01/09/2026
ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ፤
*****
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤
ውድ አገራዊና ሰብዓዊ ጉዳዮች የሚያሳስባችሁ ወገኖቻችን፤
አገራችን ኢትዮጵያ በምትገኝበት በዚህ ውስብስብና ፈታኝ ወቅት የዜጎች በሕይወት የመኖር ተፈጥሮአዊ መብት፣ የደኅንነት ዋስትና እና የሕግ የበላይነት መከበር የአገራችን ዘላቂ ሰላምና አንድነት መሠረቶች ናቸው። በየትኛውም የአገራችን ክፍል የሚኖሩ ዜጎች ከሥጋት ነፃ ሆነው የመንቀሳቀስ፣ የመሥራትና በሰላም የመኖር መብታቸውን ማስከበር የትኛውም መንግሥታዊ ሥርዓት የመጨረሻውና ዋናው የመኖሩ ዋስትና ነው።
ሆኖም ግን ከሰሞኑ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በንጹኃን ዜጎች ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶችና የተከሰቱት ተደጋጋሚ ሰብዓዊ ቀውሶች፣ የመንግሥትን መሠረታዊ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ውድቀት እንደገና በግልጽ ያሳዩ በመሆናቸው ንቅናቄያችን አብን በጥልቅ አሳስቦታል።
1/ የሰብዓዊ ቀውሱ አሳሳቢነት እና የመንግሥታዊ መዋቅር ተጠያቂነት
ከሰሞኑ በምሥራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ፣ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ቀርሳ ማሊማ ወረዳ፣ በምሥራቅ አርሲ እና በሰሜን ሸዋ ዞኖች አሊ ዶሮና አካባቢው በንጹኃን ዜጎች የተፈጸሙት የማንነትና የዕምነት ተኮር የግድያ፣ የንብረት ውድመት፣ የማፈናቀል እና የእምነት ተቋማት ጉዳቶች፣ እና የተጓዥ መንገደኞች ተደጋጋሚ እገታ የአገራችንን ሰላም እና ማኅበራዊ አንድነት በእጅጉ እየጎዱ ይገኛሉ።
እነዚህን ተደጋግመው የሚከሰቱ ሰብዓዊ ቀውሶችና የዜጎች ሰቆቃዎችን በተመለከተ ንቅናቄያችን የሚከተሉትን መሠረታዊና ተጠያቂነትን በጥብቅ የሚሹ ነጥቦችን ማንሳት ይፈልጋል፦
ሀ/ ጥቃቶቹን በቀጥታ የሚፈጽሟቸው አማፂያን፣ ታጣቂዎች ወይም የትኛዎቹም አካላት ይሁኑ የዜጎችን ሕይወትና ንብረት ከጥቃት የመጠበቅ፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር እና የዜጎችን ደኅንነት የማረጋገጥ ቀዳሚና የመጀመሪያ ደረጃ ሕገ-መንግሥታዊ ኃላፊነት የመንግሥት ነው። ጥቃቶችን በታጣቂዎች ላይ ብቻ በማሳበብ መንግሥት ከተጠያቂነት ነፃ ሊሆን አይችልም!
ለበርካታ ዓመታት በክልሉ ንጹኃን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች ተባብሰው መቀጠላቸው በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥትና የጸጥታ መዋቅሮች ላይ ከባድ የሕግና የመዋቅር ውድቀት እንዳለ ማሳያ ነው። በዚህ መልኩ በተደጋጋሚ ለሚከሰቱ ጥቃቶች የመንግሥት አካላት የፖለቲካና የሕግ ተጠያቂነት ሳይወስዱ ችግሩን በማድበስበስ ለማለፍ የሚያስችላቸው ምንም አይነት ተቀባይነት የለውም።
ለ/ የትኛውም አገራዊ የልማትና የዕድገት ትርክት ዋጋ ሊኖረው የሚችለው የዜጎች መሠረታዊ የሕይወትና የመንቀሳቀስ መብት ሲረጋገጥ ብቻ ሲሆን፤ የዜጎች የመኖር መብት በተጣሰበት ሁኔታ ስለ አገራዊ ብልፅግናም ይሁን ዕድገት ማውራት ተጨባጭ እውነታን የካደና ቅቡልነት የሌለው አካሄድ ነው። ሰላምና ደኅንነት ለሁሉም አገራዊ ዕቅዶች መሠረታዊ ቅድመ-ሁኔታዎች ናቸው!
