Zemen Television

Zemen Television በሀቀኛ መረጃ ትውልድ ይሰራል. የሀገር አንድነት ይሰምራል :: 🇺🇸

ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ የአቋም መግለጫ፤‎*****‎የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የማዕከላዊ ኮሚቴ ከሐምሌ 19 እስከ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ በ...
07/29/2025

ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ የአቋም መግለጫ፤
‎*****
‎የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የማዕከላዊ ኮሚቴ ከሐምሌ 19 እስከ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ፣ በአማራ ክልል፣ በሀገራዊ እና ቀጠናዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሰፊ ወይይትና ግምገማ ያደረገ ሲሆን፣ ይሄን ተከትሎ በልዩ ሁኔታ አቋም የተያዘባቸውን ጉዳዮች በመለየት የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል።

‎1. የአማራ ክልል ወቅታዊ የሰላምና ፀጥታ ሁኔታን በተመለከተ፤

‎በአማራ ክልል ውስጥ ያለው ከፍተኛ የፀጥታ፣ የሰብአዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ተባብሶ እንደቀጠለ ይገኛል። በዚህ ምክንያት በዜጎች ህይወት እና ንብረት ላይ እየደረሰ ያለው ጉዳት አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። በርካታ ንጹሃን ወገኖቻችን ህይወታቸውን እያጡ ሲሆን፣ ብዙወች አካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፣ ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል። የተፈጠረውን ግጭት፣ አለመረጋጋት እና አጠቃላይ የደህንነት ስጋት ተከተሎ የዝርፊያ ወንጀል በስፋት እየተፈፀመ ይገኛል። ስለሆነም እነዚህ የህዝባችንን ሰቆቃ ያራዘሙ የጥፋት ድርጊቶች በፍጥነት እንዲቆሙ አብን በጥብቅ ይጠይቃል።

‎በአሁኑ ወቅት የአማራ ህዝብ በክልሉ ውስጥ ለዘመናት ያላያቸው ከፍተኛ ሰቆቃዎች እና ጥፋቶች እየደረሱበት ነው። በዚህም የአማራ ልጆች ከትምህርት ገበታቸው ተስተጓጉለዋል፣ እናቶችና ህጻናት ከክትባት፣ ገበሬዎች ከእርሻ ስራ እና ከእንስሳት እርባታ ተግባራት፤ ነጋዴዎች ከንግድ እንቅስቃሴ ተሰተጓጉለው እየባከኑ ያለበት አሳዛኝ ሁኔታ ተፈጥሯል። ሴቶች ተደፍረዋል፣ ሰላማዊ ሰወች ታግተዋል፣ ተዘርፈዋል፣ በተኩስ ልውውጥ ሙሉ ቤተሰብ በከባድ መሳሪያ ተቀጥፏል፣ ንጹሀኖች በወጡበት ቀርተዋል። ባጠቃላይ ግጭቱ ክልላዊ ብሎም ሃገራዊ ፈተና የደቀነ በመሆኑ ተሳታፊ አካላቱ፣ የአማራ ህዝብ እና የህዝባችን ወዳጆች በሙሉ በቃ ሊሉት ይገባል።

በዋናነት ለአማራ ህዝብ መሰረታዊ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት እና ዘላቂ ጥቅሙን ለማስከበር ከሰላማዊ ትግል ባሻገር ያለ አዋጪ መንገድ እንደሌለ በግልፅ ሊሰመርበት ይገባል። እስካሁን ባለው የትግል ሂደት ገና እልባት ያላገኙ ጥያቄዎች መኖራቸው ግልጽ ነው። ሆኖም ከችግሮቹ ስፋት እና ውስብስብነት እንዲሁም ከጠላቶቹ ክፋትና ሴራ አኳያ በአንፃሩ አጭር በሚባል ጊዜ ቀላል የማይባሉ ድሎችን ማሳካት ተችሎ ነበር። እነዚህ ድሎች እውን የሆኑት የአማራ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቹ ጋር በተግባቦትና በትብብር ባደርገው ትግል ነው። ስለሆነም በአሁኑ ወቅት የአማራን ህዝብ እና ኢትዮጵያን በቀውስ አዙሪት ውስጥ የማስገባት ዘላቂ ግብ ያላቸው ታሪካዊ ጠላቶች ክልሉን የሴራ ፖለቲካቸው መተወኛ መድረክ አድርገው ለመጠቀም የሚያካሂዱትን የጥፋት ስምሪት የአማራ ህዝብ በግንባር ቀደምነት ሊቃወመው ይገባል።

