24 hours television

24 hours television We speak what we see, we testify what we hear!

ሀገር ወዳዱ የፅናት ተምሳሌት የጥበብ ሰው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
17/08/2025

ሀገር ወዳዱ የፅናት ተምሳሌት የጥበብ ሰው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

የጃንሆይ እንጀራ ጋጋሪና ወጥ ሰሪዋ ሴት !❤️🙏እኚህ ሴት ከ1950 ጀምሮ የቀኃሥ ታማኝ እንጀራ ጋጋሪና ወጥ ሰሪ ነበሩ።  ሙያቸውን ምግባቸውን ባንቀምሰውም መገመት እንችለን።   ደርግ ስልጣ...
15/08/2025

የጃንሆይ እንጀራ ጋጋሪና ወጥ ሰሪዋ ሴት !❤️🙏

እኚህ ሴት ከ1950 ጀምሮ የቀኃሥ ታማኝ እንጀራ ጋጋሪና ወጥ ሰሪ ነበሩ። ሙያቸውን ምግባቸውን ባንቀምሰውም መገመት እንችለን።
ደርግ ስልጣን ላይ ከወጣ በኋላ እኝህ ባለሙያ ከስራቸው አልተባረሩም። የኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማሪያም ምግብ አብሳይ በመሆን አገልግሎታቸውን ቀጥለው ነበር።
ደርግ ከወደቀ በኋላ ግን የት እንዳሉ አይታወቅም። አንዳንዶች ባልደራስ ሙያቸውን ቀጥለው ነበር ይላሉ።

(✍️አበበ ሐረገወይን ( PhD))

የዑጋንዳን ኘሬዚዳንት ፎቶ አንስቶ ያለፊልተር የፖሰተው ኬኒያዊ ጋዜጠኛ እየተፈለገ ነውጋዜጠኛው ያለበትን ለጠቆመ መቶ ሺህ ዶላር እንደሚሰጡ የዑጋንዳ መንግሥት ተናግሯል ጋዜጠኛው ከተያዘ የእድ...
03/08/2025

የዑጋንዳን ኘሬዚዳንት ፎቶ አንስቶ ያለፊልተር የፖሰተው ኬኒያዊ ጋዜጠኛ እየተፈለገ ነው
ጋዜጠኛው ያለበትን ለጠቆመ መቶ ሺህ ዶላር እንደሚሰጡ የዑጋንዳ መንግሥት ተናግሯል ጋዜጠኛው ከተያዘ የእድሜ ልክ እስራት ይጠብቀዋል

ኢትዮጵያ አንድ ቢሊየነር አስመዘገበች።ቢሊየነርስ አፍሪካ በኢትዮጵያ ውስጥ 10 እጅግ የናጠጡ ሀብታሞችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል፡፡መፅሔቱ ግብፅ፣ ናይጄሪያና ደቡብ አፍሪካ በቢሊዮን የሚቆጠር ሀ...
30/07/2025

ኢትዮጵያ አንድ ቢሊየነር አስመዘገበች።

ቢሊየነርስ አፍሪካ በኢትዮጵያ ውስጥ 10 እጅግ የናጠጡ ሀብታሞችን ዝርዝር ይፋ አድርጓል፡፡

መፅሔቱ ግብፅ፣ ናይጄሪያና ደቡብ አፍሪካ በቢሊዮን የሚቆጠር ሀብት ያላቸው ባለሀብቶችን ማፍራት የቻሉ ቢሆንም ኢትዮጵያ ግን ያላት ቢሊየነር አንድ ብቻ ነው፡፡ እሳቸውም ሼክ መሀመድ አልአሙዲ ናቸው፡፡

በመከተል በአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ ተፅእኖ መፍጠር የሚችሉ በርካታ ሚሊየነሮች በኢትዮጵያ እንዳሉ ዘገባው አስረድቷል፡፡

አልአሙዲ በቁጥር አንድነት የተቀመጡ ሲሆን፣ የሀብታቸው መጠን 9.56 ቢሊዮን ዶላር መሆኑ ተገልጿል፡፡ በሁለተኛ የተቀመጡት በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩትና የሳንሻይን ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሳሙኤል ታፈሰ ናቸው፡፡

በቢሊየነርስ አፍሪካ ዝርዝር በሶስተኛነት የተቀመጡት የበላይነህ ክንዴ ግሩፕ ባለቤት አቶ በላይነህ ክንዴ ናቸው፡፡

በአራተኛ ደረጃ የተቀመጡት ደግሞ ከሀይል አቅርቦት እስከ ሸቀጣ ሸቀጥና ሪል ስቴት ዘርፍ ባሉ ስራዎች ላይ የተሰማሩት አቶ ቴዎድሮስ አሸናፊ ናቸው፡፡

መፅሄቱ በአምስተኛ ደረጃ ያስቀመጣቸው በዋሽንግተን ዲሲና ኒውዮርክ ከተሞች በርካታ የነዳጅ ማደያዎች ያላቸውና በቨርጂኒያ የሪል ስቴት ዘርፍ ላይ የተሰማሩትን አቶ ኢዮብ ማሞ ነው፡፡

