Zemen Television

Zemen Television በሀቀኛ መረጃ ትውልድ ይሰራል. የሀገር አንድነት ይሰምራል :: 🇺🇸

ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ፤*****የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤ውድ አገራዊና ሰብዓዊ ጉዳዮች የሚያሳስባችሁ ወገኖቻችን፤አገራችን ኢትዮጵያ በምትገኝበት በዚህ ውስብስብ...
01/09/2026

ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ፤
*****
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤
ውድ አገራዊና ሰብዓዊ ጉዳዮች የሚያሳስባችሁ ወገኖቻችን፤

አገራችን ኢትዮጵያ በምትገኝበት በዚህ ውስብስብና ፈታኝ ወቅት የዜጎች በሕይወት የመኖር ተፈጥሮአዊ መብት፣ የደኅንነት ዋስትና እና የሕግ የበላይነት መከበር የአገራችን ዘላቂ ሰላምና አንድነት መሠረቶች ናቸው። በየትኛውም የአገራችን ክፍል የሚኖሩ ዜጎች ከሥጋት ነፃ ሆነው የመንቀሳቀስ፣ የመሥራትና በሰላም የመኖር መብታቸውን ማስከበር የትኛውም መንግሥታዊ ሥርዓት የመጨረሻውና ዋናው የመኖሩ ዋስትና ነው።

ሆኖም ግን ከሰሞኑ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በንጹኃን ዜጎች ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶችና የተከሰቱት ተደጋጋሚ ሰብዓዊ ቀውሶች፣ የመንግሥትን መሠረታዊ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ውድቀት እንደገና በግልጽ ያሳዩ በመሆናቸው ንቅናቄያችን አብን በጥልቅ አሳስቦታል።

1/ የሰብዓዊ ቀውሱ አሳሳቢነት እና የመንግሥታዊ መዋቅር ተጠያቂነት

ከሰሞኑ በምሥራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ፣ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ቀርሳ ማሊማ ወረዳ፣ በምሥራቅ አርሲ እና በሰሜን ሸዋ ዞኖች አሊ ዶሮና አካባቢው በንጹኃን ዜጎች የተፈጸሙት የማንነትና የዕምነት ተኮር የግድያ፣ የንብረት ውድመት፣ የማፈናቀል እና የእምነት ተቋማት ጉዳቶች፣ እና የተጓዥ መንገደኞች ተደጋጋሚ እገታ የአገራችንን ሰላም እና ማኅበራዊ አንድነት በእጅጉ እየጎዱ ይገኛሉ።

እነዚህን ተደጋግመው የሚከሰቱ ሰብዓዊ ቀውሶችና የዜጎች ሰቆቃዎችን በተመለከተ ንቅናቄያችን የሚከተሉትን መሠረታዊና ተጠያቂነትን በጥብቅ የሚሹ ነጥቦችን ማንሳት ይፈልጋል፦

ሀ/ ጥቃቶቹን በቀጥታ የሚፈጽሟቸው አማፂያን፣ ታጣቂዎች ወይም የትኛዎቹም አካላት ይሁኑ የዜጎችን ሕይወትና ንብረት ከጥቃት የመጠበቅ፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር እና የዜጎችን ደኅንነት የማረጋገጥ ቀዳሚና የመጀመሪያ ደረጃ ሕገ-መንግሥታዊ ኃላፊነት የመንግሥት ነው። ጥቃቶችን በታጣቂዎች ላይ ብቻ በማሳበብ መንግሥት ከተጠያቂነት ነፃ ሊሆን አይችልም!

ለበርካታ ዓመታት በክልሉ ንጹኃን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች ተባብሰው መቀጠላቸው በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥትና የጸጥታ መዋቅሮች ላይ ከባድ የሕግና የመዋቅር ውድቀት እንዳለ ማሳያ ነው። በዚህ መልኩ በተደጋጋሚ ለሚከሰቱ ጥቃቶች የመንግሥት አካላት የፖለቲካና የሕግ ተጠያቂነት ሳይወስዱ ችግሩን በማድበስበስ ለማለፍ የሚያስችላቸው ምንም አይነት ተቀባይነት የለውም።

ለ/ የትኛውም አገራዊ የልማትና የዕድገት ትርክት ዋጋ ሊኖረው የሚችለው የዜጎች መሠረታዊ የሕይወትና የመንቀሳቀስ መብት ሲረጋገጥ ብቻ ሲሆን፤ የዜጎች የመኖር መብት በተጣሰበት ሁኔታ ስለ አገራዊ ብልፅግናም ይሁን ዕድገት ማውራት ተጨባጭ እውነታን የካደና ቅቡልነት የሌለው አካሄድ ነው። ሰላምና ደኅንነት ለሁሉም አገራዊ ዕቅዶች መሠረታዊ ቅድመ-ሁኔታዎች ናቸው!

2/ የአብን ጥሪና የመፍትሔ አቅጣጫዎች፣

የተከሰቱትን ሰብዓዊ ቀውሶች በአስተማማኝ ሁኔታ ለመቅረፍ፣ የሕግ የበላይነትን ለማስፈን እና የዜጎችን ደኅንነት ዘላቂ በሆነ መንገድ ለማረጋገጥ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የሚከተሉትን ጥብቅ ጥሪዎች ያቀርባል፦

ሀ/ የፌደራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት በወለጋ፣ በምሥራቅ አርሲ፣ በሰሜን ሸዋ እና በሌሎች የሥጋት ቀጠናዎች በአስቸኳይ የተቀናጀና ውጤታማ የሕግ ማስከበር እርምጃ በመውሰድ የንጹኃን ዜጎችን ሕይወትና ንብረት የመታደግ ግዴታቸውን በአስቸኳይ እንዲወጡ እንጠይቃለን።

ለ/ በንጹኃን ላይ ጥቃት ባደረሱ አካላት በጥብቅ ሕግ ከማስፈኑ ጎን ለጎን፣ የዜጎችን ደኅንነት በማስጠበቅ ረገድ በየደረጃው የታዩ ተቋማዊና መዋቅራዊ ድክመቶችን፣ እንዲሁም የባለሥልጣናትን ድዳተኝነትና ኃላፊነት አለመወጣት መርምሮ ግልጽ የሆነ የሕግና የፖለቲካ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እናሳስባለን።

ሐ/ በቀጠናው የሚከናወኑ የጸጥታና የሕግ ማስከበር ስምሪቶች የንጹኃን ዜጎችን ሰላም የሚያረጋግጡ፣ ሕጋዊነትን የተከተሉና ከማንኛውም ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ፣ የብሔራዊ ሰብዓዊ መብት ተቋማትና ገለልተኛ አካላት የሚሳተፉበት የክትትልና የምርመራ ሥርዓት በአስቸኳይ እንዲዘረጋ እንጠይቃለን።

መ/ በጥቃቱ ምክንያት የተፈናቀሉ፣ ንብረታቸው የወደመባቸውና የነፍስ አድን እርዳታ የሚሹ ዜጎቻችን በአስቸኳይ አስፈላጊው የምግብ፣ የሕክምና እና የማህበራዊ ድጋፍ እንዲደርሳቸው፣ እንዲሁም ወደ ቀደመ ቀያቸው ተመልሰው በዘላቂነት እንዲቋቋሙ መንግሥትና የሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች የተቀናጀ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤

የዜጎች ደኅንነት፣ ፍትህና የሕግ የበላይነት ለድርድር የማይቀርቡ አገራዊ እሴቶቻችን ናቸው። ንቅናቄያችን አብን ለዜጎች እኩልነት፣ ለሕግ የበላይነትና ለዘላቂ ሰላም መከበር የሚያደርገውን መርኅ-ተኮር፣ ሰላማዊና ሕጋዊ ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል።

ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ንጹኃን ወገኖቻችን አስቸኳይ ፍትህና ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲሰጥ በድጋሜ በአጽንኦት እንጠይቃለን!

