Zemen Television

Zemen Television በሀቀኛ መረጃ ትውልድ ይሰራል. የሀገር አንድነት ይሰምራል :: 🇺🇸

09/01/2025
የስራ ማስታወቂያ እንሆ
08/19/2025

የስራ ማስታወቂያ እንሆ

የስራ ማስታወቂያ ከአመልድ ኢትዮጵያ ORDA Ethiopia
08/19/2025

የስራ ማስታወቂያ ከአመልድ ኢትዮጵያ
ORDA Ethiopia

✿ የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ 32 የስራ መደቦች ለ 150+ ክፍት ቦታዎች የስራ ቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል። ኮሚሽኑ የስራ መደቦቹን አስመልክቶ በሰጠው ማብራርያ መሰረት:-- ምዝገባው...
08/19/2025

✿ የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ 32 የስራ መደቦች ለ 150+ ክፍት ቦታዎች የስራ ቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል።

ኮሚሽኑ የስራ መደቦቹን አስመልክቶ በሰጠው ማብራርያ መሰረት:-

- ምዝገባው ከማክሰኞ ነሐሴ 13/2017 ዓም ጀምሮ ለሰባት ተከታታይ የስራ ቀናት ይቆያል።

- ምዝገባው በሁለት አይነት መንገድ ይካሄዳል በገጽ ለገጽ እና በኦንላይን።

- ምዝገባውን ለማካሄድ ስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር ያዘጋጀው የኦንላይን ምዝገባ ሊንክ አለ።

በመሆኑም መስፈርቱን የምታሞሉ በአካል መስቀል አደባባይ ወደ ቦሌ በሚወስደው መንገድ ፍላሚንጓ ሬስቶራንት 200 ሜትር ገባ ብሎ አዲስ አባባ ኤግዚብሽን ማዕከል ጀርባ ብሔራዊ ት/ቤት ውስጥ ከማክሰኞ ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም. ምዝገባ ይጀምራል።

📌በኦላይን በዚህ ሊንክ👉 https://effoysira.com/ethiopian-civil-service-commission-vacancy

የመረጃው ምንጭ:- Civil Service Commission

ሙሼ ሰሙ እንደፃፉት!...መንግስት በአዲሱ የደሞዝ ጭማሪ ምክንያት ለ160 ቢለየን ብር ተጨማሪ ወጭ እንደሚዳረግ ገልጿል። እስኪ የጭማሪውን ፋይዳ ለመረዳት ቁጥሮችን በአንጻራዊ ስሌት እናጢናቸ...
08/19/2025

ሙሼ ሰሙ እንደፃፉት!...

መንግስት በአዲሱ የደሞዝ ጭማሪ ምክንያት ለ160 ቢለየን ብር ተጨማሪ ወጭ እንደሚዳረግ ገልጿል። እስኪ የጭማሪውን ፋይዳ ለመረዳት ቁጥሮችን በአንጻራዊ ስሌት እናጢናቸው።

ቋሚ ደሞዝተኛው ገንዘቡ ኪሱ ከመግባቱ በፊት በገቢ ግብር ምክንያት ዝቅተኛው ተከፋይ 15% ከፍተኛው ደግሞ 35% ይቆረጥበታል። ዝርዝሩ ውስጥ መግባት ስለሚያዳግት አማካዩን ቁጥር እንወሰድ።

አማካዩ (15+35)/2 = 25% ይሆናል። ወደፊት እድሜውና ጤናው ከፈቀደለት የጡረታ ተከፋይ የሚያደርገው ቢሆንም ዛሬ ላይ ለጡረታ 7% ከደሞዙ በቀጥታ ይቆረጥበታል። 25%+7% = 32% ይሆናል።

160,000,000,000*0.32= 51,200,000,000 ይሆናል። ይህ ማለት ሃምሳ አንድ ቢሊየን 200 ሚሊየን ብር የደሞዝ ጭማሪው ተቀጣሪው እጁ ከመድረሱ በፊት ወደ መንግስት ካዝና ይመለሳል። በደሞዝ መልክ የሚከፋፉለው ቀሪም 108,800,000,000 ብር ይሆናል

