EBC SPORT

EBC SPORT EBC Sport is one of Ethiopian Broadcasting Corporation social media focusing on Sports.

አርሰናል ሂንካፒዮን ከባየር ሊቨርኩስን ለማዘዋወር ተስማማ***************አርሰናል ፒሮ ሂንካፒዮን ከባየር ሊቨርኩስን ለማዘዋውር ከስምምነት ላይ ደርሷል፡፡ኢኳዶራዊ ተከላካይ ወደ አርሰ...
29/08/2025

አርሰናል ሂንካፒዮን ከባየር ሊቨርኩስን ለማዘዋወር ተስማማ
***************

አርሰናል ፒሮ ሂንካፒዮን ከባየር ሊቨርኩስን ለማዘዋውር ከስምምነት ላይ ደርሷል፡፡

ኢኳዶራዊ ተከላካይ ወደ አርሰናል የሚያደርገው ዝውውር የአንድ ዓመት የውሰት ውል ሲሆን፤ አርሰናል በቀጣዩ አመት ዝውውሩን ቋሚ የማድረግ መብት አለው ተብሏል።

የሰሜን ለንደኑ ክለብ የ23 ዓመቱን ተጫዋቹ በቋሚነት የሚያዘዋውር ከሆነ የተረጋገጥ 45 ሚሊየን ፓውንደ እና ከወደፊት ሽያጭ 10 በመቶ ባካተተ ውል ለ5 ዓመት እንደሚያስፈርም ፋቢሪዚዮ ሮማኖ ዘግቧል፡፡

አርሰናል ፒሮ ሂንካፒዮን ከባየር ሊቨርኩስን ለማዘዋውር ቀደም ብሎ ከተጫዋቹ ጋር በግል ጉዳይ ስምምነት ላይ መድረሱም ተነግሯል፡፡

ቶተንሀም ዣቪ ሲሞንስን አስፈረመ*************ቶተንሀም ሆትስፐር ተጫዋች ዣቪ ሲሞንስን   ከአርቢ ላይፕዚግ ማስፈረሙን ይፋ አደረገ፡፡በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ወደ ቼልሲ ያ...
29/08/2025

ቶተንሀም ዣቪ ሲሞንስን አስፈረመ

*************
ቶተንሀም ሆትስፐር ተጫዋች ዣቪ ሲሞንስን ከአርቢ ላይፕዚግ ማስፈረሙን ይፋ አደረገ፡፡

በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ወደ ቼልሲ ያመራል ሲባል የነበረውን ሆላንዳዊው ተጫዋች በመጨረሻም ማረፊያው ሰሜን ለንደን ሆኗል፡፡

ቶተንሀም ሆትስፐር ለ22 አመቱ ተጫዋች ዝውውር 51 ሚሊዮን ፓውንድ ወጭ አድርጓል፡፡

ሆላንዳዊው ተጫዋች ከቶተንሀም ሆትስፐር ጋር ለአምስት የሚያቆየውን ውል የፈረመ ሲሆን ተጨማሪ ሁለት አመት ማራዘም የስምምነቱ አካል ሆኗል፡፡

ኤቤሬቺ ኤዜን በከተማ ተቀናቃኙ አርሰናል የተነጠቀው ቶተንሀም በባርሴሎና ቤት ያደገውን አማካይ አስፈርሟል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የእግር ኳስ ስፖርትን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከዘርፉ አመራሮች ጋር ተወያዩ*******************የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከ...
29/08/2025

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የእግር ኳስ ስፖርትን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ከዘርፉ አመራሮች ጋር ተወያዩ
*******************

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ከባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ እና ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች ጋር በአዲስ አበባ ከተማ የእግር ኳስ ስፖርትን ይበልጥ ማጠናከር በሚቻልባቸዉ አግባቦች ላይ ፍሬያማ ውይይት አካሄደዋል፡፡

