Addis Standard Amharic

Addis Standard Amharic Addis Standard Amharic is an independent online media outlet providing news and in-depth analysis in the Amharic language.
(3)

Its contents mainly focus on current social and political affairs.
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4 Its contents mainly focus on current social and political affairs.

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል የተባለ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ገለፀ‎የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል የተባለ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ሥር አውሎ...
10/12/2025

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል የተባለ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ገለፀ

‎የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል የተባለ ተጠርጣሪን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ቲክቶከር አዶናይ ብርሃነ ሀ/ሚካኤል በቁጥጥር ሥር ሊውል የቻለው ‎"ከኢትዮጵያ ሕዝብ ባህል እና መልካም ሥነ-ምግባር በተቃራኒ በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው አስነዋሪ አለባበስ ለብሰው በአደባባይ እና በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት የታዩት አምስት ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር በዋሉበት የወንጀል ጉዳይ ጋር በተያያዘ" መሆኑን ፌደራል ፖሊስ ገልጿል።

አዶናይ በቅርቡ በተካሄደው በ3ኛው የጂ- ፓወር ቲክቶክ ክርኤቲቭ አዋርድ ላይ በአራት ዘርፎች ማሸነፉ ይታወቃል።

ፌዴራል ፖሊስ በመግለጫው ዕውቅና እና ገንዘብ ለማግኘት ብቻ በማሰብ ሚዲያዎችን ኃላፊነት በጎደለው አኳሃን እየተጠቀሙ በተለይ ወጣቱ ትውልድ በመልካም ሥነ ምግባር ተቀርጾ ሀገርን የሚጠቅሙ ተግባራትን እንዳያከናውንና በተቃራኒው በትውልዱ ላይ ርካሽ ባህልን ለመጫ የሚደረገው ተግባር ለመከላከል የጀመረውን ምርመራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በ3ኛው የጂ- ፓወር ቲክቶክ ክርኤቲቭ አዋርድ ላይ "ከኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥነ-ምግባር ባፈነገጠ አኳሃን ሰውነታቸውን የገላለጠ አለባበስ ለብሰው በአደባባይና በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት ለሕዝብ የታዩ" ተጠርጣሪዎችን ከነግብረ-አበሮቻቸው በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ መጀመሩን ይፋ አድርጓል።

ግለሰቦቹ ወንጌላዊት ገብረ እንድርያስ በርሄ፣ በርከት ፀጋዬ ጅፋር፣ መቅድም ደረጄ መንግስቱ፣ ግሩም ገዛሀኝ ቀጭኔ እና ዮሃንስ መኮንን ሀ/ማርየም ‎የተባሉ መሆናቸውን ፌዴራል ፖሊስ አመልክቷል።

በ  #ኢትዮጵያ ላይ ‘ሰርጎ ገብ’ የተሰኘው የሳይበር ጥቃት ሙከራ በከፍተኛ መጠን የሚፈጸም መሆኑን ኢመደአ አስታወቀበኢትዮጵያ ላይ ከሚፈጸሙ የሳበር ጥቃት ከሙከራዎች መካከል ከፍተኛውን መጠን...
10/12/2025

በ #ኢትዮጵያ ላይ ‘ሰርጎ ገብ’ የተሰኘው የሳይበር ጥቃት ሙከራ በከፍተኛ መጠን የሚፈጸም መሆኑን ኢመደአ አስታወቀ

በኢትዮጵያ ላይ ከሚፈጸሙ የሳበር ጥቃት ከሙከራዎች መካከል ከፍተኛውን መጠን የያዘው ‘ሰርጎ ገብ’ የተሰኘው የሳይበር ጥቃት መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር (ኢመደአ) አስታወቀ።

ይህ የሳይበር ጥቃት በድረ ገጽ፣ በቁልፍ መሠረተ-ልማቶች እና ሌሎች ዘርፎች ላይ ዒላማ ያደረገ እንደነበር የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የሳይበር መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መሐመድ ፈረጃ ገልጸዋል።

በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያ ሦስት ወራት 13ሺህ 443 ጥቃቶችና የጥቃት ሙከራዎች መመዝገባቸውንም ለኢዜአ ተናግረዋል።

