EBC SPORT

EBC SPORT EBC Sport is one of Ethiopian Broadcasting Corporation social media focusing on Sports.

ድሬዳዋ ከተማ ወላይታ ድቻን 1 ለ 0 አሸነፈ*************በ2ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ  ድሬዳዋ ከተማ በውድድር ዓመቱ የመጀመርያ ሦስት ነጥቡን አግኝቷል።አቤል ነጋሽ ...
23/10/2025

ድሬዳዋ ከተማ ወላይታ ድቻን 1 ለ 0 አሸነፈ
*************

በ2ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ በውድድር ዓመቱ የመጀመርያ ሦስት ነጥቡን አግኝቷል።

አቤል ነጋሽ የድሬዳዋ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።

በሌሎች የዛሬ ጨዋተዎች ፋሲል ከነማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲን 2 ለ 0 አሸንፏል።

በረከት ግዛው እና አቤኔዘር ዩኋንስ የፋሲል ከነማን ግቦች አስቆጥረዋል።

አዳማ ከተማ ከ ሸገር ከተማ ያደረጉት ጨዋታ ግብ ሳይቆጠርበት 0 ለ 0 ተጠናቋል።

የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤቷ ሩት ችፕንጌቲች የሶስት ዓመት እገዳ ተጣለባት***********ኬንያዊቷ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤቷ  አትሌት ሩት ችፕንጌቲች አበረታች ንጥረ ነገር ተጠቅ...
23/10/2025

የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤቷ ሩት ችፕንጌቲች የሶስት ዓመት እገዳ ተጣለባት

***********

ኬንያዊቷ የማራቶን የዓለም ክብረ ወሰን ባለቤቷ አትሌት ሩት ችፕንጌቲች አበረታች ንጥረ ነገር ተጠቅማ መገኝቷ በመረጋገጡ ለሦስት ዓመት እገደ እንደተጣለባት ይፋ ሆኗል።

ቀደም ብሎ ከጉዳዩ ጋር በተገናኘ በጊዜያዊነት ታግዳ የነበረችው የ31 ዓመቷ አትሌት የጸረ አበረታች ቅመሞችን ህግ ተላልፋ መገኘቷን የአትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ይፋ አድርጓል።

ኬንያዊቷ አትሌት የተገኝባት (ሀይድሮክሎሮቲያዛይድ) የተባለ የተከለከለ መድሀኒት መሆኑን ይፋ ያደረገው አትሌቲክስ ኢንተግሪቲ አትሌቷ ቅጣቱን መቀበሏንም አሳውቋል።

አበረታች ቅመሞችን ተጠቅማ መገኘቷ የተረጋገጠው የሦስት ጊዜ የቺካጎ ማራቶን አሸናፊዋ ሩት ችፕንጌቲች ከመጋቢት 14 ቀን 2025 በፊት ያስመዘገበቻቸው ስኬቶቿ እንደማይሰረዙ አትሌቲክስ ኢንተግሪቲ ይፋ አድርጓል።

በመሆኑም ከኢትዮጵያዊቷ አትሌት ትግስት አሰፋ እጅ የወሰደችው የዓለም የማራቶን ክብረ ወሰን በራሷ በችፕንጌቲች እጅ ተይዞ የሚቆይም ይሆናል።

አበረታች ቅመሞችን የሚጠቀሙ ኬንያውያን አትሌቶች ከጊዜ ወደ ጊዜ ቁጥራቸው እየጨመረ የመጣ ሲሆን ከ2017 በኋላ ሩት ችፕንጌቲች የተከለከለ ንጥረ ነገር ተጠቅማ የተገኘች 140ኛዋ የኬንያ አትሌትም ሆናለች። ይሄ አስደንጋጭ ቁጥር ምስራቅ አፍሪካዊቷን ሀገር አበረታች ቅመሞችን በመጠቀም ቀዳሚዋ ሀገርም አድርጓታል።

ማራቶንን ከ2 ስአት ከ10 በታች መግባት የቻለችው የመጀመርያዋ አትሌት ሩት ችፕንጌቲች የቺካጎ ማራቶንን የገባችበት 2 ስአት ከ9 ደቂቃ 56 ሰከንድ የአለም ክብረ ወሰን ሆኖ መመዝገቡም ይታወሳል፡፡

ኢትዮጵያ ቡና የመጀመርያ ሦስት ነጥቡን አገኘ************በ2ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከነገሌ አርሲ የተጫወተው ኢትዮጵያ ቡና 2 ለ 1 አሸንፏል።በ1ኛ ሳምንት በቅዱስ ጊዮርጊ...
23/10/2025

ኢትዮጵያ ቡና የመጀመርያ ሦስት ነጥቡን አገኘ
************

በ2ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከነገሌ አርሲ የተጫወተው ኢትዮጵያ ቡና 2 ለ 1 አሸንፏል።

