FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ ፋኖስ ሚዲያ ወቅታዊ ዜናዎችን፣ ተዓማኒነት ያላቸው መረጃዎች በሳል የፖለቲካ ተንታኞች አተያዮች ከኢትዮጵያና ከአለም ዙሪያ በፍጥነት ይቀርቡበታል

"እናቴ ከሀገር አትበልጥም" በዓለምላይ ዋሴለካ የጃውሳው የአጤ ካሣ የአጥንት ፍላጭ የጣልያኑ ጌታ የአባ ኮስትር በላይ የሥጋ ቁራጭ ናት!ደጃች በላይን በየሻሽወርቅ አጤ ቴዎድሮስን በዓለማየሁ ...
16/10/2025

"እናቴ ከሀገር አትበልጥም" በዓለምላይ ዋሴ

ለካ የጃውሳው የአጤ ካሣ የአጥንት ፍላጭ የጣልያኑ ጌታ የአባ ኮስትር በላይ የሥጋ ቁራጭ ናት!

ደጃች በላይን በየሻሽወርቅ አጤ ቴዎድሮስን በዓለማየሁ ለማባበል ተሞክሯል።

ቴዎድሮስ ለሀገራቸው ኢትዮጵያ እና ለራሳቸውም ክብር ብለው ራሳቸውን መሥዋዕት ሊያደርጉ በተዘጋጁ ጊዜ እንዲታቀቡ ተለምነው ነበር። “እባክዎን በሚወድዱት ልጅዎ በልዑል ዓለማየሁ ይኹንብዎ፤ በራስዎ ላይ አይጨክኑ” እያሉ ተማጠኗቸው።

ጃውሳው ካሣ ግን ፡- “ለዓለማየሁ ምንም የማወርሰው ነገር የለም። ሲያድግ ግን አባትህ አንዲት ኢትዮጵያ በዐይኑ እንደዞረች ሞተ በሉት” አሉ።

የደጃች በላይ ክንድ እንደ እሳት የፈጃቸው ፋሺስት ጣልያኖች ልጁን የሻሽወርቅን አፍነው ወስደው መልእክት ላኩበት። እርቅ እናውርድ ልጅህንም ጎጃምንም እንስጥህ አሉት።

አባ ኮስትርም:- "የእናንተ ሀገር ሮም ነው ኢትዮጵያ ደሞ የእኔ። የእኔን ሀገር ከእናንተ አልቀበልም፤ አልወሰዳችኋትም እና። አትወስዷትምም። ልጄ የሻሽወርቅ ከኢትዮጵያ አትበልጥም፤ ለእሷም እግዚአብሔር አላት" በማለት ለምልጃ የመጡትን ባንዳዎች አስተናግዶ ወሬ ነጋሪውን ቱርጁማን መልሶላቸዋል።

በዓለምም ይኽን መሰል ልመና ቀርቦላት ነበር። በቲክ ቶክ ገጿ የተስተናገደ ሲኾን ነገሩ እንዲህ ነው። የኬኳ እናት በሚል ስም አስተያየት ሰጪዋ "እባክሽ ለእናትሽ ኑሪላት" የሚል ማባበያ ታቀርብላታለች። የጀግኖቹ መንፈስ ወራሿ በዓለም ግን መልሷ እንደ አባቶቿ ፈርጣማ እና ቁርጠኛ ነበር። እንዲህ ይላል:- እናቴ "ምንም ቢኾን ከሀገር አትበልጥም።" የሚገርም ጽናት በልጅነት። ባንዳን የሚያረግፍ ታላቅነት ከእውነት አንደበት።

እናቷን ጠልታ እኮ አይደለም። የዓላማ ጽናት ተራራ ላይ ስለወጣች እንጅ። የጸና አይደለልም። ወደኋላ አይመለስም። ሞትን እንደ ውኃ ይጠጣዋል እንጅ ለሞት አይንበረከክም።
ሞት ደመወዙና ክብሩ፣ ሥልጣኑና ክብሩ፣ ታሪኩና ግብሩ ነው።

የ፲፱ ዓመቷ በዓለም ዕድሜዋ ለጋ ቢኾንም ገድሏ ግን የአባቶቿን ያኽላል።
Abayneh Kassie Dn - ዓባይነህ ካሤ - ዲን

" የወላዷን ስቃይ ሳይ ግን አልቻልኩም፣ በጣም ደከመኝ እንባዋን ሳይ እኔም ባለሁበት ቁጭ ብየ አለቀስኩ ፤ የእኔ ማልቀስ ግን ህፃኑን ማትረፍ አልቻለም፣ በዚህም በጣም አዝኛለሁ " - የአምቡ...
16/10/2025