አክለውም በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር እና ቁልፍ መሠረተ-ልማቶቹን በሚያሥተዳድሩ ተቋማት ጥረት 97 ነጥብ 16 በመቶ ለሚሆኑት የጥቃት ሙከራዎች ምላሽ ተሰጥቷል ብለዋል።

አቶ መሐመድ፣ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎቹ ቢሳኩ እንደሀገር ይደርስ የነበረው ጉዳት ከፍተኛ በመሆኑ የሳይበር ጥቃቶቹን በመቆጣጠር፣ የጉዳት መጠንን በመቀነስ፣ ድጋሚ ለጥቃት እንዳይጋለጡ ደኅንነታቸውን የማጠናከር ሥራ ተከናውኗል ሲሉ ገልጸዋል።

በቁልፍ መሠረተ-ልማቶች ላይ የሚቃጡ ዓይነተ-ብዙ የሳይበር ጥቃት ሙከራዎችን በማክሸፍ ብሔራዊ ጥቅምን የማስጠበቅ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ኃላፊው አክለው ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ ሀገራት መካከል በሰው ሰራሽ አስተውሎት እና ዲጂታላይዜሽን ምክንያት በብዛት የሳይበር ጥቃቶች ኢላማ እየሆነች መምጣቷን ቼክ ፖይንት ሶፍትዌር ቴክኖሎጂስ በ2025 የአፍሪካ የሳይበር ደህንነት በቅርቡ ባወጣው ሪፖርት አመላክቷል።

ሪፖርቱ በአሁኑ ጊዜ በአፍሪካ ያሉ ድርጅቶች በሳምንት በአማካይ ከ3 ሺህ በላይ የሳይበር ጥቃቶች እንደሚገጥማቸው አስታውቋል።

ከሀገራት መካከል #ናይጄሪያ በብዛት ጥቃት ያስተናገደች ሲሆን፣ #ኢትዮጵያ ደግሞ በሳምንት ከ11,000 በላይ የሚሆኑ ጥቃቶች ዒላማ በመሆን በከፍተኛ ሁኔታ የሳይበር ጥቃት ኢላማ ከሆኑ የአፍሪካ ሀገራት መካከል አንዷ መሆኗን የደቡብ አፍሪካው አይ አፍሪካ መዘገቡ ይታወሳል።

  በ2025 የቤት ኪራይ በጣም ውድ ከሆኑ 10 የ  #አፍሪካ ከተሞች መካከል አንዷ ሆነችአዲስ አበባ በ2025 መገባደጃ ከፍተኛ የቤት ኪራይ ከሚያስከፍሉ አስር የአፍሪካ ከተሞች መካከል መመደ...
10/12/2025

በ2025 የቤት ኪራይ በጣም ውድ ከሆኑ 10 የ #አፍሪካ ከተሞች መካከል አንዷ ሆነች

አዲስ አበባ በ2025 መገባደጃ ከፍተኛ የቤት ኪራይ ከሚያስከፍሉ አስር የአፍሪካ ከተሞች መካከል መመደቧን ቢዝነስ ኢንሳይደር ዓለም አቀፍ የኦንላይን ዳታቤዝ የሆነውን የኑምቤኦ (Numbeo) መረጃን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።

ቢዝነስ ኢንሳይደር አፍሪካ በዘገባው የአዲስ አበባ ከተማ የኪራይ መረጃ ጠቋሚ 22 ሆኖ የተመዘገበ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ 202ኛ ላይ ተቀምጣለች። በዚህም ለመኖሪያ ቤት ተከራዮች በአህጉሪቱ በጣም ውድ ከሆኑ ከተሞች መካከል አንዷ እንድትሆን አድርጓታል ብሏል።

ከአዲስ አበባ በመቀጠል የደቡብ አፍሪካዋ ኬፕ ታውን ከተማ የኪራይ መረጃ ጠቋሚ 21 (ዓለም አቀፍ ደረጃ 218) ሆኖ ሲመዘገብ ኪጋሊ ደግሞ በ16 የኪራይ መረጃ ጠቋሚ (ዓለም አቀፍ ደረጃ 264) ተቀምጣለች።

