Addis Standard Amharic

Addis Standard Amharic Addis Standard Amharic is an independent online media outlet providing news and in-depth analysis in the Amharic language.
(2)

Its contents mainly focus on current social and political affairs.
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4 Its contents mainly focus on current social and political affairs.

 #ኢዜማ ብልፅግና የመንግሥት ሠራተኞችን "በግዳጅ ወደ ፓርቲ አባልነት እያስገባ ነው" ሲል ከሰሰየኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ገዢው ብልጽግና ፓርቲ የመንግሥት ሠራተኞችን...
28/10/2025

#ኢዜማ ብልፅግና የመንግሥት ሠራተኞችን "በግዳጅ ወደ ፓርቲ አባልነት እያስገባ ነው" ሲል ከሰሰ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ገዢው ብልጽግና ፓርቲ የመንግሥት ሠራተኞችን "ያለፍላጎታቸው በተለያዩ ጫናዎች አማካኝነት የፓርቲ አባል እንዲሆኑ እያስገደደ ነው" በማለት ከሰሰ።

ፓርቲው ባወጣው ዛሬ ባወጣው መግለጫ፣ ገዢው ፓርቲ ከምርጫ 2013 አስቀድሞ ከነበረው የመጀመሪያዎቹ የለውጥ ዓመታት በስተቀር ከፍተኛ ተደራሽነት ያላቸውን መገናኛ ብዙኃን ጠፍሮ መያዝ፣ በመንግሥት መዋቅር ውስጥ የፓርቲ ሴል ስብስባዎችን ጨምሮ ሌሎች የፓርቲ ሥራዎችን በመንግሥት ሀብት መጠቀም እና የመሣሠሉትን በመፈጸም መንግሥትና ፓርቲ ይለያያሉ የሚለው መርህ ላይ በቂ ግንዛቤ እንደሌለው እያሣየ ይገኛል ብሏል።

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ደግሞ የመንግሥት ሠራተኞችን ያለፍላጎታቸው የተለያዩ ተጽዕኖዎችን በመጠቀም አባል “እንዲሆኑ ጫና እያሣደረ መሆኑን ያገኘናቸው መረጃዎች ያሣያሉ” ሲል አክሏል።

ኢዜማ፣ “ይህ ተግባር ገዢው ፓርቲ ሀሳቡን ሸጦ ቅቡልነት የማግኘት እድሉ ላይ በራስ መተማመን የሌለው መሆኑን፣ የመንግሥት ኃላፊነት የተሠጣቸው የፓርቲው አመራሮች ሥልጣንን ያለአግባብ እንደሚጠቀሙ” ያመላክታል ብሏል።

በተጨማሪም የፓርቲው ተግባር በተደጋጋሚ እገዛለታለሁ የሚለውን የሀገሪቱን ህገ መንግስት እና ሌሎች ሀገራችን የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ድንጋጌዎችን “የሚጨፈለቅ እና ለህግ የበላይነት ያለውን ምልከታ ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው” ሲል ፓርቲው በመግለጫው አክሏል።

አክሎም የመንግስት ሠራተኞችን ያለፍላጎታቸው የፓርቲ አባል ማድረግ በሕገመንግሥቱ አንቀጽ 31 የተደነገገውን የመደራጀት መብት በሚጥስ መልኩ ሠራተኞች የየትኛው የፖለቲካ ድርጅት ውስጥ የመሳተፍ ወይም ገለልተኛ ሆኖ የመቆየት መብታቸውን የሚጋፋ ነው።

የመንግስት ሠራተኞችን ያለፍላጎታቸው የፓርቲ አባል ማድረግ በሠራተኞች ላይ እየደረሰ ያለው ጫና የመደራጀት መብት (አንቀጽ 31)፣ በነፃነት ሀሳብን የመግለጽ መብት (አንቀጽ 29)፣ እና በሕግ ፊት የእኩልነት መብት (አንቀጽ 25) ን የሚጥስ ሲል ገልጿል። ሠራተኞች በፓርቲ አባልነት/አባል አለመሆን ምክንያት ከሥራ የመባረር ወይም የሥራ ዕድገት የማጣት ስጋት ውስጥ እየገቡ ነው ያለው ኢዜማ ይህ ድርጊት አገሪቱ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ እና አህጉር አቀፍ ድንጋጌዎችን የሚጨፈልቅ መሆኑን አጽንዖት ሰጥቷል።

ኢዜማ ይህንን ድርጊት እንዲያወግዙ ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ ለሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም፣ እና ለሲቪክ ማኅበራት ጥሪ አቅርቧል። በመጨረሻም ኢዜማ ለብልጽግና ፓርቲ "ሀገርና ዘላቂ የህዝብ ጥቅም ከጊዜያዊ የስልጣን ፍላጎት በላይ መሆናቸውን በመገንዘብ መንግስታዊ መዋቅርን ለፓርቲ ጥቅም የማዋል ተግባር በአስቸኳይ እንዲያቆም" ሲል አሳስቧል።