‎ከዚህ አንፃር በክልሉ ዉስጥ የሚንቀሳቀሱት የታጠቁ ኃይሎች የአማራን ህዝብ የሰላም ፍላጎት አክብረው የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ አብን ጥሪውን ያቀርባል። እንደሚታወቀዉ ባለፉት ዓመታት የአማራ ህዝብ ብሎም መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በከባድ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል። አብዛኞቻችሁ የህዝባችሁን እና የሀገራችሁን ጥሪ በቅን ልቦና ተቀብላችሁ እና በጀግነንት ተሰልፋቸሁ መታገላችሁ ይታወቃል። ነገር ግን በአሁኑ ወቅት የወሰዳችሁት አቋምና የተከተላችሁት የትግል መስመር እንደምታዩት የህዝባችንን ሁኔታ ከድጡ ወደ ማጡ ከማሸጋገርና ይባስ ብሎም ለፀረ-አማራና ፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች መጠቀሚያ ከመሆን ያለፈ ዉጤት የለውም።

ይሄን እውነታ ለመረዳት እና ውሳኔያችሁ በአማራ ህዝብ ላይ ያስከተለውን ቀውስ ለመገምገም ከበቂ በላይ ግዜ አልፏል። ስለሆነም ከምር ግባችሁ የአማራ ህዝብ ደህንነት ከሆነ በህዝባችን ላይ ከእስካሁን በደረሰው ሁለንተናዊ ጉዳት እና በቀጣይ ባለው ክልላዊና ሀገራዊ ስጋት ዙሪያ የተሻለ ግንዛቤ ይዛችኋል ብለን እናምናለን። ከሁሉም በላይ የህዝባችን አሁናዊና የነገ ሁኔታ ሊታያችሁና ሊያሳስባችሁ ይገባል። የሰላም መንገድ ረጅም ቢሆን እንኳ የህዝባችንን ዘላቂ ግብና ፍላጎትን ለማሳካት ብቸኛው አማራጭ መሆኑን በድጋሚ ማስታወስ እንሻለን።

በዚህ ረገድ፤

‎ለመላው የአማራ ህዝብ፦
እንደሚታወቀው ላለፉት በርካታ አሰርት-አመታት በኢትዮጵያ ጠል ሃይሎች የጥፋት ተልዕኮ አማካኝነት የኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ የተለየ ባለእዳ ተደርገህ በመፈረጅህ ከፍተኛና ያልተገባ ዋጋ ስትከፍል መቆየትህ ፀሐይ የሞቀው ሀቅ ነው። ይህን እኩይ የባለእዳነት ትርክትና ጥቃት ለመቀልበስ የተጀመሩ ጥረቶች ሁሉ በጠላት ሴራ እየተጠለፉ ሲዳከሙ ብሎም ሲከሽፉ ማስተዋላችን የትናንት ብቻ ሳይሆን የዛሬም ገጠመኛችን ሆኖ ባጅቷል።

‎በመሰረቱ ህዝባችን ትልቅ ህዝብ ሆኖ ሳለ ጠንካራ አደረጃጀቶችን ፈጥሮ በመታገል ልክ እንደ ጥንቱ ለራሱ ህልውና ብቻ ሳይሆን ሃገርን የሚያፀና ሚና መጫወት እንዳይችል እየተደረገ ያለበት አሻጥር በቃ ሊባል ይገባል። ህዝባችን በተደራጀ ሰላማዊ ትግል ከግብና አላማው መድረስ ይችላል በሚለው ሃቅ ላይ ቅንጣት ጥርጣሬ የለንም።

‎ለመላው ኢትዮጵያውያን፦
ሃገራችን የሰላም አየር አግኝታ በዘላቂ የህዝቧ ጥቅም መረጋገጥ ላይ እንዳታተኩር ፋታ የማይሰጥ የቀውስ አዙሪት ውስጥ እንድትቆይ ማድረግ የሩቅና የቅርብ ታሪካዊ ጠላቶቿ ስትራቴጂካዊ ግብ ሆኖ ቀጥሏል። ከዚህ የጠላት ወጥመድ መውጫ ብቸኛው መንገድ ጠንካራ የሆነ የአንድነት እና የህብረት መንፈስ ብቻ ነው። ትናንት አያት ቅድመ አያቶቻችን የጥቁር ዘር የኩራትና ክብር ምንጭ የሆነውን ድል የማስመዝገባቸው ምስጢር ኢትዮጵያዊ ህብረትና አንድነታቸው ነበር። የወቅቱን የባርነትና የቅኝ ግዛት ጥላ የገፈፉትና ያስወገዱት በህብረታቸው ነበር። የአሁኑ ትውልድም መልካቸውን ቀይረው የገጠሙትን ከትናንት ተንከባላይ ፈተናዎች መሻገሪያ ድልድይ ህብረት ብቻ መሆኑን ላፍታም መዘንጋት የለብንም።