ቢዝነስ ኢንሳይደር እንደዘገበው ከሆነ፣ በዚህ ዓመት የቤት ኪራይ ዋጋ መጨመር በአፍሪካ ከተሞች ለሚኖሩ ነዋሪዎች ዋና ፈተና ሆኗል። ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት ወጪዎች ግለሰቦችን እና ቤተሰቦችን ራቅ ወዳለ የከተማ ዳርቻዎች እንዘዋወሩ እያስገደደ መሆኑን የገለጸው ዘገባው፣ ይህም የትራንስፖርት ወጪን መጨመር፣ የጉዞ ጊዜን ማርዘም እና ምርታማነትን መቀነስ ያስከትላል ብሏል። በተለይም ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸው ቤተሰቦች በእጅጉ ተጎድተዋል ሲልም አክሏል።

በተመሳሳይ የንግድ ቤቶች ኪራይ መጨመርም በአነስተኛና መካከለኛ ንግዶች ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል ተብሏል። ብዙ ነጋዴዎች ወጪያቸውን ለመመለስ ሲሉ ወደ ሌላ ቦታ እየተዛወሩ፣ ሥራቸውን ወይም ሠራተኞችን እየቀነሱ ነው መሆኑም ተመላክቷል። ምንም እንኳን በስፋት እየተለመደ የመጣው ከቤት ሆነው የመሥራት አሰራር ለአንዳንድ ድርጅቶች መላ እንዲያገኙ ቢረዳም፣ ከፍተኛ የኪራይ ዋጋ ግን ወደ ቁልፍ የንግድ ማዕከላት የመድረስ ዕድልን እየገደበ ይገኛል ሲል ሪፖርቱ ገልጿል።

ሪፖርቱ እንደሚያመለክተው፣ ይህ ጫና በበርካታ ከተሞች የኢ-እኩልነትን አባብሷል፤ ይህም መደበኛ ያልሆኑ ሰፈራዎች እንዲስፋፉና የመኖሪያ ሁኔታ እንዲጣበብ አስተዋጽኦ በማድረግ በጤና፣ በትምህርት እና በአጠቃላይ የኑሮ ጥራት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል።

ቢዝነስ ኢንሳይደር የጠቀሳቸው ተንታኞች የመንግሥት ፖሊሲ ጣልቃገብነት አስፈላጊነት መሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል፤ ከእነዚህም መካከል የመኖሪያ ቤት ድጎማ፣ አነስተኛ ዋጋ ያላቸው የኪራይ ቤቶች መስፋፋት፣ ከፍተኛ ፍላጎት ባለባቸው አካባቢዎች የንግድ ኪራይ ቁጥጥር ማድረግ እና የከተማ ዳርቻዎችን በተሻለ ለማገናኘት የሚያስችል የትራንስፖርት መሠረተ ልማት ማሻሻል ይገኙበታል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ከ  #ፍልስጤም አቻቸው ጋር ተገናኙየውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከፍልስጤም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫርሰን አጋቤኪያን ሻሂን ጋር በጽ...
10/12/2025

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ከ #ፍልስጤም አቻቸው ጋር ተገናኙ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ከፍልስጤም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቫርሰን አጋቤኪያን ሻሂን ጋር በጽ/ቤታቸው ተገናኝተው ተወያይተዋል።

ሚኒስትሮቹ በቀጠናዊና ዓለም አቀፋዊ የሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ዙርያ ውይይት በማድረግ ሃሳብ መለዋወጣቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

================
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ቲክቶክ፡ https://rb.gy/jgdsjm

 #ኢትዮጵያ፡ የ  #ወላይታ ሕዝብ የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው  #ጊፋታ በ  #ዩኔስኮ የማይዳሰስ ቅርስነት ተመዘገበየወላይታ ሕዝብ የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ጊፋታ፣ በተባበሩት መንግሥታ...
10/12/2025

#ኢትዮጵያ፡ የ #ወላይታ ሕዝብ የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው #ጊፋታ በ #ዩኔስኮ የማይዳሰስ ቅርስነት ተመዘገበ

የወላይታ ሕዝብ የዘመን መለወጫ በዓል የሆነው ጊፋታ፣ በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) የሰው ልጅ የማይዳሰስ ባሕላዊ ቅርስ ሆኖ ተመዘገበ።

በሕንድ ኒው ዴልሂ እየተካሄደ በሚገኘው 20ኛው የዩኔስኮ የማይዳሰሱ የባሕል ቅርሶች ጥበቃ ኮሚቴ ጉባዔ ላይ ነው "ጊፋታ" የማይዳሰስ ባሕላዊ ቅርስ ሆኖ የተመዘገበው።

ጊፋታ በየዓመቱ ከመስከረም አጋማሽ እስከ ጥቅምት ወር መጀመሪያ ባለው ጊዜ የሚከበር ሲሆን፣ የወላይታ ማኅበረሰብ አዲስ ዓመት መጀመርን ያመለክታል። በዓሉ ከመድረሱ በፊት ባሉት ቀናት ቤተሰቦች ቤታቸውንና አካባቢያቸውን ያጸዳሉ፣ ግጭቶችን ይፈታሉ እንዲሁም በዓሉን በጋራ ለማክበር ወደ ቀያቸው ይመለሳሉ።

የጊፋታ በዓል በቤተሰብ ስብሰባዎች፣ በጥሬ ሥጋ፣ በባሕላዊ መጠጦች መጋራት እና በሽማግሌዎች ምርቃት ይከበራል። ምሽት ላይ ባህላዊ ዘፈንና ጭፈራ ታጅቦ በእሳት ዙሪያ መርሐግብር ይከናወናል። የአሥር ቀን በዓሉ የሚደመደመው ደግሞ በፈረስ ግልቢያ፣ በሙዚቃ እና በመጨረሻ በምርቃት በሚታጀበው ታላቅ መርሐ-ግብር በሆነው ጎሎ-ኢጄታ ነው።

በዓሉ የተለየ የፆታና የዕድሜ ድርሻ ያለው መሆኑም ከመለያዎቹ መካከል አንዱ ነው። ለአብነትም ሴት ልጆች ባህላዊ ምግቦችን እና መጠጦችን በማዘጋጀት፣ ቤታቸውን በማስዋብ እናቶቻቸውን የሚያግዙ ሲሆን፤ ወንድ ልጆች ደግሞ እንጨት በመሰብሰብ እና ቤቶችን በማደስ አባቶቻቸውን ያግዛሉ። ሽማግሌዎች ደግሞ አለመግባባቶችን በመፍታት፣ በእርሻ አሠራር ላይ ምክር በመስጠት እንዲሁም ምርቃትን በመለገስ ማኅበራዊ መስተጋብርን ያጎለብታሉ።

እንደ ዩኔስኮ ገለጻ፣ የጊፋታ ዕውቀትና ልምዶች በቤተሰብ ውስጥ የሚተላለፉ ሲሆን፣ በትምህርት ቤቶች፣ በባህላዊ ተቋማትና በአካባቢው መገናኛ ብዙኃን አማካይነት ይጠናከራሉ። በዓሉ በትውልድ መካከል ያለውን ትስስር፣ ሰላምን፣ አንድነትንና ማኅበራዊ ትብብርን የሚያጎለብት ከመሆኑም በላይ ወጣቶች የትዳር አጋሮቻቸውን የሚያገኙበት አጋጣሚም ሆኖ ያገለግላል።

ኮሚሽኑ በመዲናዋ ለሚገኙ  #ዲፕሎማቶች ስለ ሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ገለጻ አደረገ፤የ  #ትግራይ ክልል ሁኔታ እና የ   ተሳትፎ ዋነኛ ተግዳሮቶች መሆናቸውን አስገነዘበየ  #ኢትዮጵያ ሀገራዊ ም...
10/12/2025

ኮሚሽኑ በመዲናዋ ለሚገኙ #ዲፕሎማቶች ስለ ሀገራዊ ምክክር ሂደቱ ገለጻ አደረገ፤

የ #ትግራይ ክልል ሁኔታ እና የ ተሳትፎ ዋነኛ ተግዳሮቶች መሆናቸውን አስገነዘበ

የ #ኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ተቀማጭነታቸውን በ ላደረጉ አምባሳደሮችና የኤምባሲ ተወካዮች የሀገራዊ ምክክሩን የእስካሁን ሂደት፣ የቀጣይ ትኩረቶች እና የገጠሙትን ቁልፍ ተግዳሮቶች በተመለከተ ሰፊ ገለጻ አድርጓል።

በገለጻው ላይ ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር) የምክክሩን ሂደትና የገጠሙ ተግዳሮቶችን በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ የምክክሩ የመጨረሻ መዳረሻ "የዜጎች ህይወት በከንቱ የሚጠፋበት የፖለቲካ ሂደት እንዲቆም" ማድረግ እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተው አስገልዝበዋል።