በ1ኛ ሳምንት በቅዱስ ጊዮርጊስ የተሸነፈው ኢትዮጵያ ቡና ወደ አሸናፊነት የተመለሰበትን ውጤት አስመዝግቧል።

7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስቴዲየም በተደረገው ጨዋታ አቡበክር አዳሙ እና በፍቃዱ አለማየሁ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ገ/መስቀል ዱባለ የነገሌ አርሲን ብቸኛ ግብ አስቆጥሯል።

የአለማችን ምርጡ የእግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል *************የቤኔፊካ እግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል ለሁለተኛ ተከታታይ አመት የአለማችን ምርጡ የእግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሆኖ ተመርጧ...
23/10/2025

የአለማችን ምርጡ የእግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል
*************

የቤኔፊካ እግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል ለሁለተኛ ተከታታይ አመት የአለማችን ምርጡ የእግር ኳስ ማሰልጠኛ ማዕከል ሆኖ ተመርጧል።

በአለም ዙርያ በሚገኙ 49 ሊጎች የሚጫወቱ ወጣት ተጨዋቾች የሰለጠኑባቸው የልምምድ ማዕከላት ፣ እየተጫወቱባቸው የሚገኙ ክለቦች ደረጃ እና የተጫወቱበት የደቂቃ ብዛት ተመዝኖ በየዓመቱ ደረጃ ይወጣላቸዋል።

የማሰልጠኛ ማዕከላትን ደረጃ የሚያወጣው አለም አቀፉ የስፖርት ጥናቶች ማዕከል (CIES) በተቀመጡት መመዘኛዎች የቤኔፊካ የእግር ኳስ አካዳሚ የዓለም ምርጡ መሆኑን አሳውቋል።

የፖርቹጋሉ እግር ኳስ አካዳሚ ይሄንን ክብር ሲያሸንፍ በተከታታይ ለሁለተኛ ጊዜም ሆኗል

ባለፈው አመት የቤኔፊካ ማሰልጠኛ ማዕከል ያፈራቸው 93 ተጨዋቾች በ49 ሊጎች ውስጥ 2582 ደቂቃ የመጫወት ዕድል እንዳገኙ የተገለጸ ሲሆን ከ10 ተጨዋቾች ውስጥ በአማካይ 8ቱ በክለቦቻቸው በቋሚነት የመቀጠር ዕድል ማግኘታቸውን የጥናት ማዕከሉ አስታውቋል ።

የባርሴሎና ላማሲያ የማሰልጠኛ ማዕከል 76 ተጨዋቾችን በ49 ሊጎች ላይ በማጫወት ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።

የአርጀንቲናው ሪቨርፕሌት 97 ተጨዋቾቹ በ49 ሊጎች ውስጥ 2305 ደቂቃዎች የመጫወት ዕድል በማግኘት ሶስተኛ ሆኗል ።

የሆላንዱ አያክስ አምስተርዳም ፣ የአርጀንቲናው ቦካ ጁንየርስ እና የፖርቹጋሉ ስፖርቲንግ ሊዝበን ከ4ተኛ እስከ 6ተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል ።

በ2006 የተመሠረተው እና ጁዋዎ ፊሊክስ ፣ በርናንዶ ሲልቫ ፣ ሩበን ዲያዝ ፣ ጁዋዎ ኔቬስ ፣ ጎንካሎ ራሞስ ፣ ጁዋዎ ካንሴሎን የመሳሰሉ ክዋክብትን ያፈራው የቤኔፊካ የማሰልጠኛ ማዕከል 80 ዋንጫዎችን በታዳጊ ፕሮጀክቶቹ በሀገር እና በአለም አቀፍ ደረጃ ያነሳ ሲሆን ባለፉት 10 አመታት ከተጫዋቾች ሽያጭ ከ1 ቢልዮን ዶላር በላይ ገቢ አግኝቷል ።

በእስከአድማስ ሙላቱ

በዛሬዋ  ዕለት የተወለደው የዓለም የምንጊዜም ምርጡ ተጫዋች ፔሌ************የዓለም የምንጊዜም ምርጡ ተጫዋች ኤድሰን አራንተስ ዶ ናሲሜንቶ (ፔሌ) የዛሬ 85 ዓመት ልክ በዛሬዋ ዕለት ...
23/10/2025