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)

ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ፤
*****
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤
ውድ አገራዊና ሰብዓዊ ጉዳዮች የሚያሳስባችሁ ወገኖቻችን፤

አገራችን ኢትዮጵያ በምትገኝበት በዚህ ውስብስብና ፈታኝ ወቅት የዜጎች በሕይወት የመኖር ተፈጥሮአዊ መብት፣ የደኅንነት ዋስትና እና የሕግ የበላይነት መከበር የአገራችን ዘላቂ ሰላምና አንድነት መሠረቶች ናቸው። በየትኛውም የአገራችን ክፍል የሚኖሩ ዜጎች ከሥጋት ነፃ ሆነው የመንቀሳቀስ፣ የመሥራትና በሰላም የመኖር መብታቸውን ማስከበር የትኛውም መንግሥታዊ ሥርዓት የመጨረሻውና ዋናው የመኖሩ ዋስትና ነው።

ሆኖም ግን ከሰሞኑ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በንጹኃን ዜጎች ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶችና የተከሰቱት ተደጋጋሚ ሰብዓዊ ቀውሶች፣ የመንግሥትን መሠረታዊ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ውድቀት እንደገና በግልጽ ያሳዩ በመሆናቸው ንቅናቄያችን አብን በጥልቅ አሳስቦታል።

1/ የሰብዓዊ ቀውሱ አሳሳቢነት እና የመንግሥታዊ መዋቅር ተጠያቂነት

ከሰሞኑ በምሥራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ፣ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ቀርሳ ማሊማ ወረዳ፣ በምሥራቅ አርሲ እና በሰሜን ሸዋ ዞኖች አሊ ዶሮና አካባቢው በንጹኃን ዜጎች የተፈጸሙት የማንነትና የዕምነት ተኮር የግድያ፣ የንብረት ውድመት፣ የማፈናቀል እና የእምነት ተቋማት ጉዳቶች፣ እና የተጓዥ መንገደኞች ተደጋጋሚ እገታ የአገራችንን ሰላም እና ማኅበራዊ አንድነት በእጅጉ እየጎዱ ይገኛሉ።

እነዚህን ተደጋግመው የሚከሰቱ ሰብዓዊ ቀውሶችና የዜጎች ሰቆቃዎችን በተመለከተ ንቅናቄያችን የሚከተሉትን መሠረታዊና ተጠያቂነትን በጥብቅ የሚሹ ነጥቦችን ማንሳት ይፈልጋል፦

ሀ/ ጥቃቶቹን በቀጥታ የሚፈጽሟቸው አማፂያን፣ ታጣቂዎች ወይም የትኛዎቹም አካላት ይሁኑ የዜጎችን ሕይወትና ንብረት ከጥቃት የመጠበቅ፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር እና የዜጎችን ደኅንነት የማረጋገጥ ቀዳሚና የመጀመሪያ ደረጃ ሕገ-መንግሥታዊ ኃላፊነት የመንግሥት ነው። ጥቃቶችን በታጣቂዎች ላይ ብቻ በማሳበብ መንግሥት ከተጠያቂነት ነፃ ሊሆን አይችልም!

ለበርካታ ዓመታት በክልሉ ንጹኃን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች ተባብሰው መቀጠላቸው በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥትና የጸጥታ መዋቅሮች ላይ ከባድ የሕግና የመዋቅር ውድቀት እንዳለ ማሳያ ነው። በዚህ መልኩ በተደጋጋሚ ለሚከሰቱ ጥቃቶች የመንግሥት አካላት የፖለቲካና የሕግ ተጠያቂነት ሳይወስዱ ችግሩን በማድበስበስ ለማለፍ የሚያደርጉት ጥረት ይበልጥ ሊያጋልጣቸው ካልሆነ በቀር ምንም አይነት ተቀባይነት አይኖውም።

ለ/ የትኛውም አገራዊ የልማትና የዕድገት ትርክት ዋጋ ሊኖረው የሚችለው የዜጎች መሠረታዊ የሕይወትና የመንቀሳቀስ መብት ሲረጋገጥ ብቻ ሲሆን፤ የዜጎች የመኖር መብት በተጣሰበት ሁኔታ ስለ አገራዊ ብልፅግናም ይሁን ዕድገት ማውራት ተጨባጭ እውነታን የካደና ቅቡልነት የሌለው አካሄድ ነው። ሰላምና ደኅንነት ለሁሉም አገራዊ ዕቅዶች መሠረታዊ ቅድመ-ሁኔታዎች ናቸው!

2/ የአብን ጥሪና የመፍትሔ አቅጣጫዎች፣

የተከሰቱትን ሰብዓዊ ቀውሶች በአስተማማኝ ሁኔታ ለመቅረፍ፣ የሕግ የበላይነትን ለማስፈን እና የዜጎችን ደኅንነት ዘላቂ በሆነ መንገድ ለማረጋገጥ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የሚከተሉትን ጥብቅ ጥሪዎች ያቀርባል፦

ሀ/ የፌደራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት በወለጋ፣ በምሥራቅ አርሲ፣ በሰሜን ሸዋ እና በሌሎች የሥጋት ቀጠናዎች በአስቸኳይ የተቀናጀና ውጤታማ የሕግ ማስከበር እርምጃ በመውሰድ የንጹኃን ዜጎችን ሕይወትና ንብረት የመታደግ ግዴታቸውን በአስቸኳይ እንዲወጡ እንጠይቃለን።

ለ/ በንጹኃን ላይ ጥቃት ባደረሱ አካላት በጥብቅ ሕግ ከማስፈኑ ጎን ለጎን፣ የዜጎችን ደኅንነት በማስጠበቅ ረገድ በየደረጃው የታዩ ተቋማዊና መዋቅራዊ ድክመቶችን፣ እንዲሁም የባለሥልጣናትን ዳተኝነትና ኃላፊነት አለመወጣት መርምሮ ግልጽ የሆነ የሕግና የፖለቲካ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እናሳስባለን።

ሐ/ በቀጠናው የሚከናወኑ የጸጥታና የሕግ ማስከበር ስምሪቶች የንጹኃን ዜጎችን ሰላም የሚያረጋግጡ፣ ሕጋዊነትን የተከተሉና ከማንኛውም ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ፣ የብሔራዊ ሰብዓዊ መብት ተቋማትና ገለልተኛ አካላት የሚሳተፉበት የክትትልና የምርመራ ሥርዓት በአስቸኳይ እንዲዘረጋ እንጠይቃለን።

