
19/09/2025
ኤርትራ መልስ ሰጠች‼️
ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የድርድር ጥያቄ ኤርትራ መልስ ሰጥታለች፡፡
ጠቅላዩ በሳምንቱ መጀመሪያ አዲሱን መጽሀፋቸውን ባስመረቁበት ወቅት ‹‹አምስት አመት ሙሉ የቆየነው ውጊያን ለማስቀረት ነው፤ ወንድም እህቶቻችን በአስቸኳይ እራሳቸውን ለድርድር አዘጋጁ›› ብለው ነበር፡፡ ለዚህ የአብይ ንግግር ኤርትራ የመልስ ምት ሰጥታለች፡፡ ‹‹ብልጽግና ሊወረኝ እያኮበኮበ ነው›› ሲልም የድርድሩን ጥሪ ገፍቶታል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የመደመር መንግስት የተሰኘውን አዲስ መጽሀፋቸውን ባስመረቁበት ወቅት ስለ ባህር በር ጉዳይ ንግግር ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ በንግግራቸውም፣ ለድርድር ተዘጋጁ፣ በፍጹም ኢትዮጵያ መውጫ መግቢያ በሯን ዝግ አይሆንም፣ ባህር በሩ ይመጣል እናሳካዋለን›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡
ለዚህ የአብይ ንግግር ኤርትራ በማስታወቂያ ሚኒስትሩ በኩል እንደተለመደው የተቃውሞ መልስ ሰጥቷል፡፡
የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ በኤክስ ገፃቸው ባሰራጩት መልእከት፣ ብልጽግና ሉአላዊነታችንን ለመጣስ እያኮበኮበ ነው በማለት ከሰዋል፡፡ የብልጽግና ባለሥልጣናት ዘምተውብናል ሲሉ የወነጀሉት ሚኒስትሩ፤ የብልጽግና ባለሥልጣናት በባለቤትነት የሚቆጣጠሩት የባህር በር ለማግኘት ያላቸውን መሻት አጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ በተለይም አሰብን ማስመለስ እንዳለባት ኤርትራ ከተገነጠለች ማግሥት ጀምሮ የአጀንዳነት ሚዛኑ ከፍ ዝቅ ቢልም ሲነሳ እንደነበር ይታወቃል፡፡
(FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ)