
11/06/2025
ዜና፡ ፍርድ ቤቱ ለጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ የሰጠውን የዋስትና ትዕዛዝ ቢያጸናም ፖሊስ ለከተማ አስተዳደሩ ሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ ጠየቀ፤ #ሲፒጄና #አሚነስቲ ተስፋለም ወልደየስ ከእስር እንዲለቀቅ ጠየቁ
የ ከተማ አስተዳደር ይግባኝ ሰሚ ችሎት ፍርድቤት ለጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ የሰጠውን የዋስትና ትዕዛዝ ቢያጸናም ፖሊስ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ መጠየቁን የጋዜጠኛው ጠበቃ ቤተማርያም ሀይሉ ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።
ፖሊስ እሁድ በተካሄደው የ እና የ #ሲዳማ ቡና እግር ኳስ ጨዋታ "ደጋፊዎች ስታዲየም ገብተን ማየት አለብን በማለት ያስነሱትን ሁከት እና ብጥብጥ ጋዜጠኛው በቦታው ላይ ተገኝቶ መንግስት ስታዲየሙን እየተጠቀመበት ያለው የትግራይ ተወላጆች ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያደርጉበት ብቻ ነው የሚል ንግግር በቦታው ለተሰበሰቡ ሰዎች ተናግሯል" ማለቱን ጠበቃው ቤተማርያም ሀይሉ ገልጸዋል።
እስሩን ተከትሎ ዓለምአቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት ሲፒጄ እና አሚነስቲ ኢንተርናሽናል በተናጠል ባወጡት መግለጫ፤ የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት የ #ኢትዮጵያ ኢንሳይደር የበይነመረብ ሚዲያ መሥራች እና ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስን "በአስቸኳይ እንዲፈቱ" ጠይቀዋል።
ሙሉ ዘገባ፡ https://addisstandard.com/Amharic/?p=8073