Zemen Television

Zemen Television በሀቀኛ መረጃ ትውልድ ይሰራል. የሀገር አንድነት ይሰምራል :: 🇺🇸

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ ከአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን)  የተላለፈ  መልዕክት *****ታላቁ የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያዊያንን የመልማት መብት ከማረጋገጥ አኳያ ካለው...
09/11/2025

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ ከአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) የተላለፈ መልዕክት
*****
ታላቁ የህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያዊያንን የመልማት መብት ከማረጋገጥ አኳያ ካለው ትርጉም ባሻገር ሀገራዊ እና አህጉራዊ ደማቅ ምልክት ነው። ግድቡ ከጥንስሱ እስከመቋጫው ያሉ ሂደቶች ራስን የመቻልና የሉአላዊነታችን ምልክት እንዲሁም የኢትዮጵያዊያን የህብረብሄራዊ ትብብር አርማችን በመሆኑ ከፍ ያለ ትርጉም የምንሰጠው የትውልዱ ሜጋ ፖሮጀክት ነው።

በትውልድ ቅበብሎሽ የታነጸ፤ ጽኑዎች ብቻ ሊቋቋሟቸው የሚችሉ የማይቆረጡ ፈተናዎችን አልፈው ኢትዮጵያዊያን እውን ያደረጉት እና ለቀጠናው ብሎም ለአፍሪካዊያን የልማት ምልክት ከመሆኑ አንጻር የዚህ ትውልድ ዳግማዊ አድዋ ተደርጎ የሚወሰድ የታሪክ እጥፋት ነው።

የኢትዮጵያ ህዝብ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አጠናቆ ለምርቃት ሲያበቃ ቀጠናዊ ፋይዳ ያላቸው የልማት አውታሮችን የመገንባት እና አለም አቀፍ ሀብቶችን አልምቶ በፍትሀዊነት የመጠቀም እምቅ አቅሙን ለመላው አለም የተግባር ትምህርት እያስተማረ እንደሆነ አብን ይገነዘባል።

በግድቡ የግንባታ ሂደቶች ውጫዊና ውስጣዊ ተግዳሮቶች በገጠሙ ወቅት ገቢራዊ የተደረጉ ስትራቴጂዎች፣ አፍሪካዊና ሰላማዊ የህግና የፖለቲካ ጥበቦችም ከዚሁ ጋር አብረው የሚታዩ ናቸው። ውጤቱም የቀጠናውን የውሀ ፖለቲካ የወደፊት እጣፈንታን የሚወስን ሆኗል።

በዚህ ሂደት ለምርቃት የበቃው የህዳሴ ግድብ አንዱ የዘመናችን አንጸባራቂ ድል ስለሆነ የዚህ ስኬት ባለቤት ለሆነው ትውልድ አብን ምስጋና ያቀርባል።

በመሆኑም ታላቁ የህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያዊያን እና መላ አፍሪካዊያን ዘመኑን የዋጁ ድርብርብ ብሄራዊና አህጉራዊ ድልችን ለማስመዝገብ የተግባርና የሞራል ስንቅ ሆኖ እንደሚያገለግል እንተማመናለን::

አለኝ የሚለውን ሁሉ አዋጥቶ የጋራ አሻራውን ላሳረፈው የጽናት ተምሳሌት ለሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ እንኳን ለዚህ የድል በአል አደረሰህ እያልን የግድቡ ግንባታ ተጠናቆ ለምርቃት እንዲበቃ ከኢትዮጵያ ጎን ለተሰለፉ- የአፍሪካ ህብረትን የመሳሰሉ ተቋማት እና ለመላው አለም የዲፖሎማሲ ማህበረሰብ አባለት አክብሮታዊ ምስጋና እናቀርባለን። አባይን ስንገድብ፤ ሀገራዊ የውስጥ ሰላማችንን በማደፍረስ ልማት እንዳናስብና በድህነት እንድንቆይ አልመው ይሰሩ ለነበሩ በተለይ ግብጽን መሰል ውጫዊ ሀይሎች የሽንፈት ጽዋ የተጎነጩበት መሆኑን በማወጅ፤ ለውስጣዊ ሰላማችን መመለስ ደግሞ ሁላችንም በተለይም መንግስት ከመቸውም ግዜ በላይ ቁርጠኛ መሆን ይጠበቅበታል።

እንኳን አደረሰን፤ እንኳን ደስ አለን!
ሰለም ለኢትዮጵያ!