ለመንግስት ሚዲያወች እንዲሁም ለግል ሚዲያዎች፦
እንደሚታወቀው ሃገራችን በዙሪያ መለስ ፈተናዎች ውስጥ እያለፈች ነው። በዚህ አውድ ውስጥ የሚደረጉ የህዝብ ግንኙነትና የመረጃ ስርጭት ተግባራት እንድነትንና ሰላምና አንባሪ መሆን ይጠበቅባቸዋል። ‎ከዚህ አንፃር በአማራ ክልልም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች መሳሪያ ያነሱ ኃይሎች የሰላም መንገድን መርጠውና ሰላምን ተቀብለው በሚመጡበት ወቅት የመንግስት ሚዲያወች ይህንን የሰላም እርምጃ ከማበረታታትና ከመደገፍ ይልቅ አሉታዊና ገፊ የሆኑ አገላለፆችን ከመጠቀም እንዲቆጠቡ በጥብቅ እናሳሰባለን።

ለአብነትም በአማራ ክልል ውስጥ ታጣቂወች ይዘውት የነበረው መንገድ ለህዝባቸው እና ለሃገራቸው የማይበጅ መሆኑን ተረድተው የሰላም መንገድን የመረጡ ወንድሞችና እህቶች ትተውት በመጡት የቀደመ ተግባር "ፅንፈኞች" ተብለው መገለፅ የለባቸውም። በኦነግ ሸኔ ታጣቂዎችም እንዲሁ የሰላምን መንገድ መርጠው ሳለ ከሽብር ድርጅቱ ጋር መፈረጅ የለባቸውም። የሰላምን ጥሪ አዳምጦ አክብሮና ተቀብሎ ወደ ሰላም የሚመጣ ሀይልን አሁንም "ፅንፈኛ" እያሉ መፈረጅ በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን ሰቆቃ እውቅና አለመስጠትና ሰላምንም አለማበረታታት ተደርጎ የሚወሰድ ሀላፊነት የጎደለው ብያኔ ካልሆነ በቀር ሌላ ሊባል አይችልም። ‎በመሆኑም የሚዲያ አካላት በዚህ መሰል ጉዳዮች ላይ የሚኖራቸው የህዝብ ግንኙነት ስራ በጥንቃቄና ከፍተኛ ሃላፊነት በተሞላበት መንገድ እንዲሆን እናሳስባለን።

‎2. ሀገራዊ ሁኔታ፣ የፀጥታ አለመረጋጋት እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች፤

‎ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት የበርካታ ፈተናዎች ማዕከል ሆናለች። የፀጥታ አለመረጋጋት፣ የኑሮ ውድነት እና የማህበራዊ ትስስር መላላት የሀገሪቱን አንድነትና ሰላም አደጋ ላይ ጥለዋል። የዜጎች የኑሮ ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ የመጣ ሲሆን፣ የዋጋ ግሽበት የበርካታ ቤተሰቦችን አቅም አሟጧል። ‎በመሆኑም ከሁሉም ወገን በተለይም ከመንግሶቶ ለሃገራዊ መፍትሄዎች ሁሉ ያላሰለሰ ቁርጠኝነት እንዲኖረው ስንል እንጠይቃለን።

