24 hours television

24 hours television We speak what we see, we testify what we hear!

◾️የኤርትራ ሪፈረንደም(April 23-25/1993 (ሚያዚያ 15-17/1985)➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢ #በነዚህ ቀናት የኤርትራን ነፃነት ያረጋገጠው ህዝበ ውሳኔ ተካሄደ። በሪፈረንደሙ ...
05/07/2025

◾️የኤርትራ ሪፈረንደም(April 23-25/1993 (ሚያዚያ 15-17/1985)
➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢➢
#በነዚህ ቀናት የኤርትራን ነፃነት ያረጋገጠው ህዝበ ውሳኔ ተካሄደ። በሪፈረንደሙ ከተሳተፈው ህዝብ መካከል ከ98% በላይ የሚሆነው ኤርትራ ነፃ ሀገር እንድትሆን ድምፁን ሰጥቷል። በሕዝበ ውሳኔው ድምፅ በመስጠት ቀዳሚ የሆኑት ኤርትራ ነፃ ሀገር እንድትሆን ለሀምሳ ዓመታት የታገሉት ኦቦይ ወልደኣብ ወልደማሪያም ነበሩ።

#የኤርትራን ነፃነት በተመለከተ እስከ አሁን ድረስ ሁለት የተሳሳቱ ትርክቶች ይነገራሉ። አንደኛው ትርክት "በሪፈረንደሙ ለህዝቡ የቀረበው አማራጭ "ከነፃነት እና ከባርነት የትኛውን ትመርጣለህ?" የሚል ነበር" እየተባለ የሚነገረው ነው። ይህ ማስረጃ የሌለው የፈጠራ ወሬ ነው። በዚያ ሪፈረንደም ለህዝቡ የቀረበው የማማረጫ ጥያቄ "ኤርትራ ነፃ እና ሉዓላዊት ሀገር እንድትሆን ትደግፋለህን?" የሚል ነው። ህዝቡም "እደግፋለሁ" ወይንም "አልደግፍም" ከሚሉት መልሶች አንዱን ይሰጣል። በዚህም መሠረት የኤርትራን ነፃነት የደገፈው ወገን አሸንፏል።

Ethiopian History and Tourism/የኢትዮጵያ ታሪክና ቱሪዝም

በወላይታ ሶዶ ከተማ የ35 አመት ወጣቴን በቀንዱ ወግቶ የገደለው በሬ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገለጹ።ገዳዩን በሬ በቁጥጥር ስር ለማዋል በ...
29/06/2025

በወላይታ ሶዶ ከተማ የ35 አመት ወጣቴን በቀንዱ ወግቶ የገደለው በሬ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ ገለጹ።

ገዳዩን በሬ በቁጥጥር ስር ለማዋል በርካታ አባል ፖሊስ ተመድበው በሬው ላይ ከባድ የሚባል ጉዳት መድረሱን የደረሰን መረጃ ያሳያል።

የበሬው ባለቤት ከበሬው ጋር አብሮ መያዝ መቻሉን የሶዶ ከተማ ፖሊስ መረጃ ክፍል ገልጿል ሲል ዜና ወላይታ ዘግቧል።

በኢትዮጵያ የጡረተኞች ዝቅተኛ ወርሃዊ ክፍያ 4,669 ብር ሊሆን ነው ተብሏል።ከቀጣይ ሐምሌ ወር ጀምሮ በሚጀምረው አዲስ ክፍያ ለዋና ጡረተኞቹ ከ 1500 እስከ 2000 ብር ጭማሪ መደረጉን ሰ...
29/06/2025

በኢትዮጵያ የጡረተኞች ዝቅተኛ ወርሃዊ ክፍያ 4,669 ብር ሊሆን ነው ተብሏል።

ከቀጣይ ሐምሌ ወር ጀምሮ በሚጀምረው አዲስ ክፍያ ለዋና ጡረተኞቹ ከ 1500 እስከ 2000 ብር ጭማሪ መደረጉን ሰምተናል።

በዚህም መሰረት 3113 ብር የነበረው ዝቅተኛ የዋና ጡረተኛ ተከፋይ ወደ 4,669 ብር ከፍ ብሏል።
በኢትዮጵያ ዋና እና ተተኪ የግል ጡረታ ተከፋይ ብዛት ሀያ ሺ ይጠጋል።

