Zemen Television

Zemen Television በሀቀኛ መረጃ ትውልድ ይሰራል. የሀገር አንድነት ይሰምራል :: 🇺🇸

የዛሬ አምስት አመት በወያኔ የተጨፈጨፈው የመከላከያ ሰራዊት የትግራይ አረጋውያንን ሰብል ሲያጭድ ሲከምር የዋለን የመከላከያ ሰራዊት ሌሊት ረሸኑት። ግን አነስዩም መስፍን አነአባይ ወልዱ በኢት...
11/03/2025

የዛሬ አምስት አመት በወያኔ የተጨፈጨፈው የመከላከያ ሰራዊት
የትግራይ አረጋውያንን ሰብል ሲያጭድ ሲከምር የዋለን የመከላከያ ሰራዊት ሌሊት ረሸኑት። ግን አነስዩም መስፍን አነአባይ ወልዱ በኢትዮጵያዊያን የፍትህ ሰይፍ እጃቸውን አግኝተዋል።

የባህር በር ያጣነው ተገቢ ሥልጣን ባለው አካል እስካልሆነ ድረስ ቅቡልነት አይኖረውም ******************** የባህር በር ያጣነው ተገቢ ሥልጣን ባለው አካል እስካልሆነ እና በሕገ መ...
11/02/2025

የባህር በር ያጣነው ተገቢ ሥልጣን ባለው አካል እስካልሆነ ድረስ ቅቡልነት አይኖረውም
********************

የባህር በር ያጣነው ተገቢ ሥልጣን ባለው አካል እስካልሆነ እና በሕገ መንግሥት እስካልተደገፈ ድረስ ቅቡልነት አይኖረውም ሲሉ የሕግ አማካሪ እና ጠበቃ አቶ አንዱዓለም በዕውቀቱ ተናገሩ።

ቀይ ባህርን ያጣንበትን መንገድ ማሰብ መጀመራችን የባህር በሩን መልሰን የምናገኝበትን መንገድ የሚያመለክት እንደሆነም ገልጸዋል።

በኢቢሲ ቅዳሜ አመሻሽ ፕሮግራም ላይ በእንግነት ቀርበው ሐሳባቸውን ያካፈሉት የሕግ አማካሪው፣ አሰብን ያጣንበት መንገድ በሕጋዊ አግባብ ካልሆነ የጥያቄው ተገቢነት ከዚህ ይመነጫል ብለዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት ያለው መሆኑን አንሥተው፣ “የሀገርን ዳር ድንበር የሚያህል ነገር ተላልፎ የተሰጠበት መንገድ የሚያሳየው ሰነዱ የት አለ?” ተብሎ መጠየቁ አግባብነት እንዳለው ጠቁመዋል።

በዓለም አቀፍ ሕግ አንድ መንግሥት ያደረገውን ስምምነት ቀጥሎ የሚመጣው መንግሥት አልቀበለውም ማለት እንደማይችል ገልጸው፣ ሰነዱ ቢኖር እንኳን የሰነዱን ሕጋዊነት በመፈተሽ የሄደበትን ሕጋዊ መሠረት፣ ‘ብሔራዊ ጥቅምን አስጠብቋል ወይ?’ የሚለው መፈተሽ ተገቢ እና ትክክለኛ ነው ብለዋል።

“ቀይ ባህርን ያጣንበትን ውሳኔ የወሰነው ካቢኔው ነው? ወይስ ምክር ቤት ነው? የሚለውን ለማወቅ ስንፈትሽ አንድም ሰነድ ማግኘት አልቻልንም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በፓርላማ ማንሣታቸው ይታወሳል።

ኢትዮጵያ በፍትሕ እና ርትዕ ላይ ተመሥርታ የጠየቀችው የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ዓለም አቀፍ ሕጉ የሚደግፈው እና ቅቡልነት ያለው እንደሆነም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በሰጥቶ መቀበል መርሕ ላይ ተመሥርታ ያቀረበችው የባህር በር ጥያቄ አሁንም ሰላማዊ ሂደቱን ተከትሎ መቀጠል እንዳለበ አቶ አንዱዓለም ገልጸዋል።

በመሐመድ ፊጣሞ

"ጦርነት እንዲጀመር አልፈልግም፤ ከተጀመረ ግን አሰብ ደርሶ የሚመለስ የኢትዮጵያ ወታደር የለም!" _ ጀነራል ሰሞራ የኑስጀነራሉ ከሰሞኑ የአፍሪካ ቀንድ የውጥረት ምንጭ የሆነው የቀይ ባህር ጉ...
11/02/2025

"ጦርነት እንዲጀመር አልፈልግም፤ ከተጀመረ ግን አሰብ ደርሶ የሚመለስ የኢትዮጵያ ወታደር የለም!" _ ጀነራል ሰሞራ የኑስ

ጀነራሉ ከሰሞኑ የአፍሪካ ቀንድ የውጥረት ምንጭ የሆነው የቀይ ባህር ጉዳይ ላይ ሰጡ የተባለው አስተያየት ነው።

ጦርነት የማይቀር ሆኖ ከተጀመረ ውጤቱ በአሰብ ብቻ የሚገታ አይሆንም። ጦርነቱ ከተነሳ የሻዕቢያን መንግስት የሚቃወሙ ሌሎች የኤርትራ ኃይሎች ሙሉ ኤርትራን ከአስተዳደሩ ነጻ ለማውጣት ስለሚፈልጉ "አሰብን ብቻ ይዞ የሚመለስ ሰራዊት አይኖርም" ብለዋል።

10/31/2025

አብን የተባለው ፓርቲ ደሳለኝ ጫኔን ከወያኔነት ትቢያ አንስቶ ከሰው ፊት አቅርቦ ነው ጉድ የሰራን። አንዴ ወያኔ/ብአዴን የሆነ ሰው ዘላለም ተላላኪና ባንዳ ነው የተባለው በደሳለኝ ጫኔ ባንዳነት ታየ።

የኤርትራን ጥያቄ ፓርላማ ይዘው የገቡት'' የህዝብ እንደራሴው ''ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ''የቀይ ባህር አጀንዳ የውስጥ ውጥረትን ማስተንፈሻ ይመስላል! በማለት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ላቀረቡት ጥያቄ...
10/29/2025

የኤርትራን ጥያቄ ፓርላማ ይዘው የገቡት'' የህዝብ እንደራሴው ''ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ''

የቀይ ባህር አጀንዳ የውስጥ ውጥረትን ማስተንፈሻ ይመስላል! በማለት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ ላቀረቡት ጥያቄ ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የኤርትራውያን አባባል እንዴት ዞሮ ፓርላማ እንደመጣ አልገባኝም በማለት ምላሽ ሰጥቸዋል። ብልጽግና የሚመች ፓርቲ ባይሆንም በትንሹም ቢኾን ከደሳለኝ ጫኔ ይሻላል። ደሳለኝ በአማራ ክልል ያለው መከራ እንዲቆም አንዲት መፍትሄ ማፍለቅ የማይችል ያልታደሰ ብአዴን ነው። የአማራ ክልል ተመራጭ አማራን ትቶ ለኤርትራ ሲሟገት ደሳለኝ የመጀመሪያው ሰው ነው። ድቅድቅ ጨለማ የሆነ ሰው ነው።

10/29/2025
10/21/2025

ጥምዶ እንደመዝናኛ

10/20/2025

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምርጫ ከምርጫ ውድድር ባሻገር ፤ በሀገሪቱ ግጭቶች ቆመው ዘላቂ ሰላም ሊያሰፍን የሚያስችል ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት የሚጠይቅ እንደመሆኑ መጠን የተለያዩ ፖለቲካዊ ፍላጎ...

የአማራ ህዝብ በመስጅድ አይደለም በየትኛውም ቦታ ለሚሞት ሙስሊም የሚቆረቆርና ከፍትህ ጎን የሚቆም መሆኑን በኃይማኖት ስም የሚያሴሩ የስልጤ አክራሪዎች ማወቅ አለባቸው። ለወገኑ ፍትህ እያፈላለ...
10/19/2025

የአማራ ህዝብ በመስጅድ አይደለም በየትኛውም ቦታ ለሚሞት ሙስሊም የሚቆረቆርና ከፍትህ ጎን የሚቆም መሆኑን በኃይማኖት ስም የሚያሴሩ የስልጤ አክራሪዎች ማወቅ አለባቸው። ለወገኑ ፍትህ እያፈላለገ ያለው የአማራህዝብ የነሙጅብ አሚኖን ኢስላማዊ አክራሪነት ይጠየፋል፤የወንድሙን ሞት ለጥላቻ ፖለቲካ ማስፈጸሚ ሲያደርጉበት ይቃወማል። ግልጹን ስንነጋገር የስልጤ አክራሪ የአማራን ሙስሊም ለፖለቲካ መጠቀሚያው የማድረግ አላማ ያለው ሲሆን ለአማራ ክርስቲያን ግን የደም የአጥንትና የስነልቦና ወንድሙ ነው። ስለሰጤ መር ሴራው እንደተጠበቀ ሆኖ ከወንድም በላይ- ከእልት በላይ ተቆርቋሪ መምሰል አዛኝ ቅቤ አንጓችነት ነው።

አቶ ጌታቸው ረዳ ከቆሻሻና ከመቀንጨር ጋር አልቆረብንም አሉ  ከቆሻሻና ከመቀንጨር ጋር የቆረብንበት ምንም ምክንያት የለም ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አ...
10/12/2025

አቶ ጌታቸው ረዳ ከቆሻሻና ከመቀንጨር ጋር አልቆረብንም አሉ

ከቆሻሻና ከመቀንጨር ጋር የቆረብንበት ምንም ምክንያት የለም ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ።

ሚኒስትሩ ይሄንን ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከፌዴራል እና ክልል አመራሮች ጋር የገጠር ኮሪደር ሥራዎች ላይ ባደረጉት ውይይት ላይ በሰጡት ሀሳብ ነው።

ሀገር ለመቀየር በሚደረግ ጥረት ውስጥ ትልቁ ፈተና አመለካከት መሆኑን ገልጸው፤ ለአብነትም ባለቅኔው ሰለሞን ደሬሳ ብዙ ኢትዮጵያውያን ላሊበላ እና አክሱም ፊት ቆመው የሚያስቡት ቅርሶቹ አይሰሩም የሚለውን ነው ሲሉ አውስተዋል።

በሌላ በኩልም ግብርናን ለማዘመን ቴክኖሎጂ ተምረው እንዲመጡ የተላኩ መሀንዲሶችም የትም ፈቅ ልንል አንችልም የሚል ትምህርት ነው ቀስመው የመጡት ሲሉ ተናግረዋል።

የተሻለ ጥራት እና ንጽህና ለማግኘት ቦታ መቀየር አለብኝ የሚል እንጂ ያለሁበትን ቦታ ማሻሻል አለብኝ ብሎ ያለማሰብ ችግርም እንዳለ ተናግረዋል።

በገጠር ኮሪደር የተሰሩት ቤቶች ንጹህና ሁሉም ነገር የተሟላባቸው ከመሆናቸውም በላይ በራስና በአካባቢ አቅም የተሰሩ መሆናቸው መቻላችንን ያሳያሉ ነው ያሉት።

በተጨማሪም የተሻለ ኑሮ ለመኖር ወደከተማ መዛወር አለብኝ የሚል እሳቤን መስበር የሚያስችል ሥራ በሞዴል የገጠር መንደሮች መሰራቱን አመላክተዋል።

በሞዴል የገጠር መንደሮች የተመለከትኩት ነገር፣ ከቆሻሻና ከመቀንጨር ጋር የቆረብንበት ምንም ምክንያት እንደሌለ ነው ብለዋል ሲል ኢፕድ ዘግቧል፡፡

አዲስ አድማስ

ራሳቸውን የሕዝብ ብቸኛ ወኪል አድርገው የሰየሙ ግለሰቦችና ቡድኖች በአማራ ህዝብ ላይ እድ ሆነዋል አለ አብንራሳቸውን የሕዝብ ብቸኛ ወኪል አድርገው የሰየሙ ግለሰቦችና ቡድኖች፣ በአማራ ሕዝብ ...
10/07/2025

ራሳቸውን የሕዝብ ብቸኛ ወኪል አድርገው የሰየሙ ግለሰቦችና ቡድኖች በአማራ ህዝብ ላይ እድ ሆነዋል አለ አብን

ራሳቸውን የሕዝብ ብቸኛ ወኪል አድርገው የሰየሙ ግለሰቦችና ቡድኖች፣ በአማራ ሕዝብ ስም የተደራጁ የዲያስፖራ ማህበራት፣ የጦርነት ኢኮኖሚ ተዋናዮች፣ በሙስናና ዝርፊያ የተሰማሩ በእየደረጃው ያሉ አመራሮች እና አንዳንድ ወታደራዊ ዲሲፕሊን የጎደላቸው የመከላከያ አባላት፣ የዝርፊያ፣ የማዋከብ፣ የኮንትሮባንድና የሰው ማዘዋወር ወንጀለኞች ግጭቱን የኢኮኖሚያቸው ቋሚ ምንጭ በማድረግ ለሕዝባችን መከራ ዋና ተጠያቂዎች ናቸው።