መ/ በጥቃቱ ምክንያት የተፈናቀሉ፣ ንብረታቸው የወደመባቸውና የነፍስ አድን እርዳታ የሚሹ ዜጎቻችን በአስቸኳይ አስፈላጊው የምግብ፣ የሕክምና እና የማህበራዊ ድጋፍ እንዲደርሳቸው፣ እንዲሁም ወደ ቀደመ ቀያቸው ተመልሰው በዘላቂነት እንዲቋቋሙ መንግሥትና የሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች የተቀናጀ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤

የዜጎች ደኅንነት፣ ፍትህና የሕግ የበላይነት ለድርድር የማይቀርቡ አገራዊ እሴቶቻችን ናቸው። ንቅናቄያችን አብን ለዜጎች እኩልነት፣ ለሕግ የበላይነትና ለዘላቂ ሰላም መከበር የሚያደርገውን መርኅ-ተኮር፣ ሰላማዊና ሕጋዊ ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል።

ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ንጹኃን ወገኖቻችን አስቸኳይ ፍትህና ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲሰጥ በድጋሜ በአጽንኦት እንጠይቃለን!

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)

ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

የመንግስት አደረጃጀት ፓርላሜንታዊ ይሁን፣ ፕሬዚዳንታዊ ይሁን የሚለውን ጨምሮ አራት ያላስማሙ ጉዳዮች 12ዐ አባላት ባሉት ቡድን ለቀጣይ ዙር ተሻገሩ። 👉 በሥራ ቡድኑ ስምምነት የተደረሰበት "...
18/08/2026

የመንግስት አደረጃጀት ፓርላሜንታዊ ይሁን፣ ፕሬዚዳንታዊ ይሁን የሚለውን ጨምሮ አራት ያላስማሙ ጉዳዮች 12ዐ አባላት ባሉት ቡድን ለቀጣይ ዙር ተሻገሩ።

👉 በሥራ ቡድኑ ስምምነት የተደረሰበት "የውህደት ማንነት ጉዳይ" በአዘጋጅ ቡድኑ ወደ አለማስማማት ተመልሷል።

በመንግስት አደረጃጀትና ቅርፅ አጀንዳ 500 ሰዎችን በያዘው ቡድን ጭምር ሲያከራክሩ የቆዩ ሦስት እና በዚሁ ቡድን አስምምቶ የነበረ ሌላ፣ በድምሩ አራት ምክረ ሀሳቦች 120 አባላት አሉት በተባለው ሀሳብ አዘጋጅ ቡድንም ስምምነት ያልተደረሰባቸው በሚል መያዛቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተሳታፊዎች ሰምቷል።

በዚሁ አጀንዳ 500 ሰዎችን በያዘው ቡድን 53 አመካካሪ ጉዳዮች እንደነበሩ፣ 50ው ስምምነት ተደርሶባቸው ሦስቱ ሳያስማሙ እንደታለፉ ከዚህ ቀደም ተገልጾ ነበር። አንድ የአጀንዳው ተሳታፊ ትናንት በሰጡን ቃል፣ 120 አባላት ያሉት ሀሳብ አዘጋጅ ቡድን "53ቱን ጉዳዮች 62 አድርጎ ነው ያመጣቸው። ከ62ቱ አራቱ ስምምነት ያልተደረሰባቸው ተብለዋል" ብለዋል።

አዘጋጅ ቡድኑ 62 አድርጎ ያመጣቸው ሀሳቦች መጀመሪያ የነበረው አንድ ሀሳብ ሁለት እንዲሆን ያደረገበት እንጅ የይዘት ለውጥ እንደሌለው ገልጸው፣ "የውህድ ማንነት ጉዳይ" ግን ከስምምነት ወደአለማስማማት እንደመጣ ተናግረዋል።

ሳያስማሙ የቀጠሉት ጉዳዮች ምንድን ናቸው?

የዚሁ ቡድን ተመካካሪ እንደገለጹት፦
- የመንግስት አወቃቀር ፓርላሜንታዊ ይሁን፤ ፓርላሜንታዊ አይሆንም ፕሬዚዳንታዊ ይሁን
- የፌዴሬሽን ም/ቤት ወኪሎች አመራረጥ ምን ይሁን?
- በፌዴሬሽን ም/ቤት የብሔረሰቦች ውክልና ምን ይሁን?
- "የውህድ ማንነት" ጉዳይ ባለ120 አባላት ቡድኑም ያላስማሙ በሚል ተይዘዋል።

ዝርዝር ሀሳባቸው ምንድን ነው ?

1) የመንግስት አደረጃጀት

በ500 ሰዎች በተደራጀው ቡድን አጀንዳ አጠናቃሪዎች አንዱ፣ ቡድኑ የመንግስት አወቃቀር፥ "'ፓርላሜንታዊ ሆኖ ፕሬዚዳንቱ ከፓርላማ ይመረጥና የፕሬዚዳንቱንም የጠቅላይ ሚኒስትሩንም ሥራ አንድ ላይ ይስራ'" እና "'ፕሬዚዳንታዊ ሆኖ ፕሬዚዳንቱ ከህዝብ ይመረጥ' የሚሉት ሁለት አማራጮች ቀርበው በሁለቱም የጋራ ውሳኔ ሳይሰጥ ወደ ቀጣይ ሂደት አልፈዋል" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረው ነበር።

ጉዳዩ በአስማሚ ኮሚቴ፣ ካልሆነ በድምፅ ብልጫ እንዲታይ የመደረግ እድል እንዳለው ነበር ያስገነዘቡት። የዚሁ አጀንዳ ተሳታፊ ትናንት እንደነገሩን ደግሞ፣ ጉዳዩ ለአስማሚ ኮሚቴም ሆነ ድምፅ አሰጣጥ ሳያልፍ 120 አባላት ወዳሉት ሀሳብ አዘጋጅ ቡድን ተሻግሮ ቆይቷል።

ይህ በእንዲህ እያለ፣ አዘጋጅ ቡድኑ ሪፖርቱን ትናንት መልሶ ለ500ው ቡድን ሲያቀርብ፣ የጋራ ውሳኔ ይሻሉ ተብለው በነበሩት በሁለቱ የሚቃረኑ ምክረ ሀሳቦች ስምምነት ላይ ሳይደረስባቸው ባሉበት ወደ ቀጣዩ የምክክር ሂደት እንዳሳለፋቸው አስረድተዋል።

"ግን ለስምምነት አመቻችተው ፕሬዚዳታዊ ሲስተም ይኑር የሚለው የማይኖርቲ ሀሳብ ነው ብለውታል፤ ማይኖርቲ ለሚለው የተሰጠ ድምፅ የለም" ሲሉ በ500ው ቡድን የሆነውን አስታውሰዋል። ቀጣዩ የምክክር ዙር የአስማሚ ኮሚቴ ይሁን የሌላ በግልጽ እንዳላወቁ ገልጸዋል።

