EBC SPORT

EBC SPORT EBC Sport is one of Ethiopian Broadcasting Corporation social media focusing on Sports.

ድሬዳዋ ከተማ ስሑል ሽረን በማሸነፍ ከወራጅ ቀጠና ወጣ በ35ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ከስሁል ሽረ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ  ማሸነፉን ተከትሎ በሊጉ  የመቆየት  ዕድሉን  አስ...
17/06/2025

ድሬዳዋ ከተማ ስሑል ሽረን በማሸነፍ ከወራጅ ቀጠና ወጣ

በ35ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ከስሁል ሽረ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ማሸነፉን ተከትሎ በሊጉ የመቆየት ዕድሉን አስፍቷል፡፡ 9 ሰአት በወንጂ ሁለገብ ስቴዲየም ያደረገውን ጨዋታ 4 ለ 2 አሸንፏል፡፡

መስዑድ መሀመድ የድሬዳዋ ከተማን ሁለት ግበች ሲያስቆጥር ዩኋንስ ደረጄ እና ሀቢብ ከማል ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል፡፡ ብርሀኑ አዳሙ እና አላዛር ሽመለስ ከፕሪሚየር ሊጉ ቀድሞ መውረዱን ላረጋገጠው ስሑል ሽረ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡

ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ በቀረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ከነበረበት 15ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ከፍ ብሏል፡፡

አራት ክለቦች ከሊጉ በሚወርዱበት አመት አዳማ ከተማ፣ መቐለ ሰባእንደርታ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ፋሲል ከነማ መቆየታቸውን ለማረጋገጥ የመጨረሻውን ሳምንት ለመጠበቅ የተገደዱ ናቸው፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

ድሬዳዋ ከተማ ስሑል ሽረን በማሸነፍ ከወራጅ ቀጠና ወጣ *******በ35ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ከስሁል ሽረ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ  ማሸነፉን ተከትሎ በሊጉ  የመቆየት  ዕ...
17/06/2025

ድሬዳዋ ከተማ ስሑል ሽረን በማሸነፍ ከወራጅ ቀጠና ወጣ
*******

በ35ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ከስሁል ሽረ የተጫወተው ድሬዳዋ ከተማ ማሸነፉን ተከትሎ በሊጉ የመቆየት ዕድሉን አስፍቷል፡፡

9 ስዓት ላይ በወንጂ ሁለገብ ስቴዲየም ያደረገውን ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ 4 ለ 2 አሸንፏል፡፡

መስዑድ መሀመድ የድሬዳዋ ከተማን ሁለት ግበች ሲያስቆጥር ዮሐንስ ደረጄ እና ሀቢብ ከማል ቀሪዎቹን ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል፡፡ ብርሀኑ አዳሙ እና አላዛር ሽመለስ ከፕሪሚየር ሊጉ ቀድሞ መውረዱን ላረጋገጠው ስሑል ሽረ ግቦቹን አስቆጥሯል፡፡

ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ በቀረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ዛሬ ከነበረበት 15ኛ ደረጃ ወደ 12ኛ ከፍ ብሏል፡፡

አራት ክለቦች ከሊጉ በሚወርዱበት ዓመት አዳማ ከተማ ፣ መቀሌ ሰባእንደርታ ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ፣ ድሬዳዋ ከተማ ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ፋሲል ከነማ መቆየታቸውን ለማረጋገጥ የመጨረሻውን ሳምንት ለመጠበቅ የተገደዱ ናቸው፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

“ፕሮጀክት 150” የማንችስተር ዩናይትድ አዲሱ የዋንጫ ዕቅድ ይሳካ ይሆን?ማንችስተር ዩናይትድ በ2028 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን የማንሳት ዕቅድ እንዳለው ቀደም ብሎ ይፋ አድርጓል፡፡...
17/06/2025

“ፕሮጀክት 150” የማንችስተር ዩናይትድ አዲሱ የዋንጫ ዕቅድ ይሳካ ይሆን?

