጨዋታ "ደጋፊዎች ስታዲየም ገብተን ማየት አለብን በማለት ያስነሱትን ሁከት እና ብጥብጥ ጋዜጠኛው በቦታው ላይ ተገኝቶ መንግስት ስታዲየሙን እየተጠቀመበት ያለው የትግራይ ተወላጆች ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያደርጉበት ብቻ ነው የሚል ንግግር በቦታው ለተሰበሰቡ ሰዎች ተናግሯል" ማለቱን ጠበቃው ቤተማርያም ሀይሉ ገልጸዋል።

እስሩን ተከትሎ ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ሲፒጄ እና አሚነስቲ ኢንተርናሽናል በተናጠል ባወጡት መግለጫ፤ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት የ #ኢትዮጵያ ኢንሳይደር የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስን "በአስቸኳይ እንዲፈቱ" ጠይቀዋል።

ሙሉ ዘገባ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=8073

በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ"በየብስም ሆነ በባሕር የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል" ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅ...
11/06/2025

በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

"በየብስም ሆነ በባሕር የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል" ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ተናገሩ፡፡

ፊልድ ማረሻሉ ይህን የተናገሩት፤ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመከላከያ ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በገመገመበት መድረክ ነው።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚህ ወቅት እንዳሉት፤ መከላከያ ሠራዊቱ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናን ሰላምና ደህንነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራነው።

ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ከቀጣናው ሀገራት ጋር በትብብር ለመስራትና በጋራ ለመበልጸግ ያላሳለሰ ጥረት እያደረገች እንደምትገኝ መግለፃቸውንም ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል፡፡

በአሁኑ ወቅት "በየብስም ሆነ በባሕር የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት እንዲሁም የሀገሪቱን ሉዓላዊነት የሚያስከብር ሠራዊት መገንባቱን" አስገንዝበዋል ተበሏል፡፡

የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) በበኩላቸው፤ ተዓማኒነት ያለው ነጻና ገለልተኛ ወታደራዊ የፍትህ ዳኝነት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው "የሠራዊቱን አስተማማኝ የሎጂስቲክስ ክምችት ማሟላት መቻሉን" ተናግረዋል፡፡

================
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ዩቲዩብ፡ https://rb.gy/bjcbg
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ቲክቶክ፡ https://rb.gy/jgdsjm

 #ኢትዮጵያ በ  #ሩሲያ ድጋፍ የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ግንባታን 95 በመቶ ማጠናቀቋ ተገለጸከሶስት አስርት አመታት በፊት የባህር በር ያጣችው ኢትዮጵያ፤ በ  ጃን ሜዳ እያከናወነች ያ...
11/06/2025

#ኢትዮጵያ በ #ሩሲያ ድጋፍ የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ግንባታን 95 በመቶ ማጠናቀቋ ተገለጸ

ከሶስት አስርት አመታት በፊት የባህር በር ያጣችው ኢትዮጵያ፤ በ ጃን ሜዳ እያከናወነች ያለውን የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ግንባታ በቅርቡ እንደምታጠናቅቅ ተዘግቧል። የጠቅላይ መምሪያው ግንባታ 95 በመቶ መተናቀቁን ስፑትኒክ አፍሪካን ጠቅሶ አፍሪካ ቢዝነስ ኢንሳይደር ዘግቧል።

ይህም ኢትዮጵያ የባህር በር ባይኖራትም ብሔራዊ የባህር ኃይልን ዳግም ለመገንባት ያላትን ምኞት የሚያሳይ አንዱ እርምጃ መሆኑን ዘገባው አመላክቷል።

በሦስት ሄክታር ስፋት ላይ የተገነባው ባለ አራት ፎቅ የባህር ኃይል ዋና መስሪያ ቤት ሕንፃ፤ አስተዳደራዊ ቢሮዎችን፣ የሕክምና ክሊኒክን፣ የመሰብሰቢያ አዳራሾችን፣ የስፖርት ተቋማትንና ሌሎች መሠረተ ልማቶችን የሚያካትት ሲሆን ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ መሠረት በቅርቡ እንደሚጠናቀቅ ተገልጿል።

በተጨማሪም ይህ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ላይ ያላትን ተፅዕኖ መልሳ ለማግኘት ለማግኘት የምታደርገው ስትራቴጂ አካል ነው ተብሏል።

ከጎርጎሮሳውያኑ 1993 ጀምሮ ወደ የባህር በር ብታጣም፣ የኢትዮጵያ መንግስት የባህር ኃይል አቅሞች የንግድ መንገዶችን ለመጠበቅ፣ ለአለም አቀፍ የባህር አደጋዎች ምላሽ ለመስጠት እና በጂቡቲ እና በሱዳን ወደቦች በኩል ወደ ዓለም አቀፍ ውሃዎች መድረስን ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑን ገልጿል።

በመጋቢት ወር ኢትዮጵያ ከሩሲያ መንግስት ጋር የባህር ኃይል ልማትን እና ስልጠናን ለመደገፍ የትብብር ስምምነት ተፈራርማለች። ይህ ስምምነት የተደረገው ቀደም ሲል #ከፈረንሳይ ጋር የነበረው የባህር ኃይል አጋርነት መቋረጡን ተከትሎ መሆኑን ዘገባው አመላክቷል።

በጊዜው የሩሲያ ባሕር ኃይል ምክትል አዛዥ አድሚራል ቪላዲሚር ቮሮቢቭ የኢትዮጵያ ባሕር ኃይል የሚገነባቸውን የባሕር ኃይል ተቋማት ጠቅላይ መምሪያውና #ቢሾፍቱ የሚገኘውን ማሰልጠኛ ማዕከል ጎንኝተው፤ የኢትዮጵያን የባህር ኃይል አቅም ለማጠናከር #ሞስኮ ድጋፍ እንደምታደርግ ቃል መግባታቸው ይታወሳል።

================
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ዩቲዩብ፡ https://rb.gy/bjcbg
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ቲክቶክ፡ https://rb.gy/jgdsjm

ዜና፡ በፍቅር አጋሩ ሞት ተጠርጥሮ በእስር ላይ የነበረው ድምጻዊ  #አንዷለም ጎሳ ከሶስት ወራት እስር በኋላ ተፈታየፍቅር አጋሩ በሆነችው   ሞት ተጠርጥሮ በእስር ላይ የነበረው ድምጻዊ አንዷ...
11/06/2025

ዜና፡ በፍቅር አጋሩ ሞት ተጠርጥሮ በእስር ላይ የነበረው ድምጻዊ #አንዷለም ጎሳ ከሶስት ወራት እስር በኋላ ተፈታ

የፍቅር አጋሩ በሆነችው ሞት ተጠርጥሮ በእስር ላይ የነበረው ድምጻዊ አንዷለም ጎሳ ከሶስት ወር እስር በኋላ ትናንት ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ/ም መፈታቱን ጠበቃው ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

የድምጻዊው ጠበቃ ሊበን አብዲ እንደገለጸው፤ አንዷልም በ50 ሺህ ብር ዋስ ከእስር የተለቀቀው፤ ፖሊስ ሲያደረግ የነበረውን ምርመራ ካጠናቀቀ በኋላ አቃቤ ህግ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ክስ ባለመመስረቱ ነው።

ይሁን እንጂ ጉዳዩ እስካሁን ሙሉ በሙሉ አለመዘጋቱን ጠበቃው ተናግረዋል። “አቃቤ ህግ በተሰጠው ጊዜ ውስጥ ክስ አልመሰረትኩም ወይም የፖሊስ ምርመራ ውጤት ክስ ለመመስረት በቂ አይደለም ብሎ ጉዳዩን አልዘጋውም፤ ስለዚህ የአቃቤ ህግ ውሳኔ እየተጠበቀ ነው” ብሏል።