ሁለተኛው ያላስማማ ጉዳይ ደግሞ ከፌዴሬሽን ምክር ቤት ጋር የተያያዘ መሆኑን እኚሁና ሌሎች ተሳታፊዎች ገልጸዋል። አንደኛው የፌዴሬሽን ምክር ቤት አመራረጥ፣ ሲሆን፣ በፌዴሬሽን ም/ቤት የብሔረሰቦች ውክልና ደግሞ ሌላኛው ጉዳይ ነው።

2) የፌዴሬሽን ምክር ቤት ወኪሎች አመራረጥ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ወኪሎች አመራረጥ ምን ይሁን? "የም/ቤት አባላቱ እንዴት ይመሰጡ? በሚሉት ጉዳዮች፥ በአንድ በኩል "በክልሎች ም/ቤት ተመርጠው ይምጡ። ሁሉንም በክልሉ ያለውን ብሔረሰብ በሚወክል መልኩ የክልሉ ም/ቤት ክልሌን የሚወክሉት የፌዴሬሽን ም/ቤት እነዚህ ናቸው ብሎ ወደ ፌዴሬሽን ም/ቤት ይላክ" የሚል ሀሳብ በሥራ ቡድኑ መቅረቡ ይታወሳል።

በአንፃሩ ደግሞ፥ "ህዝብ በቀጥታ የሚመለከተው የብሔር ወኪሎች ስለሆነ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አባላት ህዝቡ በቀጥታ ይምረጣቸውና ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ይላካቸው፤ ሁሉም ብሔረሰቦች ውክልና ይኑራቸው" የሚል ምክረ ሀሳብ ቀርቦ ነበር፣ ሆኖም በአዘጋጅ ቡድኑም ጉዳዩቹ የጋራ ስምምነት አልተደረሰባቸውም በሚል አሳልፏቸዋል።

3) በፌዴሬሽን ም/ቤት የብሔረሰቦች ውክልና

በፌዴሬሽን ምክር ቤት የብሔረሰቦች ውክልና እንዴት እንዴት ይሁን? በሚለው ጉዳይ "በአብላጫ" ተብሎ በቀረበ ሀሳብ "አንድ ብሔረሰብ ብሔረሰብ በመሆኑ አንድ ውክልና ይኖረው። በተጨማሪ በእያንዳንዱ አንድ ሚሊዮን ህዝብ አንድ ተወካይ ይኖረው። ብዛቱ 500 ሺሕ የሆነ አንድ ብሔረሰብ ግን አንድ ተወካይ ይኑረው። አሁን ያለው አሰራር ይቀጥል" መባሉ ተገልጿል።

በተቃራኒው፥ "አነስተኛ ቁጥር ያላቸው ተሳታፊዎች ሀሳብ ተብሎ፥ ሁሉም ብሔረሰብ በፌዴሬሽን ም/ቤት እኩል ውክልና ይኑራቸው፤ ወኪሎቹ 5፣ 2፣ 4 ሳይባል ግን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ብሔረሰቦች በቁጥራቸው ልክ ይወከሉ" የሚል ሀሳብ ቀርቦ፣ በእነዚህም 120 አባላት ባሉት ቡድን ስምምነት ሳይደረስባቸው እንዳሉ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፋቸው ተመልክቷል።

4) "የውህድ ማንነት" ጉዳይ

"የውህድ ማንነት" በፓርቲ ደረጃ መቅረቡን የገለጹት የዚሁ አጀንዳ ተመካካሪ፣ "የሁለት 'ውህድ ማንነት' ያላቸው ሰዎች" እንዳሉ ተገልጾ፣ "አሁን ያለው አሰራር ለአገልግሎት መታወቂያ ሲጠየቁ በአንድ ማንነት ብቻ እንዲጠሩ ስለሚያስገድዳቸው 'ብሔር የለኝም ውህድ ነኝ' የማለት መብት ሊኖራቸው ይገባል" የሚል ምክረ ሀሳብ ቀርቦ ብዙ ተቃውሞ ቢያጋጥመውም ከሥራ ቡድኑ ወደ ሀሳብ አደራጅ ቡድኑ ተሻግሮ እንደነበር ገልጸዋል።

"ይህ የኢትዮጵያውያን እሴት አይደለም። ሰው በአባቱ ነው የሚጠራው። 'ውህድ' የምትሉት ነገር ለባዕድ እሴት በር የሚከፍት ነው" በሚል ተቃውሞ ሲነሳበት፣ "'ውህድ ማንነት' የሚለው ቀርቶ 'ውህድ የብሔር ማንነት'" በሚል ሀሳቡ አልፎ እንደነበር ተናግረዋል።

120 አባላት ባሉት ሀሳብ አዘጋጅ ቡድን ታይቶ ግን ቡድኑ ትናንት ለ500 ሰዎች ሪፖርት ሲያቀርብ፣ ጉዳዩ ለምን እንዳለፈ ጠይቆ፣ "'እንዲያውም ከሰነዱ ይውጣ' ብሎ እጅ እንዲወጣ ተደርጎ አብዛኛው ነቅፎ እጅ አወጣ። ያን ሀሳብ የሚደግፉ ተጥቂት ሰዎች እዚህ ድረስ የመጣን ሀሳብ 'በአድማ ልትቀለብሱ አትችሉም' በማለታቸው ስምምነት ያልተደረሰበት በሚል አራተኛው ምክረ ሀሳብ ሆኖ እንዲያልፍ ተደርጓል" ብለዋል።

15/08/2026
ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫየተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝብ፤የተከበርከው የአማራ ሕዝብ፤የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ዙሪያ የተሄደባቸውን መንገዶ...
15/08/2026

ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ

የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝብ፤
የተከበርከው የአማራ ሕዝብ፤

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) በሀገራዊ የምክክር ሂደቱ ዙሪያ የተሄደባቸውን መንገዶች፣ የታዩ መዋቅራዊ ግድፈቶችን፣ የመርህ ጥሰቶችን፣ እንዲሁም ሀገራችን ያለችበትን አጠቃላይ የፖለቲካና የደህንነት ሁኔታ በጥልቀት በመገምገም የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል።

የሕዝብ ጥሪ እና የአቋም መግለጫ ነጥቦች፤

አብን ወደ ሀገራዊ ምክክሩ የገባው የኢትዮጵያን ጥልቅ የፖለቲካ ችግሮች በኃይል ሳይሆን በውይይት፣ በጫና ሳይሆን በመደማመጥ፣ በአንድ ወገን የበላይነት ሳይሆን በድርድርና በጋራ መግባባት፣ እንዲሁም አንዱ አሽናፊ ሌላው ተሸናፊ የሚሆንበት ሳይሆን ሁሉንም ወገን አሽናፊ በሚያደርግና ኢትዮጵያዊነትን ማዕከል ባደረገ የሰጥቶ መቀበል መርህ ለመፍታት የሚያስችል እውነተኛ ሀገራዊ መድረክ ይፈጠራል በሚል እምነት ነበር።