ማንችስተር ዩናይትድ በ2028 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን የማንሳት ዕቅድ እንዳለው ቀደም ብሎ ይፋ አድርጓል፡፡

የክለቡ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኦማር በራዳ ከሶስት አመት በኋላ የሊጉን ዋንጫ የማንሳት እቅዳቸው ተግባራዊ እንደሚሆን አሳውቀዋል፡፡

በ2028 የተመሰረተበትን 150ኛ አመት የሚያከብረው ማንችስተር ዩናይትድ ታሪካዊውን አመት በትልቅ ክብር ማጀብ እንደሚፈልግ ዋና ስራ አስፈጻሚው ተናግረዋል፡፡

ከፕሪሚየር ሊጉ ወርዶ ከተመለሰ በኋላ ዝቅተኛ የተባለውን እና አስቸጋሪውን የውድድር አመት ለማሳለፍ የተገደደው ዩናይትድ በ42 ነጥብ 15ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡

በተጨማሪም በዩሮፓ ሊግ ፍጻሜ በቶተንሀም ተሸንፎ ዋንጫውን በማጣቱ በቀጣይ አመት ከየትኛውም የአውሮፓ መድረክ ውድድሮች ውጭ እንዲሆን አድርጎታል፡፡

በወጣቱ አሰልጣኝ ሩብን አሞሪም እምነት እንዳላቸው የገለጹት ዋና ስራ አስፈጻሚው በቀጣይ ሁለት አመት ክለቡ የሚፈልጋቸውን ተጫዋቾች እንደሚያገኝም ተናግረዋል፡፡

የ20 ጊዜ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮኑ ክለብ በሴቶቹም ከሶስት አመት በኋላ የሱፐር ሊጉን ክብር የማሳካት ዕቅድ አስቀምጦ እየሰራ እንደሚገኝ ሱፐር ስፖርት ዘግቧል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

700 ቢሊዮን ዕይታ እና 10 ቢሊየን ዶላር ገቢ ይገኝበታል ተብሎ የሚጠበቀው ዓለም ዋንጫፊፋ ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ 10 ቢሊየን ዶላር ገቢ ሊያገኝ እንደሚችል ይፋ ተደርጓል፡፡ ለመጀመርያ ...
17/06/2025

700 ቢሊዮን ዕይታ እና 10 ቢሊየን ዶላር ገቢ ይገኝበታል ተብሎ የሚጠበቀው ዓለም ዋንጫ

ፊፋ ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ 10 ቢሊየን ዶላር ገቢ ሊያገኝ እንደሚችል ይፋ ተደርጓል፡፡

ለመጀመርያ ጊዜ 48 ሀገራት በሚሳተፉበት የዓለም ዋንጫ የውድድሩ ባለቤት ፊፋ 10 ቢሊየን ዶላር ገቢ የሚያገኝበት ዕድል ሰፊ መሆኑን መቀመጫውን በለንደን ያደረገ ፒች ማርኬቲንግ ግሩፕ አሳውቋል፡፡

አሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ በጣምራ የሚያዘጋጁት የ2026ቱ ዓለም ዋንጫ መድረክ ከእስከዛሬዎቹ እጅግ ትርፋማው የስፖርት ሁነት ይሆናል ተብሏል፡፡

ተቋሙ ይፋ እንዳደረገው ለ6 ሳምንት የሚቆየውን ውድድር 5 ቢሊዮን ተመልካች ወይም ከዓለም ህዝብ ሁለት 3ኛው ያየዋል የሚል ግምት ተቀምጧል፡፡

በሌላ በኩል ከአንድ አመት በኋላ የሚደረገው የዓለም ዋንጫ በሁሉም የሚዲያ አማራጮች እስከ 700 ቢሊዮን ዕይታዎችን ሊያገኝ እንደሚችልም ተቀምጧል፡፡

በቅርብ ጊዜያት ከሚያዘጋጃቸው ውድድሮች ረብጣ ገንዘብ እያገኝ ያለው የዓለም አቀፉ እግር ኳስ ፌደሬሽኖች ማኅበር (ፊፋ) እየተካሄደ የሚገኘውን የዓለም ክለቦች ዋንጫ ጨምሮ ከ2023 እስከ 2026 በአጠቃላይ ገቢው 13 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል ተብሏል፡፡