ደሞዙ እጁ ላይ ከገባ በኋላ ደግሞ በሚሸምተው ቁሳቁስና በሚገዛው አገልግሎት ላይ 15% ቫት ይከፍላል። 108,800,000,000 *0.15 = 16,320,000,000 ይሆናል።

ይህ ማለት ደግሞ ከ160 ቢሊየን ብር ጭማሪ ውስጥ ደሞዝተኛውን ሳያገለግል በገቢ ግብር፣ በጡረታና በቫት ብቻ ወደ መንግስት ካዝና ተመልሶ የሚገባው ብር 67,520,000,000 ሲሆን ጭማሪው ደግሞ 92,480,000,000 ብር ይሆናል።

በመቀጠል ቀሪዎቹን ቀጥተኛና ቀጥተኛ ያልሆኑ የግብር ዓይነቶች እናንተው አስሏቸው። ፕሮፐርቲ ታክስ (1%)፣ ተርን ኦቨር ታክስ(2%)፣ ትራንዛክሽን ታክስ (0.1% እስከ 1.5%) ....

ከዚህ ሁሉ ቅንስናሽ በኋላ የሚገኘው የደሞዝ ጭማሪ ኢሚንት ቢሆንም አይጠቅምም ማለት በእግሩ ተጓጉዞ፣ በቀን አንዴ ቀምሶ ከሚያተርፋት "ደሞዙ" ላይ በየእለቱ ለልጆቹ ደረቅ ዳቦ የማቅረብ ግዴታ የተጣለባትን ቋሚ ደሞዝተኛ ፈተናና መከራ በቅጡና በልኩ አለመረዳት ይሆናል።

ተወደደም ተጠላ፣ አነሰም ተከመረ ጭማሪው ጎዳና ለመውጣት እየተንደረደረ የነበረውን ቋሚ የመንግስት ደሞዝተኛ እንደሚደጉምና አንድ ቀዳዳ እንደሚደፍንለት ጥርጥር የለኝም። ደሞዝ መቼም በቂ ሆኖ አያውቅም። በቂ ካልሆነ ደግሞ ጭማሪው ይቅር ለማለት ቋሚ ደሞዝተኛውን ከነ መከራው እሱና ቤተሰቡን ሆኖ መገኘትን ይጠይቃል።

የራያ መኾኒ ህዝብ ህወሓትን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ በማካሔድ ላይ ይገኛል‼️
08/19/2025

የራያ መኾኒ ህዝብ ህወሓትን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ በማካሔድ ላይ ይገኛል‼️

መልካም ዜና!237 የመንግስት የሥራ ቅጥር ለሥራ ፈላጊዎች ! የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት በተለያዩ የሥራ ዘርፎች በቋሚ ቅጥር፣ በኮንትራት ቅጥር እና ከተለያዩ የመን...
08/19/2025

መልካም ዜና!

237 የመንግስት የሥራ ቅጥር ለሥራ ፈላጊዎች !

የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት በተለያዩ የሥራ ዘርፎች በቋሚ ቅጥር፣ በኮንትራት ቅጥር እና ከተለያዩ የመንግስት ተቋማት በዝውውር ከዜሮ ዓመት እስከ አስር ዓመት የስራ ልምድ ያላቸውን ሰራተኞች አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።

በመሆኑም በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በለማው የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት (E-LMIS) በኩል የቅጥር ሂደቱ የሚፈፀም ሲሆን ከመላ የሀገሪቱ ክፍሎች 237 መስፈርቱን የሚያሟሉ ብቁ ሰራተኞች ይፈለጋሉ።

ስለሆነም የዚህ ሥራ እድል ተጠቃሚ ለመሆን lmis.gov.et ብላችሁ በመመዝገብ አቅራቢያችሁ ባለ ወረዳ/ቀበሌ የአንድ አገልግሎት መስጫ ማዕከል በመሄድ የባዮሜትሪክስ መረጃ በመስጠት የሰራተኛነት መለያ ቁጥር/ labor ID/ ይዛችሁ በዚህ ማስፈንጠሪያ (https://forms.gle/AMm2LCHBvdqMwW5AA) ላይ በመገባት ትክክለኛ የትምህርት፣ የስራ እና ሌሎች አስፈላጊ መረጃዎቻችሁን በማሰገባት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን። ይህ ማስጣውቂያ ከወጣበት ከነሀሴ 13 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለተከታታይ ሰባት ቀናት ድረስ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

መልካም ዕድል!