አቶ ከተማ ከበደ ስድስተኛ፣ አቶ አለማየሁ ከተማ ሰባተኛ፣ አቶ ብዙአየሁ ቢዘኑ ስምንተኛ፣ አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ዘጠነኛ እንዲሁም የአቪየሽን ባለሙያው አቶ ግርማ ዋቄ አስረኛ ሁነው አጠናቀዋል፡፡

የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ሕወሓት እና የፌዴራል መንግስቱን ለማነጋገር ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ፡፡እየተባባሰ የሄደውን የሕወሓት እና ፌዴራል መንግስቱን ውጥረት ተከትሎ የቀድሞው...
18/07/2025

የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ሕወሓት እና የፌዴራል መንግስቱን ለማነጋገር ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ፡፡

እየተባባሰ የሄደውን የሕወሓት እና ፌዴራል መንግስቱን ውጥረት ተከትሎ የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ፈራሚዎች ስብሰባ ለመጥራት ማቀዳቸውን አፍሪካን ኢንተለጀንስ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ ይሁንና ግን ይህ የንግግር ጥሪ ከማዕከላዊ መንግስቱ ተቃውሞ እንደገጠመው ዘገባው ጠቅሷል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አህመድ በዛሬው እለት ከትግራይ ከተወጣጡ የሀይማኖት አባቶች ጋር መነጋገራቸው የሚታወስ ነው፡፡

◾️የኤርትራ ሪፈረንደም(April 23-25/1993 (ሚያዚያ 15-17/1985)➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢ #በነዚህ ቀናት የኤርትራን ነፃነት ያረጋገጠው ህዝበ ውሳኔ ተካሄደ። በሪፈረንደሙ ...
05/07/2025

◾️የኤርትራ ሪፈረንደም(April 23-25/1993 (ሚያዚያ 15-17/1985)
➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢
#በነዚህ ቀናት የኤርትራን ነፃነት ያረጋገጠው ህዝበ ውሳኔ ተካሄደ። በሪፈረንደሙ ከተሳተፈው ህዝብ መካከል ከ98% በላይ የሚሆነው ኤርትራ ነፃ ሀገር እንድትሆን ድምፁን ሰጥቷል። በሕዝበ ውሳኔው ድምፅ በመስጠት ቀዳሚ የሆኑት ኤርትራ ነፃ ሀገር እንድትሆን ለሀምሳ ዓመታት የታገሉት ኦቦይ ወልደኣብ ወልደማሪያም ነበሩ።

#የኤርትራን ነፃነት በተመለከተ እስከ አሁን ድረስ ሁለት የተሳሳቱ ትርክቶች ይነገራሉ። አንደኛው ትርክት "በሪፈረንደሙ ለህዝቡ የቀረበው አማራጭ "ከነፃነት እና ከባርነት የትኛውን ትመርጣለህ?" የሚል ነበር" እየተባለ የሚነገረው ነው። ይህ ማስረጃ የሌለው የፈጠራ ወሬ ነው። በዚያ ሪፈረንደም ለህዝቡ የቀረበው የማማረጫ ጥያቄ "ኤርትራ ነፃ እና ሉዓላዊት ሀገር እንድትሆን ትደግፋለህን?" የሚል ነው። ህዝቡም "እደግፋለሁ" ወይንም "አልደግፍም" ከሚሉት መልሶች አንዱን ይሰጣል። በዚህም መሠረት የኤርትራን ነፃነት የደገፈው ወገን አሸንፏል።

Ethiopian History and Tourism/የኢትዮጵያ ታሪክና ቱሪዝም

በወላይታ ሶዶ ከተማ የ35 አመት ወጣቴን በቀንዱ ወግቶ የገደለው በሬ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገለጹ።ገዳዩን በሬ በቁጥጥር ስር ለማዋል በ...
29/06/2025

በወላይታ ሶዶ ከተማ የ35 አመት ወጣቴን በቀንዱ ወግቶ የገደለው በሬ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገለጹ።

ገዳዩን በሬ በቁጥጥር ስር ለማዋል በርካታ አባል ፖሊስ ተመድበው በሬው ላይ ከባድ የሚባል ጉዳት መድረሱን የደረሰን መረጃ ያሳያል።

የበሬው ባለቤት ከበሬው ጋር አብሮ መያዝ መቻሉን የሶዶ ከተማ ፖሊስ መረጃ ክፍል ገልጿል ሲል ዜና ወላይታ ዘግቧል።

በኢትዮጵያ የጡረተኞች ዝቅተኛ ወርሃዊ ክፍያ 4,669 ብር ሊሆን ነው ተብሏል።ከቀጣይ ሐምሌ ወር ጀምሮ በሚጀምረው አዲስ ክፍያ ለዋና ጡረተኞቹ ከ 1500 እስከ 2000 ብር ጭማሪ መደረጉን ሰ...
29/06/2025