በዛሬዋ ዕለት የተወለደው የዓለም የምንጊዜም ምርጡ ተጫዋች ፔሌ
************

የዓለም የምንጊዜም ምርጡ ተጫዋች ኤድሰን አራንተስ ዶ ናሲሜንቶ (ፔሌ) የዛሬ 85 ዓመት ልክ በዛሬዋ ዕለት ነበር የተወለደው።

ከ3 ዓመት በፊት ህይወቱ ያለፈው ብራዚላዊ ሦስት የዓለም ዋንጫዎችን በማንሳት የዓለም ብቸኛው ተጫዋች ነው።

የ2ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በሚደረጉ አራት ጨዋታዎች ይጀመራል**************7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስቴዲየም ኢትዮጵያ ቡና ከነገሌ አርሲ ጨዋታውን ያደርጋል።በሊጉ...
23/10/2025

የ2ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በሚደረጉ አራት ጨዋታዎች ይጀመራል
**************

7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስቴዲየም ኢትዮጵያ ቡና ከነገሌ አርሲ ጨዋታውን ያደርጋል።

በሊጉ ጅማሮ በሸገር ደርቢ በቅዱስ ጊዮርጊስ 1 ለ 0 የተሸነፈው ኢትዮጵያ ቡና በበርካታ ደጋፊዎቹ ታግዞ ወደ አሸናፊነት ለመመለስ እንደሚጫወት ይጠበቃል።

የሊጉ እንግዳ ነገሌ አርሲ በመጀመርያው ሳምንት ከአርባ ምንጭ ከተማ ጋር ነጥብ መጋራቱ ይታወሳል።

በተመሳሳይ በአዲስ አበባ ስቴዲየም 10 ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከ ከሸገር ከተማ የሚጫወቱ ይሆናል።

ሸገር ከተማ በ1ኛ ሳምንት በኢትዮ ኤሌክትሪክ 1 ለ 0 መሸነፉ የሚታወስ ሲሆን አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ መድን 0 ለ 0 ተለያይቷል።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስቴዲየም ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ከ ፋሲል ከነማ 9 ሰዓት ላይ ሲጫወቱ 12 ሰዓት ላይ ደግሞ ወላይታ ድቻ ከድሬዳዋ የሚገናኙ ይሆናል።

ሊቨርፑል እና ቼልሲ በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፉ***********በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 3ኛ ዙር ጨዋታ ሊቨርፑል አይንትራ ፍራንክፈርትን 5 ለ 1 አሸንፏል፡፡ ሁጎ ኢኪቲኬ የቀድሞ ክለቡ ላ...
22/10/2025

ሊቨርፑል እና ቼልሲ በሰፊ የግብ ልዩነት አሸነፉ
***********

በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 3ኛ ዙር ጨዋታ ሊቨርፑል አይንትራ ፍራንክፈርትን 5 ለ 1 አሸንፏል፡፡

ሁጎ ኢኪቲኬ የቀድሞ ክለቡ ላይ፣ ቨርጂል ቫን ዳይክ፣ ኢብራሂማ ኮናቴ፣ ኮዲ ጋክፖ እና ዶሚኒክ ሶቦዝላይ ግቹን አስቆጥረዋል፡፡

ክርስቲያንሰን የባለሜዳዎቹን ግብ ያስቆጠረ ተጫዋች ነው፡፡

አሰልጣኝ አርን ስሎት ሙሃመድ ሳላን ተቀያሪ ወንበር ላይ አስቀምጠው ሁጎ ኢኪቲኬን እና አሌክሳንደር ኢሳቅን በቋሚነት ባስጀመሩበት ጨዋታ ከ አራት ተከታታይ ሽንፈት በኋላ ወደ አሸናፊነት የተመለሰበትን ውጤት አስመዝግበዋል፡፡

ቼልሲም በተመሳሳይ አያክስ አምስተርዳምን 5 ለ 1 አሸንፏል፡፡
በስታምፎርድ ብርጂ በተደረገው ጨዋታ ማርክ ጊዩ፣ ኢንዞ ፈርናንዴዝ፣ ሞይሰስ ካይሴዶ፣ ኢስቴቫዎ እና ጆርጅ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡

ቬግ ሆረስት የአያክስን ብቸኛ ግብ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡

በሜዳው ሳንቲያጎ ቤርናቡ ጁቬንቱስን ያስተናገደው ሪያል ማድሪድ በጁድ ቢሊንግሀም ብቸኛ ግብ 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ አሮጊቶቹ በሻምፒዮንስ ሊግ አሁንም ማሸነፍ አልቻሉም፡፡

የጀርመኑ ሀያል ክለብ ባየር ሙኒክ ክለብ ብሩጅን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት ሲያሸንፍ ሃሪ ኬን፣ ሉዊስ ዲያዝ፣ ኒኮላስ ጃክሰን እና ካርል ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡

በሌሎች ጨዋታዎች ቶተንሀም ሆትስፐር ከሞናኮ 0 ለ 0 ሲለያይ ስፖርቲንግ ሊዝበን ማርሴይን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡

በሻምፒዮንስ ሊግ ጋላታሳራይ እና አትሌቲክ ቢልባኦ አሸነፉ ************በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 3ኛ ዙር ጨዋታ አትሌቲክ ቢልባኦ ካራባግን 3 ለ 1 በማሸነፍ የመጀመርያ 3 ነጥቡን አግ...
22/10/2025

በሻምፒዮንስ ሊግ ጋላታሳራይ እና አትሌቲክ ቢልባኦ አሸነፉ
************

በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ 3ኛ ዙር ጨዋታ አትሌቲክ ቢልባኦ ካራባግን 3 ለ 1 በማሸነፍ የመጀመርያ 3 ነጥቡን አግኝቷል።

በሳን ማሜስ በተደረገው ጨዋታ ጎርካ ጉሩዜታ ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ናቫሮ የስፔኑን ክለብ ተጨማሪ ግብ አስቆጥረዋል።

ሌአንድሮ አንድራድ የካራባግን ብቸኛ ግብ ያሰቆጠረ ተጨዋች ሆኗል።

በሌላ ጨዋታ ጋላታሳራይ ቡዶ ጊልሜትን በተመሳሳይ 3 ለ 1አሸንፏል። ቪክቶር ኦስሚህን ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር አክገን አንድ ግብ አስገንቷል።

አንድሪያስ ሄልምርሰን የጊልሜትን ግብ ያስቆጠረ ተጨዋች ነው።

ሉሲዎቹ በታንዛኒያ 2 ለ 0 ተሸነፉ**********በአፍሪካ  ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታ በአዛም ኮምፕሌክስ  ከታንዛኒያ የተጫወተው  የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን 2 ለ 0 ተሸንፏል።በሞ...
22/10/2025

ሉሲዎቹ በታንዛኒያ 2 ለ 0 ተሸነፉ
**********
በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታ በአዛም ኮምፕሌክስ ከታንዛኒያ የተጫወተው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን 2 ለ 0 ተሸንፏል።

በሞሮኮ አስተናጋጅነት ለሚደረገው የአፍሪካ ዋንጫ ለመሳተፍ ሉሲዎቹ የመልሱን ጨዋታ ከሰባት ቀን በኋላ በኢትዮጵያ የሚያደርጉም ይሆናል።

ሉሲዎቹ ከ14 ዓመት በኋላ ወደ አፍሪካ ዋንጫ ለመመለስ በመልሱ ጨዋታ ሶስት እና ከዚያ በላይ ግቦችን አስቆጥረው ማሸነፍ ይጠበቅባቸዋል።

ታንዛኒያ 1 : 0 ኢትዮጵያ ***********የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በታንዛኒያ 1 ለ 0 እየተመራ የመጀመርያው 45 ደቂቃ ተጠናቋል።
22/10/2025

ታንዛኒያ 1 : 0 ኢትዮጵያ
***********

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በታንዛኒያ 1 ለ 0 እየተመራ የመጀመርያው 45 ደቂቃ ተጠናቋል።

ሳንድሮ ቶናሊ በኒውካስትል ውሉን አራዘመ***********ጣልያናዊው አማካይ ሳንድሮ ቶናሊ ከኒውካስትል ዩናይትድ ጋር እስከ 2029 የሚያቆየውን ውል አራዝሟል፡፡ኒውካስትል የተጫዋቹን ውል ለተ...
22/10/2025

ሳንድሮ ቶናሊ በኒውካስትል ውሉን አራዘመ
***********

ጣልያናዊው አማካይ ሳንድሮ ቶናሊ ከኒውካስትል ዩናይትድ ጋር እስከ 2029 የሚያቆየውን ውል አራዝሟል፡፡

ኒውካስትል የተጫዋቹን ውል ለተጨማሪ 12 ወር የማራዘም አማራጭ እንዳለው በስምምነቱ ተቀምጧል፡፡

በ2023 ከ ኤሲ ሚላን ኒውካስትልን የተቀላቀለው ሳንድሮ ቶናሊ ውሉ 2028 ላይ የሚጠናቀቅ ቢሆንም በእንግሊዝ መቆየትን ምርጫው አድርጓል፡፡

ሉሲዎቹ ከ ታንዛኒያ ብሔራዊ ቡድን ***********የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የሚያደረገው የመጀመርያ ጨዋታ 11 ሰዓት ላይ ይጀመራል፡፡የሉሲዎቹ ቋሚ 11 ተጫ...
22/10/2025

ሉሲዎቹ ከ ታንዛኒያ ብሔራዊ ቡድን
***********
የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ወደ አፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ የሚያደረገው የመጀመርያ ጨዋታ 11 ሰዓት ላይ ይጀመራል፡፡

የሉሲዎቹ ቋሚ 11 ተጫዋቾችም ይፋ ሆነዋል፡፡

Address

Addis Ababa
3344

Telephone

+251115172539

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EBC SPORT posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share