Ewnet Hailu/ እውነት ሀይሉ

Ewnet Hailu/ እውነት ሀይሉ I LOVE MY COUNTRY
Patriotism is a thing of the heart. A man is a patriot if his heart beats true to his country. Charles Edward Jefferson

08/02/2023

ትዕቢት ውደቀትን ትቀድማለች

ሁሉን የሚችል የሚመስለው ሰው አለ። በዙሪያው ባሉት ሰዎች ስለተሞገሰ በሁሉም የሚሞገስ የሚመስለው አለ። አጠገቡ ያሉት ስለተርበደበዱ ዓለም ሁሉ የሚርበደበድለት የሚመስለው ሰው አለ። በሀገራችን እየሆነ ያለው ይህ ነው። የማይነካውን ያስነካቸው ትዕቢት ነው። የማይገባበት ውስጥ ያስገባቸው እብሪት ነው። ልጅነታቸውን ትዕቢታቸው ስለሸፈነው ከአባቶች በላይ እንደሆኑ ተሰማቸው። የነሱ መንገድ ብቻ ስለታያቸው የቀድሞይቱን መንገድ መጠየቅ አቆሙ። የቆሙ ስለመሰላቸው ውድቀታቸው አልታይ አላቸው።

ሁሉን የሚችሉ ስለመሰላቸው ሁሉን ቻይ የሆነው ፈጣሪ ተዳፈሩ። በህዝብ እንባ ተሳለቁ ጎርፍ ሆኖ እንደሚወስዳቸው አልታይ አላቸው። በፈጣሪ የታመነውን ህዝብ በሰራዊታቸው ብዛት ታምነው ተዳፈሩት። አንገታቸውን ስላደነደኑ የአባቶችን አንገት አስደፍተው አስለቀሱ።

ትዕቢት በመንገዳቸው ቀደመች። ሞገስ የሆናቸው ፈጣሪ በነውር ስራቸው ተዳፈሩት። ቀናውን መንገድ ትተው ወደ የጥፋት መንገድን መረጡ። የማይነካውን ነኩ ፤ የማይደፈረውን ደፈሩ፤ በማይመጣበት መንገድ መጡ ፤ በነውራቸው አጌጡ።ከፍታችው ለንቀት መመረጣቸውን ለርኩሰት ተጠቀሙበት።

በቀረችው ጥቂት ጊዜ ወደ ልባቸው ካልተመለሱ የእግዚአብሔር ቁጣ በላያቸው ይነዳል። ያደነደኑት አንገታቸው በድንገት ይሰበራል አወዳደቃቸውም ታላቅ ይሆናል። ከእግዚአብሔር ጋር የሚጣሉ ይደቃሉ ። ለሀጥአን የመጣ ለጻድቃን ይተርፍል እንደሚባለው የመረጡት የጥፋት መንገድ ሀገራችንንና ህዝባችንን ይዞ ከመጥፋቱ በፊት ወደልባቸው ይመለሱ ዝንድ ጸሎት እና ምኞቴ ነው።

እውነት ሀይሉ

10/03/2022

አየሁሽ አላየሁሽ

ሰሞኑን የመንግስት ሚዲያዎች በህገወጥ መንገድ የተከማቸ ዘይት መያዙን ሲዘግቡ ነው የከረሙት። እኔማ ከዜናው ብዛት የተነሳ በነጻ የምንታደል ሁሉ እየመሰለኝ በጉጉት እየጠበኩ ነው። እኔም በዜናው ጦዤ እንደጓጓሁ የዘይት ዋጋም እየናረ ተፋጠናል።

መንግስትንና ጋዜጠኞቹን ጥያቄ መጠየቅ ቢፈቀድልኝና መልስ ቢሰጡበት ቁርጤን አውቄ ቁጭ እል ነበር።

የተያዘው ዘይት የት ገባ ? የምትሉት ዘይት ተይዞ ከሆነ ለምን ገበያውን ማረጋጋት አልተቻለም ? መቼም ከኑሮዬ በላይ የናንተን ዜና እናዳጠገበኝ ታውቃላችሁ።

ከዘይት ጋር አየሁሽ አላየሁሽ ጨዋታ ጀምረናል። መንግስት ሆይ ይህን ድብብቆሽ አቁመህ ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ብትፈልግ ይሻላል። በፕሮፖጋንዳ የሚሰራ ወጥ የሚበስል ዳቦ የለም።

አንድ ሻንጣ  እና ጥንቃቄ አንድ ሻንጣ ለወገኔ በሚል እየተካሄደ ባለው ቅስቀሳ ከቅንነት ባሻገር  ጥያቄ የሚያስነሱ እና ጥሪውን ተቀብሎ ወደ ሀገር ቤት በሚገባው ዲያስፖራው ላይ እንግልት የሚ...
20/12/2021

አንድ ሻንጣ እና ጥንቃቄ

አንድ ሻንጣ ለወገኔ በሚል እየተካሄደ ባለው ቅስቀሳ ከቅንነት ባሻገር ጥያቄ የሚያስነሱ እና ጥሪውን ተቀብሎ ወደ ሀገር ቤት በሚገባው ዲያስፖራው ላይ እንግልት የሚፈጥሩ እንዳይሆኑ
ጥንቃቄ መደረግ ይኖርበታል። መንግስት በግልጽ ፈቃድ ያልሰጠባቸውን ቁሳቁሶች በቅንነት በቻ ይዞ በመግባት አላስፈላጊ ንትርክ መፍጠር አግባብ አይመስለኝም።

የጤና ሚኒስተር ወደ ሀገር ቤት እንዲገቡ የፈቀዳቸውን የህክምና መሳሪያ ዝርዝር እንዲሁም ወደሀገር ቤት ይዞ ከመግባት በፊት ለጤና ሚኒስቴር የሚያስታውቁበትን እና ጤና ሚኒስቴር ፈቃድ የሚሰጥበትን ፎርም ይህን ሊንክ ተጭነው ያገኙታል። https://onedrive.live.com/?authkey=%21AJdd8%2D1FArUIBAY&id=D024F37C0D7B30B2%211837&cid=D024F37C0D7B30B2

በግሌ ዲያስፖራው ገንዘቡን ይዞ ቢገባ ይበልጥ ይጠቅማል ባይ ነኝ። ዲያስፖራው ገንዘቡን ይዞ ቢገባ በሀገሪቱ ውስጥ ሊፈጥር የሚችለውን የኢኮኖሚ መነቃቃ ትልቅ ነው።

ጉዞዎ የተሳክ እንዲሆን ግለሰቦች በቅንነት የሚያቀርቡትን ጥሪ ሳይሆን መንግስት ያስቀመጠውን መመሪያ በመከተል ድጋፍ ያድርጉ ሀገርዎትን ያግዙ። አላስፈላጊ ውጣ ውረድን ያስወግዱ።

በጉዞዎ የሀገርዎት ኢኮኖሚ አንቀሳቅሰው ለወገንዎ ድጋፍ ያድርጉ።

እውነት ሀይሉ

እባክዎ ይህን መልዕክት ያጋሩ (Share! Share! Share ! )

13/12/2021

የእሸቴ ሞገሶች መታሰቢያ .......

መቼም የዚህን ጀግና ታሪክ ሰምቶ ያልተደነቀ ያልተገረመ የለም። እንኳንም የዚህ ጀግና ታሪክ በዓለም ተሰማ። እንኳንም ይህ ጀግንነት ተደብቆ አልቀረ። ታዲያ ይህ ጀግና የልጆቼን ነገር አደራ ባለው መሰረት ህብረተሰባችን የሚያደርገው ርብርብ ደስ የሚያሰኝ ነው። የኔ ጥያቄ እንደዚህ ጀግና ለሀገራቸው ታላቅ ተጋድሎ የፈጸሙ ነገር ግን ታሪካቸው ያልተነገረላቸው እሸቴ ሞገሶችን ጉዳይ ነው ።

እነዚህ ጀግኖቸ ትዳሬን ልጆቼን ስራዬን ሀብቴን ሳይሉ በዱር በገደሉ ተዋድቀው ለሀገራቸው ሰማዕት ሆነው አልፈዋል ። ለፈረሰ ጎጆአቸው ፣ለተበተኑት ልጆቻቸው ፣ ለባከነው ሀብታቸው ፣ ለፈሰሰው ደማቸው እውቅና የሚሰጥ ፣ጎጆአቸውን የሚገነባ ፣ ልጆቻቸውን የሚንከባከብ አደራ የማይበላ ወገን ሊኖር ይገባል ባይ ነኝ።

የእነዚህ ጀግኖች ታሪክ በማህበራዊ ሚዲያው ፤ በመገናኛ ብዝሃኑ መጥቶ እስኪነገር መጠበቅ የለብንም። በተናጠል እርዳታ አድርገንም አንዘልቀውም። የእነዚህ ጀግኖችን ታሪክ የሚዘክር ፤ አስፈላጊውን ድጋፍ የሚያደርግ ተቋም ሊቋቋም ይገባል ባይ ነኝ። ይህ ተቋም በየአካባቢው ጥናት በማድረግ የጀግኖቹን ታሪክ በመመዝገብ፤ በዋናነት ለቤተሰባቸው አስፈላጊውን ድጋፍ በማድረግ ጀግኖቹ ለሞቱለት ለቆሰሉለት ዓላማ አጋርነት ማሳየት ይገባል።

ይህን ማድረግ ካልቻልን ግን እድል የቀናው ታሪኩ ይሰማል በለስ ያልቀናው ከወደቀበት ጥሻ ውስጥ ታሪኩም ተቀብሮ ይቀራል። የግማሹ ጀግና ቤተሰብ ይጽናናል የግማሹ ጀግና ቤተሰብ በሀዘን ኑሮውን ይገፋል።

እንደ ማህበረሰብ በሰማነው ታሪክ ልባችን ሲነካ ብቻ ድጋፍ የምናደርግ ከሆነ ያልተሰማ ታሪክ ያላቸው ፤ እድል ያልገጠማቸው ጀግኖቻችንን ማን ሊያስታውሳቸው ይችላል? ስለዚህ እሸቴ ሞገሶችን ተቋማዊ በሆነ አደረጃጀት ልናግዝ ይገባል። ስያሜውን ካስፈለገ "እሸቴ ሞገሶች ማዕከል " ብለን ልንጠራው እንችላለን።

ይህ ጹሁፍ መነሻ ሀሳብ ሆኖ ሁላችሁም የበኩላችሁን አስተዋጾ አበርክታችሁ መንግስትም ትኩርት ሰጥቶት ወደ ተግባራዊነቱ የምንሻገርበት ቀን እንደሚመጣ ተስፋ አደርጋለሁ።

ክብር ለእሸቴ ሞገሶች

እውነት ሀይሉ

/ ይህን ገጽ ላይክ አድርገው ቤተሰብ እንሁን /

02/12/2021

የማይታዩ ወርቃማ እጆች

ሀገር በነጻነት ተከብራ እንድትኖር ዋጋ የከፈሉ ውድ ህይወታቸውን መሰዕዋት አድርገው ያቀረቡ ብዙ ጀግኖች አሉ። ብዙ ሰው የማይወስነውን በቆራጥነት የወሰኑ፣ ስንቱ የሚሳሳለትን ጉዳይ ንቀው ከዓላማቸው ሳያስበልጡ ሀገራቸውን ያስቀደሙ ስንት ጀግኖች አሉ። ፎቶአቸውን አላየነውም፣ የዕለት ውሎአቸው አልተወራላቸውም ፣ ስለጀግነንታቸው አልተዘመረላቸውም ፣ በመልክ እና በስም አይታወቁም ፣ ከወዳጅ ዘመዶቻቸው ውጪ የሚያውቃቸው የለም፣ ታሪካቸው አልተተረከም ፣ ገድላቸው አልተነገረም ። ግን ደግሞ ክብር ህይወታቸውን ሳይሳሱ መስዋዕት አድርገው ሀገር ያቀኑ ብዙ ጀግኖች አሉ።

የእነሱን ታሪክ ሀገር ናት ። አፈር ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው ፣ ጋራ ሸንተረሩን ወጥተው ወርደው፣ ብርድ እና ሙቀቱን ፣ የለሊቱን አስፈሪ ግርማ ታግሰው ከአራዊቱ ጋር ታግለው፣ አፈር መስለው ፣ ስለሀገር ክብር ተዋድቀው ጠላትን ደምስሰው እናት ሀገራቸውን አከብረው ተሰውተው ሀገር ቀና እንድትል የነጻነት ባንዲራዋን በኩራት እንድታውለበልብ የተዋደቁ ጀግኖች አሉ፤ ኢትዮጵያውያን ሆነው ኖረው ኢትዮጵያ ሆነው የቀሩ።

እነዚህ ጀግኖች በስም በመልክ ያልተለዩ ፤ ደጋፊ አጃቢ አጨብጫቢ የሌላቸው ፤ ዝና ክብር ሀብት ስልጣን የማያጓጓቸው ፤ የከፈሉት መስዋዕትነት በቅጡ እንኳ ያልተነገረላቸው ፤ በወርቅ ቀለም ታርክ ሲጽፉ እንጂ የጻፉበት እጃቸው የማይታይ ፤ አደባባይ እዩኝ የማያበዙ ፤ ሹመት ሽልማትን ሳይሆን ሀገር ብለው የሚኖሩ ሀገር ብለው የሚሞቱ ግን ደግሞ ያልተዘመረላቸው ጀግና የሆኑ እልፍ አእላፋት አሉ። ሀገር የምትቆመው በእነሱ ነው። ፍርድ እንዳይጓደል፤ ደሀ እንዳይበደል ቀን ከለሊት የሚሰሩ ብዙ ጀግኖች አሉ። ሀገር ሀገር የሆነችው በእነርሱ ነው።

ሌላው የሰላም አየር እንዲተነፍስ የባሩዱን ሽታ ታግሰው፤ ሌላው የሞቀ ቤቱ ውስጥ በሰላም እንዲተኛ ጉድጋድ ቆፍረው ምሽግ ሰርተው ሀገር የሚጠብቁ ወገን በሰላም ወጥቶ እንዲገባ ዘለው እሳት ውስጥ የሚገቡ፤ ትዳሬ ልጄ እናት አባቴ ሳይሉ የወገናቸውን ደህንነት ያስቀደሙ እልፍ አእላፋት ጀግኖች አሉ። መጠሪያ ስማቸው ባይታወቅ፣ መልክ እና ቁመናቸው ባይታይ፣ ፎቶ ቪዲዮ ኖሮአቸው በአደባባባይ ባይዘመርላቸው ግን ስም አላቸው የከበረ፤ ጀግና ነው መጠሪያቸው ጽናታቸው ነው መለያቸው፤ ለሀገራቸው ያላቸው ፍቅራቸው ነው ደሞዛቸው ፣ የሀገር ሰላም ነው ደስታቸው እናም ስም አላቸው ፣ ጀግኖች ናችው።

ክብር ለእናነት ይሁን፣ በስም ጠቅሰን ሳንጠራችሁ ፣ መልካችሁን ለማየት እድል ሳናገኝ ፣ ድምጻችሁን ሳንሰማችሁ ኢትዮጵያ ታፍራ እና ተከብራ እንድትኖር ኢትዮጵያ ለሆናችሁ፣ ለእኛ መኖር ሞትን የተጋፈጣችሁ ክብር ይድረሳችሁ። ጀግና ብለን ስንጣራ ጀግና ብለን ስንዘመር ሁሌም እናንተ በዚያ አላችሁ። ይሄ ነው መጠሪያችሁ። ጀግንነት ነው ክብራችሁ። ሀገራችሁ ከፍ ብላ እንድትከበር ያደረጋችሁትን ውለታ ሀገራችሁ ከፍ አድርጋ ታክብራችሁ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር።

እውነት ሀይሉ

/ ይህን ገጽ ላይክ አድርገው ቤተሰብ እንሁን /

25/11/2021

ባሻዬ

የውጭ ሀገራት ኢምባሲዎች እየተነሱ ሀገሪቱን ለቃችሁ በአስቸካይ ውጡ ይላሉ። አረ ቀስ ... መቼም እንደ ካቡል ኤርፖርት ሰው ከአውሮፕላን ላይ ተንጠልጥሎ ወድቆ ሲሞት ይሄን ያህል የመግለጫ ጋጋት አላበዛችሁም ሀገሪቱ ኢትዮጵያ ናት ቀስ ብላችሁ ውጡ አትጋፉ ቢባሉም ሊሰሙ አልቻሉም።

በየቀኑ ከሀገራችን ሀገራቸው የተሻለች እንደሆነ ውዥንብር በመፍጠር እየነገሩን ነው። ዜጎቻቸው ተከብረው የሚኖሩበት ሀገር እንዳላቸው በግልጽ አማርኛ እየነገሩን ነው። አዬ ጉድ ሱዳንም አልቀረች እኮ። ይህቺ ጎረቤታችን ሱዳን ምንው እንካ መፈንቅለ መንግስት ተካሄዶ ያልተረጋጋችው ሀገር እህ ሱዳን ዜጎቼ ከኢትዮጵያ ቶሎ ውጡ እያለች ነው። በንጽጽር ከተመለከትነው ከካርቱም አዲስ አበባ መቶ ፐርሰንት የተረጋጋች ከተማ ነች ። መቼስ ማልጎደኒ ውጡ ካለች ይውጡ በዜጋዋ እኛ ምን አገባን።

ያልተግባባንበት ጉዳይ ግን አለ

እነርሱ ከኢትዮጵያ ውጡ እና ወደ ሀገራችሁ ኑ እያሉ ዜጋቸውን ሲጣሩ እኛ መሸሻ መጠጊያችን አንባ ከለላችን የሆነችው ሀገራችን እንደምታስፈልገን ሊገባቸው አልቻለም። እየነገሩን ያለው እኮ ምንም ሆንክ ምን ሀገር እንደሚያስፈልግህ ነው ። ሀገርህን እያፈረሱ ፍርስራሹ እንዳይጎዳቸው ዜጎቻቸውን ሲጣሩ ሀገሬን አታፈርሱም ማለት በምን አግባብ ስህተት ይሆናል።

ኢትዮጵያውያን ጥያቂያቸው አንድ እና አንድ ነው ። ከውጭ እና ከውስጥ ባንዳዎች ጋር ተመሳጥራችሁ ሀገሬን ስታፈርሱ ቁጭ ብዬ አልመለከትም የሚል እምቢ ባይነት ነው ። እምቢ ለሀገሬ ማለት ደግሞ የኢትዮጵያውያን መገለጫ ነው ።

እናንተ ዜጎቻችሁን ከሀገር ስታስወጡ እኛ ደግሞ የሀገራችንን መጥፋት የሚፈልገውን ሀይል በትግላችን እናስወጠዋለን።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር።