ዜና: ኢትዮጵያ በህግ የበላይነት ምዘና አምና ከነበረችበት ዝቅ አለች፤ “የአምባገነንነት አዝማሚያ” እየተባባሱ መምጣታቸውን ሪፖርት አስጠነቀቀየአለም አቀፍ የፍትህ ፕሮጀክት (WJP) ዛሬ ባወ...
28/10/2025

ዜና: ኢትዮጵያ በህግ የበላይነት ምዘና አምና ከነበረችበት ዝቅ አለች፤ “የአምባገነንነት አዝማሚያ” እየተባባሱ መምጣታቸውን ሪፖርት አስጠነቀቀ

የአለም አቀፍ የፍትህ ፕሮጀክት (WJP) ዛሬ ባወጣው የ2025 የሕግ የበላይነት መረጃ ጠቋሚ መሠረት ኢትዮጵያ ከ143 አገሮች መካከል 132ኛ ደረጃን ይዛለች። በዚህም በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነት ከዓመት ዓመት ማሽቆልቆሉን ቀጥሏል ብሏል።

ሪፖርቱ የሀገሪቱ ውጤት ካለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በ2.4 በመቶ ዝቅ ማለቱን ጠቅሶ፤ ይህም ለአምስት ተከታታይ ዓመታት ተቋማት እየደከሙ፣ የሲቪክ ምህዳሩ እየጠበበ እና የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት እየጨመረ መምጣቱን የሚያሳይ ነው ሲል ገልጿል።

እንደ የአለም አቀፍ የፍትህ ፕሮጀክት መረጃ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሕግ የበላይነት ማሽቆልቆል በ2025 ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ 68 በመቶ የሚሆኑ አገራት ማሽቆልቆል አሳይተዋል።

የአምባገነንነት ዝንባሌዎች መስፋፋት በዓለም አቀፍ ደረጃ የህግ የበላይነት መዳከም ዋነኛ ምክንያት ነው ያለው ተቋሙ፤ ይህም በመላው ዓለም ቁጥጥርና ሚዛናዊነት መዳከሙን እና የዳኝነት ነፃነት መሸርሸሩን አመላካች መሆኑን ገልጿል።

https://addisstandard.com/Amharic/?p=9728

የ  #ደሴ ከተማ ፖሊስ ባደረገው ጥብቅ ክትትል "የቅሚያና እና የዝርፊያ ወንጀል የፈፀሙ 64 ተጠርጣሪዎችን" በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀየደሴ ከተማ ፖሊስ ባደረገው ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር...
28/10/2025

የ #ደሴ ከተማ ፖሊስ ባደረገው ጥብቅ ክትትል "የቅሚያና እና የዝርፊያ ወንጀል የፈፀሙ 64 ተጠርጣሪዎችን" በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ

የደሴ ከተማ ፖሊስ ባደረገው ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር "ማህበረሰቡን ለከፍተኛ ምሬትና ስቃይ የዳረጉ በቡድንና በግለሰብ በመደራጀት በተለይ የእጅ ስልክ ስርቆትና በሌሎች የዝርፊያ ወንጀል የተሰማሩ ቡድኖችንና ግለሰቦችን" በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታወቀ።

በዚህም መሠረት ዝርፊያ የፈፀሙ 64 ተጠርጣሪዎችን ከነተቀባዮቻቸው በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ ማድረግ መጀመሩን የከተማዋ ፖሊስ መምሪያ የወንጀል መከላከል ምክትል መምሪያ የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዋና አዛዥ ኮማንደር ደምሰው ካሳ ገልፀዋል።

ዘራፊዎቹ ተሽከርካሪን በመጠቀም፣ እንዲሁም አልፎ አልፎ ያለ ተሸከርካሪ ዝርፊያ ሲፈፅሙ የነበሩ ሲሆኑ ማህበረሰቡን ለከፍተኛ እንግልትና ምሬት ያዳረጉ እና በህግ ተደጋጋሚ በወንጀል የሚፍለጉ መሆናቸውን አብራርተዋል።

አክለውም የተዘረፉ የመሠረተ ልማት ቁሳቁሶች ግለሰቦችን ለማታለል የሚጠቀሙባቸው ሀሰተኛ የሎተሪ ወረቀቶች እና ህገወጥ የጦር መሣሪያዎች መያዛቸው ተናግረዋል።