‎ብሄራዊ ምክክር እንደ ስሙ በብሄራዊ ደረጃ ተካሂዶ የሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ተሳትፎ እንዲረጋገጥ አብን ያሳስባል። እውነተኛ እና ሁሉን አቀፍ ውይይት ከሌለ፣ የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላም እና ብልፅግና ማረጋገጥ አይቻልም። ሁሉም የፖለቲካ ኃይሎች እና ባለድርሻ አካላት በሰከነ መንፈስ ተነጋግረው ሀገራዊ መግባባትን እና ዘላቂ መፍትሄዎችን እንዲሹ ጥሪያችንን እናቀርባለን። የዜጎች ሰብአዊ መብት በሀገር ደረጃ እንዲከበር እና ሁሉም ዜጋ የህግ የበላይነት እንዲጠበቅለት አብን አጥብቆ ያሳስባል። የመድብለ ፓርቲ ስርዓት እንዲጠናከር እና ዴሞክራሲያዊ ተቋማት ገለልተኛ ሆነው እንዲሰሩ መንግስት በቁርጠኝነት እና በላቀ ነሳሽነት እንዲሰራ እንጠይቃለን። ዴሞክራሲያዊ ተቋማትን በማጠናከር ሂደቱ ከፓርቲያችን የሚጠበቅን ሚናም ያለማመንታት እንወጣለን።

‎3. ቀጠናዊ ጉዳዮች፣ የአፍሪካ ቀንድ፣ የባህር በር ጥያቄ እና የሻዕቢያ ሰሞነኛ አቋም፣

‎የአፍሪካ ቀንድ አካባቢ የፖለቲካ አለመረጋጋት እና ግጭቶች የተሞላበት ቀጠና ሲሆን፣ ይህ ሁኔታ በኢትዮጵያ ላይ ቀጥተኛ ተፅዕኖ እያሳደረ ይገኛል። የኤርትራና የሱማሊያ ጉዳይ፣ የሱዳን ቀውስ እንዲሁም በሌሎች አጎራባች ሀገራት ያሉ ችግሮች በኢትዮጵያ ውስጣዊ ጉዳዮች ላይ አሉታዊ ተፅእኖ አላቸው። የጎረቤት ሀገራት መረጋጋት ለኢትዮጵያ ሰላም ወሳኝ እንደሆነ አብን በጥብቅ ይገነዘባል። ውስጣዊ አንድነትና መረጋጋት የልማት ፍላጎታችን ማሳኪያ ብቻ ሳይሆን በዚህ አደገኛ ቀጠና ህልውናችንን የማረጋገጫ ፍኖትም ነው።

‎ከዚህም ባሻገር የባህር በር ጥያቄ የሀገሪቱን ህልውና እና ብልፅግና የሚመለከት ወሳኝ ጉዳይ ነው። ይህ ጥያቄ ብሄራዊ መግባባትን ሊፈጥር ይገባል ብለን እናምናለን። ስለሆነም የፖለቲካና ርዕዮት ዓለም ልዩነቶች በዘላቂ ብሄራዊ ጥቅሞቻችን ላይ ጥላ ማጥላት የለባቸውም። በመሆኑም የባህር በር ጥያቄን መላው ኢትዮጵያዊያን እና አደረጃጀቶች ሁሉ ልንታገልለት የሚገባ ብሔራዊ ጥቅማችን ነው ብሎ አብን በፅኑ ያምናል።

‎የባህር በር ጉዳይ የኢትዮጵያ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን የመላው ቀጠና ሰላም እና መረጋጋት ጋር የተቆራኘ መሆኑ ግንዛቤ ሊያዝበት ይገባል። ስለሆነም በዚህ ረገድ የሻቢያ መንግስት ባልተገራ ሁኔታ በሀገራችን የውስጥ ጉዳዮች የሚያድርገውን ጣለቃገብነት፣ በተለይም የሃገራችንን ሰላም ለማናጋት የሚፈጽማቸውን የፕሮፖጋንዳ፣ የሴራ እና ህቡዕ የጥፋት ስምሪቶች ባስችኳይ እንዲያቆም እናሳስባልን።

ምናልባት ሻዕቢያ በሂደት ተገንዝቦ ከጥፋት ድርጊቱ ሊታቅብ ይችል ይሆናል በሚል፣ ካልሆንም ሻዕቢያን በታሪክ ማህደር ለማስቀመጥ፤ ታሪኩን፣ ምግባሩን እና ፍላጎቱን በተመለከተ ቀደም ባሉ መግለጫዎቻችን ላይ በግልጽና በዝርዝር ለኢትዮጵያ ህዝብ ስናስገነዝብ ቆይተናል። ሆኖም አሁንም አፍራሽ ተግባራቱን አጠናክሮ የቀጠለ በመሆኑ በመጨረሻ ለሚከሰተው ጥፋት ሃላፊነት እንደሚወስድ ለማሳሰብ እንወዳለን። አንባገነኑ ሻዕቢያ የያዘው መንገድ ለጭቁን የኤርትራ ህዝቦች የማይጠቅም መሆኑንም አበክረን መግለፅ እንፈልጋለን።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)

