GMJA TUBE- ግምጃ ቲዩብ

GMJA TUBE- ግምጃ ቲዩብ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from GMJA TUBE- ግምጃ ቲዩብ, Media/News Company, Ethiopia, Addis Ababa.

01/04/2024

እለቱ እሁድ ነው።
ብዙ ሰው አለባበሱ ዘና ያለ ነው።
ወንዶች ቱታ በሸበጥ ወይም ሸራ መሳይ ስኒከር ተጫምተው ሲንቀሳቀሱ ይስተዋላሉ።
ሴቶች ደግሞ ከሌሊት ልብስ መለስ ያሉ፣ ደረታቸው ከፈት ያለ ጉርድ ቀሚሶችን በብዛት ያለ ጡት መያዣ ለብሰው ከታች ነጭ ካልስ በሸበጥ ተጫምተው ሞንደል ሞንደል ሲሉ ይውላሉ። የተሰሩት ሹርባ እንዳይፈርስ አልያም የተቀቡት ቅባት በፀሀይ እንዳይቀልጥባቸው አናታቸውን በሻሽ ሸብ የሚያደርጉም ብዙ ናቸው። ሴቶች በእረፍት ቀናቸው የውስጥ ቁምጣ እንደማይለብሱም ይታማሉ።
አሁን በዚህ ሰሞን አንድ እሁድ እኛ ሰፈር የካ አባዶ ATM ለመጠቀም ጥቁር ቱታ ሱሪ በነጭ ሸሚዝ ለብሼ ሶሉ ነጭ የሆነ ጥቁር እስኒከሬን ተጫምቼ፣ በእጄ ላይ ደግሞ ከዱባይ የመጣልኝን ወርቃማ የብረት ሰዓቴን ገርግጄ፣ በጠዋት ሻወር የረሰረሰውን ፀጉሬን በፀሀይ እያሞቅሁ ወደ ባንክ አቀናሁ።
በመጀመሪያ ያገኘሁት አዋሽ ባንክ ሁለት ATM ማሽኖቹ ቢኖሩትም ከአገልግሎት ውጪ ሆነው አገኘኋቸው፣ ብዙ ሰው በአይኑ ገልመጥ እያደረግ This ATM Machin is out of service ከሚለው ፅሁፍ ጋር ፊት ለፊት እየተጋጨ ፊቱን ቅጭም እያደረገ ይመለሳል። እኔም የካ አባዶ በተለይ እሁድ እሁድ የሚሰራ ATM ማሽን ማግኘት ከባድ እንደሆነ ስለማውቅ ብዙም ሳይገርመኝ ወደ ቀጣዩ ማሽን አመራሁ።
ዘቅዘቅ ብዬ 50 ሜትር የሆነ ርቀት ከተጓዝኩ በኋላ አስፋልት ተሻግሬ ወደ ዳሽን ባንክ ATM አቀናሁ።
ዳሽንም በተመሳሳይ ሁኔታ ከአገልግሎት ውጪ መሆኑን በፈረንጅ አፍ ፅፎ የእሁድ እረፍቱን እያጣጣመ ነው።
ይህም አልደነቀኝ። የያዝኩት የአቢሲኒያ ATM ስለነበር ለምን ወደ ባለቤቱ አልሄድም ብዬ ከG7 ባንኩ ወዳለበት 500 ሜትር የሚሆን የቁልቁል ተጓዝኩ።
ፀሀዩ የሻወር ውሀዬን ከማድረቅ አልፎ ሌላ ውሀ ከሰውነቴ እስከማመንጨት ደርሷል። ATM ማሽኑ ጋር ስደርስ አንድ ሰው ብር አውጥቶ ሲመለስ፣ አንድ ሰው ደግሞ ማሽኑን እየሞከረ አገኘሁት። ማሽኑ በመስራቱ እና ወረፋማም ባለመብዛቱ ወደ ውስጤ እፎይ ብዬ አንዱን የበረንዳ ቋሚ ብረት ተደግፌ ቆምኩ።
ትንሽ ቆይቼ አይኔን ወደ ማሽኑ ስልክ እየሞከረ ያለው ሰው ተጨናንቆ አየሁት። ጠጋ ብዬ ምነው አይሰራም እንዴ? ስል ጠየኩት
እሱም ኧረ ይሰራ ነበር፣ ከኔ በፊት የነበረው አውጥቶ ሄዷል። የኔን ካርድ ግን ጎረሰብኝ አለኝ።
ጠጋ ብዬ ስመለከት ማሽኑ ከወትሮው በተለየ መልኩ ካርዱን ሙሉ በሙሉ ሳይወስድ አብዛኛውን አካሉን ውጦ ጫፉ ይታያል።
በብረት አጣብቀን ለማውጣት እየሞከርን ሌላ ልጅ እግር መጣ፣ ልጁም ፣አይሰራም!? ብሎ ፊቱን ቅጭም አድርጎ ጠየቀን፣ ከጥያቄውና ከፊቱ ብዙ እንደዞረና እንደተበሳጨ ያስታውቃል።
አይ! ይሰራል ብለን የገጠመንን ነገርነው፣ ጠጋ ብሎ አየውና፣ መርፌ ብናገኝ አሪፍ ነበር አለና ባገኘው ነገር ወይ ወደ ውስጥ ለመግፋት ከቻለ ለማውጣት ይሞክር ጀመር።
ከዚያ ባለቤቱ ፈንጠር ብሎ ሄደና መርፌ ገዝቶ መጣ፣ ልጅ እግሩ ተጠቃሚ በመርፌ ሙከራውን ቀጠለ።
ሶስታችን ሀሳብም እየተለዋወጥን፣ በመርፌውም እየሞከርን አንዲት ከላይ እንደገለፅኩት የእሁድ ልብስ የለበሰች ሴት ሞንደል ሞንደል እያለች መጣች
እሷም ወይኔ! ይሄም አይሰራም ስትል፣
ሁለቱ ካርዱን ለማውጣት ወይ ለማስገባት ሙከራ ላይ ስለነበሩ፣ አይ! ይሰራል፣ አንድ ሰው አውጥቶ ሄዷል፣ ከሱ ቀጥሎ ያለው ሲሞክር ካርዱን ጎርሶበት ነው አልኳት።
ይህን ሳስረዳት ፊት ለፊት እየተያየን ስለነበር እስከ ደረቷ በተገለጠው ስስ ልብሷ የጡቷ ማካፈያ ሸለቆ ሙሉ በሙሉ፣ ጡቶቿ ደግሞ በከፊል ይታዩኛል።