ሆኖም በሂደቱ ውስጥ የታየው ሁኔታ ከተራ የአሠራር ግድፈት ወይም ከመደበኛ የፓለቲካ ልዩነት የዘለለ ሆኖ አግኝተነዋል። የምክክር ሂደቱን ተዓማኒነት፣ አካታችነት፣ ገለልተኝነት እና ፍትሐዊነት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገቡ ተደጋጋሚና የተደራጁ ጥፋቶች ተፈጽመዋል። በገዢው አካል የተፈጸሙ መዋቅራዊ ጥሰቶች፣ ጫናዎች እና ወገንተኛ አካሄዶች ምክንያት ሂደቱ የሚጠበቅበትን ያህል ውጤታማ እንዳይሆን ከፍተኛ ስጋት ደቅነዋል።

በዚህ ረገድ ሀገራችን ኢትዮጵያ በታሪኳ ካጋጠሟት ውስብስብ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ፈተናዎች መካከል አሁን ያለንበት ወቅት ከፍተኛ ጥንቃቄና አስተዋይነትን የሚጠይቅ ነው። ከዚህ አኳያ የሚከተሉት መሠረታዊ ጉዳዮች በጥንቃቄ እንዲታዩ እናሳስባለን።

1. የአዲስ አበባ ህዝብ ውክልና እና የራስ-አስተዳደር መብት፣
በምክክሩ ሂደት ወቅት በአዲስ አበባ ከተማ ህልውና፣ ባለቤትነት እና የራስ-አስተዳደር መብት ዙሪያ የታየውን የክህደት ተግባር በትኩረት መከታተል ያስፈልጋል። በከተማዋ ኢኮኖሚያዊና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ብቻ ሳይሆን የከተማዋን ባለቤትነትና ተጓዳኝ የፖለቲካ እና የህግ ማዕቀፎችን በሚመለከቱ መሠረታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በሚመከርበት መድረክ ላይ በበርካታ ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የከተማዋ ነዋሪዎች ድምፅና ፍላጎት ባግባቡ ሳይወከልና የከተማዋ ሕዝብ እንደ ዋና ባለቤት (Body Politic) ሳይቆጠር መታለፉ እጅግ አሳሳቢ ገመና ሆኖ ተመዝግቧል።

የከተማዋን ነዋሪዎች መብትና ዘላቂ ጥቅም ያስከብራሉ ተብለው የተወከሉ አካላትም የተጣለባቸውን አደራ በመዝንጋት የአንድን ወገን አካል ያልተገራና ድንበር የለሽ ፍላጎት ለማስፈጸም ሲሉ የከተማውን ህዝብ መብትና ጥቅም አሳልፈው ሲስጡ ተመልክተናል።

ስለሆነም የአዲስ አበባ ከተማ ህዝብ የከተማችሁን ህልውና እና መብት የሚመለከቱ ጉዳዮቹንና በዚህ ዙሪያ የሚደረጉ ውይይቶችን በከፍተኛ ንቃት እንድትከታተሉ፤ የራስ-አስተዳደርና የፖለቲካ መብታችሁን እና መጻኢ እድላችሁን ብህጋዊ መንገድ ለማስከበር በአንድነት እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

2. ድብቅና መንታ የፖለቲካ ስልቶች፣ መዋቅራዊ ስጋቶች፤

ስርዓቱ በአደባባይ የሚስተጋባቸው የሀገራዊ አንድነት፣ የጋራ ብልፅግና፣ የዜጎች እኩልነት፣ የህብረ-ብሔራዊ ወንድማማችነትና የመሻገር ድስኩሮች በተግባር መሬት ላይ ካለው እውነታ ጋር የሚጻረሩና ሰፊ ክፍተት ያለባቸው እንደሆኑ የምክክር ሂደቱ ፍንትው አድርጎ አሳይቶናል። አጠቃላይ የፖለቲካ ሂደቶችን በጥንቃቄና በሚዛናዊነት ስንመረምር (Hermeneutics of Suspicion) በአንድ በኩል ስለ ሀገራዊ አንድነትና ወንድማማችነት እየተሰበከ፣ በሌላ በኩል መንግሥታዊ መዋቅሮችን ለአንድን ቡድን ፍላጎት ማስፈጸሚያነት የማዋል ሙከራ እንደሚደረግ በስፋት አስተውለናል።

ከአዲስ አበባ በመቀጠል ጎልቶ የወጣው የመንግስት አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊዎች በምክክሩ መካከል ድንገት "በፓርላማ የሚመረጥ ፕሬዚደንት" ይሁን በሚል ያቀረቡት አማራጭ ነው። ለዚህም የደቡብ አፍሪካን ተሞክሮ በማጣቀስ ለማቅረብ ሞክረዋል። ነገር ግን ከንጽጽር ጥናት መርኅ አኳያ የኢትዮጵያ ሁኔታ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ፍጹም እንደማይመሳሰል በመግለጽ የቀረበው ሃሳብ የምድብ ስህተት (category error) እንዳለበት አስገንዝበናል። እንደሚታወቀው ደቡብ አፍሪካ አካታችና ስኬታማ የፖለቲካ ሽግግር ያደረገች፣ ጠንካራ እና ነፃ የሲቪክ ማህበራት ያሏት፣ የዳበረ የዲሞክራሲ ባህልና ህገ-መንግስታዊ ስርአት ያላት ሀገር ነች። ስለሆነም እነዚህ መሠረታዊ ተቋማዊና ፖለቲካዊ ባህሎች በሌሉባት ኢትዮጵያ፣ የደቡብ አፍሪካን ተሞክሮ በይስሙላ እያጣቀሱ ለማቅረብ መሞከር የህዝብን ትኩረት ለማሳትና አምባገነንነትን በህግ ለማፅናት የሚደረግ ሙከራ ነው።

በሊላ በኩል ድርጅታችን አብን ለሀገራችን የፕሬዚዳንታዊ ወይም ከፊል-ፕሬዚዳንታዊ ስርዓት አማራጭን ያቀረበ ሲሆን አላማውም—ዕጩዎች የመላው ሀገሪቱን ዜጎች ድምፅ ለማግኘት ሲሉ ድንበር ተሻጋሪና አስተሳሳሪ የሆኑ ሀገራዊ የፖለቲካ (Cross-cutting & Unifying Politics) አጀንዳዎችን እንዲያራምዱ ያስገድዳል በሚል እምነት ነው። በገዢው አካል በኩል የቀረበው ግን በሂደት ስልጣንን በአንድ ግለሰብ ወይም ቡድን እጅ ለማከማቸትና አምባገነንነትን ህጋዊ ሽፋን ከመስጠት ያለፈ ፋይዳ እንደሌለው ሊታወቅ ይገባል።

በተጨማሪም በአንድ በኩል ትልልቅ ሀገራዊና ቀጠናዊ አጀንዳዎችን ደጋግሞ በማስተጋባት፣ ሆኖም በተግባር የአዲስ አበባ ከተማን መሬትና አስተዳደር በተናጠል የመቆጣጠር ፍላጎት ይታያል። ይህ አካሄድ ሀገራችንን ወደ ተሻለ ዴሞክራሲያዊ ስርአት ከማሸጋጋር ይልቅ የፖለቲካ ችግሮቻችንን ይበልጥ የሚያወሳስብ በመሆኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ሂደቱን በጥንቃቄ ሊከታተለውና ሰላማዊ ትግል ሊያደርግበት ይገባል።