ኮሚሽነር አምባዬ (ዶ/ር) በሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ላይ ተጽዕኖ እያሳደሩ ያሉት ዋነኛ ተግዳሮቶች በማኅበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው የተሳሳተና አሳሳች መረጃ፣ ትግራይ ክልል ዉስጥ ባለው ነባራዊ ሁኔታ ምክንያት የምክክር ሂደቱ እስካሁን ድረስ በተሟላ ሁኔታ መጀመር አለመቻሉ እንዲሁም አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሂደቱ ውስጥ ከመሳተፍ መታቀባቸው በምክክር ሂደቱ ላይ ተፅዕኖ እያደረሰ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ኮሚሽነሩ በገለጻው ወቅት ሀገራዊ ምክክሩ "ዘርፈ ብዙ የሆኑ ዘላቂ ሀገራዊ መፍትሄዎችን እንደሚያመጣ" አጽንኦት ሰጥተው፣ እስካሁን በተከናወኑት መድረኮች ከቆዩ የልዩነት ጉዳዮች ይልቅ የወደፊት የመፍትሔ ሀሳቦች በስፋት እንዲንሸራሸሩ ዕድል መፈጠሩን ጠቁመዋል።

ኮሚሽነሩ በምክክር በሂደቱ “የተረሱና እስከዛሬ ያልተሰሙ ድምጾች መደመጥ እንዲችሉ” መደረጉንም አክለዋል።

የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር አርአያ በበኩላቸው፣ ኮሚሽኑ “93 በመቶ የሀገሪቱን መልካአ ምድር ሸፍኗል” ሲሉ ገልጸው፣ ከትግራይ ክልል በቀር በሁሉም ክልሎች አጀንዳ የማሰባሰብ ሂደት ተከናውኗል ብለዋል።

በትግራይ ክልል የምክክር ሂደቱን በማከናወን የተሟላ ምክክር ለማድረግ ኮሚሽኑ የጀመራቸውን ጥረቶች እንደሚቀጥልም ዋና ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡

“ገለልተኛነት፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት የኮሚሽኑ መርሆች” መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ኮሚሽኑ በተለያዩ አካላት መካከል ያለውን ልዩነት ወደ አንድ መድረክ በማምጣት ሀገራዊ መተማመን እንዲፈጠር ጥረት እያደረገ መሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡

የምክክሩ መሳካት ለኢትዮጵያና ለቀጣናው ወሳኝ በመሆኑ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ለሂደቱ የጀመረውን ድጋፍ አጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

ኮሚሽነር አምባዬም፣ የምክክሩ ሂደት የዜጎችን ሕይወት ለማሻሻል እና የሀገሪቱን ጥንካሬ ለማጎልበት ያለመ በመሆኑ፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ የምክክር ሂደቱ ተግዳሮቶችን ተቋቁሞ ዓላማውን እንዲያሳካ ያልተቋረጠ አጋርነቱን እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

 #አሜሪካ በ  #ሱዳን ጦርነት ተዋጊዎችን በመመልመል ላይ ባሉ የ  #ኮሎምቢያ ዜጎች ላይ ማዕቀብ ጣለችየአሜሪካ መንግሥት የሱዳንን የእርስ በእርስ ጦርነት ተጠቅመው ለመበልጸግ “ዓለም አቀፍ ...
10/12/2025

#አሜሪካ በ #ሱዳን ጦርነት ተዋጊዎችን በመመልመል ላይ ባሉ የ #ኮሎምቢያ ዜጎች ላይ ማዕቀብ ጣለች

የአሜሪካ መንግሥት የሱዳንን የእርስ በእርስ ጦርነት ተጠቅመው ለመበልጸግ “ዓለም አቀፍ መረብ” መሥርተዋል በሚል አራት የኮሎምቢያ ዜጎችና የሚያስተዳድሯቸው አራት ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ ጣለ።

የአሜሪካ ግምጃ ቤት የቀድሞ የኮሎምቢያ ወታደራዊ አባላትን በሱዳን እየተካሄደ በሚገኘው ጦርነት እንዲዋጉ ለመመልመል በተካሄደው ሴራ ውስጥ ተሳታፊ የሆኑትን ስም ይፋ ያደረገ ሲሆን እነዚህም አልቫሮ አንድረስ ኪጃኖ ቤሴራ፣ ክላውዲያ ቪቪያና ኦሊቬሮስ ፎሬሮ፣ ማቴኦ አንድረስ ዱኬ ቦቴሮ እና ሞኒካ ሙኖዝ ዩክሮስ ናቸው።