እንዲሁም በከተማዋ በሚገኙ አምስት ዋና የፖሊስ ጣቢያዎችም የምርመራ ቡድን ተዋቅሮ ስራ መጀመሩን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ‎የወንጀል ድርጊቶቹ ይፈፀምባቸዋል ተብለው በሚጠረጠሩ እና በተለዩ በሁሉም አካባቢዎች የህግ አግባብን ተከትሎ ፍተሻና ብርበራ የሚደደረግ መሆኑን ገልፀው ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

በቅርቡ በደሴ ከተማ ቦርከና ቀበሌ ሀቢታት ተብሎ በሚጠራ ቦታ ላይ በአሰቃቂ ሁኔታ ህይወቷ ያለፈው ወጣት ሊዛ ደሳለኝ ግድያ ላይ ምርመራ መጀመሩን የከተማው ፖሊስ መምሪያ ማስታወቁ ይታወሳል።

ወጣቷ መስከረም 28 ቀን 2018 ዓ.ም. ሞባይል ስልክ ለማሠራት ከምሽቱ አንድ ሰዓት አካባቢ ከቤቷ በወጣች በአንድ ሰዓት ውስጥ ጥቃት ተፈፅሞባት መንገድ ዳር ወድቃ የተገኘች ሲሆን ለሕክምና እርዳታ ወደ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ብትወሰድም ሕይወቷን ማትረፍ አለመቻሉ ተገልጿል።

ዜና፡ ማንም ሰው በሰላማዊ መንገድ ህግና ስርዓት አክብሮ የሚመጣ ከሆነ ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን አብረን ለመስራት ዝግጁ ነን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተናገሩማንም ሰው በሰላማዊ መንገ...
28/10/2025

ዜና፡ ማንም ሰው በሰላማዊ መንገድ ህግና ስርዓት አክብሮ የሚመጣ ከሆነ ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን አብረን ለመስራት ዝግጁ ነን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ ተናገሩ

ማንም ሰው በሰላማዊ መንገድ ህግና ስርዓት አክብሮ የሚመጣ ከሆነ ለመታረቅ ብቻ ሳይሆን አብረን ለመስራት ዝግጁ ነን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ተናገሩ። "ሊታረቅ የነበረን አካል እንዳይታረቁ የሚያደርጉ አካላት እንዳሉም" ጠቅሰዋል።

ዐብይ አህመድ በማብራሪያቸው “ኢትዮጵያ ደካማ ሆና እንድትኖር፣ በሁለት እግሯ እንዳትቆም የሚሹና የሚሰሩ ሀገራት ባሉበት ሁኔታ፣ ኢትዮጵያውያን ብሔራዊ ጥቅምን ለይተው ማወቅ ካልቻሉ፣ ለፖለቲካ ፍጆታ ብቻ ለጠላት ፍላጎትና ጥያቄዎች ተላልፈው ከተሰጡ፣ የተሟላ ሰላም ማምጣት ያስቸግራል” ብለዋል።

"እኛ እንደ መንግስት 'ችግር አለብኝ' ከሚል ጋር እንወያያለን። ለምሳሌ ከሸኔ ጋር ተወያይተን ከፊል የሸኔ ኃይል በሰላም ገብቶ ስልጣን ላይ የለም?፣ ከትግራይ ወገኖች ጋር ተወያይተን ከፊሎቹ ገብተው ስልጣን ላይ የሉም ወይ?" ብለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ "እኔንና #ጌታቸው ረዳን አብሮ የሚያይ ሰው አሁን ይህ መንግስት አይወያይም ብሎ ቢያስብ አይገርምም?” ሲሉም አክለው ጠይቀቃል።

"የአማራውንም ሆነ የኦሮሞውን ሸኔ ተወያይቶ የመጣን ተቀብለናል" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገሪቱ የሚንቀሳቀሱት ታጣቂዎች ተላላኪ ናቸው፤ አላማ የላቸውም፤ ታገልኩለት የሚሉትን ህዝብ እየገደሉ፣ ልማት እያደናቀፉ፣ ታገልኩልህ ማለት ምን ማለት ነው” ብለዋል።

ዝርዝሩን ለማንበብ፡
https://addisstandard.com/Amharic/?p=9722

ዜና: “የኢትዮጵያ እድገት እንደከዚህ ቀደሙ ያለ የቁጥር እድገት አይደለም፤ ዘንድሮው ያላምንም ጥርጥር ባለሁለት አሃዝ ዕድገት እናስመዘግባለን” _ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ #ኢትዮጵያ በዘንድሮው ...
28/10/2025

ዜና: “የኢትዮጵያ እድገት እንደከዚህ ቀደሙ ያለ የቁጥር እድገት አይደለም፤ ዘንድሮው ያላምንም ጥርጥር ባለሁለት አሃዝ ዕድገት እናስመዘግባለን” _ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ

#ኢትዮጵያ በዘንድሮው ዓመት "ያላምንም ጥርጥር ባለሁለት አሃዝ ዕድገት ታስመዘግባለች” ሲሉ ጠ/ሚኒስትር አብይ አስታወቁ። “የኢትዮጵያ እድገት እንደከዚህ ቀደሙ ያለ የቁጥር እድገት አይደለም፤ የሚጨበጥ፣ የሚታይ፣ የሚዳሰስ እድገት ነው” ብለዋል።

ጠ/ሚኒስትሩ ይህንን የተናገሩት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን ሁለተኛ መደበኛ ስብሰባ ዛሬ ጥቅምት 18 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደበት ወቅት ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ እና ማብራሪያ ላይ ነው።

“የኢትዮጵያን ዕድገት ጥሩ አፍንጫ ያለው ሰው ከተማ ውጥስ ሲንቀሳቀስ በሽታ ያውቀዋል። ጥሩ ዐይን ያለው ሰው በማየት ብቻ ሊገነዘበው ይችላል፤ ጥሩ ጆሮ ያለውም ሰው በማድመጥ ሊረዳው ይችላል፤ የኢትዮጵያ ዕድገት የሚያጠራጥር ጉዳይ ስላልሆነ ወይ ዐይናችሁን፣ አፍንጫችሁን ወይም ጆሯችሁን መጠቀም ብቻ ነው የሚጠበቀው።” ብለዋል።

“በ2032 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ቢያንስ ከአፈሪካ ሁለተኛው ኢኮኖሚ ይሆናል፤” ሲሉ የተናገሩት ጠ/ሚኒስትሩ “በ2036 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከአፈሪካ የመጀመሪያው ኢኮኖሚ ይሆናል፤ ይሄን እናሳካለን ማንም ሊያሰቆመን አይችልም” ሲሉመ ገለጸዋል።

ዝርዝሩን ያንብቡ፡
https://addisstandard.com/Amharic/?p=9718

ዜና: በድሬደዋ፣ ሶማሌ ክልልና ምስራቅ ሐረርጌ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 43 “የኦነግ ሸኔ” አባላት መገደላቸው ተገለፀየምስራቅ ኢትዮጵያ ጥምር የጸጥታ ግብረ ኃይል፤ “በድሬደዋ፣በሶማሌ ክልል እና ...
28/10/2025

ዜና: በድሬደዋ፣ ሶማሌ ክልልና ምስራቅ ሐረርጌ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 43 “የኦነግ ሸኔ” አባላት መገደላቸው ተገለፀ

የምስራቅ ኢትዮጵያ ጥምር የጸጥታ ግብረ ኃይል፤ “በድሬደዋ፣በሶማሌ ክልል እና በምስራቅ ሐረርጌ አዋሳኝ አካባቢዎች ላይ ምሽግ በማድረግ ከመስከረም 19 ጀምሮ ተሸሽጎ በመግባት ሲንቀሳቀሱ የነበሩ አመራሮችን ጨምሮ 43 “የኦነግ ሸኔ ቡድን” አባላት ሙሉ ለሙሉ ተደምስሰዋል” ሲል አስታወቀ።

ጥምር የጸጥታ ግብረ ኃይሉን ወክለው የድሬዳዋ ፓሊስ ጠቅላይ መምሪያ ዋና አዛዥ ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ ትናንት ሰኞ ጥቅምት 17/2018 ዓ. ም. መግለጫ ሰጥተዋል።

ኮሚሽነር ዓለሙ መግራ በመግለጫቸው፤ “ኦነግ ሸኔ የሽብር ቡድን በምዕራብ ሐረርጌ በኩል አቋርጦ በኤረርና ሁርሶ ጀርባ በማድረግ ወደ ድሬዳዋ የገጠር አካባቢዎች ገብቶ እንደነበር” አስታውሰዋል።

“ቡድኑ በአስተዳደሩና በአጎራባች ክልሎች በመሠረተ ልማት ብሎም ኢንደስትሪዎች ላይ ጥቃት ማድረስና የብሄር ግጭት ማስነሳት ተቀዳሚ ዓላማው መሆኑንም” አመልክተዋል።

በዚህም ሰባት ንዑሳንን በህብረት ያቀፈው የምስራቅ ኢትዮጵያ ጥምር የጸጥታ ልዩ ግብረ ኃይል ከመስከረም ወር ጀምሮ ባደረገው ልዩ ኦፕሬሽን “የኦነግ ሸኔ የሽብር ቡድንን በመክበብ ርምጃ ወስዷል” ያሉት ኮሚሽነሩ በተከፈተው ጥቃትም “43 ያህል የሽብር ቡድኑ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱን” አረጋግጠዋል።

የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት በበኩሉ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ፤ በምስራቅ ሐረርጌ ዳሪሞ ቂሌ ዋሻ ፣ ቀርሳ ወረዳ “የጥፋት ተልዕኮን ለመፈፀም በአካባቢው እየተንቀሳቀሰ የነበረው የሸኔ ቡድን” ላይ እርምጃ መወሰዱን አስታውቋል፡፡ “በተወሰደው እርምጃም 17 የቡድኑ አባላት ሲደመሰሱ 14 አባላት ከነ ሙሉ ትጥቃቸው መማረካቸውን” ገልጿል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ:
https://addisstandard.com/Amharic/?p=9714

  ባለፉት ሦስት ወራት ከ26 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀየኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ሦስት ወራት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ እና ተጓ...
28/10/2025

ባለፉት ሦስት ወራት ከ26 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ሦስት ወራት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ሀገራት ከቀረበ የኃይል ሽያጭ እና ተጓዳኝ አገልግሎቶች ከ26 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ።

በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አንዷለም ሲዓ በሩብ ዓመቱ ከኃይል ሽያጭ 24 ነጥብ 9 ቢሊዮን ብር ገቢ ለማግኘት ታቅዶ 26 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል።

አክለውም በሩብ ዓመቱ የተሸጠው የኃይል ምርት ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ47 በመቶ ወርሃዊ ዕድገት እንዳለው የገለጹ ሲሆን ከገቢ አንጻር ሲነጻጸር ደግሞ የ96 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን ጠቁመዋል።

‎በሩብ ዓመቱ ለሽያጭ ከቀረበው ኃይል 93 በመቶ ለሀገር ውስጥ እንዲሁም 7 በመቶ ደግሞ ለውጭ ሀገራት የቀረበ መሆኑንም አመልክተዋል።

‎ለሀገር ውስጥ ከቀረበው የኃይል ሽያጭ ውስጥ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 53 ነጥብ 6 በመቶ፣ የከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች 4 ነጥብ 6 በመቶ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች 34 ነጥብ 6 በመቶ ድርሻ እንዳላቸው ጠቁመዋል።

‎በተጨማሪም ለጎረቤት ሀገራት ከቀረበው የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ ውስጥ ኬንያ እና ታንዛኒያ 4 ነጥብ 6 በመቶ እንዲሁም ጅቡቲ 2 ነጥብ 2 በመቶ ድርሻ እንዳላቸው መግለፃቸውን ከተቋሙ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማህበር በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ከግብር በፊት የ2.9 ቢሊዮን ብር ከፍተኛ ኪሳራ ማስተናገዱን በይፋ አስታወቀ ባንኩ ይህ ኪሳራ የደረሰው የባንኩ መ...
28/10/2025

ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ አክሲዮን ማህበር በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ከግብር በፊት የ2.9 ቢሊዮን ብር ከፍተኛ ኪሳራ ማስተናገዱን በይፋ አስታወቀ

ባንኩ ይህ ኪሳራ የደረሰው የባንኩ መደበኛ ሥራ በመበላሸቱ ሳይሆን፣ መንግሥት የውጭ ምንዛሪ ገበያዎችን በማዋሐድ ባደረገው የፖሊሲ ለውጥ ምክንያት በሂሳብ አያያዝ ላይ በተከሰተ ትልቅ የ4.4 ቢሊዮን ብር የውጭ ምንዛሪ (FX Revaluation) ኪሳራ ምክንያት መሆኑን ገልጿል።

ይህ የፋይናንስ ውጤት የባንኩን ጠቅላላ ሃብት በ28 በመቶ የቀነሰ ሲሆን፣ ለባለአክሲዮኖቹ የትርፍ ክፍፍል (ዲቪደንድ) እንደማይከፈል በይፋ ተረጋግጧል።

የባንኩ ዓመታዊ ሪፖርት እንደሚያመለክተዉ ፤ ኪሳራው ሙሉ በሙሉ የተከሰተው በቀድሞው የባንኩ አስተዳደር በጣም ዝቅተኛ በሆነ የምንዛሬ ዋጋ ተገብተው ለረጅም ጊዜ በውጭ ምንዛሪ ተመዝግበው የቆዩትን ዕዳዎችና ግዴታዎች ለመክፈል መገደዱ ነው።

የወቅቱ የገንዘብ ፖሊሲ ለውጥ የውጭ ምንዛሪ ዋጋ ከመጀመሪያው ውል ከእጥፍ በላይ እንዲጨምር በማድረጉ፣ ባንኩ እዳዎቹን በአዲሱ ከፍተኛ የምንዛሬ መጠን እንዲከፍል መገደዱን አስታውቋል።

ባንኩ ከብሔራዊ ባንክ ወስዶት የነበረውን 5.85 ቢሊየን ብር ብድር ከወለዱ ከ658.4 ሚሊየን ብር ጋር በሙሉ መክፈል መቻሉን ከሪፖርቱ ለመረዳት ተችሏል።