ተጨማሪ ያንብቡ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=8066

ዜና፡ የመንግስታት ድርጅት የእርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት “የምዕራብ  #ትግራይ አከባቢዎችን አከራካሪ ብሏል” በሚል ተቃውሞ ቀረበበትየተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ...
11/06/2025

ዜና፡ የመንግስታት ድርጅት የእርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት “የምዕራብ #ትግራይ አከባቢዎችን አከራካሪ ብሏል” በሚል ተቃውሞ ቀረበበት

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት፤ አዲስ ባወጣው አመታዊ ሪፖርት፤ “የምዕራብ ትግራይ አከባቢዎችን አከራካሪ ሲል ጠርቷል” ሲሉ በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ሲቪል ማህበራት እና ፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃወሙ።

አለም አቀፉ የትግራየ ሙሁራን እና ባለሙያዎች ማህበርን ጨምሮ በክልሉ ዙሪያ የሚሰሩ 18 ሲቪክ እና የምርምር ተቋማት በጋራ ትላንት ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጡት መግለጫ፤ የመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት፤ በአመታዊ ሪፖርቱ ላይ “የምዕራብ ትግራይ አከባቢዎችን በካርታ አስደግፎ አከራካሪ በሚል የተጠቀመበትን አገላለጽ እንወግዛለን” ብለዋል።

ማስተባበሪያ ቢሮው፤ በቅርቡ ባወጣው አመታዊ ሪፖርቱም ሆነ ቀደም ሲል ባወጣቸው መግለጫዎች “በካርታ በማስደገፍ የምዕራብ ትግራይ አከባቢዎችን በአማራ ክልል እንደሆኑ አድርጎ አቅርቧል”፤ ያለው የተቋማቱ የጋራ መግለጫ፤ በተጨማሪም “አከራካሪ ቦታዎች” የሚል አገላለጽ እየተጠቀመ ነው ሲሉ ተችቷል።

በተመሳሳይ ሳልሳይ ወያነ ትግራይ ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፤ የመንግስታቱ ድርጅ “በካርታ አስደግፎ ምዕራብ ትግራይን አከራካሪ በሚል ማቅረቡን” በጽኑ እንደሚያወግዘው ጠቅሶ፣ ቢሮው የተጠቀመው ካርታ “ህገወጥና አሳሳች ነው” ሲል ተችቷል።
https://addisstandard.com/Amharic/?p=8060

የ  #ኢትዮጵያ ኢንሳይደር የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ መታሰሩ ተገለፀበሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሥር የሚተዳደረው “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነመረብ...
10/06/2025

የ #ኢትዮጵያ ኢንሳይደር የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ መታሰሩ ተገለፀ

በሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ሥር የሚተዳደረው “ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ “ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት” ወንጀል ተጠርጥሮ እሁድ ሰኔ 1 ቀን፤ 2017 በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር መዋሉ ተገለፀ።

ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዛሬ ሰኔ 3 ባወጣው መግለጫ፤ ጋዜጠኛ ተስፋለም በአዲስ አበባ ከሚገኘው ግዮን ሆቴል ቅጥር ግቢ ውስጥ ሲቪል በለበሱ የፀጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ሥር ውሎ፤ ሌሊቱን እስጢፋኖስ አካባቢ በሚገኝ የፖሊስ መምሪያ ሕንፃ ውስጥ ወንበር ላይ እንዲያሳልፍ መደረጉን ገልጧል።

ከዛም ትላንት ሰኞ ሰኔ 2 ቀን፤ 2017 ቄራ አካባቢ ወደሚገኝ የፖሊስ መምሪያ መዘዋወሩን እና ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 3 ቀን፤ 2017 በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት፣ ቂርቆስ ምድብ ችሎት ቀርቦ በ15,000 ብር ዋስትና እንዲፈታ ቢወሰንም እስካሁን ሳይለቀቅ መቅረቱን ተገልጧል።