የኢፌዴሪ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው፡፡  ኢትዮጵያ ባለፉት ዘመናት የገጠሟትን የኢኮኖሚ ስብራቶች ለመጠገንና ወደ ብልጽግና የምታደ...
08/18/2025

የኢፌዴሪ መንግሥት የዜጎችን የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል የሀገር ዐቅም የሚፈቅደውን ርምጃ እየወሰደ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ባለፉት ዘመናት የገጠሟትን የኢኮኖሚ ስብራቶች ለመጠገንና ወደ ብልጽግና የምታደርገውን ግስጋሤ ለማፋጠን አዲስ የኢኮኖሚ ልማት ዕይታ እና መንገድ እየተከተለች ትገኛለች። በተያዘው ብዝኃ ዘርፍ፣ ብዝኃ ተዋናይ እና ብዝኃ ተጠቃሚ የኢኮኖሚ ዕድገት አቅጣጫ፣ ለኢኮኖሚ ጥራትና አሳታፊነት ትልቅ ትኩረት ተሰጥቷል፡፡

እንደሚታወቀው፣ ሀገራችን የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባቶችን በመሠረታዊነት ለመፍታት ልዩ ልዩ ሪፎርሞችን ጀምራ እያሳካች ትገኛለች፡፡ የእነዚህ ሪፎርሞች ዓላማ ሁለት ነው፡፡ በአንድ በኩል ነባር ሀገራዊ ስብራቶችን መጠገንና የተንከባለሉ ዕዳዎችን ማቃለል ሲሆን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የዛሬንና የነገን ትውልድ ጥያቄዎች በመመለስ፣ የኢትዮጵያን ብልጽግና በአስተማማኝ መሠረት ላይ መገንባት ነው፡፡

ሪፎርሙን በመተግበር በተገኙ ውጤቶችና ትሩፋቶች፣ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች፣ የቢዝነስ አንቀሳቃሾችና በግል ክፍለ ኢኮኖሚ የተሠማሩ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የገቢ ሁኔታ ከኢኮኖሚ ዕድገቱ ጋር እየጨመረ መጥቷል፡፡ ነገር ግን የቋሚ ደመወዝተኞች በተለይም የመንግሥት ሠራተኞች ገቢ በተገቢው መጠን ሊጨምር አልቻለም፡፡

በአንድ በኩል በየጊዜው እየጨመረ በመጣው ሰፊ የመንግሥት ሠራተኛ ቁጥር ምክንያት የመንግሥት አጠቃላይ የደመወዝ ወጪ ድርሻ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል። በዚህም ምክንያት የኢትዮጵያ መንግሥት ለደመወዝ የሚያውለው ወጪ ከአጠቃላይ የመንግሥት ወጪ አንጻር ያለው ድርሻ ከ30 እስከ 32 በመቶ ይደርሳል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ለእያንዳንዱ የመንግሥት ሠራተኛ የሚከፈለው ደመወዝ በሚፈለገው መልክ መጨመር ባለመቻሉ አሁንም የሚከፈለው አነስተኛ ነው፡፡

