Zemen Television

Zemen Television በሀቀኛ መረጃ ትውልድ ይሰራል. የሀገር አንድነት ይሰምራል :: 🇺🇸

የማህበረሰብ ተወካዮች ጥረት አበረታች ምላሽ ያገኘ ሲሆን አፈጻጸሙ እንዲሳካ የሁሉንም አካላት ቁርጠኝነት ይጠበቃል የጣርማ በር ሰፌድ ሜዳ መንገድ ፕሮጀክት በቆረጣ ምክንያት ከተቆፋፈረ በኋላ ...
10/08/2026

የማህበረሰብ ተወካዮች ጥረት አበረታች ምላሽ ያገኘ ሲሆን አፈጻጸሙ እንዲሳካ የሁሉንም አካላት ቁርጠኝነት ይጠበቃል

የጣርማ በር ሰፌድ ሜዳ መንገድ ፕሮጀክት በቆረጣ ምክንያት ከተቆፋፈረ በኋላ ግንባታው በመቋረጡ የመንዝ፣ የግሼ፣ የጣርማ በር እና አካባቢው ማህበረሰብ እያሳለፈ ያለው መከራ ክረምት ታክሎበት እጅግ ለከፋ ለሰው ሰራሽ ስቃይ ተዳርጓል። የኢኮኖሚ ድቀቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ለታማሚ ህክምና ለነፍሰጡሮች የጤና አገልግሎት ማስገኘት አዳጋች ከሆነ ሰነባብቷል።

በዛሬው እለት ነሓሴ 4 ቀን ይህን የሚሊዮች መሰረታዊ አጀንዳ ይዘው የመጡ የማህበረሰብ ተወካዮች ለሚመለከታቸው የፌደራል ተቋማት የህዝቡን ስቃይ በማስዳትና በመፍትሄዎች ምክክር ተደርጓል። የህዝብ ተወካዮቹ እና የፌደራል መንገዶች ባለስልጣን አመራሮች ባደረጉት ውይይት መደበኛ የግንባታ ስራው እስኪጀመር መንገዱ ጊዜያዊ የጥገና ስራ እንዲከናወንና መግባባት ላይ ተደርሷል። ባለስልጣኑ በሙያተኛ፣ በበጀትና በግንባታ ግብአት ረገድ ዝግጁ መሆኑንና ወደስራ ለመግባት መወሰኑን ገልጾ ከማህበረሰቡና ከሁሉም ባለድርሻዎች ሊደረጉለት የሚጠበቁ እገዛዎችን በዝርዝር አስረድል።

የማህበረሰብ ተወካዮቹም ከዚህ የባሰ አንገብጋቡ አጀንዳ እንደሌለና ሁሉንም አቅማቸው በፈቀደ ህዝባዊ ድጋፍ እንደሚያስተባብሩ ቃል ሰጥተዋል። ከባለስልጣኑ ጋር የተደረገው ውይይት ከተጠናቀቀ በኋላ የልኡካኑ አባል የሆኑ አዛውንቶች "ህዝባችን እንዲህ አይነት አበሳ የዛሬ 50 አመት እንኳ እንዳልገጠመው እና ለችግሩ መፍትሄ ካስገኘ ማንኛውንም ዋጋ ለመክፈል" መዘጋጀታቸውን ሲገልጹ ሲቃ እየተናነቃቸው ነበር።

ለረጅም ጊዜ ሲደረጉ የቆዩ እና እየተጠናከሩ የመጡት የህዝብ ንቅናቄዎች በዛሬው የውይይት አቅጣጫ መሰረት ወደተግባር ለመግባት ቁሳዊና ሞራላዊ ግብአቶች ናቸው። በመሆኑም በደብረብርሀንና በሸዋሮቢት ያሉ የመንገዶችና ትራንስፖርት ባለስልጣን አስተባባሪዎችና ሙያተኞች ከማህበረሰብ ተወካዮቹ፣ እና ባለድርሻዎች ጋር በመናበብ በአፋጣኝ ወደ ተግባር ለመግባት የተፈጠረውን መደላድል ተጠቅመው ወደአፈጻጸም መግባች ይጠበቅባቸዋል። ህዝብ ከፊት ቀድሞ እያስተባበረ ባለበት ሁኔታ መሬት ላይ የሚከወኑ የአፈጻጸሞች ስራዎች ቀላል ናቸው።

