Zemen Television

Zemen Television በሀቀኛ መረጃ ትውልድ ይሰራል. የሀገር አንድነት ይሰምራል :: 🇺🇸

የገዳይ ክፉ በጅምላ ገድሎ ሲያበቃ አስከሬን ይወነጅላል!ወገን እግዚዎ እንበል! የአማራ ተማሪዎች በደምቢዶሎ ዩንቨርሲቲ ደብዛቸው በመጥፋቱ የደረሰብን የልብ ስብራት ሳይሽር በጎጃም ክልል ደብረ...
12/31/2025

የገዳይ ክፉ በጅምላ ገድሎ ሲያበቃ አስከሬን ይወነጅላል!
ወገን እግዚዎ እንበል! የአማራ ተማሪዎች በደምቢዶሎ ዩንቨርሲቲ ደብዛቸው በመጥፋቱ የደረሰብን የልብ ስብራት ሳይሽር በጎጃም ክልል ደብረኤልያስ ወረዳ እነዚህ ንዑሀን በተወለዱበት ቅዬ በግፍ ተጨፍጭፈዋል። አንዳንዶች እንደሚገልጹት በአማራ ክልል በተለይ በጎዣም የሸኔ ግልባጮች- አማርኛ ተናጋሪ ወያኔዎች በማፈጽሙት ግፍ የተነሳ ህዝቡ መከራውን እያየ ነው። አማራ ከወለጋ በባሰ በሰፈሩ መኖሮ አልቻለም። በአንዳንድ አካባቢ አማራ ወንድ ሴት ሳይል ወደ ስደት በህገወጥ መንገድ እየሄደ ነው።

እነዚክ "ፋኖ ነን" የሚሉ አካላት የገዳይ ክፉወች ናቸው። የአማራን ህዝብ በጅምላ እና በየቤቱ ገድለው ሲያበቁ አስከሬኑን በሀሰት ይወነጅሉታል። እጃቸው ከእስኪርበቶ እና ከማማሰያ ውጭ ጨብጦ ያማያውቅ ለጋ አማራወችን መጨፍጨፍን እንደ ትግል አድርገው በመዘገባቸው ይበልጥ አፍረናል። "ባልሽ ሚሊሻ ነው፣ የመከላከያ ሰራዊት አባል የነበረ ሰው ፍቅረኛሽ ነበር፣ ለፋኖ የዘይት ወጥ እየሰጠሽ ለራስሽ በቅቤ ትበያለሽ፤ ተራክቦ ካልፈጸምን ትግሉን አትደግፊም ማለት ነው" እየተባለች የተረሸነችን የአማራ ሴት ቤት ይቁጠራት። እግዚዎ! የሉሄ እንበል!

ጎንደር በየዘመኑ ሁኔታውን የዋጀ መሪ ትወልዳለች። ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እና አቶ አሸተ ደምለው ጭቆናን ፈንቅለው የወጡ-የበቁ- የነቁ መሪዎቻችን ናቸው።
12/23/2025

ጎንደር በየዘመኑ ሁኔታውን የዋጀ መሪ ትወልዳለች። ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እና አቶ አሸተ ደምለው ጭቆናን ፈንቅለው የወጡ-የበቁ- የነቁ መሪዎቻችን ናቸው።

የሁከትና የብጥብጥ ነጋዴዎች ያስደነገጠው የአሜሪካ ውሳኔ አሜሪካ ሀገር ሆነዋል ኢትዮጵያ ሲያተራምሱ የነበሩ የሁከትና የብጥብጥ ነጋዴዎችን በ 60 ቀናት ውስጥ ለቃችሁ ውጡ ብላለች::የፕሬዝዳን...
12/13/2025