በጂያን ኢንፋንቲኖ የሚመራው ተቋም ከ2018 እስከ 2022 ካገኘው ገቢ ጋር ሲነጻጸርም የ75 በመቶ ዕድገት ያሳየ ሆኗል፡፡

የተሳታፊ ሀገራት ቁጥር ከ32 ወደ 48 ከፍ ማለቱ እና የጨዋታ ብዛቱም ከ64 ወደ 104 ማደጉ ከተለየዩ ስፖንሰሮች በተጨማሪ በዋናነት ገቢው እንዲጨምር ከሚያደርጉት ምክንያቶች ቀዳሚዎቹ መሆናቸውን ዘ አትሌቲክ ይፋ አድርጓል፡፡

ሶስቱ ሀገራት የሚያዘጋጁት ትልቁ መድረክ በቀጣይ አመት በ16 ከተሞች የሚካሄድም ይሆናል።

በአንተነህ ሲሳይ

ድሬዳዋ  ከተማ በሊጉ ለመቆየት የሚያደርገው ጨዋታ*******በ35ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው ድሬዳዋ ከተማ  ከስሁል ሽረ ይጫወታል።9 ስዓት ላይ በወ...
17/06/2025

ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ ለመቆየት የሚያደርገው ጨዋታ
*******

በ35ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው ድሬዳዋ ከተማ ከስሁል ሽረ ይጫወታል።

9 ስዓት ላይ በወንጂ ሁለገብ ስቴዲየም በሚደረገው ጨዋታ 15ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው ድሬዳዋ ከተማ ቀድሞ መውረዱን ካረጋገጠው ስሁል ሽረ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል።

ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ በቀረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድሬዳዋ ከተማ ዛሬ ማሸነፍ ከቻለ በሊጉ የመቆየት ዕድሉን ያሰፋል፡፡

አራት ክለቦች ከሊጉ በሚወርዱበት ዓመት አዳማ ከተማ ፣ መቀሌ ሰባእንደርታ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ፣ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ፋሲል ከነማ አሁንም በሊጉ መቆየታቸውን ያላረጋገጡ ክለቦች ናቸው፡፡

ስሁል ሽረ እና ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቀድመው ከፕሪሚየር ሊጉ መሰናበታቸውን ያረጋገጡ ሆነዋል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

#ድሬዳዋ

ማቲያስ አልሜይዳ የሴቪያ ዋና አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ*******የቀድሞው የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ማቲያስ አልሜይዳ፤ ሃቪየር ጋርሺያን በመተካት የስፔኑን ክለብ ሴቪያን ተረክቧል፡፡ማቲያ...
17/06/2025

ማቲያስ አልሜይዳ የሴቪያ ዋና አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ
*******

የቀድሞው የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ማቲያስ አልሜይዳ፤ ሃቪየር ጋርሺያን በመተካት የስፔኑን ክለብ ሴቪያን ተረክቧል፡፡

ማቲያስ አልሜይዳ ከሴቪያ ጋር ለሶስት ዓመት የሚያቆየውን ውል ፈርሟል፡፡

የ51 ዓመቱ አልሜይዳ ከ2022/23 የውድድር ዓመት በኋላ በሴቪያ የተቀጠረ 8ኛው አሰልጣኝ ሆኗል፡፡

በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለመውረድ ተቃርቦ የተረፈውና 17ኛ ሆኖ ያጠናቀቀውን ክለብ ወደ ተፎካካሪነት መመለስ የአሰልጣኙ ትልቁ ሃላፊነት ይሆናል ተብሏል፡፡

የሰባት ጊዜ የዩሮፓ ሊግ አሸናፊው ክለብ ባለፉት ሁለት ዓመታት ከሁሉም የአውሮፓ መድረክ ውድድሮች ውጪ ሆኗል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

#ስፖርት

6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች በጅማ ከተማ መካሄድ ጀመረበአሁኑ ሰዓት  የመክፈቻ  መርሀ  ግብር በጅማ  ዩኒቨርሲቲ ስቴዲየም  እየተካሄደ  የሚገኝ  ሲሆን የኢፌዴሪ ምክትል  ጠቅላይ ሚንስትር...
17/06/2025