በዉይይቱ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፤ ከለውጡ ወዲህ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአጠቃላይ የስፖርት ዘርፍን ለማጠናከር እያከናወናቸው የሚገኙ ስራዎች አበረታች መሆናቸዉን አንስተዋል፡፡

ለዚህም በ2017 በጀት አመት በአገር አቀፍ ደረጃ አንደኛ በመዉጣት እዉቅና ያሰጠዉ መሆኑን ጠቅሰዉ፤ በተለይም ታዳጊዎች ላይ ለተሰጠዉ ከፍተኛ ትኩረት ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አመራሮች በበኩላቸው፤ በመጪዉ 2018 ዓ.ም የስፖርት ዘርፋን ይበልጥ ለማጠናከር በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡

በተለይም ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ስፖርታዊ ጨዋነትን ተላብሰዉ የታለመላቸዉን አላማ እንዲያሳኩ እና በዉጤታማነት እንዲያድግ ስፖርተኞች፣ የእግር ኳስ ደጋፊዎች፣ የስፖርቱ ማህበረሰብና ወጣቶች በየአካባቢው ያለዉ አመራር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚናቸዉን እንዲወጡ በትጋት ለመስራት አቅደዉ ወደ ተግባር መግባታቸዉን አንስተዋል።

በውይይቱ፤ አስተዳደሩ ለስፖርቱ ዘርፍ እድገት በሰጠው ልዩ ትኩረት 1 ሺህ 530 ያህል ደረጃቸውን የጠበቁ የተለያዩ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ገንብቶ ለህብረተሰቡ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረጉ ተገልጿል።

እንዲሁም ታዳጊ ስፖርተኞች የሚፈሩባቸው ፕሮጀክቶች እንዲስፋፉ መደረጉንና በተለይም በሁሉም የስፖርት ዘርፍ ተተኪ ምርጥ ስፖርተኞችን ማፍራት ላይ እየተሰሩ የሚገኙ ተጨባጭ ስራዎች ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ ተመላክቷል።

ሁሉም ባለድርሻ አካላት ስፖርት ለሰላም፣ ለፍቅር፣ ለአንድነት፣ ለአገር ግንባታ የሚጫወተው ሚና ላቅ ያለ በመሆኑ ለስራው ልዩ ትኩረት በመሰጠት በትብብር መሰራቱ በስፖርቱ ዘርፍ ላይ በቀጣይም እንደ አገር እመርታዊ ለውጥ ለማምጣት ሚናዉ የጎላ በመሆኑ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ተብሏል::

ለዚህም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በመቀራረብ፣ በቅንጅት እና በትብብር የላቀ ስራ ለማከናወን የተጀመሩ ስራዎችን በማጠናከር ኃላፊነትን በአግባቡ መወጣት፣ ይበልጥ ተቀራርበዉ መስራት እንደሚኖርባቸዉ መገለጹን የከንቲባ ጽ/ቤት ለኢቢሲ የላከው መረጃ ያመላክታል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን  ነገ የአቋም  መለኪያ ጨዋታውን ያደርጋል**************በአለም ዋንጫ ማጣሪያ ምድብ አንድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከግብፅ እና ሴራሊዮን ለሚያ...
29/08/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ነገ የአቋም መለኪያ ጨዋታውን ያደርጋል

**************

በአለም ዋንጫ ማጣሪያ ምድብ አንድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ከግብፅ እና ሴራሊዮን ለሚያደርገው ጨዋታ ዝግጅቱን በአዲስ አበባ ስቴዲየም እያደረገ ይገኛል።

ዝግጅታቸውን ከጀመሩ ዘጠነኛ ቀናቸው ላይ የሚገኙት ዋልያዎቹ ነገ ረፋድ ከወላይታ ድቻ የአቋም መለኪያ ጨዋታቸውን እንደሚያደርጉ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን አሳውቋል።

ዛሬ በነበረው የልምምድ መርሐ ግብር ላይ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጅራ በአዲስ አበባ ስቴዲየም በመገኘት ቡድኑን አበረታተዋል።

ኤቤሬቺ ኤዜ ከሊቨርፑል ለሚደረገው ጨዋታ ?*************አርሰናል በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሀግብር እሁድ 12 ሰአት ከ30 ላይ ከሊቨርፑል ጨዋታውን ያደርጋል፡፡የመድፈ...
29/08/2025

ኤቤሬቺ ኤዜ ከሊቨርፑል ለሚደረገው ጨዋታ ?