2/ የአብን ጥሪና የመፍትሔ አቅጣጫዎች፣
የተከሰቱትን ሰብዓዊ ቀውሶች በአስተማማኝ ሁኔታ ለመቅረፍ፣ የሕግ የበላይነትን ለማስፈን እና የዜጎችን ደኅንነት ዘላቂ በሆነ መንገድ ለማረጋገጥ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የሚከተሉትን ጥብቅ ጥሪዎች ያቀርባል፦
ሀ/ የፌደራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት በወለጋ፣ በምሥራቅ አርሲ፣ በሰሜን ሸዋ እና በሌሎች የሥጋት ቀጠናዎች በአስቸኳይ የተቀናጀና ውጤታማ የሕግ ማስከበር እርምጃ በመውሰድ የንጹኃን ዜጎችን ሕይወትና ንብረት የመታደግ ግዴታቸውን በአስቸኳይ እንዲወጡ እንጠይቃለን።
ለ/ በንጹኃን ላይ ጥቃት ባደረሱ አካላት በጥብቅ ሕግ ከማስፈኑ ጎን ለጎን፣ የዜጎችን ደኅንነት በማስጠበቅ ረገድ በየደረጃው የታዩ ተቋማዊና መዋቅራዊ ድክመቶችን፣ እንዲሁም የባለሥልጣናትን ድዳተኝነትና ኃላፊነት አለመወጣት መርምሮ ግልጽ የሆነ የሕግና የፖለቲካ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እናሳስባለን።
ሐ/ በቀጠናው የሚከናወኑ የጸጥታና የሕግ ማስከበር ስምሪቶች የንጹኃን ዜጎችን ሰላም የሚያረጋግጡ፣ ሕጋዊነትን የተከተሉና ከማንኛውም ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ፣ የብሔራዊ ሰብዓዊ መብት ተቋማትና ገለልተኛ አካላት የሚሳተፉበት የክትትልና የምርመራ ሥርዓት በአስቸኳይ እንዲዘረጋ እንጠይቃለን።
መ/ በጥቃቱ ምክንያት የተፈናቀሉ፣ ንብረታቸው የወደመባቸውና የነፍስ አድን እርዳታ የሚሹ ዜጎቻችን በአስቸኳይ አስፈላጊው የምግብ፣ የሕክምና እና የማህበራዊ ድጋፍ እንዲደርሳቸው፣ እንዲሁም ወደ ቀደመ ቀያቸው ተመልሰው በዘላቂነት እንዲቋቋሙ መንግሥትና የሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች የተቀናጀ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤
የዜጎች ደኅንነት፣ ፍትህና የሕግ የበላይነት ለድርድር የማይቀርቡ አገራዊ እሴቶቻችን ናቸው። ንቅናቄያችን አብን ለዜጎች እኩልነት፣ ለሕግ የበላይነትና ለዘላቂ ሰላም መከበር የሚያደርገውን መርኅ-ተኮር፣ ሰላማዊና ሕጋዊ ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል።
ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ንጹኃን ወገኖቻችን አስቸኳይ ፍትህና ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲሰጥ በድጋሜ በአጽንኦት እንጠይቃለን!