ይሄንን በመረዳት እና በየጊዜው በመንግሥት ሠራተኛው በተለይም ዝቅተኛ ተከፋይ በሆነው ላይ እየደረሰ ያለውን የኑሮ ጫና ለማቃለል፣ በ2017 በጀት ዓመት 91 ቢሊየን ብር ወጪ በማድረግ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝ እንዲሻሻል ተደርጓል። ያለፈው የበጀት ዓመት እንደ ሀገር ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም የገባንበትና በመንግሥት ወጪ ላይ ከፍተኛ ጫና የነበረበት ዓመት ቢሆንም፣ መንግሥት ባለው ቁርጠኛ ሰው ተኮር አቋም፣ የዝቅተኛ ተከፋይ ሠራተኛውን ደመወዝ ትርጉም ባለው ሁኔታ አሻሽሏል።

ደመወዝ ከመጨመር ባለፈ ቋሚ ገቢ ያለውን ሠራተኛ የመግዛት ዐቅም ለማሳደግ፣ መንግሥት ከ1994 ዓም ጀምሮ ሥራ ላይ በቆየው የቁርጥ ገቢ ግብር ዐዋጅ ውስጥ በተካተቱት የግብር ማስከፈያ ምጣኔ እና በተለያየ ደረጃ ግብር በሚጣልበት የገቢ ቅንፍ (income bracket) ላይ ማስተካከያ አድርጓል፡፡ በዚህም ሰፊ ማሻሻያ የተደረገ ሲሆን፣ በተለይም ከታክስ ነጻ የሆነውን የተቀጣሪ ገቢ ከብር 600 ወደ ብር 2000 ለማሳደግ ተችሏል።

መንግሥት ለዘመናት ሲንከባለል የመጣውን የመንግሥት ሠራተኛ ዝቅተኛ የክፍያ ሁኔታ እና ተያይዞ የመጣውን የኑሮ ጫና በአንድ ጊዜ በሚደረግ የደመወዝ ማሻሻያ ሊቀርፈው እንደማይችል ይገነዘባል። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ መንግሥት ከእያንዳንዱ የኢትዮጵያ ብልጽግና ምዕራፍ ሁሉም ዜጋ ተጠቃሚ መሆን አለበት ብሎ ደግሞ ያምናል። ስለሆነም ከሚወሰዱ ሌሎች ማሻሻያዎች በተጨማሪ፣ ከመስከረም 2018 ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኛው ተጨማሪ የደመወዝ ማሻሻያ ለማድረግ መንግሥት ወስኗል፡፡

በዚህ ማሻሻያ፦

1. ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 4760 ወደ ብር 6,ዐዐዐ እንዲያድግ ይደረጋል፡፡

2. ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደመወዝ ከብር 21,492 ወደ ብር 39,000 እንዲያድግ ይደረጋል፡፡

3. የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6,940 ወደ ብር 11, 500 ይሻሻላል።

4. ከሲቪል ሰርቪስ ውጭ በተለያዩ ዘርፎች የተሠማሩ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝም ማሻሻያ ይደረግበታል፡፡

ይህ የደመወዝ ማስተካከያ ከ160 ቢሊዮን ብር በላይ ተጨማሪ በጀት ጠይቋል፡፡ ይሄም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል። ይህ የደመወዝ ጭማሪ ካለን የልማት ፍላጎት አንጻር አገልግሎቶችና መሠረተ ልማት ለማስፋፋት የሚያስፈልገንን ሀብት የሚሻማ ቢሆንም፣ የመንግሥት ሠራተኛውን ኑሮ ማሻሻል ቅድሚያ የሚሰጠው በመሆኑ የተወሰነ ነው። ከዚህም ባሻገር የመንግሥት ሠራተኛው ችግር በደመወዝ ማሻሻያ ብቻ የሚፈታ ባለመሆኑ በቀጣይ የቤት አቅርቦትን እና የጤና መድን ሽፋንን ጨምሮ የተለያዩ መፍትሔዎች ይወሰዳሉ፡፡

መንግሥት ይሄንን የደመወዝ ማሻሻያ ሲያደርግ ጭማሪው በቂና የመጨረሻ ነው ብሎ በማመን አይደለም፡፡ በቀጣይነት የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም ማሻሻያው እየተተገበረ ሲሄድ ውጤትን መሠረት ያደረጉ ማሻሻያዎች ይደረጋሉ፡፡ በተጨማሪም የጀመርነው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርም ይበልጥ ውጤት እያስመዘገበ በሄደ ቁጥር፣ ሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል የትሩፋቱ ተቋዳሽ ይሆናል፡፡

ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ የመንግሥት ሠራተኞችን ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም በተገቢ ደረጃና መጠን ለመክፈል ከተፈለገ፣ ያንን የሚሸከም ሀገራዊ ኢኮኖሚ መገንባት አለብን፡፡ ኢትዮጵያ ለአገልጋዮቿ ተገቢውን ክፍያ እንድትከፍል የሚያስችላትን ኢኮኖሚ የመገንባት ኃላፊነት ደግሞ፣ በመንግሥት ሠራተኛው ላይ ጭምር የተጣለ ብሔራዊ ግዴታ ነው፡፡ ካልተከልነው ዛፍ ፍሬ፣ ካልዘራነው ሰብል ምርት ልናገኝ አንችልምና፡፡ ኢኮኖሚያችን ካላደገ፣ የመንግሥት ሠራተኞች ደመወዝና ጥቅማ ጥቅም ሊያድግ አይችልም፡፡ ለአብነት የታክስ ገቢያችንን በአንድ በመቶ ብናሳድግ እንኳን፣ ከ3ዐዐ ቢሊዮን በላይ ተጨማሪ ሀገራዊ ገቢ እናገኛለን፡፡ ይሄንን ለማሳካት ደግሞ በየመስኩ የሚገኙ የመንግሥት ሠራተኞች ከፍተኛውን ሚና ይጫወታሉ፡፡

በአጠቃላይ ዘላቂና ትርጉም ያለው የኑሮ ደረጃ መሻሻል እና ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ዓይናችንን ለአፍታም ቢሆን ከሀገራዊ ሕልማችን ሳንነቅል መረባረብ አለብን። በዚህ ሂደት ውስጥ ኢትዮጵያውያን የሚከፍሉት የውዴታ መሥዋዕትነት አለ፡፡ ይህ መሥዋዕትነት ለነገ ሲባል የሚከፈል መሥዋዕትነት ነው፡፡ ለተሻለ ነገ ስንል የተወሰኑ ፍላጎቶቻችንን እንተዋለን፡፡ ውድ ዕውቀታችንን፣ ጊዜያችንን እና ጉልበታችንን እንሠዋለን፡፡ ያደጉ ሀገራት ሁሉ የከፍታ ማማ ላይ የደረሱት በአንድ ወቅት መሥዋዕትነት በከፈሉ ትውልዶቻቸው ትከሻ ላይ ነው፡፡

እኛ ኢትዮጵያውያን በነጻነት የምንኖረው፣ ከመኖር ለሚበልጥ ሀገራዊና ሕዝባዊ ክብር ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን በሠው ዐርበኞቻችን ምክንያት ነው፡፡ የኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞች የድካማቸውን ያህል ክፍያ እንደማያገኙ ይታወቃል፡፡ ይሄም ለተሻለች ኢትዮጵያ እየተከፈለ ያለ መሥዋዕትነት እንደሆነ መንግሥት ዕውቅና ይሰጣል። ስለሆነም በዚሁ አጋጣሚ፣ በአነስተኛ ክፍያ ሕዝብና መንግሥት የሰጣቸውን ኃላፊነት በመወጣት ላይ ለሚገኙ አገልጋዮች መንግሥት ምስጋናውን ያቀርባል፡፡