ከእነዚህ ተከፋዮች መሀል 146 ሺ ፣136 ሺ እና 126 ሺ እና 106 ሺ የሚከፈላቸው አራት ከፍተኛ ጡረታ ተቀባዮች አሉ።

ተተኪ ጡረተኞች የዋናው ጡረተኛ ተከፋይ ግማሹን እንደሚያገኙ ይታወቃል።

ስህተት ነው ተብሏል‼️የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) “ከባድ የመኪና አደጋ አጋጥሟቸው በኢትዮ—ጠቢብ ሆስፒታል በጽኑ ሕሙማን ክፍል (ICU) የሕክምና ክትትል እየተደ...
28/06/2025

ስህተት ነው ተብሏል‼️
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) “ከባድ የመኪና አደጋ አጋጥሟቸው በኢትዮ—ጠቢብ ሆስፒታል በጽኑ ሕሙማን ክፍል (ICU) የሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው ነው” በሚል የተዘገበው ስህተት ነው ተብሏል።

የነዳጅ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል+++++++++++++ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ።ሚንስቴሩ የሐምሌ ወር ...
28/06/2025

የነዳጅ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል
+++++++++++++
የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ።

ሚንስቴሩ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰኔ ወር ሲሸጥ በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አሳስቧል።

2 ማስተርስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲተመስገን መምሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሁለት ማስተርስ ድግሪ ( LL. M in Business Law and MA in Logistcs & Supply Chain...
28/06/2025

2 ማስተርስ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

ተመስገን መምሩ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሁለት ማስተርስ ድግሪ ( LL. M in Business Law and MA in Logistcs & Supply Chain Managent) ዛሬ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሰ‍ኢቲ ተመርቋል።

የፖፕ ሊዮ የመጀመርያ ሹመት ኢትዮጵያንም አካቷል  | ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮን 14ኛ በሮማን ኩሪያ ውስጥ ከሚገኙት 16 ጽ/ቤቶች አንዱ ለሆነው የምንኩስና ሕይወት እና የሐዋርያዊ አገልግሎት...
28/06/2025

የፖፕ ሊዮ የመጀመርያ ሹመት ኢትዮጵያንም አካቷል

| ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮን 14ኛ በሮማን ኩሪያ ውስጥ ከሚገኙት 16 ጽ/ቤቶች አንዱ ለሆነው የምንኩስና ሕይወት እና የሐዋርያዊ አገልግሎት የሚሰጡ ማኅበራት ተቋም የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ረዳት ጳጳስ አቡነ ተስፋስላሴን ጨምረው አዳዲስ አባላትን ሾመዋል።

የሮማን ኩሪያ በ16 ጽ/ቤቶች የተደራጀ ሲሆን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት በሚመርጡት መሪ እና አማካሪ አባላት ይተዳደራል።

ከነዚህ አንዱ የሆነው የምንኩስና ሕይወትና ሐዋርያዊ አገልግሎት የሚሰጡ ማኅበራት ተቋም፣ በመነኮሳትና በሐዋርያዊ አገልግሎት ሕይወት ጉዳዮችን በማማከር አሰራርን የሚያጠናክር ተቋም ነው።

የቀድሞ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቼስኮስ በካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ሴት የኩሪያ አስተዳዳሪ (Prefect ) የመረጡበት ይህ ተቋም በሲስተር ሲሞና ብራምቢያ የሚመራ ሲሆን 22 ካርዲናሎች፣ 9 ጳጳሳትን እና ሌሎችንም በአማካሪነት የያዘ ነው።

ቅዱስነታቸው ሊዮን 14ኛ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ረዳት ጳጳስ ከሆኑት ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ ጋር ሌሎች 18 አዳዲስ አባላትን መርጠዋል።

የተመረጡት አባላት በቫቲካን የሚገኙትን የስራ አስፈፃሚዎችን የማማከር ኃላፊነት የሚኖረው ሲሆን ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ በኢትዮጵያ ከሚኖራቸው ኃላፊነት በተጨማሪ ከአዲስ አበባ ሆነው በዚህ ዘርፍ ቤተክርስቲያንን የሚያገለግሉ ይሆናል።

በቁጥጥር ስር ውሏልበሙሊኒየም አዳራሽ ተከስቶ የነበረው የዕሳት አደጋ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል ትናንት ሰኔ 20/2017 ምሽት 4:00 ሰዓት ገደማ በሚሊኒየም አዳራሽ ተከስቶ የነበረው ...
28/06/2025