6ኛው መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች በጅማ ከተማ መካሄድ ጀመረ

በአሁኑ ሰዓት የመክፈቻ መርሀ ግብር በጅማ ዩኒቨርሲቲ ስቴዲየም እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ተመስገን ጥሩነህ፣ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር አወሉ አብዲ እና የባህልና ስፖርት ሚንትሯ ሸዊት ሻንካን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የመንግስት የስራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል፡፡

በኦሎምፒክ መርህ የሚካሄደውን መላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ተመስገን ጥሩነህ የኦሎምፒክ ችቦውን በመለኮስ ለአትሌት ጌጤ ዋሚ እና አትሌት ኢብራሂም ጄይላን አስረክበዋል፡፡

ለ9 አመት ተቋርጦ በነበረው ውድድር ሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተደደሮች ተካፋይ ሆነውበታል፡፡

“ስፖርት ለህብር ኢትዮጵያ አርበኝነት” በሚል መሪ ሀሳብ በሚካሄደው መድረክ በ26 የስፖርት አይነቶች ከ4500 በላይ ስፖርተኞች የሚሳተፉበት ይሆናል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

በቪኒሺየስ ጁኒየር ላይ የዘረኝነት ጥቃት የሰነዘሩ ደጋፊዎች በእስራት ተቀጡ*******በ2023 ብራዚላዊው አጥቂ ላይ ድርጊቱን የፈጸሙ አራት ደጋፊዎች በእስራት እንዲቀጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡በስፔ...
17/06/2025

በቪኒሺየስ ጁኒየር ላይ የዘረኝነት ጥቃት የሰነዘሩ ደጋፊዎች በእስራት ተቀጡ
*******

በ2023 ብራዚላዊው አጥቂ ላይ ድርጊቱን የፈጸሙ አራት ደጋፊዎች በእስራት እንዲቀጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡

በስፔን ኮፓ ደልሬ ሪያል ማድሪድ ከአትሌቲኮ ማድሪድ ጨዋታቸውን ከማድረጋቸው በፊት የአትሌቲኮ ደጋፊዎች በልምምድ ቦታ ተገኝተው የቪኒሺየስ ጁኒየር ምስል ያለበትን ምስል በመያዝ አትሌቲኮ ሪያል ማድሪድን ይጠላል የሚል መልዕክት ማስተላለፋቸው ክስ እንዲመሰረትባቸው አድርጓል፡፡

ሶስቱ ደጋፊዎች የ14 ወር እስራት ሲፈረድባቸው አንደኛው ደግሞ የ22 ወር እስር እንደተፈረደበተ ስካይ ስፖርት ዘግቧል፡፡

በተጨማሪም ደጋፊዎቹ ከቪኒሺየስ ጁኒየር መኖሪያ አካባቢ እና የልምምድ ቦታ እስከ 1 ኪሎ ሜትር እንዳይቀርቡ ዕግድ ተጥሎባቸዋል፡፡ የላሊጋም ይሁን የስፔን ብሔራዊ ቡድንን ጨዋታ እንዳይመለከቱም ውሳኔ ተላልፏል፡፡

ብራዚላዊው ኮከብ በ2018 ማድሪድን ከተቀላቀለበት ዕለት ጀምሮ በተደጋጋሚ የዘረኝት ጥቃት ሲሰነዘርበትም ይስተዋላል፡፡

#ቪኒሺየስ #ማድሪድ

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለፕሬዝዳንት ትራምፕ የላከው መልዕክት ****************************ፖርቹጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እየተባባሰ የመጣውን የእስራኤል እና ኢራንን ጦርነት...
17/06/2025

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለፕሬዝዳንት ትራምፕ የላከው መልዕክት
****************************

ፖርቹጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እየተባባሰ የመጣውን የእስራኤል እና ኢራንን ጦርነት አስመልክቶ ለአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ መልዕክት አስተላልፏል፡፡

የ5 ጊዜ የባሎንዶር አሸናፊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ በሀገራቱ መካከል ያለው ውጥረት እንዲረግብ ሰላም ለዓለም የሚል መልዕክት ማስተላለፉ ይፋ ሆኗል፡፡