08/11/2021

ሰላም ተገኝቶ ነው ! ሆ ....
አሁን አሁን አንድ አንድ ሰላም ይሻላል ባዮችን ስመለከት የሰላም ትርጉም ይጠፋብኛል።
የሚደግፉት ወገን የሀይል ሚዛኑ ከፍ ሲል ድምጻቸውን ያጠፋሉ ወይም ከሀገራዊ ሁኔታውወጣ ብለው ስለ ቴክኖሎጂ፤ ሙዚቃ እና ፊልም ይቀደዳሉ። የሚደግፉት አካል መደቆስ ሲጀመር የሰላም ሰባኪ ሆነው ከች ይላሉ። የሚደግፉት አካል የማረካቸውን ወታደሮች ቪዲዮ እየለቀቁ ወንድም ከወንድሙ መጣላት ምን ይጠቅማል የድሀው ልጅ አለቀ እያሉ ያለቃቅሳሉ። በእነሱ ቤት የሚማረከውም የሚሞተውም ከአንድ ወገን እንደሆነ አድርገው ማሳየታቸው ነው። አስተውላችሁ ከሆነ ከሚደግፉት ወገን የተማረከ ወይም የቆሰለ ተዋጊ አያሳዩም ። የሰላምን ጥሪ ከእንደዚህ አይነት አስመሳዮች ከመስማት በላይ የሚያቅለሸልሽ ነገር የለም።
ደግሞ ለራሳቸው የሚሰጡት ግምት ገራሚ ነው ።ራሳቸውን ሲገልጹ ለህሊናቸው የሚኖሩ፤ የሰላም ሰባኪ ፤ ከፍ ያለ ስብዕና ያላቸው አድረገው ነው። ስራቸውን ስለሚያውቁ በየሳምቱ እየመጡ ስለራሳቸው ማብራሪያ ይሰጣሉ። እኔ ለህሊዬ የምኖር ሰላማዊ የሆንኩ ከሰው ከጥላቻ የራቅሁ ምናምን ምናምን እያሉ ዝባዝንኬ ይጽፉና ለራሳቸው ውዳሴ ያቀርባሉ። ማን ጠየቃቸው በቃ ሰውን ስራው ይገልጸዋል እኮ።
አሁን አሁንማ እርግማን ሁሉ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚፈጸም አድርገው ሲያወሩ አለማፈራቸው ይገርመኛል። ሌብነቱ ፤ የኑሮ ውድነቱ፤ ደስታ እና ሰላም ማጣቱ ኢትዮጵያ ላይ ብቻ እየሆነ ያስመስሉታል ። የሀገሪቱን ችግር አጋነው እያወሩ ሲኦል ማድረግ ይቀላቸዋል። ከዚያም መለስ ብለው እየሆነ ያለው ሁሉ ህዝቡ ሰላምን ስለጠላ የእነሱን የሰላም ጥሪ ስላልተቀበለ ነው ይሉናል። የሀይል ሚዛኑ ወደሚገፉት ወገን ያደላ ሲመስላቸው ድምጻቸውን ያጠፋሉ። መርጠው ያወግዛሉ። መርጠው ያለቅሳሉ።
የኢትዮጵያ ህዝብ ሰላምን ይፈልጋል ። ስለሰላም ሲል ብዙ ዋጋ የከፈለ ህዝብ ነው። ላለፉት 30 ዓመት የደረሰበትን ግፍ የተሸከመው ሰላማዊ ለውጥ ፈልጎ ነው ።
**በ1997ዓም ምርጫ ተሰፋ አድርጎ የውድ ልጆቹን ህይወት ገብሮ ጫካ ያልገባው ለምን ይመስልሃል?
*የተለያዩ የትጥቅ ጥሪዎችን አብዛኛው ሳይቀላቀል ብዙ ግፎችን የተሸከመው ለምን ይመስልሃል?
** በዘርና ፖለቲካ የተደራጀው ሀይል ሀገሪቱን እየዘረፈ በሀብት ሲናኝ በድህነት ኑሮውን እየታገለ የቆየው ለምን ይመስልሃል ?
*በየእስርቤቶች ስንት እህቶቹ እና ወንድሞቹ እየተደፈሩ ከሰላማዊ ተቃውሞ ውጪ ሌላ አማራጭ ያላድረገው ለምን ይመስልሃል ?
*ለሀገሩ ስንት ሊሰራ የሚችል ወጣት እየተሰደደ፣ እየተገደለ፣ እያበደ ጨርቁን ሲጥል የስንቱ ወጣት ራዕይ ሲመከን ዝም የተባለው ለምን ይመስልሃል ?
*ስንቱ ወገን በብሄሩ፣ በሃይማኖቱ፣ በአስተሳሰቡ እየተገረፈ፣ እየተሸማቀቀ አካለ ስንኩል እየሆነ አንገቱን አቀርቅሮ የኖረው ለምን ይምስልሃል?
*ባለፉት ሶስት አመታት ከኛ በላይ ጀግና የለም ተብሎ ከበሮ ሲደለቅ ፤ ራሱን እንደጀግና ሌላውን እንደፈሪ የሚቆጥረውና ህዝብ የሚንቀው ስብስብ እንደልቡ ሲጨፍር ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ዝም ያለው ለምን ይመስልሃል ?
ፈሪ ስለሆነ ? የሚደርስበት ግፍ ስለማይሰማው ? ባርያ ስለሆነ ? ወይስ የፈለጉት ቢያደርጉት ንቃተ ህሊናው ዝቅተኛ የሆነ ህዝብ ስለሆነ ? ወይስ ኑሮ ድልት ሙልት ስላለለት ?

እብሪተኞችና አስመሳይ የሰላም ሰባኪዎች የህዝቡን ዝምታ ከላይ ከተጠቀሱት በአንዱ ሊጠሩት ይችላሉ ። እውነታው ግን የግፉ ጽዋ ሞሎቶ እስኪፈስ እየጠበቀ ነበር። ዕብሪተኞች ጥጋባቸው ከልክ አልፎ የግፉ ጽዋ ሞልቶ ፈሰሰ። የማይነካውን ነኩ። የማይደፈረውን ደፈሩ። ሀገሪቱን አፍርሰን የሞትን ጽዋ ካልጋትንህ አሉት። ኢትዮጵያዊነትን እየተጸየፉ በኢትዮጵያዊነት የከበሩ ከሀዲዎች በማይመጣው መጡ። ይህ ህዝብ የታገሰው ሀገር ስለነበረው ነው። ሀገርህን ካላፈረስን ሲሉ ግን ቀፎው እንደተነካ ንብ ሆ ብሎ ወጣ።

አስመሳይ የሰላም ሰባኪዎቹ ታዲያ ይህን ህዝብ ጭራቅ አድርገው እየሳሉ ስለሰላም ሊሰብኩት ይፈልጋሉ። በጥባጭ ካለ ማን ጥሩ ይጠጣል እንዲሉ ሰላምን አንተ ብቻ ሰለፈለካት አታገኛትም ። በአንድ እጅ አታጨበጭብም ። የእውነት ሰላም ፈላጊ ከሆኑን በጥባጩን ቆፍጠን ብለው ይናገሩት። ይህ ህዝብ ተበጥብጦም ተወቅሶም አያዋጣውም።

አስመሳይ ሰላም ሰባኪዎች ሰላምን ከፈለጉ ለምን ሰላምን እንቢ ብሎ ሀገር እያመሰ ያለውን እብሪተኛ ቡድን እረፍ የወጣቱን ህይወት በከንቱ አታርግፍ ፤ደም በከንቱ አይፈሰስ አይሉትም ። በየማህበራዊ ሚዲያው ብቅ እያላቻሁ ይህን ስንት በደልና ግፍ ተሸክሞ የኖረውን ህዝብ አትውቀሱት። በድጋሚ ለማስታወስ በጥባጭ ካለ ማንም ጥሩ አይጠጣም። በአንድ እጅ አይጨበጨብም።

እውነት ሀይሉ
/ ገጻችን ላይክ አድርገው ቤተሰብ ይሁኑን /

03/09/2021

ይገርመኛል

ሕወሀት በአማራና በአፋር ክልል ገብቶ ግፍ መፈጸም ከጀመረ ሁለት ወር ሆነው። የብዙ ሰው ህይወት አልፎአል ። ሀብት ንብረት ወድሞአል። ሴቶች ተደፍረዋል ። ህጻናት ያለአሳዳጊ ቀርተዋል ። ሰባት መቶ ሺህ የሚጠጋ ሰው ከመኖሪያው ተፈናቅሎ ለስደት ተዳርጎአል ። ከብቶች በግፍ ተገድለዋል ። ገበሬዎች እድሜ ልካቸውን ጥረው ግረው ያፈሩት ሀብት ተዘርፎአል ። የእርሻ ማሳቸው በከባድ መሳሪያ ከጥቅም ውጭ ተደርገዋል።