በቁጥጥር ስር ውሏል

በሙሊኒየም አዳራሽ ተከስቶ የነበረው የዕሳት አደጋ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር ውሏል

ትናንት ሰኔ 20/2017 ምሽት 4:00 ሰዓት ገደማ በሚሊኒየም አዳራሽ ተከስቶ የነበረው የእሳት አደጋ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ ኮሚሽን ለኤ ኤም ኤን ዲጂታል ገልጿል።

በአደጋው በሰው ህይወት ላይ ምንም አይነት አደጋ አልደረሰም።

በኢስራኤል የተገደሉት የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ 30 የሚሆኑ ከፍተኛ ወታደራዊ እና የደህንነት ባለስልጣናት ዝርዝር!!ሌተናል ጀነራል ሆሴን ሰላሚ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) ዋ...
26/06/2025

በኢስራኤል የተገደሉት የኢራን እስላማዊ ሪፐብሊክ 30 የሚሆኑ ከፍተኛ ወታደራዊ እና የደህንነት ባለስልጣናት ዝርዝር!!

ሌተናል ጀነራል ሆሴን ሰላሚ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) ዋና አዛዥ

ሌተናል ጀነራል መሀመድ ሆሴን ባቅሪ – የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም

ሌተናል ጀነራል ጎላም አሊ ራሺድ – የኻተም አል-አንቢያ ማዕከላዊ ዋና መስሪያ ቤት አዛዥ

ሌተናል ጀነራል ጎላም አሊ ራሺድ (የእሱ ምትክ፣ ከጥቂት ጊዜ በኋላ የተገደለ)

ብሪጋዴር ጀነራል ሜህዲ ረባኒ – የጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ምክትል ለኦፕሬሽንስ

ሜጀር ጀነራል ጎላምሬዛ ሜህራቢ – የወታደራዊ መረጃ ድርጅት ምክትል ሃላፊ

ሜጀር ጀነራል መሀመድ ካዜሚ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) የመረጃ ድርጅት ሃላፊ

ሜጀር ጀነራል ሞህሰን በቀሪ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) መረጃ ምክትል ሃላፊ

ብሪጋዴር ጀነራል ሀሰን ሞሀኬክ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) መረጃ ምክትል ሃላፊ

ሜጀር ጀነራል መሀመድ ጃፋር አሰዲ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ ዋና መስሪያ ቤት ዋና ኢንስፔክተር

ሜጀር ጀነራል መሀመድ ሬዛ ናስር ባቅባን – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) የመረጃ ተወካይ

ብሪጋዴር ጀነራል መስዑድ ሸናኤ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) አዛዥ የስታፍ ሃላፊ

ሜጀር ጀነራል አሚር አሊ ሀጂዛዴህ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) የኤሮስፔስ ሃይል አዛዥ

ብሪጋዴር ጀነራል አሚር ፑርጆዳኪ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) ኤሮስፔስ ምክትል አዛዥ

ብሪጋዴር ጀነራል ኾስሮ ሀሰኒ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) ኤሮስፔስ ምክትል የመረጃ ሃላፊ

ብሪጋዴር ጀነራል ዳቩድ ሼይካን – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) የአየር መከላከያ አዛዥ

ብሪጋዴር ጀነራል መሀመድ ባቄር ታሄርፑር – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) የሰው አልባ አውሮፕላን (UAV) ክፍል አዛዥ

ብሪጋዴር ጀነራል መንሱር ሰፋርፑር – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) የቴህራን ኤሮስፔስ አዛዥ

ብሪጋዴር ጀነራል መስዑድ ጣይብ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) ኤሮስፔስ

ብሪጋዴር ጀነራል ጃቫድ ጃርሳራ – የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) ኤሮስፔስ

ብሪጋዴር ጀነራል መሀመድ ሰይድ ኢዛዲ – የፍልስጤም ዴስክ ሃላፊ፣ ቁድስ ፎርስ

ብሪጋዴር ጀነራል ቤህናም ሸህሪያሪ – የዩኒት 190 አዛዥ፣ ቁድስ ፎርስ

ሜጀር ጀነራል አሚር ሞዛፋርኒያ – የ SPND (የመከላከያ ምርምር እና ልማት ድርጅት) ሃላፊ

ብሪጋዴር ጀነራል መሀመድ ታቂ ዩሱፍቫንድ – የባሲጅ የመረጃ ሃላፊ

ጀነራል መይሳም ሪዝቫንፑር – የባሲጅ (ማህበራዊ ጉዳዮች) ምክትል አዛዥ

ብሪጋዴር ጀነራል ሰይድ ሞጅተባ ሞኢንፑር – የአልቦርዝ ክፍለ ሃገር የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) የስታፍ ሃላፊ