ሐምሌ 21 ቀን፣ 2017 ዓ.ም

07/28/2025

“ጦርነቱ በቲማቲም እንኳን ቢሆን አልዋጋም አሜባ አለብኝ”

የትግራይ ወጣት

የትግራይ ታዋቂ ሰዎች ፣ባለሀብቶች፣ በተለይ አርቲስቶች፣ በአሁን ሰአት ወጣቱና ህዝቡ ድምጽ ሁኑን ጦርነት አንፈልግም በሚልበት ሰዓት የህዝባቸውን ጥያቄ በተገቢው ሁኔታ ሲያስተጋቡ አይታይም። ህዝቡ ብቻውን ነው የቆመው። በተለይ የትግራይ አርቲስቶች ጦርነት ሲነሳ ጦርነቱን በዘፈን አሟሙቀው እነሱ ዝናና ገንዘብ ሲያግበሰብሱ እንጂ ከህዝባቸው ጎን ቆመው ጦርነትን ሲቃወሙ አይታይም። ህዝብ ይሄንንም ይታዘባል። ህዝቡ የህውሀትን አፈሙዝ ሳይፈራ “አታዋጉን” እያለ ሲጮህ ድምፅ ሳትሆን ጦርነት ሲቀሰቀስ “ጀጋኑ” እያልክ ብትዘፍ ለህዝቡ ጠብ የሚልለት ነገር የለም። ጦርነቱ በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገባደድም “ጄኖሳይድ ተፈፀመ” እያልክ ብታለቅስ ለቅሶህ ሁሉ የአዞ እንባ ይባላል። ጀግና ማለት ጦርነት ላይ ቤንዚን የሚያርከፈክፍ ሳይሆን ጦርነትን ለማስቆም የሚሰራ ነው። ስለዚህ ሁሉም ሰው ከትግራይ ህዝብ ጎን መቆም አለበት። የተቸካዩ አሮጌ የህውሀት ቡድን እብደት እንዲያበቃ ሁሉም አካል መረባረብ አለበት።

እኔ በበኩሌ ከጦርነት በፊት ስለሰላም እሰብካለሁ። ጦርነት እንዳይከሰት እሰራለሁ። ወደጦርነት ከሚያመሩ ቅስቀሳዎች እትቀባለሁ። ይህንን ሁሉ አልፎ ጦርነት ከመጣ ግን ከእናት ሐገሬ ጎን እሰለፋለሁ! ኢትዮጵያም በድል አሸንፋ ትወጣለች። የምናዝነው 20 ለማይሞሉ ሰዎች እብደት ምስኪኑ ህዝብ ዋጋ በመክፈሉ ብቻ ነው።

አልዩ አምባ:ቀዳማይ Ethiopian revenue center
07/14/2025

አልዩ አምባ:ቀዳማይ Ethiopian revenue center

07/08/2025

" ኢትዮጵያ ስለምንና እንዴት የባህር በር አጣች? የፖለቲካ ሳይንስ ተባባሪ ፕሮፌሰሩ መልስ አላቸው .Welcome to **Addis Media Network**, your premier source for all things Addis Ababa! 🌍 ...

በቀጣይም ተመሳሳይ ነው ውጤቱ። አሁንም ወያኔ እያሟሟቀ ያለው ጦርነት ለትግራይ ህዝብ አስከሬን ነው የማያተርፍለት።
07/06/2025

በቀጣይም ተመሳሳይ ነው ውጤቱ። አሁንም ወያኔ እያሟሟቀ ያለው ጦርነት ለትግራይ ህዝብ አስከሬን ነው የማያተርፍለት።

በምስራቅ ጎጃም ዞን በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ እና በአዋበል ወረዳ በትይንተ-ህዝብ የሰላም ጥሪ ቀርቧል። በቦታው የተገኘው ዘጋቢያችን የትይንተ-ህዝብ ተሳታፊዎችን ዋቢ አድርጎ እንደገለጸው በወ...
07/04/2025