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ከአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የተሰጠ መግለጫ፤
*****
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤
ውድ አገራዊና ሰብዓዊ ጉዳዮች የሚያሳስባችሁ ወገኖቻችን፤
አገራችን ኢትዮጵያ በምትገኝበት በዚህ ውስብስብና ፈታኝ ወቅት የዜጎች በሕይወት የመኖር ተፈጥሮአዊ መብት፣ የደኅንነት ዋስትና እና የሕግ የበላይነት መከበር የአገራችን ዘላቂ ሰላምና አንድነት መሠረቶች ናቸው። በየትኛውም የአገራችን ክፍል የሚኖሩ ዜጎች ከሥጋት ነፃ ሆነው የመንቀሳቀስ፣ የመሥራትና በሰላም የመኖር መብታቸውን ማስከበር የትኛውም መንግሥታዊ ሥርዓት የመጨረሻውና ዋናው የመኖሩ ዋስትና ነው።
ሆኖም ግን ከሰሞኑ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በንጹኃን ዜጎች ላይ የተፈጸሙት ጥቃቶችና የተከሰቱት ተደጋጋሚ ሰብዓዊ ቀውሶች፣ የመንግሥትን መሠረታዊ የዜጎችን ደኅንነት የማስጠበቅ ኃላፊነት ውድቀት እንደገና በግልጽ ያሳዩ በመሆናቸው ንቅናቄያችን አብን በጥልቅ አሳስቦታል።
1/ የሰብዓዊ ቀውሱ አሳሳቢነት እና የመንግሥታዊ መዋቅር ተጠያቂነት
ከሰሞኑ በምሥራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ፣ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ቀርሳ ማሊማ ወረዳ፣ በምሥራቅ አርሲ እና በሰሜን ሸዋ ዞኖች አሊ ዶሮና አካባቢው በንጹኃን ዜጎች የተፈጸሙት የማንነትና የዕምነት ተኮር የግድያ፣ የንብረት ውድመት፣ የማፈናቀል እና የእምነት ተቋማት ጉዳቶች፣ እና የተጓዥ መንገደኞች ተደጋጋሚ እገታ የአገራችንን ሰላም እና ማኅበራዊ አንድነት በእጅጉ እየጎዱ ይገኛሉ።
እነዚህን ተደጋግመው የሚከሰቱ ሰብዓዊ ቀውሶችና የዜጎች ሰቆቃዎችን በተመለከተ ንቅናቄያችን የሚከተሉትን መሠረታዊና ተጠያቂነትን በጥብቅ የሚሹ ነጥቦችን ማንሳት ይፈልጋል፦
ሀ/ ጥቃቶቹን በቀጥታ የሚፈጽሟቸው አማፂያን፣ ታጣቂዎች ወይም የትኛዎቹም አካላት ይሁኑ የዜጎችን ሕይወትና ንብረት ከጥቃት የመጠበቅ፣ የሕግ የበላይነትን የማስከበር እና የዜጎችን ደኅንነት የማረጋገጥ ቀዳሚና የመጀመሪያ ደረጃ ሕገ-መንግሥታዊ ኃላፊነት የመንግሥት ነው። ጥቃቶችን በታጣቂዎች ላይ ብቻ በማሳበብ መንግሥት ከተጠያቂነት ነፃ ሊሆን አይችልም!
ለበርካታ ዓመታት በክልሉ ንጹኃን ዜጎች ላይ የሚፈጸሙ ማንነትና ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች ተባብሰው መቀጠላቸው በየደረጃው በሚገኙ የመንግሥትና የጸጥታ መዋቅሮች ላይ ከባድ የሕግና የመዋቅር ውድቀት እንዳለ ማሳያ ነው። በዚህ መልኩ በተደጋጋሚ ለሚከሰቱ ጥቃቶች የመንግሥት አካላት የፖለቲካና የሕግ ተጠያቂነት ሳይወስዱ ችግሩን በማድበስበስ ለማለፍ የሚያደርጉት ጥረት ይበልጥ ሊያጋልጣቸው ካልሆነ በቀር ምንም አይነት ተቀባይነት አይኖውም።
ለ/ የትኛውም አገራዊ የልማትና የዕድገት ትርክት ዋጋ ሊኖረው የሚችለው የዜጎች መሠረታዊ የሕይወትና የመንቀሳቀስ መብት ሲረጋገጥ ብቻ ሲሆን፤ የዜጎች የመኖር መብት በተጣሰበት ሁኔታ ስለ አገራዊ ብልፅግናም ይሁን ዕድገት ማውራት ተጨባጭ እውነታን የካደና ቅቡልነት የሌለው አካሄድ ነው። ሰላምና ደኅንነት ለሁሉም አገራዊ ዕቅዶች መሠረታዊ ቅድመ-ሁኔታዎች ናቸው!
