Zemen Television

Zemen Television በሀቀኛ መረጃ ትውልድ ይሰራል. የሀገር አንድነት ይሰምራል :: 🇺🇸

የሸኔ ቡድን ጫካ በቃኝ ብሎ እጅ እየሰጠ ነው👉 በምስራቅ ጉጂ ዞን ሰባቦሩ  ወረዳ  አዴከላላ ቀበሌ  የሸኔ የሽብር ቡድን ታጣቂ እጃቸውን ሰጥተዋል።    1. ጃል  እፋፍ ገዳ  የቢፍቱ በሪ ...
06/25/2025

የሸኔ ቡድን ጫካ በቃኝ ብሎ እጅ እየሰጠ ነው
👉 በምስራቅ ጉጂ ዞን ሰባቦሩ ወረዳ አዴከላላ ቀበሌ የሸኔ የሽብር ቡድን ታጣቂ እጃቸውን ሰጥተዋል።
1. ጃል እፋፍ ገዳ የቢፍቱ በሪ በርጌድ 1ኛ ሻለቃ አዛዥ
2. ጃል ኑቤካ ሰባ የአጃቦቹ አስተባባሪ
3. ጃል ሙዲ መሃመድ አጃቢ
4. ጃል እፈባሲ ሰባ 3ኛ አጃቢ ሲሆን
👉 የትጥቅ ሁኔታ ፦ - ክላሾች + የክላሽ ጥይቶች + የእጅ ቦምቦች + የወገብ ትጥቆችን በመያዝ እጃቸውን ሰጥተዋል።

የኦነግ ፖለቲካ የመማር እና የፖለቲካ ንቃት መሻሻል አሳይቷል!      # # # # ******** # # # # # # # #******** # # # # # #እንደሚታወቀው የኦነግ ፍልስፍናዊ መሰ...
06/23/2025

የኦነግ ፖለቲካ የመማር እና የፖለቲካ ንቃት መሻሻል አሳይቷል!
# # # # ******** # # # # # # # #******** # # # # # #
እንደሚታወቀው የኦነግ ፍልስፍናዊ መሰረት ብሄራዊ ጥላቻ፣ ነጠላ ትርክትና የበደል ታሪክ አስተሞሮ በመሆኑ በርካታ ማንነት ተኮር ወንጀሎችን ፈጽሟል። የሻቢያና የወያኔ የክፋት አጀንዳ ተሸካሚም ሆነ የኖረ ነው። በዚህም የተነሳ ያከናወነው የትጥቅ ትግል በሲቪሊያን ላይ ሰቆቃ ከማድረስ ውጭ ለስልጣን ሳያበቃው ቆይቷል። ሆኖም በሂደት ንቃት እየጨመረና የፖለቲካ ካርድ ከሚያስጥል ፕሮፓጋንዳ እየተቆጠበ እንደመጣ የሚያሳዩ ሶስት (3) ምክንያቶችን መጥቀስ ይቻላል።

አንደኛ ኦነግ በሚንቀሳቀስባቸው ቀጠናዎች ንጹሀንን ገድሎ፣ አፈናቅሎና ዘርፎ ሲያበቃ ከደሙ ንጹህ ነኝ የሚል መግለጫ በማውጣት የሚቀድመው የለም። በሌሎች በዋናነት በመንግስታዊ ቡድኑ ያመሀኛል። አንዳንዴ በመንግስት ውስጥ በሰረጉ አባላቱም በኩል ብሄር ተኮር ጥቃትን በማስጀመር አስፋፍት ያስቀጥልና ድርጊቱን አውጋዥ ሆኖ ይቀርባልም። በዚህ መልኩ በአለም አቀፍ ወንጀል ሊያስጠይቀው የሚችል ነጥብ ላመጣል ይጥራል። ሁለተኛ የሰላም እና ድርድር ሀሳብ ሲቀርብለት "አልደራደርም- ስልጣን የመወስደው በጦርነት ብቻ ነው" የሚል አቋም በማራመድ ነጥብ አይጥልም። ማህበረሰቡ መደራደር ባይሻ እንኳ አልደራደርም ከማለት ይልቅ ጋሬጣ የሆኑ ቅድመ-ሁኔዎችን የህዝብ ጥያቄ አስመስሎ በማቅረብ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለፍትህና ለሰብአዊነት የሚታገል መስሎ ይቀርባል።የሽብር ድርጊት ቢፈጽምም ለዚህ ማረጋገጫ ከሚሆኑ መግለጫዎች ይቆጠባል።