እነዚህ የሀገሪቱ የቀድሞ ወታደሮች ምስራቅ አፍሪካዊቷ ሀገር ሱዳን ከደረሱ በኋላ፣ ከሱዳን የመንግሥት ኃይሎች ጋር ሽኩቻ ውስጥ የሚገኘውን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎችን ያሰለጥናሉ ተብለው መጠርጠራቸው ተገልጿል።

የአሜሪካ ግምጃ ቤት ባለሥልጣን የሆኑት ጆን ኬ.ሀርሊ በመግለጫቸው ላይ ሲናገሩ፥ "የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሕፃናትን ጨምሮ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት ለመሰንዘር እንደማያቅማማ ደጋግሞ አሳይቷል" ብለዋል።

አክለውም ቡድኑ የሚፈፅማቸው የጭካኔ ተግባራት ግጭቱን በማባባስ ቀጠናውን አተራምሷል ሲሉ ጠቅሰው፤ ይህም የሽብር ቡድኖች እያገነገኑ እንዲመጡ ምቹ ሁኔታን ፈጥሯል ሲሉ ጠቁመዋል።

በጎርጎሮሳውያኑ 2023 በሱዳን ጦርነት ከተቀሰቀሰ ወዲህ ከባድ ውጊያ የቀጠለ ሲሆን፤ ከ12.4 ሚሊዮን በላይ ሰዎች መኖሪያ ቤታቸውን ጥለው ለመሸሽ መገደዳቸውን አልጃዚራ በዘገባው አመልክቷል።

በ  #ጎንደር ከተማ ተጥሎ የነበረው ከፊል የሰዓት እላፊ ገደብ መነሳቱ ተገለጸ፤ የጸጥታ ሁኔታው ተሻሽሏል ተባለበአማራ ክልል ጎንደር ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ሁኔታ መሻሻልን ተከትሎ፣ በከተማ...
10/12/2025

በ #ጎንደር ከተማ ተጥሎ የነበረው ከፊል የሰዓት እላፊ ገደብ መነሳቱ ተገለጸ፤ የጸጥታ ሁኔታው ተሻሽሏል ተባለ

በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ አስተዳደር የጸጥታ ሁኔታ መሻሻልን ተከትሎ፣ በከተማዋ ታውጆ የቆየው የእንቅስቃሴ ገደብ (ከፊል የሰዓት እላፊ) መነሳቱን የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር አንተነህ ቴዎድሮስ የከተማዋ የጸጥታ ሁኔታ በመሻሻሉና አስተማማኝ ሰላም በመኖሩ" ምክንያት ገደቡ መነሳቱን ገልጸው የከተማዋ ማኅበረሰብ ያለ ምንም የጸጥታ ሥጋት ለ24 ሰዓታት መንቀሳቀስ እንደሚችል ገልጸዋል።

የእንቅስቃሴ ገደቡ መነሳቱን ተከትሎ፣ የጸጥታ ሁኔታው መሻሻልን እንደ አመላካች በመውሰድ ባለ ሶስት እግር ተሽከርካሪዎችን (ባጃጅ) ጨምሮ ሌሎች መደበኛ ተሽከርካሪዎች ለ24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ መደረጉን ኮማንደር አንተነህ ገልጸዋል።

አዛዡ አክለውም፣ የእንቅስቃሴ ገደቡ መነሳት ከተገለጸ በኋላ በጸጥታ አካላት መካከል የጋራ ግንዛቤ መፈጠሩን ጠቅሰው፣ በተለይም በቅርቡ ለሚከበረው የጥምቀት በዓል እና በጥር ወር ወደ ከተማዋ የሚመጡ እንግዶችን ለመቀበል በቂ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ፣ የከተማዋን ሰላምና መረጋጋት ለአደጋ ሊያጋልጥ የሚችል ማንኛውንም አይነት እንቅስቃሴ ወይም ጥርጣሬ የከተማው ማኅበረሰብ ለጸጥታ ኃይሎች መረጃ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል።