የተስፋለም የዋስትና መብት እንዲከበር ከተሰጠው ትዕዛዝ በኋላ መርማሪ ፖሊስ በቃል ይግባኝ እንደሚጠይቅ ገልጿል ያለው መግለጫው፤ ይሁንና እስካሁን በይፋ ፍርድ ቤት ይግባኝ አልጠየቀም ብሏል።

የተስፋለም ዋስትና እንዲከበር ሐቅ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን አስፈላጊውን ክፍያ ፈጽሞ በፍርድ ቤቱ ለቂርቆስ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የተጻፈው ደብዳቤ በሚመለከታቸው የፖሊስ መኮንን ሳይፈረምበት ቀርቷል ተብሏል። በዚህም ምክንያት ጋዜጠኛ ተስፋለም በፍርድ ቤት የተረጋገጠለት የዋስትና መብት አልተከበረም ሲል መግልጫው አስታውቋል።

ተቋሙ የዋና አዘጋጁ ተስፋለም ወልደየስ እስር በሚዲያው ሥራዎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ የሚያሳድር መሆኑን ጠቅሶ፤ በአስቸኳይ ወደ ሥራው እንዲመለስ ጥሪ አቅርቧል።

የኢትዮጵያ ኢንሳይደር የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም በ2013 ዓ/ም የኢሬቻ በዓል ላይ የተካሄደውን ተቃውሞ በቪድዮ በሚዲያው ላይ በማሰራጨቱ ምክንያት በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ እንደነበር ይታወሳል።

የፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ጠቅላላ ገቢ 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር እንደሚሆን ተገመተ በ2018 በጀት ዓመት የውጪ ርዳታን ጨምሮ የፌዴራል መንግስት ጠቅላላ ገቢ 1 ነጥብ 5 ትሪ...
10/06/2025

የፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ጠቅላላ ገቢ 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር እንደሚሆን ተገመተ

በ2018 በጀት ዓመት የውጪ ርዳታን ጨምሮ የፌዴራል መንግስት ጠቅላላ ገቢ 1 ነጥብ 5 ትሪሊዮን ብር እንደሚሆን መገመቱን የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሺዴ ለምክር ቤቱ ገለፁ።

ዛሬ በተካሄደው 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 35ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ አቶ አህመድ ሺዴ፤ ከአገር ውስጥ ምንጮች ከታክስና ታክስ ካልሆኑ ገቢዎች 1 ነጥብ 23 ትሪሊዮን ብር እንደሚሰበሰብ መታቀዱን ጠቅሰው፤ ቀሪው ከውጪ እርዳታ እንደሚገኝ የታቀደ መሆኑን ገልጸዋል።

የፌዴራል መንግስት ለ2018 በጀት ዓመት 1 ነጥብ 93 ትሪሊዮን ብር ረቂቅ በጀት ለምክር ቤት መቅረቡም ተመላክቷል።

ሚኒስትሩ ከወጪ በጀቱ ውስጥ 1 ነትብ 2 ትሪሊየን ብር ለመደበኛ ወጪ እንዲሁም 415 ቢሊዮን ለካፒታል ወጪ መመደቡን ጠቅሰው፤ 315 ቢሊዮን ብር ለክልል መንግስታት የበጀት ድጋፍ፣ 14 ቢሊዮን ብር ለክልሎች ለዘላቂ ልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የተመደበ በጀት መሆኑን አስረድተዋል።

ከፌዴራል መንግስት የወጪ በጀት ውስጥ 61 በመቶው ለመደበኛ በጀት የተመደበ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ የካፒታል በጀት ከጠቅላላ በጀቱ የ22 በመቶ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል።

የፌዴራል መንግስት የ2018 ረቂቅ በጀት ሲዘጋጅ የፊስካል ፖሊሲዎች ላይ ተመስርቶ የተዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል።