ህወሀት ይህን ሁሉ ግፍ እየፈጸመበት አንድም የአፋርም ሆነ የአማራ ሊሂቃን፣ ገበሬ ፣ ፋኖ ፤ ልዩ ሀይል፤ ዲያስፖራው የኢትዮጵያን ስም በክፉ ሲያነሳ አልተመለከትኩም። ኢትዮጵያዊነት ሲደላህ የምትደርበው ሲከፋይ የምታወልቀው ማንነት አለመሆኑን በተግባር አስመስክረዋል።

ወያኔ እና ጭፍሮቹ ላለፉት ሀያሰባት አመታት ኢትዮጵያን ሲያስተዳድሩ ሲመዘብሩ ፈላጭ ቆራጭ የነበሩት በኢትዮጵያዊነት ስም ነበር። የስልጣን መንበራቸው መነቃነቅ ሲጀምር ኢትዮጵያዊነታቸውን ጥያቄ ውስጥ ከተቱት። ወያኔዎች እና ጭፍራዎቻቸው ሀገራቸው እና ሀይማኖታቸው ምቾታቸው ብቻ ነው። ይህቺ ምቾት ስትነካ ሀገርም ሆነ ሀይማኖት ዋጋ የላቸውም።

ብዙ ሰው ወያኔ ኢትዮጵያዊነትን ጥያቄ ምልክት ውስጥ ያስገባው ጦርነቱ ከተጀመረ በኃላ የሚመስለው አለ። የዋህነት ነው ። ከምስረታቸው ጀምሮ አራት ኪሎ እስኪገቡ ከዛም ስልጣን ከተቆናጠጡ በኃላ ለእነሱ የምትመች ኢትዮጵያ ገንብተው ካልተመቻቸው ደግሞ ሊያፈርሷት በዓላማ ነበር ሀገሪቱን ሲገዙ የኖሩት ። መቀሌ ከመሸጉ በኃላ ግን ይህን እኩይ እቅዳቸውን ለመተግበር የፌደራል መንግስቱን ሲገዳደሩ ቆዮ። የተለያዩ የጦር ትርዕይንቶችን እያሳዩ ጡንቻቸውን ለማሳየት ሞከሩ። በመቀሌ ስታዲዮም ውስጥ ህዝብ ሰብስበው በፌደራል መንግስቱ ተሳለቁ። ሀገረ መንግስት የመሰረቱ ይመስል ከፌደራል መንግስቱ ጋር ትከሻ ተለካኩ በስተመጨረሻም እብሪት ልባቸውን ድፍን አድርጎት የሰሜን ጦር ላይ ጥቃት ፈጸሙ። ይሄን ሁሉ ሲፈጽሙ ግን ኢትዮጵያዊነት ላይ እየተሳለቁ ነበር ።

ሂሳብ እናወራርዳለን ባሉት መሰረት በአፋር እና በአማራ ክልል ላይ ያልተፈጸመ የግፍ አይነት የለም። ግን አንድም የዲያስፖራ ኮሚኒቲ ሰላማዊ ስለፍ ወጥቶ ወያኔ በፈጸመው ግፍ ኢትዮጵያን ሲያንቋሽሽ እና የሀገሪቱን ገጽታ ጥላሸት ሲቀባ አልተመለከትኩም። በየትዊተር ዘመቻውም ወያኔ የሚፈጽመውን ግፍ ለዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ ከማሳወቅ የዘለለ የሀገርን ክብር በሚነካ መልኩ አንድም ዘመቻ አልተካሄደም። ኢትዮጵያዊነት ከችግራችን በላይ ከፍ ያለ ማንነት ነው። ለዚህ ታላቅ ማንነት ደግሞ እስከ ህይወት መስዋዕትነት የሚከፍሉ እልፍ አእላፍ ጀግኖች መኖራቸውን ሳስብ ይገርመኛል ።

የፖለቲካ ልዩነቱ ቢኖርም ፣ መንግስታት ቢለዋወጡ ፣ ሀያላን ቢፈራረቁ ፣ ደስታ እና ሀዘኑ ቢለዋወጡ ፣ ሁሉም በሀገር ነው። የሀገር ክብርን እና ማንነትን በትንሹም በትልቁም ለማዋረድ እና ለመካድ ለምትርጦ ሆድ አደሮች ባለፉት ሁለት ወር በአማራ እና አፋር ክልል እየተፈጸሙ ያሉትን ግፎች ተመልክታችሁ ግፍን እየተቀበሉ ያሉት ወገኖች ኢትዮጵያዊነታችን ኩራታቸው መሆኑን በተግባር ሲያስመሰክሩ ተመልክታችሁ ትምህርት ውሰዱ ።

በተለይ በዲያስፖራው ውስጥ የምትገገኙ የወያኔ ደጋፊዎች ከአፋር እና ከአማራ የወያኔ ጥቃት ሰለባዎች የኢትዮጵያዊነት ስነልቦና ከፍታን ተማሩ።

እውነት ሀይሉ

30/08/2021

ሰላም ተገኝቶ ነው ! ሆ ....

አሁን አሁን አንድ አንድ ሰላም ይሻላል ባዮችን ስመለከት የሰላም ትርጉም ይጠፋብኛል።

የሚደግፉት ወገን የሀይል ሚዛኑ ከፍ ሲል ድምጻቸውን ያጠፋሉ ወይም ከሀገራዊ ሁኔታውወጣ ብለው ስለ ቴክኖሎጂ፤ ሙዚቃ እና ፊልም ይቀደዳሉ። የሚደግፉት አካል መደቆስ ሲጀመር የሰላም ሰባኪ ሆነው ከች ይላሉ። የሚደግፉት አካል የማረካቸውን ወታደሮች ቪዲዮ እየለቀቁ ወንድም ከወንድሙ መጣላት ምን ይጠቅማል የድሀው ልጅ አለቀ እያሉ ያለቃቅሳሉ። በእነሱ ቤት የሚማረከውም የሚሞተውም ከአንድ ወገን እንደሆነ አድርገው ማሳየታቸው ነው። አስተውላችሁ ከሆነ ከሚደግፉት ወገን የተማረከ ወይም የቆሰለ ተዋጊ አያሳዩም ። የሰላምን ጥሪ ከእንደዚህ አይነት አስመሳዮች ከመስማት በላይ የሚያቅለሸልሽ ነገር የለም።