  ለየትኛውም ሚዲያ ዝግ አለመሆኑን የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ አፅንኦት ሰጥተው ተናገሩየኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ለየትኛውም ሚዲያ ዝግ አለመሆኑን የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ...
09/12/2025

ለየትኛውም ሚዲያ ዝግ አለመሆኑን የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ አፅንኦት ሰጥተው ተናገሩ

የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ለየትኛውም ሚዲያ ዝግ አለመሆኑን የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ አፅንኦት ሰጥተው ገልፀዋል።

ሰብሳቢዋ ይህን ያሉት በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙሃን ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ነው።

በዚሁ ወቅት መገናኛ ብዙኃን አንድ ለአንድ ቃለመጠይቅ እንደሚጠይቁ የገለጹት ሰብሳቢዋ ያንን ቃለመጠየቅ መስጠት ይገባል ብለዋል።

ሆኖም ካለው የስራ ጫና አንፃር ማግኘት የማይቻል ከሆነ አንድ ላይ ሰብሰብ ብለን የሚነሱ ጥያቄዎችን ቦርዱ መመለስ ስላለበት ጋዜጣዊ መግለጫው መዘጋጀቱን አውስተዋል።

አያይዘውም ምርጫ ቦርድ ለየትኛውም ሚዲያ ዝግ አለመሆኑን አፅንኦት ሰጥተዋል።

ሙሉ መግለጫውን ይመልከቱ:
https://youtu.be/A7UWc4BwMEA

ዜና፡  #ኢሰመኮ የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎች የድጋፍ ፊርማ የማሰባሰብ ግዴታ ተፈጻሚ እንዳይሆን መታገዱን በበጎ እንደሚመለከተው ገለፀኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የሕዝብ ተወካዮ...
09/12/2025

ዜና፡ #ኢሰመኮ የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎች የድጋፍ ፊርማ የማሰባሰብ ግዴታ ተፈጻሚ እንዳይሆን መታገዱን በበጎ እንደሚመለከተው ገለፀ

ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ኅዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ በምርጫ ለመወዳደር የሚቀርቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች እጩዎች የድጋፍ ፊርማ እንዲያሰባስቡ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ድንጋጌ ለ7ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ተፈጻሚ እንዳይሆን ማገዱን በበጎ እንደሚመለከተው አስታወቀ።

ኢሰመኮ ትናንት ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የድጋፍ ፊርማ ለማሰባሰብ አስቻይ ሁኔታ አለመኖሩን በመጥቀስ እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓርቲዎች የሚቀርቡለትን ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ ከዚህ ግዴታ ተፈጻሚነት ጋር የተያያዙ ጥያቄዎችን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲያቀርቡ መቆየታቸውን ባደረኩት ክትትሎች ተገንዝቢያለሁ ብሏል።

ኮሚሽኑ፣ የምክር ቤቱ እርምጃ ተጨባጭ ሁኔታዎችን ያገናዘበ፣ በምርጫ የሚወዳደሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላነሷቸው ጥያቄዎች ምላሽ የሰጠ እንዲሁም ምርጫው አካታችና አሳታፊ እንዲሆን ከማድረግ አንጻር አስቻይ ሁኔታዎችን በማመቻቸት የምርጫ እና በሕዝብ አስተዳደር ጉዳዮች ላይ ተሳትፎ የማድረግ መብቶችን ለማጠናከር አዎንታዊ አስተዋጽዖ የሚያደርግ ነው ሲል ውሳኔውን ደግፏል።

ተጨማሪ ያንብቡ:
https://addisstandard.com/Amharic/?p=10108

የ   በሽታን ለመከላከል የሚያስችል የሙከራ ክትባት መስጠት ተጀመረየጤና ሚኒስቴር የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል የሚያስችል ክትባት በደቡብ ኢትዮጵያ እና ሲዳማ ክልል በተመረጡ አከባቢ...
09/12/2025

የ በሽታን ለመከላከል የሚያስችል የሙከራ ክትባት መስጠት ተጀመረ

የጤና ሚኒስቴር የማርበርግ ቫይረስ በሽታን ለመከላከል የሚያስችል ክትባት በደቡብ ኢትዮጵያ እና ሲዳማ ክልል በተመረጡ አከባቢዎች ፈቃደኛ ለሆኑ ተሳታፊዎች መስጠት መጀመሩን አስታወቀ።