በኢትዮጵያ የጡረተኞች ዝቅተኛ ወርሃዊ ክፍያ 4,669 ብር ሊሆን ነው ተብሏል።

ከቀጣይ ሐምሌ ወር ጀምሮ በሚጀምረው አዲስ ክፍያ ለዋና ጡረተኞቹ ከ 1500 እስከ 2000 ብር ጭማሪ መደረጉን ሰምተናል።

በዚህም መሰረት 3113 ብር የነበረው ዝቅተኛ የዋና ጡረተኛ ተከፋይ ወደ 4,669 ብር ከፍ ብሏል።
በኢትዮጵያ ዋና እና ተተኪ የግል ጡረታ ተከፋይ ብዛት ሀያ ሺ ይጠጋል።

ከእነዚህ ተከፋዮች መሀል 146 ሺ ፣136 ሺ እና 126 ሺ እና 106 ሺ የሚከፈላቸው አራት ከፍተኛ ጡረታ ተቀባዮች አሉ።

ተተኪ ጡረተኞች የዋናው ጡረተኛ ተከፋይ ግማሹን እንደሚያገኙ ይታወቃል።

ስህተት ነው ተብሏል‼️የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) “ከባድ የመኪና አደጋ አጋጥሟቸው በኢትዮ—ጠቢብ ሆስፒታል በጽኑ ሕሙማን ክፍል (ICU) የሕክምና ክትትል እየተደ...
28/06/2025

ስህተት ነው ተብሏል‼️
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) “ከባድ የመኪና አደጋ አጋጥሟቸው በኢትዮ—ጠቢብ ሆስፒታል በጽኑ ሕሙማን ክፍል (ICU) የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ነው” በሚል የተዘገበው ስህተት ነው ተብሏል።

የነዳጅ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል+++++++++++++ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ።ሚንስቴሩ የሐምሌ ወር ...
28/06/2025

የነዳጅ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል
+++++++++++++
የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ።

ሚንስቴሩ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰኔ ወር ሲሸጥ በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

2 ማስተርስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲተመስገን መምሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሁለት ማስተርስ ድግሪ ( LL. M in Business Law and MA in Logistcs & Supply Chain...
28/06/2025

2 ማስተርስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

ተመስገን መምሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሁለት ማስተርስ ድግሪ ( LL. M in Business Law and MA in Logistcs & Supply Chain Managent) ዛሬ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሰ‍ኢቲ ተመርቋል።

የፖፕ ሊዮ የመጀመርያ ሹመት ኢትዮጵያንም አካቷል  | ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮን 14ኛ በሮማን ኩሪያ ውስጥ ከሚገኙት 16 ጽ/ቤቶች አንዱ ለሆነው የምንኩስና ሕይወት እና የሐዋርያዊ አገልግሎት...
28/06/2025

የፖፕ ሊዮ የመጀመርያ ሹመት ኢትዮጵያንም አካቷል

| ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮን 14ኛ በሮማን ኩሪያ ውስጥ ከሚገኙት 16 ጽ/ቤቶች አንዱ ለሆነው የምንኩስና ሕይወት እና የሐዋርያዊ አገልግሎት የሚሰጡ ማኅበራት ተቋም የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ረዳት ጳጳስ አቡነ ተስፋስላሴን ጨምረው አዳዲስ አባላትን ሾመዋል።

የሮማን ኩሪያ በ16 ጽ/ቤቶች የተደራጀ ሲሆን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በሚመርጡት መሪ እና አማካሪ አባላት ይተዳደራል።

ከነዚህ አንዱ የሆነው የምንኩስና ሕይወትና ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚሰጡ ማኅበራት ተቋም፣ በመነኮሳትና በሐዋርያዊ አገልግሎት ሕይወት ጉዳዮችን በማማከር አሰራርን የሚያጠናክር ተቋም ነው።

የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ በካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት የኩሪያ አስተዳዳሪ (Prefect ) የመረጡበት ይህ ተቋም በሲስተር ሲሞና ብራምቢያ የሚመራ ሲሆን 22 ካርዲናሎች፣ 9 ጳጳሳትን እና ሌሎችንም በአማካሪነት የያዘ ነው።

ቅዱስነታቸው ሊዮን 14ኛ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ረዳት ጳጳስ ከሆኑት ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ ጋር ሌሎች 18 አዳዲስ አባላትን መርጠዋል።

የተመረጡት አባላት በቫቲካን የሚገኙትን የስራ አስፈፃሚዎችን የማማከር ኃላፊነት የሚኖረው ሲሆን ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ በኢትዮጵያ ከሚኖራቸው ኃላፊነት በተጨማሪ ከአዲስ አበባ ሆነው በዚህ ዘርፍ ቤተክርስቲያንን የሚያገለግሉ ይሆናል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251920212223

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when 24 hours television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share