እስኪ እኔ ልሞክር ብላ ወደ ማሽኑ ስትራመድ ደግሞ የውስጥ ቁምጣ እንዳለበሰች የሚያሳብቀው ስስ እና አጭር ቀሚሷ ዳሌዋን ጎላ አድርጎታል። ያንን ዳሌ ክፉኛ እያበሳጨችው ሄደች።
ጎንበስ ብላ በመርፌው ካርዱን ለማውጣት ወይ ለማስገባት ስትሞክር ደግሞ ዳሌዋ ምን አባህ ታየኛለህ በሚመስል ግልምጫ አፈጠጠብን።
ባቷ እንደተወለወለ የክላሽ ሰደፍ ያበራል፣ ብር ለማውጣት ከፍተኛ ጉጉት እንዳላት ያስታውቃል። እያገላበጠችና እየተገላበጠች ሞከረች፣
በመርፌው አልሳካ ሲላት በተቀጠለው ጥፍሯ፣ ጥፍሩ እንኳን የእሷ አይደለም፣ በውበት ባለሙያዎች እገዛ የተቀጠለላት ሰው ጥፍር እንደሆነ ያስታውቃል፡፡
በዚህ ጥፍሯ ሞከረች፣ የህመም ስሜት ሲሰማት፣ አይኗን ስልምልመ አድርጋ፣ ውይ! ብላ ጣቶቿን ወደ አፏ ከታ ዘገም ባለ አላላስ የማቀዝቀዝ አገልግሎት ሰጠችው፣ ወጣ ገባ ስታደርገው ጣት ሳይሆን ሌላ ነገር እያስገባች፣እያስወጣች ይመስላል፡፡
ቀጠለችና በመርፌው ሙከራዋን ቀጠለች፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ ተሳካላት፣ ካርዱ ወደ ውስጥ ገባላት። ዋው ብላ ዘለለች። ያን ጊዜ የሸበጧ ድምፅ ለጆሯችን ደረሰ፣ አይናችን ደግሞ ስትዘል ክፉኛ የሚበሳጨውን ዳሌዋን ተሳለመ።
በዚህ ጊዜ የተጠቃሚዎች ቁጥር ጨምሯል። መጀመሪያ እሷ አወጣች፣ ቀጥሎ እኔ ነበርኩ ተረኛ፣ ዳሩ ግን ያንን የሚበሳጭ ዳሌ በደንብ ለማየት ካለኝ ጉጉት ገንዘቧን ይዛ ስትመለስ እስከ አስፋልቱ በአይኔ ሸኘኋት።
አንድ ሰው ካወጣ በኋላ፣ ጀለስ አታወጪም እንዴ ካልሆነ እኛ እናውጣ ሲል አንዱ ከኋ ያለ ተጠቃሚ በማጉረምረም ድምፅ አባነነኝ፣ እኔም ከእንቅልፉ እንደባነነ ጡት የሚጠባ ህፃ ብንን ብዬ በመስገብገብ ስሜት ተንደርድሬ ካርዴን ማሽ ላይ ሰካሁት፡፡