*************
አርሰናል በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሀግብር እሁድ 12 ሰአት ከ30 ላይ ከሊቨርፑል ጨዋታውን ያደርጋል፡፡

የመድፈኞቹ አለቃ ሚካኤል አርቴታ ከሊቨርፑል የሚያደርጉትን ጨዋታ በተመለከተ በሰጠው ምግለጫ አዲሱ ፈራሚ ኤቤሬቺ ኤዜ ለቡድኑ ትልቅ ጉልበት መሆኑን ተናግሯል፡፡

ኤቤሬቺ ኤዜ በሚጫወትበት ቦታ ላይ በርካታ አማራጮች አሉን ያለው ሚካኤል አርቴታ የ27 አመቱ እንግሊዛዊ የእሁዱ ጨዋታ ላይ ያለውን ተሳትፎ በተመለከተ ጊዜው ሲደርስ የምናየው ይሆናል ብሏል፡፡

የቡካዮ ሳካ እና የማርቲን ኦዴጋርድ ጉዳት ምን አልባትም ኤቤሬቺ ኤዜ በአርሰናል መለያ የመጀመርያ ጨዋታውን እንዲያደርግ ዕድል ሊከፍትለት ይችላል ተብሏል፡፡

ቡካዮ ሳካ ለሳምንታት በጉዳት ከሜዳ እንደሚርቅ ያሳወቀው ሚካኤል አርቴታ እሁድ 12 ሰአት ከ30 ላይ በአንፊልድ ሮድ ለሚደረገው ጨዋታ ክርስቲያን ኖርጋርድ፣ ቤን ዋይት እና ሌአንድሮ ትሮሳርድ የመድረሳቸው ነገር አጠራጣሪ መሆኑን ተናግሯል፡፡

በሊድስ ዩናይትድ ጨዋታ ላይ የተጎዳው አምበሉ ማርቲን ኦዴጋርድ በማገገም ላይ እንዳለ አሰልጣኙ ይፋ አድርጓል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

ክሪስታል ፓላስ ዬርሚ ፒኖን ከቪያሪያል አስፈረመ*************ክሪስታል ፓላስ ዬርሚ ፒኖን ከቪያሪያል ማስፈረሙን አስታውቋል።ክሪስታል ፓላስ ስፔናዊውን የመስመር ተጫዋች በ26 ሚሊዮን ፓ...
29/08/2025

ክሪስታል ፓላስ ዬርሚ ፒኖን ከቪያሪያል አስፈረመ

*************
ክሪስታል ፓላስ ዬርሚ ፒኖን ከቪያሪያል ማስፈረሙን አስታውቋል።

ክሪስታል ፓላስ ስፔናዊውን የመስመር ተጫዋች በ26 ሚሊዮን ፓውንድ የግሉ አድርጓል፡፡

የ22 አመቱ ተጫዋች በደቡብ ለንደን ለአምስት አመት የሚቆየውን ውል የተፈራረመ ሲሆን 10 ቁጥር መለያ እንደሚለብስም ተረጋግጧል፡፡

ለቪያሪል 175 ጨዋታዎችን ያደረገው ፒኖ 45 ግቦችንም አስቆጥሯል፡፡

በሴራን ታደሰ

20 ዓመት በመቆየት እና በመልቀቅ መካከል፡- ሩብን አሞሪም*************ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ነገ በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከበርንሌይ ጨዋታቸውን ከማድረጋቸው በፊት ዛሬ...
29/08/2025