የሁከትና የብጥብጥ ነጋዴዎች ያስደነገጠው የአሜሪካ ውሳኔ

አሜሪካ ሀገር ሆነዋል ኢትዮጵያ ሲያተራምሱ የነበሩ የሁከትና የብጥብጥ ነጋዴዎችን በ 60 ቀናት ውስጥ ለቃችሁ ውጡ ብላለች::የፕሬዝዳንት ትራምፕ አስተዳደር፣ ከትግራዩ ጦርነት ጋር በተያያዘ የቀድሞው ፕሬዝዳንት የባይደን አስተዳደር ለኢትዮጵያዊያን የሠጠውን “ጊዜያዊ ከለላ” አነሳ። የአሜሪካ የአገር ውስጥ ጉዳይ መስሪያ ቤት፣ አሜሪካ ውስጥ ለመቆየት የሚያበቃ “የተለየ ሕጋዊ ምክንያት” የሌላቸው ከለላ ተሠጥቷቸው የነበሩ ኢትዮጵያዊያን በፍቃዳቸው እንዲወጡ 60 ቀናት ብቻ ሠጥቷል። ከለላው የተነሳው፣ ኢትዮጵያዊያን ወደ አገራቸው ቢመለሱ “አሳሳቢ የደኅንነት ስጋት አይገጥማቸውም” በሚል ድምዳሜ ላይ ተመስርቶ መኾኑን መስሪያ ቤቱ ገልጧል። መስሪያ ቤቱ፣ በቀነ ገደቡ በፍቃዳቸው የማይወጡ ኢትዮጵያዊያን “ታስረው ወደ አገራቸው እንደሚባረሩ” እና “በድጋሚ በሕጋዊ መንገድ ወደ አሜሪካ እንዳይገቡ” ሊታገዱ እንደሚችሉ አስጠንቅቋል።

የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ለፖሊስና ሌሎች ፀጥታ አባላትና አመራሮች ስልጠና መስጠት ጀመረ፤ቢሮው ከUNDP peace support facility ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ከደብረ ብርሃን ከ...
12/12/2025

የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ለፖሊስና ሌሎች ፀጥታ አባላትና አመራሮች ስልጠና መስጠት ጀመረ፤

ቢሮው ከUNDP peace support facility ባገኘው የገንዘብ ድጋፍ ከደብረ ብርሃን ከተማና ከሰሜን ሸዋ ዞን ለተውጣጡ የፖሊስና ሌሎች የጸጥታ አባላት እና አመራሮች በሰብአዊ መብት አያያዝና በማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዘዴዎች ዙሪያ ስልጠና መስጠት ጀምሯል።

የደብረ ብርሃን ከተማ ሰላምና ፀጥታ መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ መኳንንት አበበ የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር አድርገው ስልጠናውን አስጀምረዋል።

የአለም አቀፍ መምህር ዳምጠው ተሰማ(ረ/ፕ) በሰብዓዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ስልጠና እየሰጡ ነው።

በስልጠናው የክልል፣የደብረ ብርሃንና የሰሜን ሸዋ ዞን ከፍተኛ የፖሊስ መኮንኖች እና ሌሎች ፀጥታ ተቋማት አመራሮች እና የጸጥታ መዋቅር አካላት ተሳትፈዋል።https://www.facebook.com/share/p/17c4b2mK33/
https://www.facebook.com/share/1DFQozh8dt/

African Union Hails Landmark Peace Agreement in Ethiopia, Welcomes Signing Between Amhara Region and FANO-AFPO.The Afric...
12/04/2025

African Union Hails Landmark Peace Agreement in Ethiopia, Welcomes Signing Between Amhara Region and FANO-AFPO.

The African Union (AU) today witnessed and welcomed a significant step towards lasting peace in Ethiopia with the signing of a sustainable peace agreement between the Amhara National Regional State and the Amhara FANO Popular Organization (FANO-AFPO).

The signing ceremony, held in Addis Ababa, was attended by H.E. Selma Malika Haddadi, Deputy Chairperson of the African Union Commission, who represented the continental body, and Mr. Mohamed Abdi Ware, Deputy Executive Secretary of the Intergovernmental Authority on Development (IGAD).

In her statement at the event, the Deputy Chairperson commended the parties for their commitment to dialogue and peaceful resolution. She emphasized that this agreement represents a crucial milestone not only for Ethiopia but for the entire African continent.

“Each peace agreement inches us closer to achieving our goal of Silencing the Guns in Africa,” stated H.E. Selma Malika Haddadi. “On behalf of the African Union, I congratulate the parties for reaching this important milestone. This achievement demonstrates the power of African-led solutions to African challenges”.

The African Union reaffirms its unwavering commitment to supporting the implementation of this agreement and the broader peace in Ethiopia.