ልቤ እየተበሳጨ በሄደው ዳሌላ ልቡ ተሰቅሎ፣ ያንን በሸለቆ የተከፈለ ጡት እያስታወስኩ፣ ብሬን አውጥቼ ሄድኩ።
ብሬን እየቆጠርኩኝ፣ ልጅቱን እያሰብኩኝ ወደ ቤቴ ስመለስ የአባዶ ATM አገልግሎት እያብከነከነኝ ቤቴ ደረስኩ
አባዶ ATM ማሽን ላይ ቆሞ የራሱን ገንዘብ ለማውጣት የሚፀልየውን ሰው በተደጋጋሚ ስታዘብ ባንኮች የሚሰጡን የራሳችንን ገንዘብ ሳይሆን የራሳቸውን ገንዘብ እየመፀወቱን ሲመስለኝ ድፍን ሁለት አመት ሞላኝ።

የዛሬ መልዕክት
08/12/2023

የዛሬ መልዕክት

በሹፌሩ የተሰረቀ ደብል ፒካፕ መኪና በቁጥጥር ስር ዋለ ከአፋር ክልል በአሽከርካሪው የተሰረቀ የመንገድ ስራ ድርጅት ተሽከርካሪ በሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ወረዳ እሮቢት ከተማ ሰኔ 10 ቀን 2...
21/06/2023

በሹፌሩ የተሰረቀ ደብል ፒካፕ መኪና በቁጥጥር ስር ዋለ

ከአፋር ክልል በአሽከርካሪው የተሰረቀ የመንገድ ስራ ድርጅት ተሽከርካሪ በሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ወረዳ እሮቢት ከተማ ሰኔ 10 ቀን 2015 ዓ.ም በቁጥጥር ስር መዋሉን የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል ።

ንብረትነቱ የሻንድንግሉቸው ማንዳ ቡሬ መንገድ ስራ ድርጅት የሆነ የሰሌዳ ቁጥር አ.አ B 14630 ደብል ፒካፕ ቲዮታ መኪና ሲሆን መነሻውን ከአፋር ክልል አንድ ኤሊዳር ወረዳ ያደረገ እንደሆነ ተገልጿል ።

አሽከርካሪው በፀጥታ ሀይል ክትትል እየተደረገበት መሆኑን ተረድቶ በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ወረዳ እሮቢት ከተማ መኪናውን አቁሞ የተሰወረ መሆኑን የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ ሃላፊ ኮማንደር ተመስገን በረሳው ተናግረዋል ።

መኪናው የተሰረቀው በድርጅቱ ሾፌር በሆነ አለም በሪሁን በተባለ ግለሰብ መሆኑንና ሌላ የድርጅቱን መኪና ከተመለከተ በኋላ መኪናውን አዙሮ እሮቢት ከተማ መመለሱ ተነግሯል ። ነገር ግን ሌላኛው የድርጅቱ መኪና በአካባቢው ለስራ በጉዞ ላይ የነበረ እንደሆነ ተገልጿል ።

ተሽከርካሪውን የሰሜን ወሎ ዞን ፖሊስ መምሪያ ባለንብረት ለሆነው ድርጅት በትናንትናው ዕለት ያስረከበ መሆኑንና ወንጀል ፈፃሚውን ለመያዝ ክትትል እያደረገ እንደሚገኝ ተገልጿል ።