የአማራን ሕዝብ ለማጥፋትና ለማደናቀፍ አቅደው የሚንቀሳቀሱ ቡድኖች የትጥቅ እንቅስቃሴውን መልካም አጋጣሚ በማድረግ ቀጥተኛና ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ እየተሳተፉ ነው። ዋናዎቹም ሻዕቢያና ህወሓት ሲሆኑ፣ ሕዝባችን የእነዚህ ጠላቶች የትብብር ድር መስሪያ ሆኗል። ይህም ሕዝቡን ለከፋ የደህንነት ስጋት፣ ለኢኮኖሚ ድቀት አልፎም ለህልውና አደጋ አጋልጧል። ‎
የአማራን ሕዝብ አንድነት በማዳከምና ትግሉን ማዕከል አልባ በማድረግ የፖለቲካ ግቦችን ከስልታዊ መንገድ የማውጣት የጠላት ኃይሎች ዓላማ ከሞላ ጎደል ተሳክቷል። በአሁኑ ሰዓት የአማራ ፖለቲካ ወዳጅና ጠላት የማይለይበት፣ የሕዝብ ድምፅ የታፈነበትና የሰው ሕይወት ለሸፍጠኞች ግብዓት የተደረገበት ሁኔታ ተፈጥሯል።

‎በብዙሃኑ የሃገራችን ህዝቦችና ልሂቃን ዘንድ ሰፊ ተደማጭነት ያገኙ የነበሩት የአማራ ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎች በአሁኑ ወቅት በአሉታዊነት፣ በጥርጣሬና በስጋት እንዲታዩ ተደርጓል ። ይህ የሆነው የተሳሳተ የፖለቲካ አሰላለፍ በሚከተሉ ኃይሎች ጥፋት እንዲሁም በጠላት የተቀናጀ ፕሮፖጋንዳና ሴራ ነው ብለን እናምናለን።

‎አብን (የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ) የግጭትና የጦርነት ፖለቲካ በኢትዮጵያ ታሪክ ዘላቂ መፍትሔ እንደማያመጣ ፤ በጠላትነት ትርክት እርስ በርስ የተቆላለፉ ኃይሎች በትብብር የሚያጸኑት ፍትሕም ሆነ መንግሥት እንደማይኖር፤ እንዲሁም በሴራና በኃይል ሚዛን ላይ የተመሰረተ ግንኙነት ከወቅታዊ ጊዜያዊ ጥቅም ባለፈ ሊቀጥል አይችልም ብሎ ያምናል።

‎የመፍትሔ አቅጣጫዎችና ጥሪዎች
‎አሁን በአማራ ሕዝብ ስም እየተካሄደ ያለው የትጥቅ እንቅስቃሴ የሕዝቡን መሠረታዊ ጥያቄዎች የማያሳካ፣ ይልቁንም የሻዕቢያና የወያኔ "ፅምዶነት" እንዲሰምርና ለታሪካዊ ጠላቶች በር የሚከፍት ነው። ስለዚህ፣ መፍትሔውም በቡድን ወገንተኝነት ያልተሸፈነ፣ በእውነት ላይ የተመሰረተና የህዝባችን ነባራዊ ሁኔታ መሰረት ያደረገና ችግሩን የሚመጥን መሆን ይኖርበታል ብለን እናምናለን።

‎‎የክልሉ መንግስት፡- ምንም እንኳን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ህዝቡን ለሰላምና ለልማት ለማነሳሳት የተደረጉ ጥረቶች የሚደነቁ ቢሆንም የክልሉ በየደረጃው ያለው አመራርና የፌዴራል መንግሥትአመራሮች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ ባለመወጣታቸው ግጭቱ ሊቀለበስና ዘላቂ ሰላም ሊሰፍን አልቻለም። በተለይም በክልሉ መንግሥት ውስጥ የተሰገሰጉ ከ'ወያኔያዊ' አስተሳሰብ ነፃ ያልወጡና የጎጥ ፖለቲካ ሰለባ የሆኑ አካላት ለችግሩ መባባስ ምክንያት ናቸው ብለን እናምናለን። በመሆኑም የክልሉ መንግሥት በውስጡ ያሉትን ሁለት-ረገጥ አካላት ለይቶ በሕግ ተጠያቂ እንዲያደርግ አብን አጥብቆ ይጠይቃል።