ደግሞ ለራሳቸው የሚሰጡት ግምት ገራሚ ነው ።ራሳቸውን ሲገልጹ ለህሊናቸው የሚኖሩ፤ የሰላም ሰባኪ ፤ ከፍ ያለ ስብዕና ያላቸው አድረገው ነው። ስራቸውን ስለሚያውቁ በየሳምቱ እየመጡ ስለራሳቸው ማብራሪያ ይሰጣሉ። እኔ ለህሊዬ የምኖር ሰላማዊ የሆንኩ ከሰው ከጥላቻ የራቅሁ ምናምን ምናምን እያሉ ዝባዝንኬ ይጽፉና ለራሳቸው ውዳሴ ያቀርባሉ። ማን ጠየቃቸው በቃ ሰውን ስራው ይገልጸዋል እኮ።

አሁን አሁንማ እርግማን ሁሉ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የሚፈጸም አድርገው ሲያወሩ አለማፈራቸው ይገርመኛል። ሌብነቱ ፤ የኑሮ ውድነቱ፤ ደስታ እና ሰላም ማጣቱ ኢትዮጵያ ላይ ብቻ እየሆነ ያስመስሉታል ። የሀገሪቱን ችግር አጋነው እያወሩ ሲኦል ማድረግ ይቀላቸዋል። ከዚያም መለስ ብለው እየሆነ ያለው ሁሉ ህዝቡ ሰላምን ስለጠላ የእነሱን የሰላም ጥሪ ስላልተቀበለ ነው ይሉናል። የሀይል ሚዛኑ ወደሚገፉት ወገን ያደላ ሲመስላቸው ድምጻቸውን ያጠፋሉ። መርጠው ያወግዛሉ። መርጠው ያለቅሳሉ።

የኢትዮጵያ ህዝብ ሰላምን ይፈልጋል ። ስለሰላም ሲል ብዙ ዋጋ የከፈለ ህዝብ ነው። ላለፉት 30 ዓመት የደረሰበትን ግፍ የተሸከመው ሰላማዊ ለውጥ ፈልጎ ነው ።

**በ1997ዓም ምርጫ ተሰፋ አድርጎ የውድ ልጆቹን ህይወት ገብሮ ጫካ ያልገባው ለምን ይመስልሃል?
*የተለያዩ የትጥቅ ጥሪዎችን አብዛኛው ሳይቀላቀል ብዙ ግፎችን የተሸከመው ለምን ይመስልሃል?

** በዘርና ፖለቲካ የተደራጀው ሀይል ሀገሪቱን እየዘረፈ በሀብት ሲናኝ በድህነት ኑሮውን እየታገለ የቆየው ለምን ይመስልሃል ?

*በየእስርቤቶች ስንት እህቶቹ እና ወንድሞቹ እየተደፈሩ ከሰላማዊ ተቃውሞ ውጪ ሌላ አማራጭ ያላድረገው ለምን ይመስልሃል ?

*ለሀገሩ ስንት ሊሰራ የሚችል ወጣት እየተሰደደ፣ እየተገደለ፣ እያበደ ጨርቁን ሲጥል የስንቱ ወጣት ራዕይ ሲመከን ዝም የተባለው ለምን ይመስልሃል ?

*ስንቱ ወገን በብሄሩ፣ በሃይማኖቱ፣ በአስተሳሰቡ እየተገረፈ፣ እየተሸማቀቀ አካለ ስንኩል እየሆነ አንገቱን አቀርቅሮ የኖረው ለምን ይምስልሃል?

*ባለፉት ሶስት አመታት ከኛ በላይ ጀግና የለም ተብሎ ከበሮ ሲደለቅ ፤ ራሱን እንደጀግና ሌላውን እንደፈሪ የሚቆጥረውና ህዝብ የሚንቀው ስብስብ እንደልቡ ሲጨፍር ዝም ያለው ለምን ይመስልሃል ?

ፈሪ ስለሆነ ? የሚደርስበት ግፍ ስለማይሰማው ? ባርያ ስለሆነ ? ወይስ የፈለጉት ቢያደርጉት ንቃተ ህሊናው ዝቅተኛ የሆነ ህዝብ ስለሆነ ? ወይስ ኑሮ ድልት ሙልት ስላለለት ? እብሪተኞችና አስመሳይ የሰላም ሰባኪዎች ከላይ ከተጠቀሱት በአንዱ ሊጠሩት ይችላሉ ። እውነታው ግን የግፉ ጽዋ ሞሎቶ እስኪፈስ እየጠበቀ ነበር። ዕብሪተኞች ጥጋባቸው ከልክ አልፎ የግፉ ጽዋ ሞልቶ ፈሰሰ። የማይነካውን ነኩ። የማይደፈረውን ደፈሩ። ሀገሪቱን አፍርሰን የሞትን ጽዋ ካልጋትንህ አሉት። ኢትዮጵያዊነትን እየተጸየፉ በኢትዮጵያዊነት የከበሩ ከሀዲዎች በማይመጣው መጡ። ይህ ህዝብ የታገሰው ሀገር ስለነበረው ነው። ሀገርህን ካላፈረስን ሲሉ ግን ቀፎው እንደተነካ ንብ ሆ ብሎ ወጣ።

አስመሳይ የሰላም ሰባኪዎቹ ታዲያ ይህን ህዝብ ጭራቅ አድርገው እየሳሉ ስለሰላም ሊሰብኩት ይፈልጋሉ። በጥባጭ ካለ ማን ጥሩ ይጠጣል እንዲሉ ሰላምን አንተ ብቻ ሰለፈለካት አታገኛትም ። በአንድ እጅ አታጨበጭብም ። የእውነት ሰላም ፈላጊ ከሆኑን በጥባጩን ቆፍጠን ብለው ይናገሩት። ይህ ህዝብ ተበጥብጦም ተወቅሶም አያዋጣውም።

አስመሳይ ሰላም ሰባኪዎች ሰላምን ከፈለጉ ለምን ሰላምን እንቢ ብሎ ሀገር እያመሰ ያለውን እብሪተኛ ቡድን እረፍ የወጣቱን ህይወት በከንቱ አታርግፍ ፤ደም በከንቱ አይፈሰስ አይሉትም ። በየማህበራዊ ሚዲያው ብቅ እያላቻሁ ይህን ስንት በደልና ግፍ ተሸክሞ የኖረውን ህዝብ አትውቀሱት። በድጋሚ ለማስታወስ በጥባጭ ካለ ማንም ጥሩ አይጠጣም። በአንድ እጅ አይጨበጨብም።

እውነት ሀይሉ
/ ገጻችን ላይክ አድርገው ቤተሰብ ይሁኑን /

26/08/2021

የማናውቃቸው ይመስል

የህወሃት አመራሮች በአፋር እና በአማራ ክልል በሀይል በተቆጣጠሯቸው ቦታዎች የሚገኙ ነዋሪዎችን እየሰበሰቡ እኛ ጠባችን ከአብይ እና አገኘሁ ተሻገር ጋር እንጂ ከእናንተ ጋር አይደለም እያሉ ህዝቡን ሊደልሉ ሲሞክሩ ተመለከትን። ስለ ህዝባዊነታቸው ገበሬውን በሚያማልል ቃላት ሲያታልሉት ቪዲዮ እየቀረጹ በየሚዲያው አስኮመኮሙን። እኔማ አንድ አንድ ጊዜ ለአሜሪካ ዜጎች ራሳቸውን እያሰተዋወቁ ይመስለኛል ። አስባችሁታል የሰላሳ አመት የትዳር አጋራችሁ እንደ አዲስ እንተዋቀ ሲላችሁ ?