2/ የአብን ጥሪና የመፍትሔ አቅጣጫዎች፣
የተከሰቱትን ሰብዓዊ ቀውሶች በአስተማማኝ ሁኔታ ለመቅረፍ፣ የሕግ የበላይነትን ለማስፈን እና የዜጎችን ደኅንነት ዘላቂ በሆነ መንገድ ለማረጋገጥ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) የሚከተሉትን ጥብቅ ጥሪዎች ያቀርባል፦
ሀ/ የፌደራልና የክልሉ የጸጥታ አካላት በወለጋ፣ በምሥራቅ አርሲ፣ በሰሜን ሸዋ እና በሌሎች የሥጋት ቀጠናዎች በአስቸኳይ የተቀናጀና ውጤታማ የሕግ ማስከበር እርምጃ በመውሰድ የንጹኃን ዜጎችን ሕይወትና ንብረት የመታደግ ግዴታቸውን በአስቸኳይ እንዲወጡ እንጠይቃለን።
ለ/ በንጹኃን ላይ ጥቃት ባደረሱ አካላት በጥብቅ ሕግ ከማስፈኑ ጎን ለጎን፣ የዜጎችን ደኅንነት በማስጠበቅ ረገድ በየደረጃው የታዩ ተቋማዊና መዋቅራዊ ድክመቶችን፣ እንዲሁም የባለሥልጣናትን ዳተኝነትና ኃላፊነት አለመወጣት መርምሮ ግልጽ የሆነ የሕግና የፖለቲካ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እናሳስባለን።
ሐ/ በቀጠናው የሚከናወኑ የጸጥታና የሕግ ማስከበር ስምሪቶች የንጹኃን ዜጎችን ሰላም የሚያረጋግጡ፣ ሕጋዊነትን የተከተሉና ከማንኛውም ወገንተኝነት የጸዱ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ፣ የብሔራዊ ሰብዓዊ መብት ተቋማትና ገለልተኛ አካላት የሚሳተፉበት የክትትልና የምርመራ ሥርዓት በአስቸኳይ እንዲዘረጋ እንጠይቃለን።
መ/ በጥቃቱ ምክንያት የተፈናቀሉ፣ ንብረታቸው የወደመባቸውና የነፍስ አድን እርዳታ የሚሹ ዜጎቻችን በአስቸኳይ አስፈላጊው የምግብ፣ የሕክምና እና የማህበራዊ ድጋፍ እንዲደርሳቸው፣ እንዲሁም ወደ ቀደመ ቀያቸው ተመልሰው በዘላቂነት እንዲቋቋሙ መንግሥትና የሰብዓዊ ድጋፍ ሰጭ ድርጅቶች የተቀናጀ እርምጃ እንዲወስዱ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች፤
የዜጎች ደኅንነት፣ ፍትህና የሕግ የበላይነት ለድርድር የማይቀርቡ አገራዊ እሴቶቻችን ናቸው። ንቅናቄያችን አብን ለዜጎች እኩልነት፣ ለሕግ የበላይነትና ለዘላቂ ሰላም መከበር የሚያደርገውን መርኅ-ተኮር፣ ሰላማዊና ሕጋዊ ትግል አጠናክሮ ይቀጥላል።
ለተጎዱና ለተፈናቀሉ ንጹኃን ወገኖቻችን አስቸኳይ ፍትህና ሰብዓዊ ድጋፍ እንዲሰጥ በድጋሜ በአጽንኦት እንጠይቃለን!
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን)
ነሐሴ 26/2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