3. የአብን አቤቱታዎች፣ የቀጠሉ ጥሰቶች እና ቀሪው የምክክር ሂደት፤

ድርጅታችን በምክክር ሂደቱ ውስጥ የታዩትን አግላይና አፋኝ አካሄዶች በዝምታ አላለፋቸውም። ይልቁንም በሂደቱ የታዩትን ያልተገቡ ጣልቃገብነቶችና ሕገ-ወጥ ድርጊቶች በጽናት በመቃወም የሚከተሉትን እርምጃዎች ወስዷል፦

ሀ/ ለሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ፦ሁለት ጊዜ መዋቅራዊ ግድፈቶች እንዲታረሙ የሚያስገነዝቡ ይፋዊ የአቤቱታ ደብዳቤዎችን አስገብተናል፤ ሁለት ጊዜ በጊዜያዊ የኮሚሽኑ ጽሕፈት ቤት ተገኝተን በሂደቱ ላይ ያየናቸውን ስጋቶች በፊት ለፊት ውይይት አስረድተናል።

ለ/ ለገዢው የብልፅግና ፓርቲ ጽሕፈት ቤት፦ የሚፈጸሙ ጥሰቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ የሚያሳስብ ደብዳቤ የጻፍን ሲሆን፣ ከፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ጋር በአካል ተገናኝተን የተፈጸሙትን ጥሰቶችና አላስፈላጊ ጣልቃገብነቶች በመጥቀስ ባስቸኳይ እንዲታረሙ በአጽንኦት ጠይቀናል። ነገር ግን እስካሁን ድረስ እነዚህን መሠረታዊ ግድፈቶች ለማረም የተወሰደ አዎንታዊ እርምጃ አለመኖሩ እጅግ አሳዛኝ ነው።

እስካሁን ከታዩት አጠቃላይ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች በመነሳት ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሊገነዘቡት የሚገባው ዋና ነጥብ፦ ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ አንድ እርምጃ ወደፊት በሄደ ቁጥር፣ ገዢው አካል የራሱን የፖለቲካ ፍላጎት ለማስፈጸም የሚያደርገው ስልታዊ ተፅዕኖ እና ጣልቃገብነት እየጨመረ እንደሚሄድ አሁናዊ ሁኔታዎች ያመላክታሉ። በተለይም ገዢው አካል በቁጥጥሩ ስር ያሉትን የፓርላማ፣ የህግ አስፈጻሚና የጸጥታ መዋቅሮች በመጠቀም ከምክክር መድረኩ የሚመጡ ምክረ-ሀሳቦችን በተዛባ መልኩ ወደ ራሱ የፖለቲካ መስመር ለማስገባት ሊሞክር ይችላል።

ሆኖም በዚህ ዙሪያ ያለንን ጽኑ አቋም ዳግም በመግለጽ—እነዚህ መዋቅራዊ ጥሰቶች የሚቀጥሉ ከሆነ፣ እንዲሁም አንድ ወገን ብቻውን የሚወስንበት፣ አግላይና አምባገነናዊ ስርዓትን የመጫን እንቅስቃሴ የማይቆም ከሆነ ድርጅታችን አብን በከፍተኛ ንቃትና ብስለት ሂደቱን ከመከታተል ባለፈ፣ አሁንም ይሁን ወደፊት ለእንደዚህ ዓይነቱ የይስሙላ የፖለቲካ ድራማ (Facade) ፈጽሞ እውቅና የማንሰጥና የማንተባበር መሆናችንን በአጽንኦት እንገልፃለን።

ከፊታችን ያለው መንገድ ፈታኝ ቢሆንም፣ ያሉትን ክፍተቶች ለማስተካከልና አገራዊ መግባባቱን ወደ ትክክለኛ አቅጣጫ ለማስኬድ የተሻለ የፖለቲካ ንቃት፣ ጥንቃቄና ብርቱ ሰላማዊ ትግል ማድረግ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን እንረዳለን። በመሆኑም ህዝባችን በቀሪዎቹ የምክክር ምዕራፎችና በቀጣይ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በንቃትና በተደራጀ መንገድ እንዲሳተፍ እናሳስባለን።

4. ለሚዲያዎች የቀረበ ማሳሰቢያ፤

ሀገራዊ የምክክር ሂደቱ አሁንም እየተካሄደ ባለበትና ድርጅታችን አብን የተፈጸሙትን ጥሰቶችና መዋቅራዊ ግድፈቶች ለኮሚሽኑ፣ ለገዢው ፓርቲና ለመላው ህዝባችን ይፋ ባደረገበት በዚህ ወቅት፤ አንዳንድ የግል ሚዲያዎችና የመንግስት ብዙኃን መገናኛዎች የተሳሳቱ ዘገባዎችን (*Wrong Framing*)፣ የተቀናጁ ሀሰተኛና አሳሳች መረጃ የማሰራጨት ዘመቻዎችን (Disinformation & Misinformation Campaigns) በማካሄድ ላይ ይገኛሉ።

እነዚህ ሚዲያዎች ያቀረብናቸውን መሠረታዊ አቤቱታዎች አፋልሰው በማቅረብ፣ የገዢውን አካል አጀንዳዎች ብቻ በማቀንቀን፣ እስካሁን የነበረውን ሂደትና ውጤት ሆነ ብለው በተዛባ መልኩ በመዘገብ የቀረቡ ቅሬታዎችን ዋጋ ለማሳጣትና የገዢውን አካል የወደፊት የፖለቲካ ፍላጎት ህጋዊ ለማስመሰል የሚያደርጉት ጥረት መሆኑን ታዝበናል።

በመሆኑም አብንም ሆነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የእነዚህን ሚዲያዎች ወገንተኛና አድሏዊ አካሄድ በደንብ እንደሚያውቁትና በንቃት እንደሚከታተሉት እናምናለን። ሚዲያዎቹ ሚዛናዊና ነፃ የመረጃ ሽፋን የመስጠት ሙያዊና ታሪካዊ ኃላፊነታቸውን የዘነጉ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ከእንደዚህ ዓይነቱ አሳሳችና የአንድ ወገን አጀንዳን ለማስፈጸም ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ እንዲቆጠቡ በጥብቅ እናሳስባለን።
5. ለተከበረው የኦሮሞ ሕዝብ የቀረበ ጥሪ፤

ድርጅታችን አብን "ለተከበረው የኦሮሞ ሕዝብ በከፍተኛ አክብሮትና በኃላፊነት ስሜት ሀገርን በጋራ እናሻግር የሚል" ጥሪ ያቀርባል። በኦሮሞ ህዝብ ስም የጸነፈ ፖለቲካ የሚያቀነቅኑ ኃይሎች የሚያራምዱት የአካባቢያዊነትና አግላይ ፖለቲካ የሰፊውን የኦሮሞ ህዝብ ዘላቂ ጥቅም ሊያስከብ አይችልም።