ሲጠቃለል ለህዝቡ ከዚህ የባሰ የነጻነትና የህልውና ጥያቄ ስለሌለ በምንም አይነት ሰበብ ኮምፕሮማይዝ የሚደረግ ጉዳይ እንዳይደለ የትኛው ባለድርሻ አካል ሊገነዘብ እና ችግሩ እንዲቃለል በተግባር የሚገለጽ አሻራውን ማሳረፍ ይኖርበታል።

( 'እግረኛው' በተሰኘው የዩቲዩብ ቻናሉ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖት ቀጠሮ ተጠይቆበታልየፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛውን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረ...
31/07/2026

( 'እግረኛው' በተሰኘው የዩቲዩብ ቻናሉ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖት ቀጠሮ ተጠይቆበታል

የፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛውን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረበው ሲሆን፣ "ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨትና ፍትህን ለማዛባት በመሞከር" ወንጀል እንደጠረጠረው ለችሎቱ አስታውቋል።

ፍርድ ቤቱም የፖሊስን የክስ መዝገብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበለትን የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ በመቀበል ለሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም አቶ ተክለሀይማኖት እስከ ቀጠሮው ዕለት ድረስ በማረሚያ ቤት በእስር የሚቆይ ይሆናል።

የጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር መዋል መነሻ ምክንያት በውል ባይታወቅም በቅርቡ ከ'ፊንቴክ' (Fintech) የመኪና ማጭበርበር ጉዳይ ጋር በተያያዘ ክስ ከተመሰረተባቸው አርቲስቶች ጋር ያደረገው ቃጠይቅ የፍትህ ስርዓት ሂደትን የሚያዛባና በዳኝነት/በፍርድ አሰጣጥ ላይ ጫና የሚፈጥር በመሆኑ ሊያሳስረው ይችላል።

ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ !የ"እግረኛው ሚዲያ" መስራችና ባለቤት የሆነው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።ጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር የዋ...
31/07/2026

ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ !

የ"እግረኛው ሚዲያ" መስራችና ባለቤት የሆነው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።

ጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር የዋለው በትናንትናው ዕለት ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሆነ የታወቀ ሲሆን፣ ለእስሩ ምክንያት ከመከላከያ ሰራዊት አልባሳት (ዩኒፎርም) ጋር ተያይዞ ከቀረበው ዘገባ ጋር ሳይያያዝ እንዳልቀረ ምንጮቹ ጠቁመዋል ሲል ጉርሻ page ነው የዘገበው።

"ማን ያርዳ የቀበረ ማን ያውጋ የነበረ" አይደል ነገሩ።የአማራ ህዝብ ቁጥር ቅሸባ የተፈጸመበት በህወሀት ዘመን እንደሆነ የሚታወቅ ነው። ከሰሞኑ የድርጊቱ ፈጻሚ ድርጅት ዋና መሪ ሆኑት አቶ አ...
21/07/2026

"ማን ያርዳ የቀበረ ማን ያውጋ የነበረ" አይደል ነገሩ።
የአማራ ህዝብ ቁጥር ቅሸባ የተፈጸመበት በህወሀት ዘመን እንደሆነ የሚታወቅ ነው። ከሰሞኑ የድርጊቱ ፈጻሚ ድርጅት ዋና መሪ ሆኑት አቶ አማኑኤል አንደገለጹት የአማራ ህዝብ ቁጥር 80 ሚሊዮን ነው። የአማራ ልሂቃን ከ1984 ጀምሮ በተለይ በ1999 የህዝብና ቤት ቆጠራ ሪፖርት የተደረገው ህዝባችን ቁጥር በምንም መስፈርት አያሳምንም የሚል አቋም ሲያንጸባርቁ ለዚህም ሸፍጥ ወያኔን ዋነኛ ተከሳሽ አድርገውት ነበር። ዳግም ይቆጠር በሚልም እየሞገቱ ናቸው። ሰምኑን የህወሀት ሊቀመንበር አቶ አማኑኤል ድርጅታቸው የፈጸመውን ሸፍጥ አምነዋል። 55 ሚሊዮን የሚሆነው አማራ ሪፖርት አልተደረገም ነበር ብለዋል። እንደ አማኒኤል መረጃ ባለፈፉት 23 አመታት ከ80 ሚሊይን የአማራ ህዝብ 25 ሚሊዮኑ ብቻ ከበጀት እንሚያገኝ እና ቀሰፈሪውን 55 ሚሊዮን ሀገሪቱ እንደማታውቀው ተረጋግጧል። ለዳግም ቆጠራ @መነሻ የሚሆን መረጃ ነው የሰጡት። "ማን ያርዳ የቀበረ ማን ያውጋ የነበረ" በመሆኑ የመረጃው ታማኝነት ደረጃ ከፍተኛ ነው።