Read @ https://au.int/en/pressreleases/20251204/au-hails-landmark-peace-agreement-ethiopia

በአማራ ክልል መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተደረገ። በአማራ ክልል መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የዘላ...
12/04/2025

በአማራ ክልል መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተደረገ።

በአማራ ክልል መንግሥት እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) መካከል የዘላቂ ሰላም ስምምነት ተደርጓል።

ስምምነቱ የክልሉ መንግሥት ለሰላም የሰጠው አማራጭ አንዱ አካል የኾነ እና ለቀጣይ የሕዝብ ሰላማዊ እፎይታ መሠረት የሚጥል ነው ተብሏል።

በሁለቱ ወገኖች ስምምነት በአደራዳሪነት የአፍሪካ ኅብረት እና ኢጋድ ተሳትፈዋል።

የሰላም ስምምነቱ በአማራ ክልል ርእሰ መስተዳድር አረጋ ከበደ እና በአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት (አፋሕድ) ተወካይ ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ መካከል ተደርጓል።

በስምምነት ሥነ ስርዓቱ ላይ ከጦርነት ያተረፈም ኾነ በጦርነት የተጠናቀቀ ግጭት ባለመኖሩ ይህ ድርድር ለክልሉ ሕዝብ ሰላም መነሻ እና ለሰላም የተሰጠ ተግባር ነው ተብሏል ሲል የዘገበዉ አሚኮ ነዉ።

ለጋዜጠኞች ሲከፈል የነበረው ደመወዝ ተቋረጠ❗️❗️❗️ለኢትዮ ፎረም ጋዜጠኞች ይከፈል የነበረው ደሞዝ ከዛሬ ህዳር 21/2018 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቆረጥ መወሰኑን ተሰምቷል። አገር ውስጥ ለሚገኙ ...
11/30/2025

ለጋዜጠኞች ሲከፈል የነበረው ደመወዝ ተቋረጠ❗️❗️❗️

ለኢትዮ ፎረም ጋዜጠኞች ይከፈል የነበረው ደሞዝ ከዛሬ ህዳር 21/2018 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቆረጥ መወሰኑን ተሰምቷል። አገር ውስጥ ለሚገኙ የህወሀት አክቲቪስቶች በሚከፈለው ደሞወዝና ለኢትዮ ፎረም ጋዜጠኞች ሲከፈል የነበረው ደሞወዝ መካከል ሰፊ ልዩነት ያለው በመሆኑ ነው የሚሉ መረጃዎች ይሰሙ እንጂ ህዉሀት በውጭ ቋንቋ የሚሰሩ ሚዲያዎች ጋር ለመስራት ውሳኔ ላይ በመድረሱ እንደሆነ ታውቋል።በጉዳዩ ላይ ከኢትዮ ፎረም ሆነ ከህውሀት ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የተደረገው ጥረት አልተሳካም።

በሌላ መረጃ "ትግራይ ወደ ቀደመ ገናናነቷ" በሚል መሪ ቃል ክልላዊ ኮንፈረንስ ሊደረግ ነው፡፡ በትግራይ ክልል ውስጥ ያለውን የፖለቲካ ልዩነት በውይይትና በድርድር ለመፍታት በጊዜያዊ አስተዳደሩ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት ክልላዊ ኮንፈረንስ ሊካሄድ ነው፡፡ በቅርቡ በሚከናወነው በዚህ ኮንፈረንስ ላይ 2300 ያህል ተሳታፊዎች እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ሲቪክ ማህበራትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በዚህ ኮንፈረንስ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ የሚደረግ ሲሆን በህዳር ወር መጨረሻ ላይ ለ3 ቀናት እንደሚከናወን ተሰምቷል።

አማራ ክልል ከመንግስት ጋር መሳሪያ አንስተው ግጭት ውስጥ ከገቡ የፋኖ መሪዎች መካከል ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ ትናንት ምሽት እጁን ለመንግስት የፀጥታ ኃይሎች የመስጠቱ ዜና ተረጋግጧል። በማስረሻ...
11/30/2025

አማራ ክልል ከመንግስት ጋር መሳሪያ አንስተው ግጭት ውስጥ ከገቡ የፋኖ መሪዎች መካከል ካፒቴን ማስረሻ ሰጤ ትናንት ምሽት እጁን ለመንግስት የፀጥታ ኃይሎች የመስጠቱ ዜና ተረጋግጧል። በማስረሻ ውሳኔ ደስ ያለውም የከፋውም አለ። ሆኖም ሰፊው ህዝብ አልከፈውም እየተባለ ነው።

የወልቃይት ልባም ትውልድ የሰላም ዘብ፤  የሰብአዊነት ጋሻ ሆነ ተከስቷል። ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ብርቅዬ የመርህ ሰው
11/21/2025

የወልቃይት ልባም ትውልድ የሰላም ዘብ፤ የሰብአዊነት ጋሻ ሆነ ተከስቷል። ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ብርቅዬ የመርህ ሰው

Address

Fairyland
Silver Spring, MD
20904

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share