ሶስተኛ ኦነግ-ሼኔ ራሱን የኦሮሞ ተወካይ አስመስሎ ያቅርብ እንጂ ከራሱ ተገንጥለው ሰላማዊ መንገድ ከመረጡ አካላት ጋር በመፋተግ ብዙ ጊዜ አያጠፋም። ለምሳሌ ህጋዊ ሰውነት ወስዶ ስልጣን የተጋራው የኦነግ ክንፍ ጉባኤ ሲያደርግ እና በአዲስ አበባ ዋና መስሪያ ቤቱን ሲያስመርቅ በጫካ ያለው ቡድን ሲቃወም አናይም። በሀገር ውስጥና በድያስፖራ ያሉ የኦነግ ደጋፊዎች ዩቲዩብ ላይ እየወጡ ስልጣን የተጋራውን የነቀጀላን ኦነግ ሲያወግዙ አይውሉም። ይፍረሱ የሚል ዘመቻማ የለም-በአንጻራዊነት ተቋም ለማፍረስ የመክለፈለፍ ልማድ እየተገታም ይመስላል። እነከማል ገልቹ እና ወደ ቤተ-መንግስት ቀርበዋል የተባሉትን እነዲማ ነጋዎን፣ ሌንጮ ባቲን ወዘተ በጠላትነት ፈርጆ የማጥፋት የሚዲያ ዘመቻስ አለ? ሌላው ቀርቶ የሽምቅ ውጊያ በቃኝ ብሎ ከጃል መሮ የተገነጠለው የጃል ሰኚ ቡድን ከመሮና ከደጋፊዎቹ የተሰነዘረበት ውግዘት አናሳ ነው። ቶሎ በርዷል። እንዲሁም የሰላም ጥሪ የሚያቀርቡ የፖለቲካ ኃይሎችን በባንዳነት፣ በከሀዲነት፣ በሆዳምነት የመፈረጅ ሁኔታ እምብዛም ነው ወይም በአንጻራዊነት በተለይም በአማራ ካለው ሁኔታ አንጻር የማጠልሸት ፖለቲካ ቀንሷል ማለት ይቻላል።

ይህን የመማርና የመሰልጠን ማሳያ ተደርጎ የሚወሰድ ሁኔታ ሀገራዊ ሰላምንና ፍትህን ለማምጣት ምን ፈይዷል? እና በጥላቻ ትርክት የተቃኘውን የፖለቲካ አየር ለውጧል ወይ? ወዘተ ከሚሉ ጥያቄዎች አንጻር ከመዘነው ፋይዳው ሊቀልብን ይትላል ይሆናል።

የጎሳ ወረዳ አስተዳደር፣ የጉሳ  ብሄር ልዩ ወረዳ፣ የብሄር ዞን፣ የብሄር ክፍለ-ከተማ የብሄረሰብ ክልል የመመስረት ጥያቄ  እንደአሸን እየተፈሉ ናቸው። ከጋሞ ዞን ሁለት ጎሳዎችና እና አንድ ...
06/18/2025