11/07/2026
" የሲቪል ሰርቪስ ተቀጣሪው የሚኖረው አኗኗር እጅግ አስከፊ ነው ! " - የምክር ቤት አባልየምክር ቤት አባል አቶ ባርጤማ ፍቃዱ ምን ጠየቁ ?" ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ይህች ሀገር የሁላችን...
07/07/2026

" የሲቪል ሰርቪስ ተቀጣሪው የሚኖረው አኗኗር እጅግ አስከፊ ነው ! " - የምክር ቤት አባል

የምክር ቤት አባል አቶ ባርጤማ ፍቃዱ ምን ጠየቁ ?

" ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ይህች ሀገር የሁላችንም ቤት ፣ መኖሪያችን ማንም የበኩር ልጅ ማንም የእንጀራ ልጅ መሆን የለበትም፤ እርሶም በዚህ ያምናሉ።

ነገር ግን ዛሬ ዛሬ አንዱ የሚኖርባት ሌላው የሚያኗኑርባት ፤ ኑሮ ዘይቤው የተለየባት የሆነች ሀገር ሆናለች።

በተለይ የሲቪል ሰርቪስ ተቀጣሪው የሚኖረው አኗኗር እጅግ አስከፊ ነው።

በዋጋ ግሽበት፣ በገበያ አለመረጋጋት፣ የቤት ኪራይና የትራንስፖርት ወጪ አቅሉን አስተውት ብቻው ሲናገር የሚጓዘው ህዝብ ቢሮ ገብቶ እንዴት ውጤታማ ስራ ሊሰራ ይችላል ?

ከደመወዙ 35% ግብር ፣ 7% ጡረታ በድምሩ 42% ይቆረጣል። ከ58% ደመወዙ ላይ በእያንዳንዱ በሚሸምተው ሸቀጥ 15% ቫት (VAT) ይቆረጣል። ትራንዛክሽን ላይ ንግድ ባንክ ለሰርቪስና ቫት እያለ ሌሎችም የማይታወቁ ተቆራጮችን ይቆርጣል። ሰራተኛው ለውሃ፣ ለመብራት ለሌሎችም አገልግሎቶች ይቆረጥበታል።

እነዚህ ሁሉ ተዳምረው ኑሮን መቋቋም አቅቶታልና ለዚህ ታጋሽ ሲቪል ሰርቪስ እና አነስተኛ ኑሮ ላይ ላለው ዜጋ ምን ታስቦለታል ? ከሚመሰርቱት መንግሥት ምን እንጠብቅ ?

በዚህ አጋጣሚ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን አመሰግናለሁ። የተማሪዎች ምገባ ከፍተኛ ዋጋ ያለው ተግባር ነው።

በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎችን በቀን ሁለቴ መግቦ ፣ የትምህርት ቁሳቁስ አሟልቶ ማስተማር እጅግ ከፍተኛ ኃላፊነት መወጣት ስለሆነ እውቅና ሊሰጣቸው ይገባል።

ይህ የምግባ ፕሮግራምን የትኛውም ባለሃብት ፣ ሀገር ወዳድ ዜጎች፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፣ ልበ ቀና ዜጎች ሊደግፉት የሚገባ ተግባር ነው። ነገር ግን አዲስ አበባ ያለው ትልቅ ተግባር ሌሎች ክልሎች ሲተገብሩት አይታይም። በሁሉም ክልሎች ወይም በአብዛኛው ክልሎች አልተጀመረም።

ምግብ ማግኘት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ስለሆነ ለዚህ ለምግብ ፕሮግራም በጠቅላይ ሚኒስትሩ በኩል ኢኒቬቲቭ ቢሆን ውጤታማ ይሆናል። ለክልሎች አስገዳጅ ሆኖ ቢቀርብ ምን ይመስሎታል ? "

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ/ም

Address

Addis Abeba
Addis Ababa
43657

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share