የመንግስት ሠራተኛው ያለውን የኑሮ ውድነት ተቋቁሞ ለመላው የንግዱ ማህበረሰብ ተገቢውን አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ የንግዱ ማህበረሰብ መንግስት ለሚወስዳቸው የሪፎርም እርምጃዎች አጋዥ እየሆነ መጥተዋል። ይሄው ተግባር አሁንም ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል። ይሁንና እንዳንድ የንግዱ ህብረተሰብ አካላት ከእዚህ ቀደም በተለምዶ የደመወዝ ጭማሪ ተደረገ በሚል በሸቀጦች ዋጋ ላይ እንደሚጨምሩ ይታወቃል፡፡ በሰሞኑ በሚደረገው የደመወዝ ጭማሪ አስታኮ እና ለኑሮ ውድነቱ መቋቋሚያ ተብሎ በተደረገው የደመወዝ ማሻሻያ ዜና በመስማት ህገወጥና ምንም ምክንያት በሌለው መንገድ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉት ላይ መንግስት ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ ይሆናል፡፡ ህገወጥ የዋጋ ጭማሪ አድርገው በሚገኙት ላይ ደግሞ መንግሥት አስተማሪ እርምጃ የሚወስድ መሆኑን በቅድሚያ ያሳውቃል፡፡

በመጨረሻም ሕዝባችንን በንጽሕናና በትጋት በማገልገል፤ ከሚገባንና ከሚጠበቅብን በላይ በመሥራት፤ ሙስናና ብልሹ አሠራርን በመታገል፤ ከዕቅዶቻችን በላይ በማከናወን፤ የኢትዮጵያን ብልጽግና እንደምናረጋግጥ መንግሥት ጽኑ እምነት አለው፡፡ የብልጽግና ጉዟችን በቀጠለ መጠን፣ በየምዕራፉ ሁላችንም የብልጽግናን ትሩፋት መቋደሳችን አይቀሬ ነው፡፡ ለዚያ ደግሞ ሁላችንም ወገባችንን አጥብቀንና ታጥቀን መትጋት አለብን፡፡

ይህ ሲሳካ ነጻነታችንን በደማቸው እንዳጎናጸፉን ቀደምት አባቶቻችን እና እናቶቻችን ሁሉ፣ እኛም ሀገራቸውን ለማበልጸግ ዋጋ የከፈሉ ትውልዶች ተብለን ታሪክ ሲዘክረን ይኖራል።

የፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን

አሰብን ለማስመለስ 150 ሺህ ፊርማ ያሰባሰቡት ፕሮፌሰር ሀገራችን ወደብ አልባ መሆኗ ከከነከናቸው ቀዳሚዎች መካከል አንዱ ናቸው። ጦር ሰብቀን ወደብ እናግኝ ግን አላሉም። በጊዜው የነበረው መ...
08/13/2025

አሰብን ለማስመለስ 150 ሺህ ፊርማ ያሰባሰቡት ፕሮፌሰር

ሀገራችን ወደብ አልባ መሆኗ ከከነከናቸው ቀዳሚዎች መካከል አንዱ ናቸው።

ጦር ሰብቀን ወደብ እናግኝ ግን አላሉም። በጊዜው የነበረው መንግሥት አልባሌ ሥም እየለጠፈ ቢያሸማቅቃቸውም ካፓርቲያቸው ጋር ሆነው 150 ሺህ ፊርማ አሰባስበዋል።

እኝህ ሰው ፕሮፌሰር አድማሱ ገበየሁ ይባላሉ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አሁንም እያገለገሉ ይገኛሉ።

ሕወሓት ኤርትራ ስትገነጠል በአሰብ ጉዳይ መደራደር ይችል ነበር ይላሉ ፕሮፌሰር አድማሱ በቁጭት።

በጊዜው ኤርትራ አጥብቃ የኔ ነው የምትለው ነገር እንዳልነበራት አንስተው፤ ኢትዮጵያም ወደ ኋላ የምታፈገፍግበት ምክንያት አልነበራትም በማለት ይገልጻሉ።

ጉዳዩን የተለያዩ ኮንፍረንሶችን አዘጋጅቶ ታሪካዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ሁኔታውን ሚዛን ውስጥ አስገብቶ መከራከር ይቻል ነበር ሲሉም ነው የሚያስረዱት።

እስከ 1997 ዓ.ም ድረስ የፖለቲካ ፓርቲ መሪ ነበርኩ ያሉት ፕሮፌሰር አድማሱ፤ በወቅቱ ፓርቲያቸው ኢዲአፓ መድኅን እንደነበርና አንዱ አጀንዳው የአሰብ ጉዳይ እንደነበር ይገልጻሉ።

