22/05/2026
"የሕዝብን የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጥ ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም" የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን)
ደብረ ብርሀን : ግንቦት 14/2018ዓ.ም. (አሚኮ) ምርጫ ማከናወን በአንድ በኩል የመንግስት ሕጋዊ ግዴታ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የዜጎችን መሠረታዊ መብቶች ማረጋገጫ መንገድ መሆኑን የአብን የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ እና በሰሜን ሸዋ ዞን የመሃል ሜዳ ምርጫ ክልል የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት እጩ ተወዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሠር ዳምጠው ተሰማ ተናግረዋል።
ምርጫ ዜጎች በወኪሎቻቸው በኩል በገዛ እጣ ፈንታቸው ላይ የሚወስኑበት ፖለቲካዊ መብት ነው።
ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ አንጻርም ፖለቲካዊ ምርጫ ከሕዝባችን የስልጣን ባለቤትነት ጋር በቀጥታ የሚገናኝ ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል።
በመሆኑም በዚህ ጠቅላላ ምርጫ ወኪልን ከመምረጥ ባሻገር መላው ሂደቱ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ከእያንዳንዱ ዜጋ አሻራውን የማሳረፍ ትልቅ ኃላፊነት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁሞ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የወሰነው ሂደቱ የሕጋዊ ሥርዓት ግንባታ ምሰሶ አምኖበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፓርቲው ከሃሳብ ፖለቲካና ከተቋማዊ ትግል ውጭ ባሉ ልምምዶች የተነሳ ሕዝቡ እየከፈለ ያለውን ዋጋ በመረዳት ምርጫውን ለድርድር እንደማያቀርበው አስታውቋል።
በምርጫ የሕዝብን የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጥ እና ዘላቂ ሰላም የማስፈን ተልዕኮዎችን ከግብ ለማድረስ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ እና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ አሁን ላይ ሁሉን አቀፍ ሁለንተናዊ ጥረቶች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል።
በመሆኑም ጥቂት ቀናት የቀሩትን ሀገራዊ የምርጫ ሂደቶች ሰላማዊ ለማድረግ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሆኑ የመራጩ ሕዝብ ቅንጅት ወሳኝ መሆኑንም ገልጸዋል።
https://www.facebook.com/share/1CmB7RmCgi/
"የሕዝብን የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጥ ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም" የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን)
ደብረ ብርሀን : ግንቦት 14/2018ዓ.ም. (አሚኮ) ምርጫ ማከናወን በአንድ በኩል የመንግስት ሕጋዊ ግዴታ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የዜጎችን መሠረታዊ መብቶች ማረጋገጫ መንገድ መሆኑን የአብን የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ እና በሰሜን ሸዋ ዞን የመሃል ሜዳ ምርጫ ክልል የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት እጩ ተወዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሠር ዳምጠው ተሰማ ተናግረዋል።
ምርጫ ዜጎች በወኪሎቻቸው በኩል በገዛ እጣ ፈንታቸው ላይ የሚወስኑበት ፖለቲካዊ መብት ነው።
ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ አንጻርም ፖለቲካዊ ምርጫ ከሕዝባችን የስልጣን ባለቤትነት ጋር በቀጥታ የሚገናኝ ቁልፍ ጉዳይ ነው ብለዋል።
በመሆኑም በዚህ ጠቅላላ ምርጫ ወኪልን ከመምረጥ ባሻገር መላው ሂደቱ በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ከእያንዳንዱ ዜጋ አሻራውን የማሳረፍ ትልቅ ኃላፊነት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በርካታ ፈተናዎችን ተቋቁሞ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመሳተፍ የወሰነው ሂደቱ የሕጋዊ ሥርዓት ግንባታ ምሰሶ አምኖበት መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፓርቲው ከሃሳብ ፖለቲካና ከተቋማዊ ትግል ውጭ ባሉ ልምምዶች የተነሳ ሕዝቡ እየከፈለ ያለውን ዋጋ በመረዳት ምርጫውን ለድርድር እንደማያቀርበው አስታውቋል።
በምርጫ የሕዝብን የስልጣን ባለቤትነት ማረጋገጥ እና ዘላቂ ሰላም የማስፈን ተልዕኮዎችን ከግብ ለማድረስ የሁሉንም ባለድርሻ አካላት ርብርብ ይጠይቃል ብለዋል።
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት እንዲጠናቀቅ እና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ አሁን ላይ ሁሉን አቀፍ ሁለንተናዊ ጥረቶች እንደሚያስፈልጉ ተናግረዋል።
በመሆኑም ጥቂት ቀናት የቀሩትን ሀገራዊ የምርጫ ሂደቶች ሰላማዊ ለማድረግ የፖለቲካ ፓርቲዎችም ሆኑ የመራጩ ሕዝብ ቅንጅት ወሳኝ ነው መሆኑንም ገልጸዋል።
ዮናስ ታደሰ