የፌዴራል መንግስት፡- የፌዴራል መንግሥት የሕዝብን ሰላም እና ደኅንነት የማስጠበቅ ብሔራዊ ኃላፊነት አለበት። ስለሆነም ከሁለት ዓመት በላይ በሕዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን መከራ መቀልበስ የሚያስችሉ ሕጋዊና ፖለቲካዊ መፍትሔዎችን በአፋጣኝ እንዲሰጥ ጥሪ እናስተላልፋለን።

በተለያዩ ሀገራዊ የሰላም ማስፈን ተልዕኮዎች የሚሳተፉ የሀገራችን የቁርጥ ቀን ልጆች እና ህዝባችን ዋጋ የሚከፍለው በሁለት ቢላ በሚበሉ ሁለት-ረገጥ የፖለቲካና የጸጥታ አመራሮቹ እና ከውጭ ጠላት ጋር በሚተባበሩ አካላት ሴራ በመሆኑ መንግስት በእነዚህ ላይ የማያዳግም ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስድ አጥብቀን እንጠይቃለን።

ታጣቂ ቡድኖች ወደ ድርድር እንዲመጡ የሚያበረታታ የፖለቲካ ምህዳር እንዲፈጥርና የመልሶ ማቋቋም ስትራቴጅዎችን አስቀድሞ እንዲያዘጋጅ።

አንጻራዊ ሰላም በሰፈነባቸው አካባቢዎች የተቋረጡ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች እንዲቀጥሉና አዳዲስ ፕሮጀክቶች እንዲጀመሩ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጥሪ እናስተላልፋለን።

ለታጠቁ ኃይሎች የቀረበ ጥሪ
በልዩ ልዩ ምክንያቶች እንዲሁም የህዝባችን መሰረታዊ ጥያቄዎች ለማስመለስ በሚል ወደ ትጥቅ ትግል የገባችሁ ወንድምና እህቶቻችን የአሁኑ የትጥቅ እንቅስቃሴ ህዝባችን በእጅጉ የጎዳና ለታሪካዊ ጠላቶች ጥቃት በር እንደሚከፍት በመገንዘብ እንዲሁም‎ አሁን ባለው አደገኛ ሁኔታ መቆየት የሕዝቡን ክብር እንደማይመጥን በመገንዘብ ወደ ድርድርና ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ መድረክ በመምጣት ለአማራ ሕዝብ ታሪካዊ ውለታ እንድትውሉለት አብን አጥብቆ ይጠይቃል።

ለአማራ ሕዝብ የቀረበ ጥሪ
በስሙ የሚደረግን የፖለቲካ ንግድና የባንዳነት ተግባር በቃኝ ብሎ ዘላቂ ጥቅሞቹን የሚያከብርበትን መንገድ እንዲከተል። በጥቂት ልጆቹ የባንዳነት ተግባር ታሪኩንና ህልውናውን ሊያጠፋ ለሚችል እንቅስቃሴ መተባበር እንደሌለበት አውቆ፣ በመሠረታዊ ጥያቄዎቹ ላይ ትኩረት ካደረጉ ሐቀኛ የትግል እንቅስቃሴዎች ጎን ጸንቶ እንዲቆም ጥሪ እናስተላልፋለን።

ለመላው ኢትዮጵያውያን
ሀገራችን ከመቼውም ጊዜ በላይ በርስ በርስ ግጭትና መጠፋፋት ውስጥ ትገኛለች። ዜጎች በየትኛውም ቦታ በሰላም መንቀሳቀስና መሥራት ካለመቻላቸው በተጨማሪ የእገታ፣ የዘፈቀደ የደቦ ፍርድ፣ የአስገድዶ መድፈርና የግድያ ወንጀሎች ሰለባ የመሆናቸው ጉዳይ የአደባባይ ሀቅ ነው። በመሆኑም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ይህንን ችግር ለማስቆም የተቻላቸውን ሁሉ እንዲያደርጉና ለሰላም የሚደረገውን ጥሪ እንዲደግፉ ጥሪ እናስተላልፋለን፡፡

*****
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)
መስከረም/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ሸዋ፣ ኢትዮጵያ

Address

Fairyland
Silver Spring, MD
20904

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share