በምስራቅ ጎጃም ዞን በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ እና በአዋበል ወረዳ በትይንተ-ህዝብ የሰላም ጥሪ ቀርቧል። በቦታው የተገኘው ዘጋቢያችን የትይንተ-ህዝብ ተሳታፊዎችን ዋቢ አድርጎ እንደገለጸው በወረዳዎቹ የሚደረገው የነፍጥ እንቅስቃሴ ጫና፣ በህዝብ ላይ የሚጣለው ቀረጥ፣ የአገልግሎቶች መቋረጥ እና የዘፈቀደ ፍርድ እርሸና የአርሶ አደሩን ኑር የምድር ሲኦል አድርጎታል።

የሸኔ ቡድን ጫካ በቃኝ ብሎ እጅ እየሰጠ ነው👉 በምስራቅ ጉጂ ዞን ሰባቦሩ  ወረዳ  አዴከላላ ቀበሌ  የሸኔ የሽብር ቡድን ታጣቂ እጃቸውን ሰጥተዋል።    1. ጃል  እፋፍ ገዳ  የቢፍቱ በሪ ...
06/25/2025

የሸኔ ቡድን ጫካ በቃኝ ብሎ እጅ እየሰጠ ነው
👉 በምስራቅ ጉጂ ዞን ሰባቦሩ ወረዳ አዴከላላ ቀበሌ የሸኔ የሽብር ቡድን ታጣቂ እጃቸውን ሰጥተዋል።
1. ጃል እፋፍ ገዳ የቢፍቱ በሪ በርጌድ 1ኛ ሻለቃ አዛዥ
2. ጃል ኑቤካ ሰባ የአጃቦቹ አስተባባሪ
3. ጃል ሙዲ መሃመድ አጃቢ
4. ጃል እፈባሲ ሰባ 3ኛ አጃቢ ሲሆን
👉 የትጥቅ ሁኔታ ፦ - ክላሾች + የክላሽ ጥይቶች + የእጅ ቦምቦች + የወገብ ትጥቆችን በመያዝ እጃቸውን ሰጥተዋል።

የኦነግ ፖለቲካ የመማር እና የፖለቲካ ንቃት መሻሻል አሳይቷል!      # # # # ******** # # # # # # # #******** # # # # # #እንደሚታወቀው የኦነግ ፍልስፍናዊ መሰ...
06/23/2025

የኦነግ ፖለቲካ የመማር እና የፖለቲካ ንቃት መሻሻል አሳይቷል!
# # # # ******** # # # # # # # #******** # # # # # #
እንደሚታወቀው የኦነግ ፍልስፍናዊ መሰረት ብሄራዊ ጥላቻ፣ ነጠላ ትርክትና የበደል ታሪክ አስተሞሮ በመሆኑ በርካታ ማንነት ተኮር ወንጀሎችን ፈጽሟል። የሻቢያና የወያኔ የክፋት አጀንዳ ተሸካሚም ሆነ የኖረ ነው። በዚህም የተነሳ ያከናወነው የትጥቅ ትግል በሲቪሊያን ላይ ሰቆቃ ከማድረስ ውጭ ለስልጣን ሳያበቃው ቆይቷል። ሆኖም በሂደት ንቃት እየጨመረና የፖለቲካ ካርድ ከሚያስጥል ፕሮፓጋንዳ እየተቆጠበ እንደመጣ የሚያሳዩ ሶስት (3) ምክንያቶችን መጥቀስ ይቻላል።

አንደኛ ኦነግ በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች ንጹሀንን ገድሎ፣ አፈናቅሎና ዘርፎ ሲያበቃ ከደሙ ንጹህ ነኝ የሚል መግለጫ በማውጣት የሚቀድመው የለም። በሌሎች በዋናነት በመንግስታዊ ቡድኑ ያመሀኛል። አንዳንዴ በመንግስት ውስጥ በሰረጉ አባላቱም በኩል ብሄር ተኮር ጥቃትን በማስጀመር አስፋፍት ያስቀጥልና ድርጊቱን አውጋዥ ሆኖ ይቀርባልም። በዚህ መልኩ በአለም አቀፍ ወንጀል ሊያስጠይቀው የሚችል ነጥብ ላመጣል ይጥራል። ሁለተኛ የሰላም እና ድርድር ሀሳብ ሲቀርብለት "አልደራደርም- ስልጣን የመወስደው በጦርነት ብቻ ነው" የሚል አቋም በማራመድ ነጥብ አይጥልም። ማህበረሰቡ መደራደር ባይሻ እንኳ አልደራደርም ከማለት ይልቅ ጋሬጣ የሆኑ ቅድመ-ሁኔዎችን የህዝብ ጥያቄ አስመስሎ በማቅረብ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለፍትህና ለሰብአዊነት የሚታገል መስሎ ይቀርባል።የሽብር ድርጊት ቢፈጽምም ለዚህ ማረጋገጫ ከሚሆኑ መግለጫዎች ይቆጠባል።