የወደብ ጉዳይ ተሸፋፍኖ ኢትዮጵያ ወደብ እንድታጣ የተደረገበትና በታሪኳ በር ተዘግቶባት እንድትቀር ያደረገ ሁኔታ መሆኑን ጠቅሰው፤ የአሰብን ጉዳይ በጉልበት ሳይሆን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት መሞከራቸውን ያነሳሉ።

በመነጋገርና በመወያየት እልባት ሊገኝለት ይችላል የሚል እምነት ስላደረብን ፖለቲካዊ አጀንዳ አድርገን መስቀል አደባባይ ሁለት ጊዜ ሕዝባዊ ሰልፍ አካሂደናል በማለት ይናገራሉ።

ከ150 ሺህ በላይ የተረጋገጠ አድራሻ ያላቸውን ሰዎች ፊርማ ማሰባሰባቸውን እና የሰነዱን ቅጂዎች ለአፍሪካ ኅብረት እና ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ማስረከባቸውንም ነው የሚያስረዱት።

አሁን በኤርትራ የሚገኙ ወደቦችን የመጠቀም ዕድልን በተመለከተም ሲገልጹ፤ አሰብንም ሆነ ምፅዋን ወደብን ለመጠቀም የሚፈልግ ሌላ ጎረቤት ሀገር የላቸውም።

ወደቡን በመጠቀም እድገታቸውን ለማፋጠን ባለመምረጥ ምክንያታዊ ያልሆነ አቋም መያዛቸው ይገርመኛል ይላሉ።

ኢትዮጵያ በተለያዩ ትርፋማ የልማት ድርጅቶቿ ውስጥ ድርሻ እንዲኖራቸው በማድረግ ጭምር በሰጥቶ መቀበል መርሕ በጋራ ተጠቃሚ እንሁን የሚል ጥያቄ እያቀረበች ነው ሲሉም ገልጸዋል።

የኤርትራ መንግሥት ይህን ዕድል ገፍቶ ከግብፅም ሆነ ከሌሎች ወገኖች ጋር ከወገነ በአንደኛ ደረጃ እየበደለ ያለው የራሱን ሕዝብ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ታሪካችንን ከተመለከትን ተለያይተን የኖርነው ትንሽ ጊዜ ነው ያሉት ፕሮፌሰሩ፤ አንድ ሀገር ሆነን መቀጠል ባንችልም እንኳን እንደ ጎረቤት ሀገር ከየትኛውም ጎረቤት ሀገር በላይ ለእኛ የሚቀርቡ ናቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያን ጥቅም በተመለከተ አብረን መቆም አለብን ሲሉም መክረዋል።

ሰሞኑን አማራ ክልል ነበርኩ። በተለይ በሰፈሮቼ በጎጃም እና በጎንደር ተዘዋውሬአለሁ። እያንዳንዱ ከተማ ውስጥ ፋኖ የለም። በእያንዳንዱ ከተማ ያለው ሚሊሻ እና አድማ ብተና ነው። ትልልቅ ከተሞ...
08/11/2025

ሰሞኑን አማራ ክልል ነበርኩ። በተለይ በሰፈሮቼ በጎጃም እና በጎንደር ተዘዋውሬአለሁ።

እያንዳንዱ ከተማ ውስጥ ፋኖ የለም። በእያንዳንዱ ከተማ ያለው ሚሊሻ እና አድማ ብተና ነው። ትልልቅ ከተሞች ላይ ደግሞ መከላከያ።

ሸማቂው ጠቅላላ ገጠር ውስጥ ነው።

ምንም ይኹን ግን ሕዝቡ መከራ ውስጥ ነው። አስከፊ ኹኔታ ላይ ነው ያለው።

አንድ አባት የ12 ዓመት ልጁን ዳራት። ለምን ብለን ስንጠይቅ "ሴቱን ኹሉ ታጣቂ እያስረገዘው ነው፤ አረብ አገር እንኳን እንዳልካት ገንዘብ የለኝ። አካሏም ለአረብ አገር ስራ ገና አልጠናም። ቢያንስ ባል አላት ብለው አይነኳትም ብየ ነው። " አለን።