ጳጉሜን 04፥ 2017 ዓ.ም

የዓለምን ትኩረት የሳበው የአሜሪካዊው ቲክቶከር  የሕዳሴ ግድብ ዘገባበሰዓታት ውስጥ ከ11 ሚ. በላይ ሰዎች ተመልክተውታልከ17 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሉትና በቅፅል ስሙ ‘ኒውስ ዳዲ’ በመባ...
09/10/2025

የዓለምን ትኩረት የሳበው የአሜሪካዊው ቲክቶከር የሕዳሴ ግድብ ዘገባ

በሰዓታት ውስጥ ከ11 ሚ. በላይ ሰዎች ተመልክተውታል

ከ17 ሚሊዮን በላይ ተከታዮች ያሉትና በቅፅል ስሙ ‘ኒውስ ዳዲ’ በመባል የሚታወቀው አሜሪካዊው ቲክቶከር ዲለን ፔጅ፣ ስለሕዳሴ ግድብ የሠራው ዘገባ የዓለምን ትኩረት መሳብ ችሏል።

ፈጣን በሆኑ የዜና ዘገባዎቹ፣ በአጭርና በቀላል አቀራረቡ ታዋቂ የሆነው ዲለን ፔጅ፣ ከሰዓታት በፊት በቲክቶክ በለቀቀው በዚህ ቪዲዮ የግድቡን ከፍተኛ የኃይል ማመንጨት አቅምና ለሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን የሚሰጠውን ጠቀሜታ አሳይቷል።

ይህ የዲለን ፔጅ አጭር ዘገባ በተለቀቀ በሰዓታት ውስጥም በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ ከ11 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ተመልክተውታል።

“ዛሬ በአፍሪካ ውስጥ ታሪክ ተሠራ” በማለት የጀመረው የዲለን ፔጅ ዘገባ፣ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ ለልማት ምን ያህል ወሳኝ እንደሆነ አስረድቷል።

ዲለን ፔጅ አያይዞም፤ የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መመረቅ በኢትዮጵያ አሁን ያለውን የኤሌትሪክ አቅም በእጥፍ እንደሚያሳድግ ገልጾ፣ በዓለም ከሚገኙ 20 ትላልቅ ግድቦች አንዱ እንደሚሆንም ገልጿል።

ይህንን መረጃውን እስካሁን ከ1.3 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ወድደውለታል (ላይክ አድርገውለታል)።

ቲክቶከር ዲለን ፔጅ የሕዳሴ ግድብን በተመለከተ እንዲዘግብ ኢትዮጵያውያን ቲክቶከሮች በዘመቻ መልክ ከፍተኛ ጥቆማ አድርገውለት የነበረ ሲሆን፤ ያንን ተቀብሎ ዘገባውን ለመሥራት ችሏል።

Ebሲ

09/09/2025
09/01/2025
የስራ ማስታወቂያ እንሆ
08/19/2025

የስራ ማስታወቂያ እንሆ

የስራ ማስታወቂያ ከአመልድ ኢትዮጵያ ORDA Ethiopia
08/19/2025

የስራ ማስታወቂያ ከአመልድ ኢትዮጵያ
ORDA Ethiopia

✿ የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ 32 የስራ መደቦች ለ 150+ ክፍት ቦታዎች የስራ ቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል። ኮሚሽኑ የስራ መደቦቹን አስመልክቶ በሰጠው ማብራርያ መሰረት:-- ምዝገባው...
08/19/2025

✿ የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ 32 የስራ መደቦች ለ 150+ ክፍት ቦታዎች የስራ ቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል።

ኮሚሽኑ የስራ መደቦቹን አስመልክቶ በሰጠው ማብራርያ መሰረት:-

- ምዝገባው ከማክሰኞ ነሐሴ 13/2017 ዓም ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ የስራ ቀናት ይቆያል።

- ምዝገባው በሁለት አይነት መንገድ ይካሄዳል በገጽ ለገጽ እና በኦንላይን።

- ምዝገባውን ለማካሄድ ስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ያዘጋጀው የኦንላይን ምዝገባ ሊንክ አለ።

በመሆኑም መስፈርቱን የምታሞሉ በአካል መስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ፍላሚንጓ ሬስቶራንት 200 ሜትር ገባ ብሎ አዲስ አባባ ኤግዚብሽን ማዕከል ጀርባ ብሔራዊ ት/ቤት ውስጥ ከማክሰኞ ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም. ምዝገባ ይጀምራል።

📌በኦላይን በዚህ ሊንክ👉 https://effoysira.com/ethiopian-civil-service-commission-vacancy

የመረጃው ምንጭ:- Civil Service Commission

ሙሼ ሰሙ እንደፃፉት!...መንግስት በአዲሱ የደሞዝ ጭማሪ ምክንያት ለ160 ቢለየን ብር ተጨማሪ ወጭ እንደሚዳረግ ገልጿል። እስኪ የጭማሪውን ፋይዳ ለመረዳት ቁጥሮችን በአንጻራዊ ስሌት እናጢናቸ...
08/19/2025

ሙሼ ሰሙ እንደፃፉት!...