ሶስተኛ ኦነግ-ሼኔ ራሱን የኦሮሞ ተወካይ አስመስሎ ያቅርብ እንጂ ከራሱ ተገንጥለው ሰላማዊ መንገድ ከመረጡ አካላት ጋር በመፋተግ ብዙ ጊዜ አያጠፋም። ለምሳሌ ህጋዊ ሰውነት ወስዶ ስልጣን የተጋራው የኦነግ ክንፍ ጉባኤ ሲያደርግ እና በአዲስ አበባ ዋና መስሪያ ቤቱን ሲያስመርቅ በጫካ ያለው ቡድን ሲቃወም አናይም። በሀገር ውስጥና በድያስፖራ ያሉ የኦነግ ደጋፊዎች ዩቲዩብ ላይ እየወጡ ስልጣን የተጋራውን የነቀጀላን ኦነግ ሲያወግዙ አይውሉም። ይፍረሱ የሚል ዘመቻማ የለም-በአንጻራዊነት ተቋም ለማፍረስ የመክለፈለፍ ልማድ እየተገታም ይመስላል። እነከማል ገልቹ እና ወደ ቤተ-መንግስት ቀርበዋል የተባሉትን እነዲማ ነጋዎን፣ ሌንጮ ባቲን ወዘተ በጠላትነት ፈርጆ የማጥፋት የሚዲያ ዘመቻስ አለ? ሌላው ቀርቶ የሽምቅ ውጊያ በቃኝ ብሎ ከጃል መሮ የተገነጠለው የጃል ሰኚ ቡድን ከመሮና ከደጋፊዎቹ የተሰነዘረበት ውግዘት አናሳ ነው። ቶሎ በርዷል። እንዲሁም የሰላም ጥሪ የሚያቀርቡ የፖለቲካ ኃይሎችን በባንዳነት፣ በከሀዲነት፣ በሆዳምነት የመፈረጅ ሁኔታ እምብዛም ነው ወይም በአንጻራዊነት በተለይም በአማራ ካለው ሁኔታ አንጻር የማጠልሸት ፖለቲካ ቀንሷል ማለት ይቻላል።

ይህን የመማርና የመሰልጠን ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ ሁኔታ ሀገራዊ ሰላምንና ፍትህን ለማምጣት ምን ፈይዷል? እና በጥላቻ ትርክት የተቃኘውን የፖለቲካ አየር ለውጧል ወይ? ወዘተ ከሚሉ ጥያቄዎች አንጻር ከመዘነው ፋይዳው ሊቀልብን ይትላል ይሆናል።

የጎሳ ወረዳ አስተዳደር፣ የጉሳ  ብሄር ልዩ ወረዳ፣ የብሄር ዞን፣ የብሄር ክፍለ-ከተማ የብሄረሰብ ክልል የመመስረት ጥያቄ  እንደአሸን እየተፈሉ ናቸው። ከጋሞ ዞን ሁለት ጎሳዎችና እና አንድ ...
06/18/2025

የጎሳ ወረዳ አስተዳደር፣ የጉሳ ብሄር ልዩ ወረዳ፣ የብሄር ዞን፣ የብሄር ክፍለ-ከተማ የብሄረሰብ ክልል የመመስረት ጥያቄ እንደአሸን እየተፈሉ ናቸው። ከጋሞ ዞን ሁለት ጎሳዎችና እና አንድ የራሱ ቋንቋ ያለው ብሄረሰብ የማንነት አስተዳደር አስመላሽ ፖርቲዎች እና ኮሚቴዎች አደራጅተው በመበቀት ላይ ናቸው። ይከጉራጌ ዞን ማረቆ፣ መለኔ እና ቀበና በረዶ የተቀላቀለበት የወሰን ማስመለስ እና የመገንጠል ጥያቄ አላቸው። በአማራ ክልል የወያኔ እጅ ስራ የሆነው የቅማንት ኮሚቴ በአንድ በኩል በክላሽ በሌላ በኩል በፓርቲ የድጎማ በጀት ያለው ወረዳ እና ክልል አማረኝ እያሉ ይገኛሉ። ኦሮሚያ ትግረ ወርጅን ጨምሮ ብዙዎችን በዝሆን ኩምቢ ገላምጣ የማንነት ዘጭ ዘጭን ጸጥ ረጭ በማድረጓ ጫጫታ አጥፍታለች።
ምንጫችን በዛሬው አለት በአብይ አህመድ የተመራው የፓርቲዎች ውይይት ነው።