በ2018 በጀት ዓመት የመንግሥትን ገቢ አሰባሰብ ለማሳደግ እንደሚሰራ ጠቅሰው፤ አዳዲስ የታክስ ፖሊሲዎችን በስራ ላይ ለማዋልና በሥራ ላይ ያሉት ላይ ማሻሻያ ለማድረግ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።

ምክር ቤቱ የፌዴራል መንግስት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ላይ በመወያየት ረቂቅ የበጀት አዋጁን ለዝርዝር እይታ ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ እንደሚመራም ኢፕድ ዘግቧል።

የማዳበሪያ ዋጋ በእጥፍ በመጨመሩ በቀጣይ ዓመት 'የምርት ማነስ' ሊኖር እንደሚችል የ  #አማራ ክልል አርሶ አደሮች አስጠነቀቁየማዳበሪያ ዋጋ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በእጥ...
10/06/2025

የማዳበሪያ ዋጋ በእጥፍ በመጨመሩ በቀጣይ ዓመት 'የምርት ማነስ' ሊኖር እንደሚችል የ #አማራ ክልል አርሶ አደሮች አስጠነቀቁ

የማዳበሪያ ዋጋ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በእጥፍ በመጨመሩ ዋና ዋና የምግብ እህሎች ላይመረቱ እንደሚችሉ እና ‘የምርት ማነስ' ሊኖር እንደሚችል የአማራ ክልል አርሶ አደሮች አስጠነቀቁ።

በሰሜን ጎጃም ዞን የአቸፈር ወረዳ አርሶ አደር፤ ከዚህ ቀደም እስከ 8 ኩንታል ማዳበሪያ ገዝቶ ይጠቀም የነበረው አርሶ አደር አሁን ባለው የዋጋ ጭማሪ ምክንያት ከ2 ኩንታል በላይ መግዛት ባለመቻሉ የእርሻ ማሳዎች ያለጥቅም እየቀሩ ነው ሲሉ ለዶይቸ ቬሌ ተናግረዋል።

አርሶ አደሩ ብዙም ለምግብ አገልግሎት የማይውለውንና ማዳበሪያ የማያስፈልገውን “ግብጦ” የተባለ የእህል ዓይነት ለመዝራት እየተገደደ እንደሆነም ገልጠዋል።

የምሥራቅ ጎጃም ዞን አንድ አርሶ አደር በበኩላቸው በማዳበሪያ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመሩ ምክንያት ጦም የሚያድሩ የእርሻ ማሳዎች ሊኖሩ ይችላሉ ብለዋል።

ባለፈው ዓመት 1,600 ብር ይሸጥ የነበረው 50 ኪሎ ማዳበሪያ በዚህ ዓመት በ3,800 ብር እየተሸጠ ነው ሲሉ ዶይች ቬሌ ያነጋገራቸው የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር የደሀና ወረዳ አርሶ አደር ገልጠዋል። ይህ ደግሞ አርሶ አደሩን አማርሮታል ብለዋል።

ሌላኛው አርሶ አደር “የተለያዩ ሰበቦችን እየፈለጉ የአንዱን ኩንታል ዋጋ እሰከ 10ሺህ ብር አድርሰውታል” ሲሉ አስረድተዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ክላስተር ልማት አስተባባሪና የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ድረስ ሣህሉ የማዳበሪያ ዋጋ ከዶላር ዋጋ ማደግ ጋር ተያይዞ መጨመሩን አመልክተው፣ በዚህም ምክንያት የአንድ ኩንታል ማዳበሪያ ዋጋ 12,600 ብር እንደሚደርስ ጠቁመዋል። ሆኖም ክልሉ በአንድ ማድበሪያ የ3,600 ብር ድጎማ በማድረጉ የአንድ ኩንታል ማዳበሪያ ዋጋ ከ8000 ብር እንዳይበልጥ መደረጉን ገልጠዋል።