ሰበር ዜናሜርኩሪ የተባለ ንጥረ ነገር (ኬሚካል) ቁስ በሕገ ወጥ መንገድ ሲያዘዋወር የነበረ ተጠርጣሪ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ።      ሰኔ 14/2015 ዓ.ም(አአሰፀአቢ)           ...
21/06/2023

ሰበር ዜና

ሜርኩሪ የተባለ ንጥረ ነገር (ኬሚካል) ቁስ በሕገ ወጥ መንገድ ሲያዘዋወር የነበረ ተጠርጣሪ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር ዋለ።

ሰኔ 14/2015 ዓ.ም(አአሰፀአቢ)

*********

ሜርኩሪ የተባለ ንጥረ ነገር (ኬሚካል) ቁስ በሕገ ወጥ መንገድ ሲያዘዋወር የነበረ ተጠርጣሪ ግለሰብ በቁጥጥር ሥር መዋሉን የአዲስ አበባ ሰላም እና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው የሕዝብ አደረጃጀት ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ መላኩ ታምሩ እንደገለፁት ንጥረ ነገሩ የተያዘዉ ሰኔ 14/2015 ዓ.ም በአራዳ ከ/ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ሥፍራው ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ጀርባ ከረፋዱ 5:15 ላይ መሆኑን ገልፀዋል።

ም/ቢሮ ኃላፊው እንደገለፁት ንጥረ ነገሩን ሲያዘዋውር የነበረው ተጠርጣሪ በቁጥጥር ሥር የዋለው ከሕብረተሰቡ በደረሰ ጥቆማ መሆኑን ገልፀዋል።

ሜርኩሪ በመባል የሚታወቀው ንጥረ ነገር (ኬሚካል) ቁስ በፈሳሽ መልክ የሚገኝ እጅግ ውድ የሆነ የብረት ንጥረ ነገር ሲሆን ከንጥረ ነገሩ አደገኛነት የተነሳ በህግ ከተፈቀደላቸው የአያያዝ ጥንቃቄዎች፣ ተቋማት እና አገልግሎቶች ውጪ እንዳያገለግሉ ክልከላ ከተጣለባቸው ቁሶች መሃል አንዱ ነውም ተብሏል።

አቶ መላኩ ጨምረውም በተጠርጣሪው እና በንጥረ ነገሩ ዙሪያ ፓሊስ ተጨማሪ ምርመራዎች በማድረግ ላይ ነውም ብለዋል።

ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ጥቆማው ከደረሰ ቀን ጀምሮ እጅግ ውስብስብ እና እልህ አስጨራሽ መሰናክሎችን በማለፍ ለዚህ ስኬት መብቃታችን አስደስቶናል ካሉ በኋላ ለዚህ ያበቁንን ሕብረተሰቡንና የፀጥታ ኃይሎችን አመሰግናለሁ፣በቀጣይም ህብረተሰቡ ተመሳሳይ አጠራጣሪ ነገር ሲያጋጥመው ለፀጥታ ኃሎች ጥቆማ እንዲያደርግ ጥሪዬን አቀርባለሁ ብለዋል።

አሳዛኝ ዜና‼️በትራፊክ  አደጋ 15  የመደወላቡ ዩንቨርሲቲ  መምህራን ህይወታቸው  አለፈ‼️15 የመደወላቡ ዩንቨርሲቲ መምህራን ዛሬ ማለዳ ለማስተማር ወደ ሻሸመኔ ካምፓስ በመጓዝ ላይ እያሉ ...
20/05/2023

አሳዛኝ ዜና‼️

በትራፊክ አደጋ 15 የመደወላቡ ዩንቨርሲቲ መምህራን ህይወታቸው አለፈ‼️

15 የመደወላቡ ዩንቨርሲቲ መምህራን ዛሬ ማለዳ ለማስተማር ወደ ሻሸመኔ ካምፓስ በመጓዝ ላይ እያሉ በደረሰ የትራፊክ አደጋ ህይወታቸው ሊያልፍ ችሏል፡፡
የሮቤ ከተማ ከንቲባ አቶ ንጋቱ ሞቱማ ተሸከርካሪው መንገድ በመሳት በተፈጠረው አደጋ እስካሁን 15 የዩንቨርሲቲው መምህራን ህይወት ማለፉን ገልፀዋል።