በተለይ አዲስ አበባ የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ አንጡራ የአንድነት ጌጥ እና የሉአላዊነታችን መገለጫ፣ የፌደራል መንግሥቱ መቀመጫ እና የነዋሪዎቿ የራስ-አስተዳደር ማዕከል ሆና እንድትቀጥል አብን ያቀረበው ምክንያታዊ እና ሚዛናዊ የመፍትሔ ሀሳብ ለመላው የሀገሪቱ ህዝብ የሚጠቅም ከመሆኑ በተጨማሪ ወንድም የኦሮሞ ህዝብም ከአዲስ አበባ እንደሌላው ኢትዮጵያዊ ከሚያገኘው ትሩፋት በተጨማሪ ከዘላቂ ሰላምና ከጤናማ ሀገራዊ ፖለቲካ አኳያ የሚመዘኑ ጥቅሞችን ስለሚያረጋጥ ነው።
ስለሆነም በኦሮሞ ህዝብ ስም የሚደረግ ማናቸውም የብቸኛ ባለቤትነት ወይም የሌሎችን መብት የመጋፋት ፍላጎት፣ በህዝቦች መካከል የቆየውን ታሪካዊ ወንድማማችነት እና አንድነት የሚጎዱ በሂደትም የኦሮሞን ህዝብ የሚነጥልና የሚጎዳ የታሪክ ስህተት እንዳይሆን ለማሳሰብ እንወዳለን።
ከዚህ ውጭ ኦሮሚያ ከከተማዋ ባላት መልከዓ-ምድራዊ ቅርበት የተነሳ የሚያገኘውን የማህበረ-ኢኮኖሚ ጥቅሞችንና የመሰረተ-ልማት ትስስርንም እንደ-ጸጋ በመውሰድ በቀጣይ የላቀ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንዲሁም ከኢንዱስትሪዎች እና ከከተማዋ መስፋፋት ጋር በተያያዘ የሚከሰቱ ችግሮች በዘላቂነት እንዲቀረፉ በሚደረጉ ትግሎች ከኦሮሞ ህዝብ ጎን እንደምንቆም ጥርጥር የለውም።

በተጨማሪም ድርጅታችን አብን በአማራ ህዝብ ስም በአንዳንድ አካላት የሚሰነዘሩ አክራሪ ፍላጎቶችን (Maximalist Claims) እና ህዝባችንን የማይገልጹ አስተሳሰቦችን ውድቅ በማድረግ መሀለኛና አሰታራቂ ሀገራዊ መፍትሔዎች ላይ አበክሮ እየሰራ እንደቆየው ሁሉ የኦሮሞ የፖለቲካ ኃይሎችም ህዝብን ከህዝብ የሚያጋጩና በኦሮሞ ህዝብ ስም ፍላጎታቸውን በኃይል ለመጫን የሚሞክሩ አካላትን አቋም ውድቅ በማድረግ ለእውነተኛ የጋራ እድገትና ሰላም በጽናት እንዲቆሙ ታሪካዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

6. ለተከበርከው የአማራ ሕዝብ፤

ካለፉት ስርዓቶች የተወረሰው ጸረ-አማራ ትርክት ባለመቀልበሳቸው በምክክር ሂደቱም በተወሰኑ አካላት አማካኝኘት ሲንጸባረቁ ከመታየታቸው በተጨማሪ በህዝባችን ላይ የተጋረጡ መዋቅራዊ መድሎወች አሁንም እንደቀጠሉ ናቸው። ይህንን ፈተና ለመሻገር ሰፊና የተደራጀ የቤት ሥራ ከፊታችን ይጠብቀናል። ስለሆነም በዚህ አሳሳቢ ወቅት ከከፋፋይ አመለካከቶችና ከፍረጃ አዙሪት በመላቀቅ በአንድነት እንዲቆም እና በሕዝባችን መካከል ቅራኔንና ክፍፍልን የሚዘሩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አስፈላጊውን ሁሉ እንዲደረግ እያሳሰብን አሁን ያለንበት ወቅት በውስጥ ልዩነቶች ላይ ጊዜ የምናባክንበት ሳይሆን ለህልውናችን፣ ለእኩልነታችንና ለዘላቂ ሰብአዊ ደህንነታችን በጋራ የምንቆምበት መሆኑን እንገልጻለን።

7. ለፖለቲካ ፓርቲዎች እና ለኢፌድሪ መንግሥት የቀረበ ጥሪ፤

የሀገራችን የፖለቲካ ፓርቲዎች እስካሁን የነበረውን የመጠራጠርና የመነቃቀፍ ፖለቲካ በማስወገድ፣ ለሀገርና ለህዝብ ዘላቂ ጥቅም ሲባል በጋራና በስፋት እንድንሰራ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

የኢፌዴሪ መንግስትም እየተከናወነ ያለውን ሀገራዊ የምክክር ለቡድናዊ አላማ ብቻ ከመጠቀም ይልቅ ሀገራዊ ዘላቂ ሰላምን ለማስፈንና ወንድማማችነትን ለማጠናከር እንዲጠቀምበት እና በሀገሪቱ ውስጥ ያለውን የፖለቲካና የማህበራዊ ክፍፍል በልኩ ተረድቶ እውነተኛ የፖለቲካ መታረቂያ መንገዶችን እንዲከተል እና ለጋራ ትግል የተከፈቱ ጭላንጭሎችን እንዳያሰፋ ጥሪ እናስተላልፋለን።

እንዲሁም ስምንት ዓመት በፊት አምባገነኑን፣ አድሏዊውንና ዘውጌያዊውን የኢሕአዴግ ሥርዓት በመጣል አሁን ያለው መንግሥት ወደ ሥልጣን እንዲመጣ በተደረገው መራራ ትግል ውስጥ መላው የአማራ ሕዝብ ያደረገው እልህ አስጨራሽ ታሪካዊ ተጋድሎ እና የከፈለውን መስዋዕትነት እውቅና የመንፈግ እና ገዢው ቡድን በራሱ ጥረትና አቅም ብቻ ስልጣኑን እንደተቆጣጠረ አድርጎ የመውሰድ ዝንባሌ ከወዲሁ እንዲታረም በአጽንኦት እንመክራለን።

8. ለተከበርከው የኢትዮጵያ ሕዝብ፤

አብን የሕዝቡን ታሪካዊ አደራ በመሸከም ለመላው ኢትዮጵያዊያን የተመቸ ሀገራዊ ስርዓት ይገነባ ዘንድ መዋቅራዊ ችግሮችን በጽናትና በሰለጠነ መንገድ እየታገለ ያለ ሀገራዊ ፓርቲ ነው። እያከናወን ያለነው ትግል የፍትህ፣ የእኩልነት እና የነፃነት ትግል የሕግ የበላይነትና እውነተኛ ዴሞክራሲ ማረጋገጥን ያለመ መሆኑን አውቆ አላማችን ከግብ እንዲደርስ ከጎናችን እዲቆሙ ለመላው ኢትዮጵያዊያን ጥሪ አናቀርባለን።

በመጨረሻም ለሀገራችን የፖለቲካ ቀውስ ዘላቂው መፍትሔ እውነተኛ ምክክር፣ ድርድር፣ በሰጥቶ-የመቀበል ላይ የተመሰረተ የጋራ ድል እና ወንድማማችነት ብቻ ነው" ብለን የምናምን መሆናችንን እናረጋግጣለን።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)**
ነሐሴ 08/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