በሌላ በኩል ንብ ባንክ እንዳስታወቀዉ ገቢው በ4.6 በመቶ ጨምሮ 11.3 ቢሊየን ብር የደረሰ ሲሆን፣ ተቀማጭ ገንዘብ በ14 በመቶ አድጎ 51.3 ቢሊየን ብር መድረሱን አመልክቷል።

(ካፒታል ጋዜጣ)

 #ሩሲያ ከ  #ብሪክስ ለመውጣት ያሰበ ሀገር ስለመኖሩ ምንም መረጃ የላትም — የሩሲያ ዲፕሎማትሞስኮ ከብሪክስ ለመውጣት ያሰበ ሀገር ስለመኖሩ ምንም መረጃ አልደረሳትም ሲሉ የሩሲያ የውጭ ጉዳ...
27/10/2025

#ሩሲያ ከ #ብሪክስ ለመውጣት ያሰበ ሀገር ስለመኖሩ ምንም መረጃ የላትም — የሩሲያ ዲፕሎማት

ሞስኮ ከብሪክስ ለመውጣት ያሰበ ሀገር ስለመኖሩ ምንም መረጃ አልደረሳትም ሲሉ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ተናገሩ።

ቃል አቀባይዋ ይህን የተናገሩት 'ሜድ ኢን ሩሲያ ፎረም' (Made in Russia forum) መድረክ ጎን ለጎን ለታስ ዜና ወኪል በሰጡት ቃለ ምልልስ ነው።

ዲፕሎማቷ አንዳንድ የብሪክስ ሀገራት በአሜሪካ ከፍተኛ ታሪፍ የመጣል ማስፈራሪያ ምክንያት ማኅበሩን ሊለቁ ይችላሉ የሚሉ የመገናኛ ብዙሃን ዘገባዎችን በተመለከተ አስተያየት ሲሰጡ፤ “የአሜሪካ ታሪፍ ለብዙዎቹ በሥራ ላይ ቢሆንም፣ በሩሲያ ወገን ከማኅበሩ አባልነት ለመልቀቅ ያሰበ ሀገር ስለመኖሩ ምንም አይነት መረጃ የለም” ብለዋል።

ቃል አቀባይዋ፣ “ብሪክስ በፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ ዓለም አቀፍ በይነ መንግስታዊ ማኅበር ነው” ሲሉ አስታውሰዋል። እናም ሞስኮ ሁል ጊዜም የአጋሮቿን ሉዓላዊ የውጭ ፖሊሲ እታከብራለች ብለዋል።

በአሁኑ ጊዜ በብሪክስ ወስጥ ሩሲያ፣ #ብራዚል፣ #ግብፅ፣ #ህንድ፣ #ኢንዶኔዥያ፣ #ኢራን፣ #ቻይና፣ #የተባበሩት ዓረብ ኤምሬትስ፣ #ኢትዮጵያ እና በአባልነት ይገኙበታል።

================
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ቲክቶክ፡ https://rb.gy/jgdsjm

የ  #ጂቡቲ ፓርላማ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ለ  #ስድስተኛ ጊዜ ለሥልጣን እንዲወዳደሩ በሕገ መንግሥት ላይ የተቀመጠውን የዕድሜ ገደብን አነሳ የጂቡቲ ፓርላማ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር...
27/10/2025

የ #ጂቡቲ ፓርላማ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ለ #ስድስተኛ ጊዜ ለሥልጣን እንዲወዳደሩ በሕገ መንግሥት ላይ የተቀመጠውን የዕድሜ ገደብን አነሳ

የጂቡቲ ፓርላማ የአገሪቱ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ ለስድስተኛ ጊዜ ምርጫ እንዲወዳደሩ መንገድ ለመክፈት የዕድሜ ገደብን በአንድ ድምፅ አነሳ።

በአፍሪካ ቀንድ የምትገኘው ትንሿ አገር ጂቡቲ፣ የዩናይትድ ስቴትስ፣ የፈረንሳይና የቻይና ጦር ሰፈሮችን የምታስተናግድ ቁልፍ የወደብ ሀገር ስትሆን ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ ደግሞ ከጎርጎሮሳውያኑ 1999 አንስቶ ሀገሪቱን በመምራት ላይ ይገኛሉ።

የሀገሪቱ ሕገ መንግሥት አንድ መሪ ዕድሜው 75 ዓመት ካለፈው ለፕሬዝዳንትነት መወዳደር እንደማይችል ይከለክላል። ይህም የ77 ዓመቱን አዛውንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ በሚቀጥለው ሚያዚያ 2026 (እ.ኤ.አ.) በሚደረገው ምርጫ እንዳይወዳደሩ አግዷቸው ነበር።

