
07/08/2025
ጋና በሄሊኮፕተር አደጋ መሪዎቿን አጣች!
በጋና የአየር ሃይል ሄሊኮፕተር ተከስክሶ የሀገሪቱ ቁልፍ ባለስልጣናት መሞታቸው ተሰማ ።
የጋና ኮሚኒኬሽን እንደገለፀው ከሆነ ረቡዕ ከጠዋቱ 9፡00 ሰዓት ከአክራ ተነስቶ ከዋና ከተማው በስተሰሜን ምዕራብ ወደምትገኘው ወደ ኦቡአሲ ከተማ በማምራት ላይ የነበረ ሶስት የበረራ ሰራተኞችን እና አምስት የሀገሪቱን ከፍተኛ ባለስልጣናት የያዘ ዜድ-9 ሄሊኮፕተር
በገጠመው የመከስከስ አደጋ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ ሁሉም ሰወች ህይወት ማለፉን ገልጿል ።
በአደጋዉም የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር ኤድዋርድ ኦማን ቦአማህ እና የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሩ ኢብራሂም ሙርታላ መሐመድ ከብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ኮንግረስ ገዥ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር፣ የብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ አማካሪ እና የበረራ አባላት በጥቅሉ አስር ሰዎች ህይወታቸው ወዲያውኑ ማለፉን አረጋግጧል ።
የሄሊኮፕተሯ ስብርባሪ በአሻንቲ አዳንሲ አካባቢ መገኘቱን የገለፀው መግለጫው የአደጋው መንስኤ እስካሁን ያልታወቀ ሲሆን፥ ወታደራዊ ሃይሉም ምርመራ እየተካሄደ ነው ብሏል።
ከአደጋዉ በኋላ ባለስላጣናቱ በቦአማህ መኖሪያ እና በፓርቲው ዋና ፅህፈት ቤት የተሰበሰቡ ሲሆን የጋና መንግስት አደጋውን “ሀገራዊ አሳዛኝ” ሲል ገልጿል።
"ፕሬዝዳንቱ እና መንግስት ለጓዶቻችን ቤተሰቦች እና ለሀገር በማገልገል ላይ ለሞቱት አገልጋዮች ሀዘናችንን እና ሀዘናችንን እንገልፃለን" ሲሉ የማሃማ ዋና ሰራተኛ ጁሊየስ ዲብራህ ተናግረዋል ።
በሁሉም የመንግስትና የግል መስርያ ቤቶች ባንዲራዎች ዝቅ ብለዉ እንዲውለበለቡ ያሉት ፕሬዚዳንቱ በበኩላቸው ማሃማ የዕለቱን ይፋዊ እንቅስቃሴያቸውን መሰረዛቸውን ተናግረዋል።
የረቡዕ አደጋ ከአስር አመታት በላይ በጋና ካጋጠሙት አስከፊ የአየር አደጋዎች አንዱ ነው።
ለዘገባው ፍራንስ 24 ቢቢሲ አፍሪካ ኒዉስን ተጠቅመናል ።
FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