አብዛኞቹ ወጣቶች ወደ አረብ ሀገር እየተሰደዱ ነው። አብዛኞቹ ደግሞ በሕገ ወጥ በባሕር እየሞከሩ የሞት ሲሳይ እየኾኑ ነው።

በርካታ ልጆች ሰካራም ኹነዋል። አረቂ ቤት ጠላ ቤት እያመሹ እየሰከሩ ይመጣሉ። ወላጆቻቸው ጋር ይጣላሉ።
ለምን ብለን ስንጠይቅ
"ትምህርት አትማሩ ተባሉ፤ ሥራም የለ፤ እርሻ እረሱ ብንላቸውም እምቢ አሉ። በዚህ እድሜያቸው በየመሸታ ቤቱ ይውላሉ፤ ያመሻሉ" አሉን።

ከአንድ ቤት 2 ወንድማማቾች ሙተዋል። አንዱን የተገደለው ፋኖ ነኝ እያለ ሲዘርፍ ነው። "። አንዱን ደግሞ የገደለው የፋኖ ነኝ የሚለው ነው፤ "የብልጽግና አባል ነህ " ብሎ።

አንድ ማውቀው ጀግና ገበሬ ነበር። ከተማ ከአንድ ሕንጻ ስር ፍዝዝ ብሎ ተቀምጦ አገኜሁት። ሔጀ ሰላም አልኩትና ትንሽ አወጋሁት።

ችግር ገጥሞት የገጠር ንብረቱን ሻሽጦ ከተማ ቤት ተከራይቶ እየኖረ እንደኾነ ነገረኝ። ከሌላ ሰው ሳጣራ ሚስቱን ዐይኑ እያየ ለ4 ደፍረውበት አፍሮ ነው ቀየውን ጥሎ የመጣ አሉ።

አፋብኃ እና አፋህድ እየተባባሉ እየተገዳደሉ ነው። የዐይንህ ቀለም አላማረኝም ጀርባህ ሸክኮኛል እያሉም ይገዳደላሉ።

ትምህርት የለም። መምህራን ችግር ላይ ናቸው። ደመወዛቸው ይገባላቸዋል፤ ግን ከተማ ኹነው ያልተገባ ወጭ እያወጡ ለችግር እየተጋለጡ ነው። የመንግሥት ሠራተኛ ኹሉ ብልጽግና ነው በሚል ማርክ ይደረጋል። አንዳንዱም ፋኖ ነህ ተብሎ ማርክ ይደረጋል።

በድጋሜ የምናገረው ሥለ ኤድስ ነው። HIV AIDS በአማራ ክልል እንደ ፈለገ እየተንሰራፋ ነው።

አማራ በተለያየ የማጥፊያ ዘዴ እየጠፋ ነው። ቁጥሩ እየቀነሰ ነው። ነገ ላይ የተማረ ኃይል አይኖርም። የሐሳብ ሰው የለም። የሚመራመር የሚያሰላስል ሰው አይኖርም።

በጥቅሉ "የህልውና ትግል" በሚል ስም ህልውናችንን እያጣን ነው። ወደ መቃብር እየሔድን ነው። ውኃ ሲወስድ እያሳሳቀ ነው ይባል የል፤ ይኽ ውድቀታችን ራሱ እንደ ጀብድ እየተተረከልን ነው።

ከጭፍን ጥላቻ እና ከአጉል መናናቅ ወጥተን ቆም ብለን እናስብ።

ተወደደም ተጠላም
፩ኛ. ትምህርት በኹሉም ቦታ እንዲጀመር እንፈልጋለን
፪ኛ. ቢያንስ የግብርና፣ የጤና እና የፋይናንስ ተቋማት ያለ ምንም ሥጋት ሥራ ላይ መኾን አለባቸው።

Address

Fairyland
Silver Spring, MD
20904

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Television posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share