የጎሳ ወረዳ አስተዳደር፣ የጉሳ ብሄር ልዩ ወረዳ፣ የብሄር ዞን፣ የብሄር ክፍለ-ከተማ የብሄረሰብ ክልል የመመስረት ጥያቄ እንደአሸን እየተፈሉ ናቸው። ከጋሞ ዞን ሁለት ጎሳዎችና እና አንድ የራሱ ቋንቋ ያለው ብሄረሰብ የማንነት አስተዳደር አስመላሽ ፖርቲዎች እና ኮሚቴዎች አደራጅተው በመበቀት ላይ ናቸው። ይከጉራጌ ዞን ማረቆ፣ መለኔ እና ቀበና በረዶ የተቀላቀለበት የወሰን ማስመለስ እና የመገንጠል ጥያቄ አላቸው። በአማራ ክልል የወያኔ እጅ ስራ የሆነው የቅማንት ኮሚቴ በአንድ በኩል በክላሽ በሌላ በኩል በፓርቲ የድጎማ በጀት ያለው ወረዳ እና ክልል አማረኝ እያሉ ይገኛሉ። ኦሮሚያ ትግረ ወርጅን ጨምሮ ብዙዎችን በዝሆን ኩምቢ ገላምጣ የማንነት ዘጭ ዘጭን ጸጥ ረጭ በማድረጓ ጫጫታ አጥፍታለች።
ምንጫችን በዛሬው አለት በአብይ አህመድ የተመራው የፓርቲዎች ውይይት ነው።

በሕንድ የአውሮፕላን መከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ የአንድ ቤተሰብ አባላት …አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዶክተር ፕራቲክ ጆሺ ኑሮን ለማሸነፍ ከባለቤቱ እና ሶስት ልጆቹ ...
06/13/2025

በሕንድ የአውሮፕላን መከስከስ አደጋ ሕይወታቸውን ያጡ የአንድ ቤተሰብ አባላት …

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዶክተር ፕራቲክ ጆሺ ኑሮን ለማሸነፍ ከባለቤቱ እና ሶስት ልጆቹ ተለይቶ ለስድስት ዓመታት ኑሮውን በእንግሊዝ ለንደን አድርጎ ነበር፡፡

በጊዜ ሒደት ውድ ባለቤቱን እና ልጁቹን ወደ ለንደን አምጥቶ ደስተኛ ሕይወት የመኖር ሕልምን ሰንቆ ብዙ ችግሮችን አሳልፏል፡፡

ከዓመታት ውጣ ውረድ በኋላም አስፈላጊውን ሁሉ በማሟላት ቤተሰቦቹን ወደ ለንደን የመውሰዱ እቅድ እውን ሆነ፡፡

ባለቤቱ፣ ሁለት መንታ ልጆችና አንድ ሴት ልጁም በለንደን የተሻለ ሕይወት ለመኖር ሒደቱ ማለቁን ሲሰሙ ተደሰቱ፤ ለጉዞም መሰናዳት ጀመሩ፡፡

በምትኖርበት አካባቢ እውቅ የሕክምና ባለሙያ የሆነችው ባለቤቱ ዶክተር ኮሚ ቪያስ ከጉዞ ሁለት ቀናት በፊት ሥራዋን በፈቃደኝነት ለቀቀች፡፡

ከዚያም ቤተሰቡ ወደ ለንደን ለመብረር ሻንጣውን ሸከፈ፡፡ በለንደን በአዲስ መንፈስ አዲስ ሕይወት ለመጀመር በማለምም ወዳጅ ዘመዶቻቸውን ተሰናበቱ፡፡

የአንድ ቤሰተብ አባላቱ ለዓመታት የጠበቁት ቀን ደርሶም በጉጉትና በተስፋ ወደ ለንደን ለመብረር በአሕመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ ተገኝተዋል፡፡

የበረራ ቁጥሩ 171 በሆነው አውሮፕላን ከገቡ በኋላም በረራ ከመጀመራቸው በፊት ከታች የተቀመጠውን በራሳቸው የተነሳ ፎቶ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው አጋሩ፤ ወዳጅ መዘዶቻቸውም መልካሙን ሁሉ ተመኙሏቸው፡፡