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ “ጨዋታ ለሰላም” የሚል ያልተጠበቀ ስጦታ ከክርስቲያኖ ሮናልዶ እንደተላከላቸውም አሳውቀዋል፡፡

ሮናልዶ የፈረመበትን የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን መለያ ከአውሮፓ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ እጅ የተረከቡት የሪፐብሊካኑ ተወካይ በአሁኑ ሰዓት ለቡድን ሰባት ስብሰባ ካናዳ ይገኛሉ፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

በማራቶን ውድድር መጨረሻ ወጥቶ እንደ ጀግና የሚታየው አትሌት ****************************ከአሸናፊነትም ከወርቅ ሜዳልያም በላይ የገዘፈ፣ ሀገር ማለት ምን እንደሆነ በተግባር ...
17/06/2025

በማራቶን ውድድር መጨረሻ ወጥቶ እንደ ጀግና የሚታየው አትሌት
****************************

ከአሸናፊነትም ከወርቅ ሜዳልያም በላይ የገዘፈ፣ ሀገር ማለት ምን እንደሆነ በተግባር የተገለጠበት፣ ምን አልባትም ሊደገም የማይችል፣ ከአዕምሮ በላይ የሆነ የአንድ አፍሪካዊ አትሌት ገድል ነው፡፡ “ሀገሬ የላከችኝ እንዳቋርጥ አይደለም” ብሎ አስደናቂ ምላ ሰጥቷል።

ለአንድ አትሌት ሀገርን በኦሎምፒክ መድረክ መወከል ከፍ ሲል ደግሞ አሸናፊ መሆን ትልቁ ግብ ነው፡፡ ይህንን ያደረጉ ዕልፍ ናቸው፡፡ ይሄኛው ታሪክ ግን ከዚህ ይለያል፡፡ ማሸነፍ ቀርቶ መጨረሻ ለመውጣት እንኳን በርካታ ሰዓት የወሰደበት፣ ነገር ግን ኦሎምፒክ ሲታወስ ሁሌም ስሙ ከአሸናፊዎች በላይ ገዝፎ የሚነሳ ሰው ታሪክ ነው፡፡

ጊዜው 1968 ሜክሲኮ ኦሎምፒክ ሲሆን ታሪኩ የሚጀምረውም እዚህ ጋር ነው፡፡ በመድረኩ በማራቶን 78 አትሌቶች ለአሸናፊነት ተዘጋጅተዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ደግሞ በግብርና ሙያ ከሚተዳደሩ ቤተሰቦቹ የተገኘው እና ታንዜንያን የወከለው አትሌት አንዱ ነው፡፡

ከ42 ኪሎ ሜትር ዘለግ የሚለው ውድድር ተጀመረ፡፡ ይህ ሰው እስከ 19 ኪሎ ሜትር ጠንካራ ተፎካካሪ ሆኖ ዘለቀ፡፡ 19ኛው ደቂቃ ላይ ግን ታጅበው ከሚሮጡት አትሌቶች ውስጥ የሚገኘው ይህ አትሌት ተደነቃቅፎ በመውደቁ እግሩ እና እጁ ክፉኛ ተጎዳ። ብዙዎቹ አትሌቶች በወደቁበት የህክምና ዕርዳታ ተደርጎላቸው ወድድሩን በዚያው ሲያቋርጡ ይህ አትሊት ግን አይደለም ለመሮጥ ለመንቀሳቀስ እንኳን ፈታኝ ከነበረው ህመሙ ጋር እየታገለ መሮጡን ቀጠለ፡፡

ከባህር ጠለል በላይ 2200 ከፍታ ባለው ቦታ እና እጅግ ፈታኝ በሆነው የአየር ጸባይ ምክንያት ብዙዎች በኦክስጅን ታግዘው ከውድድሩ ሲሰናበቱ እሱ ግን ደም እየፈሰሰው እግር እና እጁን በፋሻ ታስሮ በዝግታ መሮጡን ቀጥሏል፡፡ የህክምና ባለሙያዎች ጉዳቱ እንዳይባባስ እንዲያቋርጥ በተደጋጋሚ ቢነግሩትም እሱ ግን ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ሁነቱን ስቴዲየም ውስጥ ሆነው በቴሌቪዥን የሚከታተሉ ተመልካቾች ለአሸናፊነት ከሚደረገው ትንቅንቅ በላይ ይሔኛው ትኩረታቸውን ስቦታል፡፡