ነገር ግን፣ የዕድሜ ገደቡን ለማንሳት የቀረበው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ትናንት እሁድ ዕለት በስብሰባው ላይ በተገኙት በ65ቱ የፓርላማ አባላት ሙሉ ድጋፍ አግኝቷል ሲሉ አፈ-ጉባኤ ዲሌይታ መሐመድ ዲሌይታ ለኤኤፍፒ ተናግረዋል። አክለውም ፕሬዝደንቱ ውሳኔውን ሊያጸድቁ ወይም ሕዝበ ውሳኔ ሊጠሩ እንደሚችሉ ለጣቢያው ገልፀዋል።

ውሳኔው የሚፀድቅ ከሆነ፣ ፓርላማው በመጪው ህዳር 2 (እ.ኤ.አ) ለሁለተኛ ጊዜ ድምጽ ይሰጥበታል ተብሎ ይጠበቃል።

ዲሌይታ ከኤኤፍፒ ጋር በነበራቸው ቆይታ "ሕገ መንግሥታዊ ለውጡ አስፈላጊ የሆነው ችግር በበዛበት የአፍሪካ ቀንድ ቀጠና ውስጥ የምትገኘውን ትንሿን አገር መረጋጋት ለማረጋገጥ መሆኑን" ገልፀዋል። አያይዘውም "ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው ሕዝብ ይህንን እንደሚደግፍ አስባለሁ" ብለዋል።

"ልለው የምችለው ነገር ቢኖር ሀገሬን በጣም ስለምወዳት፣ ኃላፊነት በጎደለው ጀብዱ ውስጥ ገብቼ ለክፍፍል ምክንያት አልሆንም" ሲሉ ተናግረዋል። ጉዳዩ "አስገራሚ አይደለም" ሲሉ የገለጹት ደግሞ በሊል ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ የአፍሪካ ቀንድ ጉዳዮች ተመራማሪ ሶንያ ሌ ጉሪየሌክ ናቸው።

"በማኅበራዊ ሚዲያ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች እየተካሄዱ ነው" ያሉት ሶንያ ነገር ግን "ተቃዋሚዎች በጂቡቲ ራሳቸውን ለመግለጽ የሚያስችል ዕድል አይኖራቸውም ብዬ እሰጋለሁ" ሲሉ ተናግረዋል።

የጂቡቲ ሰብዓዊ መብቶች ሊግ (LDDH) ፕሬዝዳንት ኦማር አሊ ኢዋዶ በበኩላቸው፣ የሕገ መንግሥት ማሻሻያው ለፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌ የዕድሜ ልክ ፕሬዝዳንትነት የሚያዘጋጅ መሆኑን ጠቅሰው በሀገሪቱ "ዲሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር" እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

27/10/2025

“እንዴት በ2 ሚሊዮን ማህበረሰብ ጥቅም የ200 ሚሊዮን ሕዝብ ጥቅም ይዘጋል?” – ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ኢትዮጵያ ሰላም፣ ልማት እና የባህር በር መዳረሻ እንደሚያስፈልጋት አጽንኦት ሰጥተው ተናገሩ፤ የኢትዮጵያን ወደብ አልባ (Landlocked) መሆኗን በተመለከተም የፍትሐዊነት ጥያቄ አንስተዋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ባሳለፍነው ቅዳሜ ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም ቢሾፍቱ በሚገኘው የባህር ኃይል የስልጠና ማዕከል በተከበረው 118ኛው የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቀን ላይ ንግግር ያደረጉ ሲሆን “የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር አሁን ላይ 130 ሚሊዮን መድረሱን” ተናግረዋል።

“በሚቀጥሉት 25 ዓመታት ውስጥ ደግሞ [የሕዝብ ቁጥሩ] 200 ሚሊዮን ይደርሳል” ያሉት ፊልድ ማርሻሉ አያያይዘውም “እንዴት በ2 ሚሊዮን ማህበረሰብ ጥቅም የ200 ሚሊዮን ሕዝብ ጥቅም ይዘጋል? ፍትሐዊ አይደለም፣ ዓለም አቀፍ ሕግም አይደለም፣ ምክንያታዊም አይደለም” ብለዋል።

ፊልድ ማርሻሉ በስም ያልጠቀሷቸው ነገር ግን “ታሪካዊ ጠላቶች” ሲሉ የገለጿቸው አካላት ኢትዮጵያን የባህር በር እንዳታገኝ ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል። አክለውም “መከላከያ ሰራዊታችንን እናጠናክራለን፣ ልማታችንን እናፋጥናለን፣ ባህር በር እናገኛለን” ሲሉ ተናግረዋል።