ይሁን እንጂ የተሳፈሩበት አውሮፕላን በረራ በጀመረ 30 ሰከንዶች ውስጥ በአሰቀቂ ሁኔታ ተከሰከሰ፤ ዶ/ር ፕራቲክ ጆሺ፣ ባለቤቱ፣ ሁለት መንታ ወንድ እና አንዲት ሴት ልጆቹ በአደጋው ሕይወታቸው አለፈ፡፡

የዶ/ር ፕራቲክ ጆሺ እና ቤተሰቦቹ በለንደን አብሮ የመኖር ሕልምም በአሳዛኝ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ሆነ፡፡

ከምዕራብ ሕንድ አሕመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ 242 ሰዎችን አሳፍሮ ወደ ለንደን በመብረር ላይ የነበረ የሕንድ አውሮፕላን ትናንት የመከስከስ አደጋ ያጋጠመው መሆኑ ይታወቃል።

Fbc

በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ አብርሃ እና አጽበሃ እና ክንደያ ትምህርት ቤቶች 20 ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እንዳይፈተኑ መደረጉን በቦታው ያሉ ታማኝ ምን...
06/11/2025

በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ አብርሃ እና አጽበሃ እና ክንደያ ትምህርት ቤቶች 20 ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እንዳይፈተኑ መደረጉን በቦታው ያሉ ታማኝ ምንጮች ጠቁመዋል። ሀወሀት በሚል ይጠራ የነበረው ድርጅት ትግራይን የአፈና ደሴት አድርጓት ነው የፈረሰው።

06/08/2025
የደብረፂሆንና የታደሰ ወረደ ፍጥጫ‼️ጀኔራል ታደሰ በነደብረፂዮንን የተጠራውን ስብሰባ ረግጠው ወጡ።ዛሬ ጠዋት በደብረፂዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን ስራ አስፈፃሚዎች ፕሬዝዳንቱን ጄኔራል ታደሰ...
06/08/2025

የደብረፂሆንና የታደሰ ወረደ ፍጥጫ‼️

ጀኔራል ታደሰ በነደብረፂዮንን የተጠራውን ስብሰባ ረግጠው ወጡ።

ዛሬ ጠዋት በደብረፂዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን ስራ አስፈፃሚዎች ፕሬዝዳንቱን ጄኔራል ታደሰ ወረዳን ጠርተው ማነጋገር እንፈልጋለን ብለው ውይይት መቀመጣቸው ታውቋል።

የነደፂ ቡድን፤አንተ በኛ መንገድ አትሄድም (ነገርንህ) የትግራይ ህዝብ አደጋ ላይ እየወደቀ ያለው እኛን መስማት ስላልቻልክ ነው ማለታቸው ተሰምቷል።

ጄኔራል ታደሰ ወረደ የተወሰኑትን ሰዎች ቃል ከሰሙ በኋላ፣ሌሎቹ እንዳይቀጥሉ አስቁመው፤እናንተ ሰዎች አይደላችሁም? ስለዚህ ከቻላችሁ ቆም ብላችሁ ማሰብ ጀምሩ ብለዋል።

ጀነራሉ ሲቀጥሉም በጣም ዘግይቷል ግን አሁንም አልረፈደም፤ሥራ አለኝ እና በዚህ አጀንዳ ላይ ተጨማሪ ጊዜ ማጥፋት አልፈልግም" ብለው ስብሰባ አቋርጠው መውጣታቸው ተነግሯል።

ገጻችንን like,share,follow እንዲሁም ገንቢ አስተያየት በመስጠት አሁኑኑ ቤተሰብ ይሁኑ‼️

ሲዳማ ቡና ወላይታ ዲቻን በመርታት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ወሰደ።  ጨዋታው 1ለ2 የተጠናቀቀ ሲሆን ሲዳማ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫ በማግኘት ታሪክ ጽፏል።
06/08/2025

ሲዳማ ቡና ወላይታ ዲቻን በመርታት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ወሰደ። ጨዋታው 1ለ2 የተጠናቀቀ ሲሆን ሲዳማ ለመጀመሪያ ጊዜ ዋንጫ በማግኘት ታሪክ ጽፏል።