ቃል አቀባያቸው ጌታቸው ረዳ በተደጋጋሚ ከአማራ ኢሊት ጋር ሂሳብ እናወራርዳለን ሲል የአማራ ኢሊት ከሰማይ ወደ ምድር ዱብ ያለ እንጂ ከገበሬው አብራክ የተገኘ እንደሆነ ለአፍታም ትዝ አይለውም። ገበሬው ለፍቶ አስተምሮ ለቁም ነገር ያበቃውን ልጁን ፤ በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ይመለከተኛል ብሎ ንቁ ተሳትፎ የሚያደርገውን ልጁን ፤ በአማራ ልሂቃን ስም ሂሳብ አወራርዳለሁ እያለው ህዝባዊ ነን እኛ እያለ ሲሸነግለው ለህዝቡ ያለውን ንቀት በግልጽ አመላካች ነው ።

ቆይ ግን ወያኔ በለው የትግራይ ህዝባዊ ሰራዊት በለው በህዝባዊነት ስም ራሳቸውን የሚያስተዋውቁት ለማን ነው ? ለአፋር አርብቶ አደር ወይስ ለአማራ ገበሬ? ወይስ ለቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ? ላለፉት 27 አመታት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያደረሱት ግፍ እና በደልን ይቅር ብሎ አብረን በእኩልነት በሰላም እንኑር ባለ በእብሪት ከእኛ በላይ ላሳር ብለው ሀገሪቱን እዚህ የጦርነት እሳት ውስጥ ከተው ሲያበቁ ህዝባዊ እና ዲሲፒሊንድ የሆነ ሰራዊት ያለን ነን ብለው ራሳቸውን እንደ አዲስ ሲያስተዋውቁ መመልከት በራሱ የንቀታቸው ጥግ እና ከትላንት ምንም አለመማራቸውን በግልጽ ያሳያል።

ላለፉት ሃያ ሰባት ዓመት በኢህአዲግ የኢትዮጵያ ህዝብ ብዙ የመከራ ህይወትን አሳልፎአል። ሀገሪቱ የጥቂቶች የሀብት ማካበቻ ነበረች ። ከተረጂነት እንዳትወጣ የምዕራባውያኑ ስንዴ እየተሰፈረላት እንድትኖር ተደርጎአል። የልጅ ልጆቻችን ከፍለው የማይጨረሱት እዳ ውስጥ ተዘፍቃለቸ። ጥቂቶች በብድር ወይም በእርዳት ስም ወደ ሀገር የገባውን ዶላር ለግል ጥቅማቸው አውለውታል። ህዝቡን የእርዳታ እጆችን ተመልካች አድርገው እነርሱ ግን ከምንገምተው በላይ በተንደላቀቀ ኑሮ ህይወታቸውን ኖረዋል። ስንቱ በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት እንደወጣ ቀርቶአል። ሀበት ንብረቱን አጥቶአል። ከሀገሩ ተሰዶአል ። ውድ ህይወቱን አጥቶአል ። ኑሮው ተመሰቃቅሎአል ። አካለ ጎዶሎ ሆኖአል ። የግፋቸው እሳት የስንቱን ቤት ፈጅቶታል ።

ግን ግን የኢትዮጵያ ህዝብ ይህን ሁሉ ይቅር ብሎ ዳግም እድል ሰጣቸው። ይቅርታውን እንደ አላዋቂነት ቆጠሩት። ተበድሎ ይቅርታ አድራጊውን ህዝብ ንቃተ ህሊናው ዝቅተኛ እነሱ ግን የተለዩ እና እራሳቸው የሀገሪቱ ፈጣሪ አድርገው ራሳቸውን ቆጠሩ ። እብሪታቸውን ማስታመም አቃታቸው ። የለኮሱት እሳት ሀገሪቱን ዋጋ እያሰከፈላት ይገኛል ።እንደቅጠል የሚረግፈውን ወጣት ቤቱ ይቁጠረው ። ስንቱ ከሞቀ ኑሮው ተፈናቀለ። ሴቶች ተደፈሩ ፤ ህጻናት ከትምህርት ገበታቸው ተፈናቀሉ ። አዛውንቶች ያልጧሪ ቀባሪ ቀሩ ። ሀብት ንብረት ወደመ ። ብዙ ህዝብ የእለት ጉርሱን ለማግኘት ተቸገረ ። የሀገሪቱ መሰረተ ልማቶች ወደሙ። አሁንም ህልማቸውን ከማሳካት ውጭ ስለሚጠፋው የሰው ልጅ ህይወት እና ስለሚወድመው የሀገር ሀብት ግድ የሚሰጣቸው አይመስሉም ። ህልማቸው ለማሳካት ግን ህዝባዊ ነን እያሉ ሊደልሉን ይሞክራሉ ።

ያልፈጠረባቸውን ከየተም አያመጡትም ። ሲገቡ ህዝባዊ ነን በዲሲፒሊን የታነጸ ሰራዊት ነው ያለን ብለው ሊደልሉት የሞከረቱን ገበሬ በሀይል እንዲለቁ ሲደረጉ ሀበት ንብረቱን አውደመው ከበቶቹን ገድለው ፤ ህይወት አጥፍተው ፤ የህክምን አግልግሎት መስጫዎችን አፈራርሰው ፤ ብዙ ጸያፍ ተግባራትን ፈጽመው ወጥተዋል። ድንቄም ህዝባዊነት ።

እነ ጌታቸው ረዳ ሊገነዘቡት የሚገባው ነገር ቢኖር በወሬ ሳይሆን በተግባር ጥንቅቅ አድርጎ ከሚያውቃቸው ህዝብ ጋር እየተዋጉ መሆኑን ነው ። ይህ እውነት እስኪገለጽላቸው ድረስ የስንቱ ኢትዮጵያዊ ህይወት ይቀጠፍ ይሆን ? ስንቱ ከቀየው ይፈናቀል ይሆን ? ስንቱ ሀብት ንብረቱን ያጣ ይሆን ?