የማህበረሰብ ተወካዮች ጥረት አበረታች ምላሽ ያገኘ ሲሆን አፈጻጸሙ እንዲሳካ የሁሉንም አካላት ቁርጠኝነት ይጠበቃል የጣርማ በር ሰፌድ ሜዳ መንገድ ፕሮጀክት በቆረጣ ምክንያት ከተቆፋፈረ በኋላ ...
10/08/2026

የማህበረሰብ ተወካዮች ጥረት አበረታች ምላሽ ያገኘ ሲሆን አፈጻጸሙ እንዲሳካ የሁሉንም አካላት ቁርጠኝነት ይጠበቃል

የጣርማ በር ሰፌድ ሜዳ መንገድ ፕሮጀክት በቆረጣ ምክንያት ከተቆፋፈረ በኋላ ግንባታው በመቋረጡ የመንዝ፣ የግሼ፣ የጣርማ በር እና አካባቢው ማህበረሰብ እያሳለፈ ያለው መከራ ክረምት ታክሎበት እጅግ ለከፋ ለሰው ሰራሽ ስቃይ ተዳርጓል። የኢኮኖሚ ድቀቱ እንደተጠበቀ ሆኖ ለታማሚ ህክምና ለነፍሰጡሮች የጤና አገልግሎት ማስገኘት አዳጋች ከሆነ ሰነባብቷል።

በዛሬው እለት ነሓሴ 4 ቀን ይህን የሚሊዮች መሰረታዊ አጀንዳ ይዘው የመጡ የማህበረሰብ ተወካዮች ለሚመለከታቸው የፌደራል ተቋማት የህዝቡን ስቃይ በማስዳትና በመፍትሄዎች ምክክር ተደርጓል። የህዝብ ተወካዮቹ እና የፌደራል መንገዶች ባለስልጣን አመራሮች ባደረጉት ውይይት መደበኛ የግንባታ ስራው እስኪጀመር መንገዱ ጊዜያዊ የጥገና ስራ እንዲከናወንና መግባባት ላይ ተደርሷል። ባለስልጣኑ በሙያተኛ፣ በበጀትና በግንባታ ግብአት ረገድ ዝግጁ መሆኑንና ወደስራ ለመግባት መወሰኑን ገልጾ ከማህበረሰቡና ከሁሉም ባለድርሻዎች ሊደረጉለት የሚጠበቁ እገዛዎችን በዝርዝር አስረድል።

የማህበረሰብ ተወካዮቹም ከዚህ የባሰ አንገብጋቡ አጀንዳ እንደሌለና ሁሉንም አቅማቸው በፈቀደ ህዝባዊ ድጋፍ እንደሚያስተባብሩ ቃል ሰጥተዋል። ከባለስልጣኑ ጋር የተደረገው ውይይት ከተጠናቀቀ በኋላ የልኡካኑ አባል የሆኑ አዛውንቶች "ህዝባችን እንዲህ አይነት አበሳ የዛሬ 50 አመት እንኳ እንዳልገጠመው እና ለችግሩ መፍትሄ ካስገኘ ማንኛውንም ዋጋ ለመክፈል" መዘጋጀታቸውን ሲገልጹ ሲቃ እየተናነቃቸው ነበር።

ለረጅም ጊዜ ሲደረጉ የቆዩ እና እየተጠናከሩ የመጡት የህዝብ ንቅናቄዎች በዛሬው የውይይት አቅጣጫ መሰረት ወደተግባር ለመግባት ቁሳዊና ሞራላዊ ግብአቶች ናቸው። በመሆኑም በደብረብርሀንና በሸዋሮቢት ያሉ የመንገዶችና ትራንስፖርት ባለስልጣን አስተባባሪዎችና ሙያተኞች ከማህበረሰብ ተወካዮቹ፣ እና ባለድርሻዎች ጋር በመናበብ በአፋጣኝ ወደ ተግባር ለመግባት የተፈጠረውን መደላድል ተጠቅመው ወደአፈጻጸም መግባች ይጠበቅባቸዋል። ህዝብ ከፊት ቀድሞ እያስተባበረ ባለበት ሁኔታ መሬት ላይ የሚከወኑ የአፈጻጸሞች ስራዎች ቀላል ናቸው።

ሲጠቃለል ለህዝቡ ከዚህ የባሰ የነጻነትና የህልውና ጥያቄ ስለሌለ በምንም አይነት ሰበብ ኮምፕሮማይዝ የሚደረግ ጉዳይ እንዳይደለ የትኛው ባለድርሻ አካል ሊገነዘብ እና ችግሩ እንዲቃለል በተግባር የሚገለጽ አሻራውን ማሳረፍ ይኖርበታል።

( 'እግረኛው' በተሰኘው የዩቲዩብ ቻናሉ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖት ቀጠሮ ተጠይቆበታልየፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛውን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረ...
31/07/2026

( 'እግረኛው' በተሰኘው የዩቲዩብ ቻናሉ የሚታወቀው ጋዜጠኛ ተክለሀይማኖት ቀጠሮ ተጠይቆበታል

የፌዴራል ፖሊስ ጋዜጠኛውን ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አንደኛ የወንጀል ችሎት ያቀረበው ሲሆን፣ "ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨትና ፍትህን ለማዛባት በመሞከር" ወንጀል እንደጠረጠረው ለችሎቱ አስታውቋል።

ፍርድ ቤቱም የፖሊስን የክስ መዝገብ ከመረመረ በኋላ፣ የቀረበለትን የጊዜ ቀጠሮ ጥያቄ በመቀበል ለሐምሌ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። በመሆኑም አቶ ተክለሀይማኖት እስከ ቀጠሮው ዕለት ድረስ በማረሚያ ቤት በእስር የሚቆይ ይሆናል።

የጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር መዋል መነሻ ምክንያት በውል ባይታወቅም በቅርቡ ከ'ፊንቴክ' (Fintech) የመኪና ማጭበርበር ጉዳይ ጋር በተያያዘ ክስ ከተመሰረተባቸው አርቲስቶች ጋር ያደረገው ቃጠይቅ የፍትህ ስርዓት ሂደትን የሚያዛባና በዳኝነት/በፍርድ አሰጣጥ ላይ ጫና የሚፈጥር በመሆኑ ሊያሳስረው ይችላል።

ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ !የ"እግረኛው ሚዲያ" መስራችና ባለቤት የሆነው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።ጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር የዋ...
31/07/2026

ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ !

የ"እግረኛው ሚዲያ" መስራችና ባለቤት የሆነው ጋዜጠኛ ተክለሃይማኖት አዳነ በቁጥጥር ስር መዋሉ ተሰምቷል።

ጋዜጠኛው በቁጥጥር ስር የዋለው በትናንትናው ዕለት ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሆነ የታወቀ ሲሆን፣ ለእስሩ ምክንያት ከመከላከያ ሰራዊት አልባሳት (ዩኒፎርም) ጋር ተያይዞ ከቀረበው ዘገባ ጋር ሳይያያዝ እንዳልቀረ ምንጮቹ ጠቁመዋል ሲል ጉርሻ page ነው የዘገበው።

Address

Addis Abeba
Addis Ababa
43657

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share