"ውድ የአሻራ ሚዲያ ቤተሰቦች የአሻራ ሚዲያ ቻናልን ላይክና ሰብስክራይብ በማድረግ ድጋፋችሁን ታሳዩን ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።"

ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ ከእስር ተፈቱመጋቢት 21/5015 ዓ.ም )ወቅታዊ): በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እና በጄነራል ታደሰ ወረደ መዝገብ ተ...
30/03/2023

ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ ከእስር ተፈቱ

መጋቢት 21/5015 ዓ.ም )ወቅታዊ): በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል እና በጄነራል ታደሰ ወረደ መዝገብ ተከስሰው በእስር ላይ የነበሩ የህወሓት ሲቪል እና ወታደራዊ አመራሮች ዛሬ ሐሙስ መጋቢት 21፤ 2015 አመሻሽ ላይ ከእስር መፈታታቸውን የተከሳሾቹ ጠበቆች አስተባባሪ የሆኑት አቶ ሃፍቶም ከሰተ ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለት ከእስር ተለቅቀው ወደ ቤታቸው መግባታቸው ከተረጋገጡ ተከሳሾች ውስጥ፤ የህወሓት ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም፣ ዶ/ር አብርሃም ተከስተ እና ዶ/ር አዲስዓለም ባሌማ እንደሚገኙበት ጠበቃው አስታውቀዋል። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት

ቴሌግራም:- https://t.me/+AlLxDyZsHt4wZWM0
YouTube-: https://youtube.com/
Facebook:- https://www.facebook.com/GMJA2015/?mibextid=ZbWKwL

መከታተል ይችላሉ።

የተበላሸ ቴምር ተያዘመጋቢት 21/2015 ዓ.ም (ወቅታዊ):- ለገበያ ሊቀርብ የተዘጋጀ ንፅህናውን ያልጠበቀ እና የተበላሸ በርካታ ቴምር በግለሰብ መኖሪያ ግቢ ውስጥ ተከማችቶ መገኘቱን የአዲስ...
30/03/2023

የተበላሸ ቴምር ተያዘ

መጋቢት 21/2015 ዓ.ም (ወቅታዊ):- ለገበያ ሊቀርብ የተዘጋጀ ንፅህናውን ያልጠበቀ እና የተበላሸ በርካታ ቴምር በግለሰብ መኖሪያ ግቢ ውስጥ ተከማችቶ መገኘቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 2 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራ ይገኛል።
***
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉት መጋቢት 21 ቀን 2015 ዓ/ም በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታው ታይዋን ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኝ የግለሰብ መኖሪያ ግቢ ውስጥ ነው።

ግለሰቦቹ በመኖሪያ ግቢያቸው በሚገኝ መጋዘን ውስጥ የተበላሸና በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት ሊያስከትል የሚችል በርካታ ቴምር ንፅህና በጎደለው ሁኔታ አስቀምጠው ለአትራፊ ነጋዴዎች በፌስታል አሽገው የ92 ሺህ ብር ከሸጡላቸው በኋላ ቴምሩ የተበላሸ መሆኑን የተገነዘቡት ገዢዎቹ ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ መሰረት ሊያዙ ችለዋል፡፡ መረጃው የደረሰው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የእፎይታ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ከፍርድ ቤት የመበርበሪያ ትዕዛዝ በማወጣት እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በተጠርጣሪዎቹ መኖሪያ ግቢ በሚገኘው መጋዘን ውስጥ ባደረገው ፍተሻ መጥፎ ጠረን ያለው እና የተበላሸ በርካታ ቴምር ተከማችቶ መገኘቱን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

የወረዳ 10 አስተዳደር የምግብና መድሃኒት ቁጥጥር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሀብቱ መካ በበኩላቸው በቁጥጥር ስር የዋለው ቴምር ወደ ህብረተሰቡ ቢሰራጭ በጤና ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያስከትል እንደሚችል ተናግረው ከተጠርጣሪዎቹ የገዙትን የተበላሸ ቴምር ለህዝብ ሳይሸጡ እና የግል ጥቅም ሳያጓጓቸው ለሰዎች ጤና በማሰብ ለፖሊስ ጥቆማ መስጠታቸው ሊመሰገኑ ይገባል ብለዋል፡፡