ይመልከቱ

የ  #ሳዑዲው ኩባንያ ለ  #ኢትዮጵያ ጭነት ቁልፍ መግቢያ የሆነውን የታጁራ ወደብ ለ30 ዓመታት ለማስተዳደር ስምምነት ተፈራረመየሳዑዲ ዓረቢያው ሬድ ሲ ጌትዌይ ተርሚናል (RSGT) የታጁራ ወ...
27/10/2025

የ #ሳዑዲው ኩባንያ ለ #ኢትዮጵያ ጭነት ቁልፍ መግቢያ የሆነውን የታጁራ ወደብ ለ30 ዓመታት ለማስተዳደር ስምምነት ተፈራረመ

የሳዑዲ ዓረቢያው ሬድ ሲ ጌትዌይ ተርሚናል (RSGT) የታጁራ ወደብን ለ30 ዓመታት ለማስተዳደር ከጅቡቲ የወደቦች እና ነጻ ቀጠናዎች ባለሥልጣን (DPFZA) ጋር ስምምነት ተፈራረመ።

ስምምነቱ በጎርጎሮሳውያኑ መጋቢት ወር 2025 በሁለቱ ወገኖች መካከል በባህር ትራንስፖርትና በሎጅስቲክስ ዘርፎች ትብብርን ለማጠናከር ከተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ በኋላ የመጣ ነው ሲል ማሪታይም ኤክስኪዩቲቭ ድረገፅ ዘግቧል።

በተጨማሪም ስምምነቱ በኢትዮጵያና በሰሜናዊ ጅቡቲ መካከል ያለውን የባለብዙ-ትራንስፖርት ትስስርን የማስፋፋት ዕቅዶች ጋር የሚጣጣም መሆኑ ተጠቁሟል።

ለአብነትም ባሳለፍነው ሳምንት የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን የሰሜን ኢትዮጵያን አካባቢዎች የቀይ ባህር ወደቦች ከሆኑት ታጁራ፣ አሰብ እና ምፅዋ ጋር የሚያገናኝ የመደበኛ መስመር ባቡር ለመገንባት 1.58 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጣ ፕሮጀክት ይፋ ማድርጉ ይታወቃል።

ወደቦቹ ለሰሜናዊ ኢትዮጵያ አከባቢዎች ቅርብ ሲሆኑ፣ ለፖታሽ ማዕድን ቁፋሮ እና ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶችን በማምረት ላይ ያተኮሩ ሌሎች ኢንዱስትሪዎችን ፍላጎት መሳባቸውም ተመላክቷል።

እ.ኤ.አ በ2017 ሥራ የጀመረው የታጁራ ወደብ፣ የጅቡቲን ሰሜናዊ ክፍል የመሰረተ ልማት ዝርጋታን ለማስፋፋት ባላት ዕቅድ መሠረት የተገነባ ነው።

ይህ ወደብ በዋናነት ከኢትዮጵያ አፋር ክልል ከዳናኪል ዝቅተኛ ቦታዎች ወደ ውጭ የሚላከውን ፖታሽ እንዲሁም እንደ እንስሳትና ሰሊጥ ያሉ የኢትዮጵያን አጠቃላይ የጭነት ምርቶችም ያስተናግዳል።

የሳዑዲ ዓረቢያው ሬድ ሲ ጌትዌይ ተርሚናል (RSGT) አዲሱ ስምምነት የታጁራ ወደብን በአከባቢው "ተመራጭ ባለብዙ አገልግሎት መስጫ ጣቢያ" ለማድረግ ያለመ መሆኑን ገልጿል።

በሚቀጥሉት ዓመታት የወደቡ ዓመታዊ ጭነት የመያዝ አቅም አምስት ሚሊዮን ቶን እንደሚደርስ ይጠብቃል የተባለ ሲሆን፤ ይህም ለኢትዮጵያ የገቢና የወጪ ንግድ ያለውን ሚና የበለጠ ያጠናክረዋል ተብሏል።

በተጨማሪም ጅቡቲን በአፍሪካ ቀንድና በቀይ ባህር የሎጂስቲክስና የባህር ንግድ ማዕከል ያላትን ስትራቴጂካዊነት የበለጠ እንደሚያጠናክረው ተመላክቷል።

አዲሱ የባቡር እና የወደብ ግንባታ የኢትዮጵያን ሰሜናዊ የውጪ ንግድ መስመሮች እንደሚያሳድጉ፣ የሎጅስቲክስ ወጪዎችን እንደሚቀንሱ እና በጅቡቲ ቀይ ባህር በሮች በኩል ወደ ዓለም አቀፍ ገበያዎች የሚደረገውን ተደራሽነት እንደሚያሰፋ ይጠበቃል።

Address

Opposite CMC
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 12:30

Telephone

+251970048900

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Standard Amharic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Standard Amharic:

Share