ህዝባዊ ድርጅት አልበራችሁም ህዝባዊ መሆን አቅቶአችሁ ከስልጣን የተባረራችሁ ዕብሪተኞች ናችሁ ። የኢትዮጵያ ህዝብ በቲቪ እና በሶሻል ሚዲያው ሳይሆን በህይወቱ ጠንቅቆ ያውቃችኃል ። ህዝብ አንቅሮ ከተፋህ በኃላ መንፈራገጡ ለመላላጥ መሆኑን አውቃችሁ ለሰላም በራችሁን ክፈቱ ።

እውነት ሀይሉ

11/08/2021

"ሰላም ይሻላል" ስንል ባለፉት ሃያ ምናምን አመታት የተፈፀሙትን በደሎችና ጥፋቶች በማን መሪነት እንደተፈፀሙ እረስተን አይደለም...
"ሰላም ይሻላል" ስንል ጦርነቱ በማን እምቢተኝነት እንደተጀመረ እረስተነው አይደለም...
"ሰላም ይሻላል" ስንል ማን በየሳምንቱ ጦር እያሰለፈ ሾው ሲያደርግ እንደነበር እረስተነው አይደለም...
"ሰላም ይሻላል" ስንል "ከፈለግን በሳምንት ታንክ ነድተን አራት ኪሎ እንገባለን" የተባለውንም ትምክህተኛ ንግግር እረስተነው አይደለም....
"ሰላም ይሻላል! ስንል በጦርነት ውስጥ ስለተደፈሩ እህቶቻችን ስታወሩ ያዘነውን ያህል ባለፉት ሃያ ምናምን አመታት በሃገር ሰላም በየእስርቤቶች ስንት እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን እንደተደፈሩም እረስተን አይደለም....
"ሰላም ይሻላል!" ስንል ስንት ወጣት እንደተሰደደ፣ እንደተገደለ፣ እንዳበደ እረስተን አይደለም...
"ሰላም ይሻላል!" ስንል ስንቱ በብሄሩ፣ በሃይማኖቱ፣ በአስተሳሰቡ እንደተገረፈ፣ እንደተሸማቀቀ፣ እንደተገፋ እረስተነው አይደለም...
"ሰላም ይሻላል!" ስንል ስንት ሰው በአሻጥር ከስራው ከቢዝነሱ እንደተገለለ ወህኒ እንደተወሩወረ እረስተን አይደለም....
"ሰላም ይሻላል" ስንል ስንት ቤት የቴዲ አፍሮን ጃ ያስተስርያልን እና የሃጫሉን ዘፈን ከፈትክ ተብሎ እንደታሸገ ስት ሰው ይሄን ጋዜጣ አተምክ አነበብክ ተብሎ ስንት በደል እንደደረሰበት እረስተነው አይደለም...
"ሰላም ይሻላል" ስንል ብዙ ብዙ የተደረጉ ጥፋቶችንና በደሎችን እረስተን ሳይሆን የሰላምን ዋጋ ስለምናውቅና ከጦርነት አናተርፍም ብለን ነው:: ህዝባችን ያልቃል፣ ይሰደዳል፣ ይራባል፣ የድሃ ሃገር ንብረት ይወድማል፣ ልጅ ያለ ወላጅ፣ ሽማግሌ ያለጧሪ ይቀራል፣ በጦርነት ሃገር ትዳከማለች ብለን እንጂ ሁሉንም እረስተን አይደለም!
"ሰላም ይሻላል" ስንል ሃገርን ለማዳን ይህ በደል እንዳይደገም የሚከፈል መሰዋትነትን ለማሳነስ አይደለም!
አይዞሽ ኢትዮጵያዬ! አይዞሽ ሃገሬ! ይሄም ቀን ያልፋል!

Habtish Dôø Yilma

10/08/2021

ሀገራችሁን የመጠበቅ ጉዳይ የራሳችሁ ሀላፊነት ነው / አሜሪካ /

አፍጋኒስታንን ለቃ የወጣችው አሜሪካ “ሃገራቸውን የመጠበቁ ጉዳይ የራሳቸው የአፍጋናውያኑ ነው” ብላለች። ሀያ ዓመት በአፍጋኒስታን ጦር አስፍራ ስትዋጋ የቆየችው አሜሪካ በአሜሪካ መከላከያ (ፔንታጎን) ጽህፈት ቤት ቃል አቀባይ ጆን ኪርቢ በኩል ነው ይህን መግለጫ የሰጠችው።

እኛ ኢትዮጵያውያን የምንነግራትን ለመስማት ስንት አመት ያስፈጋት ይሆን ? ሀገራችንን መጠበቅ የእኛ ጉዳይ ነው በውስጥ ጉዳይ እየገባሽ አትፈትፍቺ ፤ የሚበጀንን እምናውቀው እኛው ነን ፤ በእሳቱ የተለበለብነው እኛው ነንና ህመማችንን እናውቀዋለን። አድቢ እያልናት ነው። አሃ ቆይ ሰዎቹ ጦር አዝምተው ሀገር አፍርሰው ሲበቃቸው ነው እንዴ እሚገለጽላቸው?

" አፍጋኒስታንን የመጠበቁ ጉዳይ የራሳቸው የአፍጋናውያን መሆኑን አሜሪካ አስታወቀች" የሚል ዜና አንብበህ የኛንስ ሀገር የመጠበቁ ጉዳይስ ስትል እጆቻን ዘርግታ ካላማሰልኩ ስትል ትመለከታታለ ። በወጉ ማማሰልም የአባት ነው ። አማስላ ያሳረረችው እንጂ ያጣፈጠችው ሀገር የለም። ሊቢያ ፤ ሶርያ ፤ አፍጋንሲታን ፤ የመን ፤ ኢራቅ ... በምሳሌነት ይጠቀሳሉ።

የሀገሬ ሰው የሀገርህ እጣ ፋንታ የሚወሰነው በአንተ ብቻ ነው። የራስህን እና የልጆችህ መጻኢ እድል የምትወስነው አንተው ነህ። ምዕራብያውያኑ በአገርህ ቢመጡ ግዙፍ እና ዘመናዊ መሳሪያ ይዘው ነው። መሬትህን እና ነፍስህ የምትገብረው ግን አንተው ነው። ቆፍጠን ብልሀ ጣልቃ ገብነት ተቃወም ። በቻልከው መንገድ በሀገርህ ጉዳይ የምዕራብውያኑን ያልተገባ ጣልቃ ገብነት ተቃወም። ድምጽህን አሰማ።

"አያያዙን አይተው ጭብጦውን ቀሙት" እንደሚባለው አያያዙን አላውቅበት ብለን ሀገራችንን እንዳናስቀማ መጠንቀቅ ያስፈልጋል።

ሀሎ አሜሪካ "ሀገራችንን የመጠበቅ ጉዳይ የራሳችን ሀላፊነት ነው"። ይሰማል???

እውነት ሀይሉ

https://www.defense.gov/Newsroom/Transcripts/Transcript/Article/2725063/pentagon-press-secretary-john-f-kirby-holds-a-press-briefing/

Address

Gobenastreet
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ewnet Hailu/ እውነት ሀይሉ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share