20 ዓመት በመቆየት እና በመልቀቅ መካከል፡- ሩብን አሞሪም

*************
ፖርቹጋላዊው አሰልጣኝ ነገ በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከበርንሌይ ጨዋታቸውን ከማድረጋቸው በፊት ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡

ካደረጓቸው ሁለት የሊግ ጨዋታዎች በአርሰናል ተሸንፈው ከፉልሀም ነጥብ የተጋሩት አሰልጣኙ አጀማመራቸው አልሰመረላቸውም፡፡

አሰልጣኙ ነገ በሜዳቸው ኦልድ ትራፎርድ የሚያደርጉትን ጨዋታ በተመለከተ በሰጡት መግለጫ ከገጠማቸው የውጤት ቀውስ አንጻር አንዳንድ ጊዜ ከስራቸው መልቀቅ እንደሚያስቡ ሌላ ጊዜ ደግሞ ለረጅም አመታት መቆየት እንደሚፈልጉ ተናግረዋል፡፡

ከአሁን በፊት ከዩናይትድ ለቀጣዮቹ 20 ዓመታት መቆየት እንደሚፈልጉ ተናግረው የነበሩት የ40 አመቱ አሰልጣኝ የቱንም ያክል አጀማመራቸው ባይሰምርላቸውም ነገሮችን ለማስተካካል እየሰሩ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ዩናይትድ በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሀግብር 11 ሰአት ላይ ከበርንሌይ ይጫወታል፡፡

በአንተነህ ሲሳይ

አርኖልድ ከ እንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ስብስብ ውጭ ሲሆን ራሽፎርድ ጥሪ ደርሶታል*************የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ እንግሊዝ ከአንዶራ እና...
29/08/2025

አርኖልድ ከ እንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን ስብስብ ውጭ ሲሆን ራሽፎርድ ጥሪ ደርሶታል

*************
የእንግሊዝ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ቶማስ ቱሄል በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ እንግሊዝ ከአንዶራ እና ሰርቢያ ጋር ላለባት ጨዋታ ለተጨዋቾች ጥሪ አድርገዋል።

በክረምቱ የዝውውር መስኮት ከሊቨርፑል ሪያል ማድሪድን የተላቀለው ተከለካዩ ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድ ለብሔራዊ ቡድኑ ሳይጠራ ቀርቷል።

የማንችስተር ዩናይትዱ ሀሪ ማጓየር እና የሲቲው ፊል ፎደን በጀርመናዊው በአሰልጣኝ ተመራጭ ያልሆኑ ተጫዋቾች ሆነዋል፡፡

ከማንችስተር ዩናይትድ ባርሴሎናን በዉሰት የተቀላቀለው ማርከስ ራሽፎርድ በቶማስ ቱሄል ጥሪ ተደርጎለታል።

ለአለም ዋንጫ ማጣሪየው አርሰናል አራት ተጫዋቾችን ሲያስመርጥ ከማንችስተር ዩናይትድ አንድም ተጫዋች አልተመረጠም፡፡

በሀብተሚካኤል ክፍሉ

ፖርቶ ኪቪዮርን ለማስፈረም ተስማማ**********የፖርቹጋሉ ፖርቶ ጃኮብ ኪቪዮርን ከአርሰናል ለማስፈረም ስምምነት ላይ ደርሷል።ክለቡ ለፖላንዳዊው ተከላካይ  ዝውውር 23 ሚሊዮን ፖውንድ ለመክ...
29/08/2025

