23/10/2025
ድሬዳዋ ከተማ ወላይታ ድቻን 1 ለ 0 አሸነፈ
*************
በ2ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ በውድድር ዓመቱ የመጀመርያ ሦስት ነጥቡን አግኝቷል።
አቤል ነጋሽ የድሬዳዋ ከተማን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
በሌሎች የዛሬ ጨዋተዎች ፋሲል ከነማ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርስቲን 2 ለ 0 አሸንፏል።
በረከት ግዛው እና አቤኔዘር ዩኋንስ የፋሲል ከነማን ግቦች አስቆጥረዋል።
አዳማ ከተማ ከ ሸገር ከተማ ያደረጉት ጨዋታ ግብ ሳይቆጠርበት 0 ለ 0 ተጠናቋል።