በሕንድ የአውሮፕላን መከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ የአንድ ቤተሰብ አባላት …አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዶክተር ፕራቲክ ጆሺ ኑሮን ለማሸነፍ ከባለቤቱ እና ሶስት ልጆቹ ...
06/13/2025

በሕንድ የአውሮፕላን መከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ የአንድ ቤተሰብ አባላት …

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዶክተር ፕራቲክ ጆሺ ኑሮን ለማሸነፍ ከባለቤቱ እና ሶስት ልጆቹ ተለይቶ ለስድስት ዓመታት ኑሮውን በእንግሊዝ ለንደን አድርጎ ነበር፡፡

በጊዜ ሒደት ውድ ባለቤቱን እና ልጁቹን ወደ ለንደን አምጥቶ ደስተኛ ሕይወት የመኖር ሕልምን ሰንቆ ብዙ ችግሮችን አሳልፏል፡፡

ከዓመታት ውጣ ውረድ በኋላም አስፈላጊውን ሁሉ በማሟላት ቤተሰቦቹን ወደ ለንደን የመውሰዱ እቅድ እውን ሆነ፡፡

ባለቤቱ፣ ሁለት መንታ ልጆችና አንድ ሴት ልጁም በለንደን የተሻለ ሕይወት ለመኖር ሒደቱ ማለቁን ሲሰሙ ተደሰቱ፤ ለጉዞም መሰናዳት ጀመሩ፡፡

በምትኖርበት አካባቢ እውቅ የሕክምና ባለሙያ የሆነችው ባለቤቱ ዶክተር ኮሚ ቪያስ ከጉዞ ሁለት ቀናት በፊት ሥራዋን በፈቃደኝነት ለቀቀች፡፡

ከዚያም ቤተሰቡ ወደ ለንደን ለመብረር ሻንጣውን ሸከፈ፡፡ በለንደን በአዲስ መንፈስ አዲስ ሕይወት ለመጀመር በማለምም ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ተሰናበቱ፡፡

የአንድ ቤሰተብ አባላቱ ለዓመታት የጠበቁት ቀን ደርሶም በጉጉትና በተስፋ ወደ ለንደን ለመብረር በአሕመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተዋል፡፡

የበረራ ቁጥሩ 171 በሆነው አውሮፕላን ከገቡ በኋላም በረራ ከመጀመራቸው በፊት ከታች የተቀመጠውን በራሳቸው የተነሳ ፎቶ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው አጋሩ፤ ወዳጅ መዘዶቻቸውም መልካሙን ሁሉ ተመኙሏቸው፡፡

ይሁን እንጂ የተሳፈሩበት አውሮፕላን በረራ በጀመረ 30 ሰከንዶች ውስጥ በአሰቀቂ ሁኔታ ተከሰከሰ፤ ዶ/ር ፕራቲክ ጆሺ፣ ባለቤቱ፣ ሁለት መንታ ወንድ እና አንዲት ሴት ልጆቹ በአደጋው ሕይወታቸው አለፈ፡፡

የዶ/ር ፕራቲክ ጆሺ እና ቤተሰቦቹ በለንደን አብሮ የመኖር ሕልምም በአሳዛኝ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ሆነ፡፡

ከምዕራብ ሕንድ አሕመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ 242 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ ለንደን በመብረር ላይ የነበረ የሕንድ አውሮፕላን ትናንት የመከስከስ አደጋ ያጋጠመው መሆኑ ይታወቃል።

Fbc

በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ አብርሃ እና አጽበሃ እና ክንደያ ትምህርት ቤቶች 20 ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እንዳይፈተኑ መደረጉን በቦታው ያሉ ታማኝ ምን...
06/11/2025

በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ አብርሃ እና አጽበሃ እና ክንደያ ትምህርት ቤቶች 20 ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እንዳይፈተኑ መደረጉን በቦታው ያሉ ታማኝ ምንጮች ጠቁመዋል። ሀወሀት በሚል ይጠራ የነበረው ድርጅት ትግራይን የአፈና ደሴት አድርጓት ነው የፈረሰው።

Address

Fairyland
Silver Spring, MD
20904

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share