ፖርቶ ኪቪዮርን ለማስፈረም ተስማማ

**********

የፖርቹጋሉ ፖርቶ ጃኮብ ኪቪዮርን ከአርሰናል ለማስፈረም ስምምነት ላይ ደርሷል።

ክለቡ ለፖላንዳዊው ተከላካይ ዝውውር 23 ሚሊዮን ፖውንድ ለመክፈል ተስማምቷል ተብሏል።

አርሰናል ፒሮ ሂንካፒን ከባየር ሊቨርኩሰን ለማስፈረም መቃረቡ የኪቪዮርን ወደ ፖርቶ መጓዝ አፋጥኖታል ተብሏል።

በአንተነህ ሲሳይ

ምሽት በዙሪክ በተደረገው የሴቶች 3ሺ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር አትሌት ፋንታዬ በላይነህ አሸናፊ በመሆን የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላታል፡፡
29/08/2025

ምሽት በዙሪክ በተደረገው የሴቶች 3ሺ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር አትሌት ፋንታዬ በላይነህ አሸናፊ በመሆን የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላታል፡፡

ምሽት በዙሪክ በተደረገው የሴቶች 3ሺ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር አትሌት ፋንታዬ በላይነህ አሸናፊ በመሆን የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላታል፡፡ ...

ኮቢ ማይኖ ማንችስተር ዩናይትድን ለመልቀቅ ጥያቄ አቀረበ*******እንግሊዛዊው የማንችስተር ዩናይትድ አማካይ ኮቢ ማይኖ ማንችስተር ዩናይትድን በውሰት ለመልቀቅ ጥያቄ ሲል ስካይ ስፖርት ዘግቧ...
29/08/2025

ኮቢ ማይኖ ማንችስተር ዩናይትድን ለመልቀቅ ጥያቄ አቀረበ
*******

እንግሊዛዊው የማንችስተር ዩናይትድ አማካይ ኮቢ ማይኖ ማንችስተር ዩናይትድን በውሰት ለመልቀቅ ጥያቄ ሲል ስካይ ስፖርት ዘግቧል።

ማይኖ በአሰልጣኝ ኤሪክ ቴን ሃግ የአሰልጣኝነት ጊዜ ወደ ዋናው ቡድን ያደገ ሲሆን፤ በማንችስተር ዩናይትድ የመሀል ክፍል ላይ አስደናቂ እንቅስቃሴዎችን በማሳየት ይታወቃል።

በአዲሱ የውድድር ዘመን በአሰልጣኝ ሩበን አሞሪም በቂ የመጫወቻ ጊዜ ያላገኘው ማይኖ በዚህ የውድድር ዘመን በውሰትም ቢሆን ማንችስተር ዩናይትድን ለመልቀቅ እንደሚፈልግ አሳውቋል።

በሃብተሚካኤል ክፍሉ

ዌስትሃም ማትየስ ፈርናንዴዝን ከሳውዝሀምፕተን አስፈረመ*************ዌስትሃም ዩናይትድ ፖርቱጋላዊውን አማካይ ማትየስ ፈርናንዴስን በ40 ሚሊየን ፓውንድ ከሳውዝሀምፕተን ማስፈረሙን ይፋ ...
29/08/2025

ዌስትሃም ማትየስ ፈርናንዴዝን ከሳውዝሀምፕተን አስፈረመ

*************
ዌስትሃም ዩናይትድ ፖርቱጋላዊውን አማካይ ማትየስ ፈርናንዴስን በ40 ሚሊየን ፓውንድ ከሳውዝሀምፕተን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡

በ2024/25 የውድድር ዘመን በግሉ ምርጥ ጊዜ ያሳላፈው የ21 አመቱ ወጣት ከለንደኑ ክለብ ጋር ለአምስት አመት የሚያቆየውን ውል ፈርሟል፡፡

የስፖርቲንግ ሲፒ አካዳሚ ውጤት የሆነው ፈርናንዴዝ ለፖርቹጋል ከ21 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድንም ተጫዋች ነው።

ተጫዋቹ ከሉካስ ፓኩዌታ እና ሰባስቲያን ሀል በመቀጠል የክለቡ 3ኛው ውዱ ፈራሚም ሆኗል፡፡

በሴራን ታደሰ

Address

Addis Ababa
3344

Telephone

+251115172539

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EBC SPORT posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share