የማዳበሪያ ዋጋ ከቦታ ቦታ መጠነኛ የዋጋ ልዩነት እንዳለው ጠቅሰው ይህም ራቅ ወዳሉ አካባቢዎች የነዳጅና ሌሎች ወጪዎች ስለሚኖሩ ነው ብለዋል።

የትግራዩ ጄኔራል  #ህወሓትን በመቃወም "አራት ክፍለ ጦር ያለው" ሠራዊት ማደራጀታቸውን ተናገሩህወሓትን በመቃወም የትጥቅ ትግል ውስጥ የገቡት ብርጋዴር ጄነራል ገብረእግዚአብሄር በየነ፤ በ  ...
10/06/2025

የትግራዩ ጄኔራል #ህወሓትን በመቃወም "አራት ክፍለ ጦር ያለው" ሠራዊት ማደራጀታቸውን ተናገሩ

ህወሓትን በመቃወም የትጥቅ ትግል ውስጥ የገቡት ብርጋዴር ጄነራል ገብረእግዚአብሄር በየነ፤ በ #አፋር እና በ #ትግራይ ክልሎች ውስጥ “አራት ክፍለ ጦር” ያለው የራሳቸውን ሠራዊት ማደራጀታቸውን ተናገሩ።

#ከትግራይ ኃይሎች በመለየት የራሳቸውን ሠራዊት እየገነቡ መሆናቸውን የጠቀሱት ብርጋዴር ጄነራል ገብረእግዚአብሄር፤ "አዲስ ነገር ለመፍጠር" ወደ በረሃ መውደረዳቸውን እና "ከፓርቲ ነጻ የሆነ ኃይል ለመፍጠር፣... ፓርቲ የማያዝዘው ሠራዊት ለመፍጠር" እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገልፀዋል።

ጄነራሉ ከቢቢሲ ትግርኛ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፤ ከትግራይ ሠራዊት አመራሮች ጋር የተለያዩት ከጥር 15/20017 ዓ.ም. ጀምሮ መሆኑን አስረድተዋል።

የትግራይ ሠራዊት ከፍተኛ አመራሮች ጥር 15 ተሰብስበው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራውን ጊዜያዊ አስተዳደር ሲያወግዙ፣ ተቃውመው ስብሰባውን ረግጠው ከወጡ አመራሮች መካከል አንዱ ጄነራል ገብረ እግዚአብሄር በየነ ናቸው።

ይህንንም ተከትሎ የሠራዊቱ አመራሮች ጄነራል ገብረ እግዚአብሄር በየነን እና ሌሎች የሠራዊቱን ውሳኔ የተቃወሙትን ማገዳቸው ይታወሳል።

ጄነራል ገብረ እግዚአብሄር "ከፓርቲ ጋር ተጣብቆ ማህተም የሚነጥቅ፣ ከፓርቲ ጋር ተጣብቆ የሚሾም እና የሚሽር ኃይል ለወጣቱ ትውልድ ትተን መሄድ አንፈልግም። ወገንተኛ ያልሆነ ፍትሃዊ ኃይል ለመፍጠር እንጂ፣ የሆነ ፓርቲ አሽከርነት የለንም፤ አናደርገውም" ብለዋል።

ለተቃውሟቸው ጠመንጃ ማንሳትን መምረጣቸው በጦርነት ውስጥ የቆየውን የትግራይ ክልል ዳግም ወደ ግጭት አዙሪት አይከተውም ወይ ተብለው የተጠየቁት ጄነራሉ "እኔ ኢንተርናሽናል ጄነራል ነኝ። ይህንን ሆኜ የህወሓት ሚሊሻ መሆን አልፈልግም። ህወሓት ፓርቲያችን ነው የሚሉ የእርሱን ሚሊሻ እንደሆኑ ነው የሚቆጥረው። ሚሊሻነትን ደግሞ አልቀበልም" ብለዋል።

https://www.bbc.com/amharic/articles/c8d136gld16o

የ  #ኢትዮጵያ እና  #ኢትሃድ አየር መንገድ ‘የኮድ ሼር’ ስምምነትን ተግባራዊ አደረጉየኢትዮጵያ እና ኢትሃድ አየር መንገድ በመጋቢት ወር በ   የተፈራረሙትን ‘የኮድ ሼር ስምምነት’ ተግባራ...
10/06/2025

