17/10/2021
በቦረና እና ጉጂ ዞን የተከሰተው ድርቅና ጉዳቱ
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት በቦረናና ጉጂ ዝናብ አጠር በሆኑ ቆላማ
አካባቢዎች የተፈጠረው ድርቅ የከፋ ጉዳት እንዳያስከትል ግብረኃይል
በማቋቋም የድጋፍ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ፡፡
ችግሩን በዘላቂነት ለመቅረፍ የክልሉ መንግሥት 100 ሚሊዮን ብር በጀት
በመያዝ የተጠናከረ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን አስውቋል፡፡
በቦረና ዞን 8 ወረዳዎች በጉጂ ዞን ደግሞ 5 ወረዳዎች ወቀቱን የጠበቀ ዝናብ
ባለመዝነቡ ከፍተኛ የመኖ እና ውሃ እጥረት ተከስቷል። ይህም በእንስሳት ላይ
ጉዳት እያስከተለ ነው፡፡
የክልሉ የመስኖ ልማትና አርብቶ አደር ቢሮ ምክትል ኃላፊ ሮባ ቱርጬ በዞኑ
የዝናብ እጥረት እንደሚያጋጥም የክልሉ መንግሥት የቅድመ ትንበያ መረጃ
ስለነበረው ከ6 ወራት በፊት ጀምሮ የክትትልና የድጋፍ ሥራ ሲሰራ መቆየቱን
ገልፀዋል፡፡
በዚህም 100 ሚሊየን ብር በጀት ተመድቦ ቢሮው ሲንቀሳቀስ እንደነበረ ነው
ያስረዱት፡፡ ይሁን እንጂ እንደዛም ሆኖ ይጠበቅ የነበረው ዝናብ ሳይዘንብ
በመቆየቱ ችግሩ ሊያጋጥም ችሏል ነው ያሉት፡፡
ያጋጠመው የዝናብ እጥረት ቀጣይነት ሊኖረው የሚችልበት እድል ስላለ
መንግሥት እርሱን ያገናዘበ መልሶ የማቋቋም ሥራ ለመስራት በሚያስችል
አደረጃጀት የድጋፍና ክትትል ሥራዎችን በቀጣይነት ይሰራል ብለዋል፡፡
የክልሉ መንግሥትም ያጋጠመውን ድርቅ ዘላቂነት ለመፍታት የተቀናጀ ሥራ
እየሰራ እንደሆነም ተመላክቷል፡፡
ልዩ መረጃ!!!