በቁጥጥር ስር በዋሉት ሁለቱ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ እየተጣራ እንደሚገኝ የጠቀሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ፤ ጊዜና ወቅትን እየጠበቁ ህገወጥ ተግባር የሚፈፅሙ ነጋዴዎችም ሆኑ ሌሎች ግለሰቦች ከህግ ተጠያቂነት እንደማያመልጡ ተገንዝበው ከድርጊታቸው ሊቆጠቡ እንደሚገባ አሳስቧል፡፡

ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት

ቴሌግራም:- https://t.me/+AlLxDyZsHt4wZWM0
YouTube-: https://youtube.com/
Facebook:- https://www.facebook.com/GMJA2015/?mibextid=ZbWKwL

መከታተል ይችላሉ።

ሀላፊዋ በመሬት ሙስና ተጠርጥረው ታገዱመጋቢት 20/2048 ዓ.ም (ወቅታዊ):- የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማት ማኔጅመንት ፅ/ቤት ሀላፊ ከሙስና ጋር በተያያዘ ከስራ ታገ...
29/03/2023

ሀላፊዋ በመሬት ሙስና ተጠርጥረው ታገዱ

መጋቢት 20/2048 ዓ.ም (ወቅታዊ):- የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማት ማኔጅመንት ፅ/ቤት ሀላፊ ከሙስና ጋር በተያያዘ ከስራ ታገዱ

የክፍለ ከተማው አስተዳደር ከመሬት ልማት ማናጅመንት ፅ/ቤት አመራሮችና አጠቃላይ ባለሙያዎች ጋር ሰፊ ውይይትና ግምገማ ካደረገ በኋላ ለሌብነትና ብልሹ አሰራር ተጋላጭ የሆኑ አመራሮችና ባለሙያዎች ላይ እርምጃ ወስዷል ።

በዚህም የክፍለ ከተማው መሬት ልማት ማኔጅመንት ሀላፊ ከስራ መታገዳቸውን የመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።

ከሀላፊዋ በተጨማሪ ሌሎች የፅ/ቤቱ ዝቅተኛ ሀላፊዎች እና ባለሙያዎችም በብልሹ አሰራር ተጠርጥረው ከስራ መታገዳቸው ተገልጿል።

አስተዳደሩ ከአገልግሎት አሰጣጥ ፣ከብልሹ አሰራር እንዲሁም ከሌብነት ጋር የተያየዙ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ንጋቱ ዳኛቸው በተገኙበት ዝርዝር ግምገማ ማድረጉም ታውቋል።

የክፍለ ከተማው አስተዳደር በጉዳዩ ዙሪያ በቅርብ ቀናት ለሚድያ መግለጫ እንደሚሰጥም የውስጥ የመረጃ ምንጫችን ጠቁመዋል።
ESAT

ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት

ቴሌግራም:- https://t.me/+AlLxDyZsHt4wZWM0
YouTube-: https://youtube.com/
Facebook:- https://www.facebook.com/GMJA2015/?mibextid=ZbWKwL

መከታተል ይችላሉ።

የስንታየሁ ቸኮል ልጅ አሳዛኝ መልዕክትመጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም"ዝምታ ቢነግስም፤ፀጥታ ቢበረታም አንተ አስታዋሽ ብታጣም አንድ ቀን ይመጣል ስለ አንተ ፅናት እና ብርታት አፍን ከፍቶ የሚ...
26/03/2023

የስንታየሁ ቸኮል ልጅ አሳዛኝ መልዕክት

መጋቢት 17 ቀን 2015 ዓ.ም

"ዝምታ ቢነግስም፤ፀጥታ ቢበረታም አንተ አስታዋሽ ብታጣም አንድ ቀን ይመጣል ስለ አንተ ፅናት እና ብርታት አፍን ከፍቶ የሚናገርበት፤የሚመሰክርበት አንተም በተራክ ከልጆችክ ጋር የምትስቅበት ቀን ይመጣል። ሁሉንም ትተክ ልጆቼ ሳትል ወጣትነት ዕድሜዬን ሳትል ለተበደሉት ድምፅ እሆናለሁ ማለትክን ሰዎች ቢክዱ ማመን ባይፈልጉ ያለህበት አዋሽ 7 ምስክር ነው።አባቴ ሁሉም ዝም ቢልም እኔ ዝም አልልም!"
ምዕራፍ ስንታየሁ

ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት

ቴሌግራም:- https://t.me/+AlLxDyZsHt4wZWM0
YouTube-: https://youtube.com/
Facebook:- https://www.facebook.com/GMJA2015/?mibextid=ZbWKwL

መከታተል ይችላሉ።

ታጋይ ስብሀት ነጋታጋይ ስብሀት ነጋ ዋሺንግተን ዲሲ ገብተዋል።የህወሓት ቁንጮ በመባል የሚታወቁት እና በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ተይዘው በእስር ላይ የቆዩት ስብሀት ነጋ ዲሲ ገብተዋል።እርሳቸው በ...
25/03/2023

ታጋይ ስብሀት ነጋ

ታጋይ ስብሀት ነጋ ዋሺንግተን ዲሲ ገብተዋል።

የህወሓት ቁንጮ በመባል የሚታወቁት እና በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ተይዘው በእስር ላይ የቆዩት ስብሀት ነጋ ዲሲ ገብተዋል።

እርሳቸው በጠነሰሱት ጦርነት በሚሊዮን የሚቆጠሩ የትግራይ ወጣቶች ህይወታቸውን ሲያጡ በርካቶች የአካል ጉዳት ሰለባ ሆነዋል።

ከትግራይ በተጨማሪ የአማራ እና የአፋር ወጣቶች ተገድለዋል፣እናቶች እና ህፃናት ተደፍረዋል፣ ንብረትም ወድሟል።

ሀገር ጠባቂው መከላከያም ክህደት ተፈፅሞበት ተረሽኗል።

ከመገደል ቢተርፉም ቢያንስ የእድሜ ልክ እስራት ይጠብቃቸዋል የተባሉት አቶ ስብሀት ነጋ ወራትን እእንኳን በእስር ቤት ሳይቆዩ መለቀቃቸው ይታወሳል።

ከእስር ቢለቀቁም የቁም እስረኛ ይሆናሉ የሚል ግምት ቢኖርም ዛሬ ዋሺንግተን ዲሲ ገብተዋል።

ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት

ቴሌግራም:- https://t.me/+AlLxDyZsHt4wZWM0
YouTube-: https://youtube.com/
Facebook:- https://www.facebook.com/GMJA2015/?mibextid=ZbWKwL

መከታተል ይችላሉ።

ካህኑ በድንጋይ ተቀጥቅጠው ሞቱ=====================በአዲስ አበባ ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ መጋቢት 14/2015 ዓ.ም ቀሲስ ዐባይ መለሰ የተባሉ ካህን ቅዳሴ ጨርሰው ወደ ቤታቸው በ...
24/03/2023

ካህኑ በድንጋይ ተቀጥቅጠው ሞቱ
=====================

በአዲስ አበባ ኃይሌ ጋርመንት አካባቢ መጋቢት 14/2015 ዓ.ም ቀሲስ ዐባይ መለሰ የተባሉ ካህን ቅዳሴ ጨርሰው ወደ ቤታቸው በመሄድላይ እንዳሉ በድንጋይ ተወግረው ሕይወታቸው ማለፉን የዐይን እማኞች ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ገለፁ።

የሆርሲሳ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የነበሩት ቀሲስ ዐባይ መለሰ ሕይወታቸው ሲያልፍ ችግሩ ታወቀ እንጂ አስቀድሞ በአካባቢው አገልጋዮች ላይ ዛቻ እና ማስፈራሪያ ይደርስ እንደነበር መረጃ ሰጭዎቻችን በቦታው ለተገኘው ዘጋቢያችን ገልፀዋል።

ካህኑ በድንጋይ ተደብድበው እያሉ ምስልና ቪዲዮ ለማስረጃ ለመያዝ ቢሞክሩም በአካባቢው የፀጥታ ኃይሎች ሞባይል እየተሰበሰበ መሰረዙንም ነግረውናል።

ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት

ቴሌግራም:- https://t.me/+AlLxDyZsHt4wZWM0
YouTube-: https://youtube.com/
Facebook:- https://www.facebook.com/GMJA2015/?mibextid=ZbWKwL

መከታተል ይችላሉ።

Address

Ethiopia
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GMJA TUBE- ግምጃ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share