የ #ኢትዮጵያ እና #ኢትሃድ አየር መንገድ ‘የኮድ ሼር’ ስምምነትን ተግባራዊ አደረጉ

የኢትዮጵያ እና ኢትሃድ አየር መንገድ በመጋቢት ወር በ የተፈራረሙትን ‘የኮድ ሼር ስምምነት’ ተግባራዊ አደረጉ። ይህም በ #አፍሪካ እና በ #እስያ፣ በ #አውስትራሊያ እና በመካከለኛው ምስራቅ መካከል ያለውን ትስስር የሚያጠናክር ነው ተብሏል።

የኮድ ሼር’ ስምምነት ተግባራዊ መሆን፤ በሁለቱ አየር መንገዶች መካከል በመጋቢት ወር የተፈረመውን የጋራ የቢዝነስ ስምምነት ተግባራዊ የሚያደርግ የመጀመሪያው እርምጃ ነው። ስምምነቱ፤ በሁለቱም በኩል ላሉ ለተጓዦች የተሻል ዓለም አቀፍ የጉዞ ዕድሎችን ይከፍታል ተብሏል።

የኮድ ሼር አገልግሎት፤ ተጓዦች ሁለቱ አየር መንገዶች የሚደረጉትን የተላያዩ በረራዎችን መጠቀም የሚችሉበት አማራጭ የሚያቀርብ ስርዓት ነው። በተጨማሪም ሻንጣዎችን ወደ መጨረሻ መድረሻቸው በቀላሉ በማስተላለፍ ጉዞን የሚያቃልል መሆኑንም ታይምስ ኦፍ ኤሮስፔስ ዘግቧል።

በዚህ አጋርነት መሰረት፤ የኢትሃድ አየር መንገድ ተጓዦች፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ሰፊ የአፍሪካ ሀገራት በረራ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ። በዚህም በአዲስ አበባ በኩል #ኢንቴቤ፣ #ኪንሻሳ፣ #ኪጋሊ፣ #ሉሳካ፣ #ሃረሬ እና ጨምሮ በ33 ሀገሮች ወደሚገኙ 55 መዳረሻዎች መጓዝ ይችላሉ።

በተመሳሳይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጓዦች፤ በአቡ ዳቢ በኩል ከኢቲሃድ ጋር የሚገናኙ በረራዎችን መጠቀም የሚችሉ ሲሆን በዚህም #ሲድኒ፣ #ክራቢ፣ #ኮሎምቦ እና #ፍኖም ፔንን ጨምሮ በእስያ፣ በአውስትራሊያ እና በመካከለኛው ምስራቅ ወደሚገኙ 20 ዋና ዋና መዳረሻዎች የበረራ አገልግሎት ያገኛሉ ተብሏል።

በተጨማሪም በስምምነቱ መሰረት፤ ኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሀምሌ 8 ቀን 2017 ጀምሮ ከአዲስ አበባ ቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ወደ አቡ ዳቢ ዛይድ አለም አቀፍ አየር ማረሪያ እንዲሁም ኢትሃድ አየር መንገድ ከመስከረም 21 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከአቡዳቢ-አዲስ አበባ ቀጥታ የበራራ አገልግሎት የሚጀምሩ ይሆናል።

================
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ዩቲዩብ፡ https://rb.gy/bjcbg
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ቲክቶክ፡ https://rb.gy/jgdsjm

ዜና፡  #በመቀለ እና ጄኔቫ “አምስተኛ ክረምት በሸራ መጠለያ ማሳለፍ ይብቃን” በሚል መሪ ቃል በቀጣይ ሳምንት የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚካሄድ ተገለጸ“አምስተኛ ክረምት በሸራ መጠለያ ማሳለፍ ይብ...
10/06/2025