ብሪጋዴር ጀነራል ሞጅተባ ካራሚ – የአልቦርዝ ክፍለ ሃገር የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ (IRGC) ምክትል አዛዥ

ብሪጋዴር ጀነራል አክባር ኢናያቲ – የአልቦርዝ ክፍለ ሃገር የማህበራዊ ጉዳዮች ምክትል አዛዥ

ጀነራል አሊሬዛ ሎጥፊ – የፖሊስ መረጃ ድርጅት (ሳፋ) ሃላፊ

ብሪጋዴር ጀነራል አባስ ኑሪ – የምድር ሃይል ዋና መስሪያ ቤት የሎጀስቲክስ ምክትል አዛዥ

የኢራን የድል አዋጅ ፣ በእስራኤል ጥቃት የተወገዱ ኪሳራን ወደ ድል ለመቀየር የሚደረግ የፕሮፓጋንዳ ስልት ነው ወይስ ኢራን በዓለም ፊት ካቀረበችው ትርክት በስተጀርባ የተደበቀ ሌላ እውነት አለ?

የእስራኤል የፋይናንስና የግብር ባለ ስልጣን ከኢራን ጋር በተደረገው ጦርነት በግንቦች በደረሰው ውድመት ከ 3 ቢልዮን ዶላር በላይ እንደሚገመት ገልፆል። በደቡባዊቷ ቴል አቪቭ ባት ያም ከተማ ...
26/06/2025

የእስራኤል የፋይናንስና የግብር ባለ ስልጣን ከኢራን ጋር በተደረገው ጦርነት በግንቦች በደረሰው ውድመት ከ 3 ቢልዮን ዶላር በላይ እንደሚገመት ገልፆል። በደቡባዊቷ ቴል አቪቭ ባት ያም ከተማ ብቻ በ 109 ግንቦች ጉዳት የደረሰ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ 22 ግንቦች በኢራን ሚሳይል ሙሉ በሙሉ መውደማቸውን የከተማው ማዘጋጃ ቤት አስታውቋል።

የግድያ ሙከራ‼️በህወሓት ወታደራዊ አመራር ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ።የህወሓት ታጣቂ አርሚ 44 ዋና አዛዥ  ጀነራል ገብረዮሃንስ ኣባተ(ወዲ ኣባተ) የሰማዕታት ቀንን ለማክበር ወደ ሓውዜን እ...
25/06/2025

የግድያ ሙከራ‼️
በህወሓት ወታደራዊ አመራር ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ።
የህወሓት ታጣቂ አርሚ 44 ዋና አዛዥ ጀነራል ገብረዮሃንስ ኣባተ(ወዲ ኣባተ) የሰማዕታት ቀንን ለማክበር ወደ ሓውዜን እየተጓዘ በነበረበት ወቅት የግድያ ሙከራ እንደተደረገበት ምንጮቻችን ያረጋገጡ ሲሆን ወዲ አባተ መጠነኛ ጉዳት እንደደረሰበት እና መኪኖችም ላይ ከላይ በሚታየው መልኩ ጉዳት ደርሶባቸዋል።

በትግራይ ክልል 61 ሺህ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ማኅበረሰቡ ተቀላቀሉ*****************በትግራይ ክልል በእስካሁኑ ሂደት 61 ሺህ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ማኅበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረጉን...
25/06/2025

በትግራይ ክልል 61 ሺህ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ማኅበረሰቡ ተቀላቀሉ
*****************

በትግራይ ክልል በእስካሁኑ ሂደት 61 ሺህ የቀድሞ ታጣቂዎች ወደ ማኅበረሰቡ እንዲቀላቀሉ ማድረጉን ብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አስታወቀ።

የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ብርጋዴር ጄኔራል ደርቤ መኩሪያ እንደገለፁት በመጀመሪያው ምዕራፍ በትግራይ ክልል 75 ሺህ የቀድሞ ታጣቂዎችን ወደ ማኀበረሰቡ ለመቀላቀል ታስቦ 48 ሺዎቹን መቀላቀል ተችሏል።

ቀሪዎቹን በቀሩት ሁለት ወራቶች ለመቀላቀል ይሰራል ብለዋል።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251920212223

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when 24 hours television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share