መንግስት በአዲሱ የደሞዝ ጭማሪ ምክንያት ለ160 ቢለየን ብር ተጨማሪ ወጭ እንደሚዳረግ ገልጿል። እስኪ የጭማሪውን ፋይዳ ለመረዳት ቁጥሮችን በአንጻራዊ ስሌት እናጢናቸው።

ቋሚ ደሞዝተኛው ገንዘቡ ኪሱ ከመግባቱ በፊት በገቢ ግብር ምክንያት ዝቅተኛው ተከፋይ 15% ከፍተኛው ደግሞ 35% ይቆረጥበታል። ዝርዝሩ ውስጥ መግባት ስለሚያዳግት አማካዩን ቁጥር እንወሰድ።

አማካዩ (15+35)/2 = 25% ይሆናል። ወደፊት እድሜውና ጤናው ከፈቀደለት የጡረታ ተከፋይ የሚያደርገው ቢሆንም ዛሬ ላይ ለጡረታ 7% ከደሞዙ በቀጥታ ይቆረጥበታል። 25%+7% = 32% ይሆናል።

160,000,000,000*0.32= 51,200,000,000 ይሆናል። ይህ ማለት ሃምሳ አንድ ቢሊየን 200 ሚሊየን ብር የደሞዝ ጭማሪው ተቀጣሪው እጁ ከመድረሱ በፊት ወደ መንግስት ካዝና ይመለሳል። በደሞዝ መልክ የሚከፋፉለው ቀሪም 108,800,000,000 ብር ይሆናል

ደሞዙ እጁ ላይ ከገባ በኋላ ደግሞ በሚሸምተው ቁሳቁስና በሚገዛው አገልግሎት ላይ 15% ቫት ይከፍላል። 108,800,000,000 *0.15 = 16,320,000,000 ይሆናል።

ይህ ማለት ደግሞ ከ160 ቢሊየን ብር ጭማሪ ውስጥ ደሞዝተኛውን ሳያገለግል በገቢ ግብር፣ በጡረታና በቫት ብቻ ወደ መንግስት ካዝና ተመልሶ የሚገባው ብር 67,520,000,000 ሲሆን ጭማሪው ደግሞ 92,480,000,000 ብር ይሆናል።

በመቀጠል ቀሪዎቹን ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ የግብር ዓይነቶች እናንተው አስሏቸው። ፕሮፐርቲ ታክስ (1%)፣ ተርን ኦቨር ታክስ(2%)፣ ትራንዛክሽን ታክስ (0.1% እስከ 1.5%) ....

ከዚህ ሁሉ ቅንስናሽ በኋላ የሚገኘው የደሞዝ ጭማሪ ኢሚንት ቢሆንም አይጠቅምም ማለት በእግሩ ተጓጉዞ፣ በቀን አንዴ ቀምሶ ከሚያተርፋት "ደሞዙ" ላይ በየእለቱ ለልጆቹ ደረቅ ዳቦ የማቅረብ ግዴታ የተጣለባትን ቋሚ ደሞዝተኛ ፈተናና መከራ በቅጡና በልኩ አለመረዳት ይሆናል።

ተወደደም ተጠላ፣ አነሰም ተከመረ ጭማሪው ጎዳና ለመውጣት እየተንደረደረ የነበረውን ቋሚ የመንግስት ደሞዝተኛ እንደሚደጉምና አንድ ቀዳዳ እንደሚደፍንለት ጥርጥር የለኝም። ደሞዝ መቼም በቂ ሆኖ አያውቅም። በቂ ካልሆነ ደግሞ ጭማሪው ይቅር ለማለት ቋሚ ደሞዝተኛውን ከነ መከራው እሱና ቤተሰቡን ሆኖ መገኘትን ይጠይቃል።

የራያ መኾኒ ህዝብ ህወሓትን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ በማካሔድ ላይ ይገኛል‼️
08/19/2025

የራያ መኾኒ ህዝብ ህወሓትን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ በማካሔድ ላይ ይገኛል‼️

መልካም ዜና!237 የመንግስት የሥራ ቅጥር ለሥራ ፈላጊዎች ! የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት በተለያዩ የሥራ ዘርፎች በቋሚ ቅጥር፣ በኮንትራት ቅጥር እና ከተለያዩ የመን...
08/19/2025

መልካም ዜና!

237 የመንግስት የሥራ ቅጥር ለሥራ ፈላጊዎች !

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት በተለያዩ የሥራ ዘርፎች በቋሚ ቅጥር፣ በኮንትራት ቅጥር እና ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት በዝውውር ከዜሮ ዓመት እስከ አስር ዓመት የስራ ልምድ ያላቸውን ሰራተኞች አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

በመሆኑም በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በለማው የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (E-LMIS) በኩል የቅጥር ሂደቱ የሚፈፀም ሲሆን ከመላ የሀገሪቱ ክፍሎች 237 መስፈርቱን የሚያሟሉ ብቁ ሰራተኞች ይፈለጋሉ።

ስለሆነም የዚህ ሥራ እድል ተጠቃሚ ለመሆን lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ ወረዳ/ቀበሌ የአንድ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር/ labor ID/ ይዛችሁ በዚህ ማስፈንጠሪያ (https://forms.gle/AMm2LCHBvdqMwW5AA) ላይ በመገባት ትክክለኛ የትምህርት፣ የስራ እና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎቻችሁን በማሰገባት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። ይህ ማስጣውቂያ ከወጣበት ከነሀሴ 13 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ድረስ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

መልካም ዕድል!

Address

Fairyland
Silver Spring, MD
20904

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share