ዜና፡ #በመቀለ እና ጄኔቫ “አምስተኛ ክረምት በሸራ መጠለያ ማሳለፍ ይብቃን” በሚል መሪ ቃል በቀጣይ ሳምንት የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚካሄድ ተገለጸ

“አምስተኛ ክረምት በሸራ መጠለያ ማሳለፍ ይብቃን” በሚል መሪ ቃል ከቀያቸው ተፈናቅለው በተለያዩ #የትግራይ ከተሞች ተጠልለው የሚገኙ የክልሉን ነዋሪዎችን ለቤታቸው ለማብቃት በሚል በክልሉ ዋና ከተማ መቀለ እና #በሲዊዘርላንድ #ጄኔቫ በቀጣይ ሳምንት የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚካሄድ ተገለጸ።

ሰልፉ የሚካሄደው ከሰኔ 11 እስከ 13 ቀን 2017 ዓ.ም መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን የሰልፉ ዋና አላማ በክልሉ በተካሄደው ጦርነት ከቀያቸው ተፈናቅለው በተለያዩ የመጠለያ ጣቢያዎች እና በስደተኛ ካምፖች የሚኖሩ የክልሉ ነዋሪዎች ቀጣዩ ክረምት ሳይመጣ ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ ለማስቻልነው ሲሉ አስተባባሪዎቹ ተናግረዋል።

በተጨማሪም የፕሪቶሪያ ስምምነት ፈራሚዎች እና አፈራራሚ ወገኖች ላይ ተእኖ ለመፍጠር ነው ሲሉ አስተባበሪዎቹ ገልጸዋል፤ በተለይም በፌዴራል መንግስት እና በአለም አቀፍ ማህበረሰብ ላይ ጫና ለመፍጠር ያለመ ነው ማለታቸውም ተጠቁሟል።
https://addisstandard.com/Amharic/?p=8052

ዜና: ኦነግ አዲስ አበባ የሚገኘው ዋና ቢሮው ከአራት ዓመታት በኋላ እንደተመለሰለት አስታወቀየኦሮሞ ነፃነት ግንባር ( #ኦነግ) ከነሃሴ 2012 ዓ.ም ጀምሮ ተዘግቶ የነበረውን እና በአዲስ አ...
09/06/2025

ዜና: ኦነግ አዲስ አበባ የሚገኘው ዋና ቢሮው ከአራት ዓመታት በኋላ እንደተመለሰለት አስታወቀ

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ( #ኦነግ) ከነሃሴ 2012 ዓ.ም ጀምሮ ተዘግቶ የነበረውን እና በአዲስ አበባ የሚገኘውን ዋና ቢሮው በይፋ እንደተመለሰለት የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

"በይበልጥ የአዲስአበባ ከተማ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የቻለውን ያህል ጫና ሲያደርግ ነበረ" ያሉት አቶ ለሚ የምክር ቤቱ እንዲሁም ሌሎች ተወካዮች በተገኙበት ቢሯችን ለማስመለስ ችለናል ብለዋል።

አክለውም "ወደ ቢሯችን እንድንመለስ የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ የራሱን አስተዋጽኦ አድርጓል" ሲሉ አስታውቀዋል።

አያይዘውም ፓርቲያቸው ከ200 በላይ ጽህፈት ቤቶች እንዳሉት ጠቅሰው በቀጣይ በተዋረድ የተዘጉ ጽሕፈት ቤቶቻችን እንዲከፈቱልን ውትወታችን ይቀጥላል ብለዋል። ወደፊትም አደረጃጀቶቻችንን ለማጠናከር ተስፋ አድርገን እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።

https://addisstandard.com/Amharic/?p=8047

Address

Opposite CMC
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 12:30

Telephone

+251970048900

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Standard Amharic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Standard Amharic:

Share