ክትባቱ በዓለም ዙሪያ በተደረጉ ቅድመ ጥናቶች ደህንነቱ የተረጋገጠ መሆኑን የገለፀው ሚኒስቴሩ፣ ከአንድ አመት በፊትም በሩዋንዳ በተከሰተው ተመሳሳይ የማርበርግ በሽታ ጥቅም ላይ ዉሎ በሽታውን ለመከላከል ተስፋ ሰጭ ውጤቶችን አሳይቶ እንደነበር አስታውሷል።

ክትባቱ በቅድሚያ ተጋላጭ ለሆኑ ጤና ባለሙያዎች እንዲሁም በቫይረሱ ተይዘው ከነበሩ ሰዎች ጋር ግንኙነት ለነበራቸው በፈቃደኝነት ይሰጣል የተባለ ሲሆን ሂደቱም በዓለም ጤና ድርጅት እና በኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ባለስልጣን መመሪያዎች መሰረት ደረጃውን ጠብቆ እንደሚከናወን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

በቫይረሱ ዙሪያ እስካሁን ባለው መረጃ መሰረት 1,530 የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በ13 ሰዎች ላይ ቫይረሱ የተገኘ ሲሆን ስምንት ሰዎች በቫይረሱ ህይወታቸው ማለፉን እና አራት ሰዎችም ከቫይረሱ ማገገማቸዉ ተመላክቷል።

================
የአዲስ ስታንዳርድ አማርኛ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን ይቀላቀሉ፡
ቴሌግራም: https://rb.gy/rekjr
ፌስቡክ: https://rb.gy/xwxb3
ትዊተር (X)፡ https://rb.gy/34uh4
ድረገጽ: https://rb.gy/5td6n
ቲክቶክ፡ https://rb.gy/jgdsjm

ዜና፡ ምርጫ ቦርድ በአቶ ጌታቸው ረዳ  ለሚመራው  #ስምረት የክልል ፓርቲነት ህጋዊ እውቅና ሰጠየ  #ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቀድሞ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና ...
09/12/2025

ዜና፡ ምርጫ ቦርድ በአቶ ጌታቸው ረዳ ለሚመራው #ስምረት የክልል ፓርቲነት ህጋዊ እውቅና ሰጠ

የ #ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቀድሞ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት እና በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የምሥራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው በማገልገል ላይ ባሉት በአቶ ጌታቸው ረዳ ለሚመራው ትግራይ ዴሞክራሲያዊ ስምረት (ስምረት) የክልል ፓርቲነት ህጋዊ እውቅና ሰጠ።

በቀድሞው የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች የተመሠረተው የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ስምረት (ስምረት) ፓርቲ በጥቅምት ወር አቶ ጌታቸው ረዳን ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል።

ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጊዜያዊ የምዝገባ ፈቃድ የተሰጠው ፖርቲው፣ በትግራይ ክልል አዲስ የፖለቲካ እይታ ለማቅረብ እና “ #ህወሓትም ሆነ #ኢህአዴግ በዓለም ማሕበረሰብ ዘንድ ይቀርብባቸው የነበረ ሂስን ከመሰረቱ ለሚያርም” የተመሰረተ መሆኑን መስራቾቹ ገልጸዋል።

የስምረት የውጭ ግንኙነት አስተባባሪ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ከዚህ ቀደም ለአዲስ ስታንዳርድ እንደተናገሩት፤ ፓርቲው የተመሰረተው “ዓለማችን አሁን የደረሰችበት አስተሳሰብ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የአካባቢያውን እና የሀገሪቱን አጠቃላይ ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ እንዲሁም ትግራይ ወስጥ በተለይ አርሶ አደሩ፣ በወጣቱና በምሁሩ እየተቀጣጠለ ያለው የለውጥ ፍላጎት ለማሟላላት ታሳቢ ያደረገ አስተሳሰብ አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ ነው” ብለዋል።

ተጨማሪ ለማንበብ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=10103

Address

Opposite CMC
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:30 - 17:30
Tuesday 08:30 - 17:30
Wednesday 08:30 - 17:30
Thursday 08:30 - 17:30
Friday 08:30 - 17:30
Saturday 08:30 - 12:30

Telephone

+251970048900

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Standard Amharic posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Standard Amharic:

Share