በዚህ መሀል አሸናፊው ታወቀ፡፡ ኢትዮጵያዊው አትሌት ማሞ ወልዴ አድካሚውን ውድድር በበላይነት አጠናቀቀ፡፡ በአትሌት አበበ ቢቂላ በ1960 ሮም ኦሎምፒክ የተጀመረው የባዶ እግር የማራቶን ድል ለ3ኛ ተከታታይ ጊዜ በአትሌት ማሞ ወልዴ ሀትሪክ የተሰራበት ሆነ፡፡ በመድረኩ የሁለት ጊዜ የኦሎምፒክ ባለ ድሉ አበበ ቢቂላ ቢያቋርጥም ማሞ ወልዴ ኢትዮጵያ ሌላ አዲስ ጀግና እንዳላት ለአለም ያሳየችበትም ሆነ፡፡

ከባድ ጉዳት ያጋጠመው ስቴፋን አክዋሪ ግን የቱንም ያክል ከአሸናፊዎቹ በብዙ ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ቢሆንም እጅ አልሰጠም። ከ1ኛ እስከ 3ኛ የወጡት አትሌቶች ሜዳልያቸውን ለመቀበል ወደ ፖዲየም አመሩ፡፡ ሽልማቱ እየተበረከተላቸው እያለ በስቴዲየም የሚገኝው ተመልካች ሩጫውን ያላጠናቀቀ አትሌት አለ ሽልማቱ መዘግየት አለበት በማለት ስሙን እየጠሩ መጮሀቸውን ቀጥለዋል፡፡

ከሽልማት ስነ ስርአቱ በኋላ መምሸቱን ተከትሎ ሁሉም ሰው ሲበተን አዘጋጆቹ እና የተወሰኑ ተመልካቾች ብቻ የስቴፋን አክዋሪ መጨረሻ ለማየት በስቴዲየም ተቀምጠዋል፡፡ በወደቀበት ሰአት ጉልበቱ ቦታውን የለቀቀው እና ስብራት ያጋጠመው አትሌት ህመሙን፣ ስቃዩን እና ሀገሩ ታንዜንያን ተሸክሞ እየወደቀም እየተነሳም አሸናፊው ማሞ ወልዴ ከገባበት አንድ ሰአት ዘግይቶ ስቴዲየም ደረሰ፡፡ በዚያ ያሉ ተመልካቾች በደስታ ጮቤ ረገጡ፡፡ ያላቸውንም ክብር ገለጹለት፡፡

23 ኪሎ ሜትሮችን ከከባድ ህመም ጋር የታገለው ሰው በጽናት 57ኛ በመሆን የመጨረሻውን ደረጃ ይዞ አጠናቀቀ፡፡ ስቴፋን አክዋሪ 21 አትሌቶች በጉዳትም በድካምም ውድድሩን ማጠናቀቅ ባልቻሉበት የሜክሲኮ ኦሎምፒክ 3 ሰአት ከ25 ደቂቃ ከ17 ሰከንድ ርቀቱን ለማጠናቀቀ የወሰደበት ሰአት ሆኖም በክብር ተመዝግቧል፡፡ በነገሩ ሁሉ የተገረሙ ጋዜጠኞች ጠየቁት “ሀገሬ የላከችን እንድጀምር ሳይሆን እንዳጠናቅቅ ነው” በማለት መለሰላቸው፡፡

ያጋጠመውን ሁሉ የተመለከተው አንድ የ9 አመት ልጅ ከወላጆቹ ጋር ሆኖ አድናቆቱን ገለጸለት፡፡ በአንድ ወቅት ወደ ታንዜንያ አምርቶም እንደሚጎበኝው ቃል ገባለት፡፡ ከአመታት በኋላም የያኔው ልጅ ቃሉን መፈጸሙን ስቴፋን አክዋሪ ተናግሯል፡፡