የቀዳማዊ_ኃይለስላሴ አለም አቀፍ ተቀባይነት የናኘ ስለነበር   የእርሳቸውን ያህል 20 የክብር ዶክተሬት የተሰጠው የአፍሪካ የኤዢያ፣ የደብብ አሜሪካ፣ ወዘተ መሪ አልነበረም።ግርማዊ ቀዳማዊ ኃ...
06/01/2025

የቀዳማዊ_ኃይለስላሴ አለም አቀፍ ተቀባይነት የናኘ ስለነበር
የእርሳቸውን ያህል 20 የክብር ዶክተሬት የተሰጠው የአፍሪካ የኤዢያ፣ የደብብ አሜሪካ፣ ወዘተ መሪ አልነበረም።
ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ በአለማችን ካሉ 20 ታላላቅ ዩኒቨርሲቲዎች የክብር ዶክተሬት ድግሪ ተቀብለዋል! በየዩኒቨርሲቲዎቹም ተገኝተው ታላላቅ መሪዎችና ምሁራን በታደሙበት ውብ ንግግሮች አድርገዋል፡፡
1- ግንቦት 20 ቀን 1946 ዓ.ም ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
2- ግንቦት 25 ቀን 1946 ዓ.ም ከኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ በሕግ
3- ግንቦት 28 ቀን 1946 ዓ.ም ከሞንትሪያል ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክተሬት
4- ግንቦት 30 ቀን 1946 ዓ.ም ከሚቺጋን ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
5- ግንቦት 1946 ዓ.ም ከመክጊል ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
6- ሐምሌ 16 ቀን 1946 ዓ.ም ከኬምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
7- ሐምሌ 29 ቀን 1946 ዓ.ም ከአቴና ብሐራዊና ካፓዲስትሪን ዩኒቨርሲቲ በፍልስፍና የክብር ዶክተሬት ድግሪ
8- 1946 ዓ.ም አትላንታ ጆርጂያ ከሚገኘው ሞርሐውስ ኮሌጅ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
9- ጥቅምት 10 ቀን 1947 ዓ.ም ከኢክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
10- ከቦን ዩኒቨርሲቲ በእርሻ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
11- ሕዳር 4 ቀን 19 49 ዓ.ም ከባናራስ ሂንዱ ዩኒቨርሲቲ የሥነ-ጽሑፍ ዶክተሬት ድግሪ
12- ሐምሌ 5 ቀን 1951 ዓ.ም ከሞስኮ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
13- ሐምሌ 8 ቀን 1951 ዓ.ም ከፕራግ ከቻርልስ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የዶክተሬት ድግሪ
14- ህዳር 27 ቀን 1952 ዓም ከላይቤሪያ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
15- መስከረም 22 ቀን 1956 ዓ.ም ከጆርጅ ታውን ዩኒቨርሲቲ በሥነ-ጽሑፍ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
16- መስከረም 18 ቀን 1957 ዓ.ም ከሩማኒያ ከቡካሬስት ዩኒቨርሲቲ የሕግ የክብር ዶክተሬት ድሪ
17- መስከረም 30 ቀን 1959 ዓ.ም ከሊባኖስ ዩኒቨርሲቲ የሀገሪቱ ፕሬዘዳንት ቻርልስ ሄሉ ባሉበት ክብር ዶክተሬት
18- ሚያዚያ 24 ቀን 1960 ዓ.ም ከታይላንድ ከተማስት ዩኒቨርሲቲ የህግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
19- ግንቦት 9 ቀን 1960 ዓም ከምዕራብ አውስትራሊያ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የክብር ዶክተሬት ድግሪ
20- ግንቦት 13 ቀን 1960 ዓም ከደቡብ ኮሪያ ዩኒቨርሲቲ የህግ ዶክሬት ድግሪ ተቀብሏል፡፡

Address

Fairyland
Silver Spring, MD
20904

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share