ሩጫ ካቆመ በኋላ ወደ ግብርናው የተመለሰው ጽኑ ሰው በ2000 ሲድኒ ኦሎምፒክ የማራቶን አሸናፊዎችን እንዲሸለም ተጋብዞ ወደ አውስትራሊያ ሲያመራ የወቅቱን ሻምፒዮን ገዛህኝ አበራን የወርቅ ሜዳልያ ያጠለቀለት እሱ ነው፡፡

የአለም አቀፉ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጥሩነሽ ዲባባ እና ቀነኒሳ በቀለ በ5 ሺህ እና 10 ሺህ አራት የወርቅ ሜዳልያ ባመጡበት የ2008 የቤጂንግ ኦሎምፒክ የክብር አምባሳደር አድርጎ እውቅና ሲሰጠው ሀገሩም የምንጊዜም ጀግና ብላ የክብር ኒሻን ሸልማዋለች፡፡

ጥንካሬን እና ተስፋን ከግብርናው የወሰደው፣ የኦሎምፒክን ትርጉም የገለጠው እና የአፍሪካውያን የጽናት ተምሳሌት መሆኑን በተግባር ያሳየው ጆን ስቴፋን አክዋሪ አሁን 83ኛ አመቱ ላይ ይገኛል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ጅማ የደረሰው የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ችቦ ደማቅ አቀባባል ተደረገለት***********************ለዘጠኝ ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ዘንድሮ...
16/06/2025

ከዘጠኝ ዓመት በኋላ ጅማ የደረሰው የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ችቦ ደማቅ አቀባባል ተደረገለት
***********************

ለዘጠኝ ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ዘንድሮ በጅማ ከተማ አስተናጋጅነት ይደረጋል።

ከሲዳማ ክልል ሀዋሳ ከተማ መነሻውን ያደረገው የመላ ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ችቦ በርካታ ከተሞችን አቋርጦ ዛሬ ጅማ ከተማ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።

በአቀባበል ስነ ስርዓቱ ላይ የባሕል እና የስፖርት ሚኒስትር የስፖርት ዘርፍ ሚኒስትር ደኤታ መኪዩ መሀመድን ጨምሮ በርካታ የጅማ ከተማ ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

ችቦው የተነሳበት የሲዳማ ክልል ለአዘጋጁ የጅማ ከተማ ችቦውን በደማቅ ስነ ስርዓት አስረክቧል።

በዓለም የክለቦች ዋንጫ ቼልሲ ከሎስ አንጀለስ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃልየአለም የክለቦች ዋንጫ ዛሬም ቀጥሎ ሲደረግ  ምድብ አራት ላይ የሚገኝው ቼልሲ ከአሜሪካው ሎስ አንጀለስ ጋር ይገናኛል...
16/06/2025

በዓለም የክለቦች ዋንጫ ቼልሲ ከሎስ አንጀለስ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

የአለም የክለቦች ዋንጫ ዛሬም ቀጥሎ ሲደረግ ምድብ አራት ላይ የሚገኝው ቼልሲ ከአሜሪካው ሎስ አንጀለስ ጋር ይገናኛል።

በዚህ የውድድር መድረክ ቼልሲ 3ኛ ተሳትፎውን ሲያደርግ ሎስ አንጀለስ የመጀመሪያው ተሳትፎው ነው።

በቼልሲ በኩል አዲስ ፈራሚዎቹ ሊያም ዴላፕ እና ማማዱ ሳር የመሰለፍ ዕድል ሊያገኙ ይችላሉ ተብሏል።

ጨዋታው ምሽት 4 ሰዓት ላይ በሜርሴዲስ-ቤንዝ ስታዲየም የሚደረግ ይሆናል።

በሌላ መርሀ ግብር የአርጀንቲናው ቦካጁንየርስ ከፖርቹጋሉ ቤኔፊካ ሌሊት 7 ሰዓት ይጫወታሉ።

የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በሀርድ ሮክ ስታዲየም ይካሄዳል።

በሴራን ታደሰ

Address

Addis Ababa
3344

Telephone

+251115172539

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EBC SPORT posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share