" የወላዷን ስቃይ ሳይ ግን አልቻልኩም፣ በጣም ደከመኝ እንባዋን ሳይ እኔም ባለሁበት ቁጭ ብየ አለቀስኩ ፤ የእኔ ማልቀስ ግን ህፃኑን ማትረፍ አልቻለም፣ በዚህም በጣም አዝኛለሁ " - የአምቡላንስ ሹፌር

በጎፋ ዞን መሎ ጋዳ አካባቢ አንድ የአምቡላንስ ሹፌር አንዲት ወላድ እናትን ወደ ሆስፒታል ይዞ ሲጓዝ አምቡላንሷ በጭቃ ተውጣ እና ሹፌሩ መኪናዋን ለማውጣት የቻለውን በሙሉ አድርጎ ሲያቅተው በጭቃው ላይ ቁጭ ብሎ ሲያለቅስ የሚያሳይ ምስል በተለያዩ የማህበራዊ ገጾች ላይ ተዘዋውሮ ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም ይህንን የአምቡላንስ ሹፌር በስልክ አግኝቶ ስለተፈጠረው ነገር አነጋግሯል።

ይህ ሹፌር ሀብታሙ ደርጉ ደረሰ ይባላል።

ሹፌር ሀብታሙ ደርጉ ደረሰ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አለ ?

" ችግሩ የተፈጠረው ከመሎ ጋዳ ወረዳ አንዲት ወላድ እናት በወሊድ ምክንያት ሪፈር ተጽፎላት ወደ ጎፋ ዞን ሆስፒታል ይዤ እየሄድኩ እያለ ልዩ ስሙ ጃውላ መንገድ ተብሎ በሚጠራው ቦታ ላይ ጥቅምት 2/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 8 ስአት ላይ ነው።

ከወላዷ ጋር የነበሩ ሰዎች ከእኔ ጋር በመሆን መኪናዋን ከጭቃው ለማውጣት እየታገልን እያለ ወላዷ በዚሁ ቦታ ላይ ወለደች፣ የሚያሳዝነው ግን የተወለደው ህጻን ሞቷል።

በመቀጠልም ስለተፈጠረው ነገር ለሃላፊዬ ደወልኩና ነገርኩት፣ እናትየዋ የደም ካንሰር ስላለባት በህይወት ለመቆየት ወደ ሆስፒታል መድረስ አለባት አልኩት። ከዛም ከቡልቄ ወረዳ ሌላ አምብላንስ መጥቶ እናትየዋን እንድወስዳት ተደረገ።

ይህ ነገር ከመሆኑ በፊት ግን እናትየዋን እና ህፃኑን በህይወት ለማዳን የግድ አምብላንሷን ከጭቃው ማላቀቅ ስለነበረብኝ ብዙ ስቆፍር ነበር። ነገር ግን አልሆነም፣ እኔም በዚያ ብርድ ላይ ስቆፍር አድሬ ሰኞ እለት ጠዋት 2:30 አካባቢ ላይ ወደ ጋዳ ተመልስኩ።

በሰአቱ የተሰማኝ ስሜት ከባድ ነው፣ ቆፍሬ፣ ቆፍሬ ሲደክመኝ በአካባቢው ያሉ ሰዎች እንዲረዱን አምቡላንሷን ሳስጮሀት ነበር። ግን መጀመሪያ ላይ ማንም አልመጣልንም። አብረውኝ የህክምና ባለሙያን ጨምሮ የወላዷ ባለቤት እና አማቿ ነበሩ።

በሰአቱ የወላዷን ስቃይ ሳይ አልቻልኩም፣ በጣም ደከመኝ፣ እንባዋን ሳይ እኔም ባለሁበት ቁጭ ብየ አለቀስኩ ፤ የእኔ ማልቀስ ግን ህፃኑን ማትረፍ አልቻለም፣ በዚህም በጣም አዝኛለሁ።

በህይወት የሌለ ልጅ የወለደችው እናት በስአቱ በጣም ደክሟት ነበር፣ ምክንያቱም የደም ካንሰር አለባት። ሌለኛው አምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ወስዶ ካደረሳት በሗላ ወደ ጥቁር አንበሳ ሪፈራል ሆስፒታል ሪፈር ተጽፎላታል፣ ነገር ግን ለህክምናው የተጠየቀችው ገንዘብ ወደ 800 ሺህ ብር ስለሆነ ገና እርዳታ እያሰባሰብን ነው።

በአምቡላንስ ሹፍርና እያገለገልኩ ሁለት አመት ቆይቻለሁ፣ ብዙ ጊዜም ተመሳሳይ ችግር ይገጥመኛል፣ ሁለት እና ሶስት ቀን መንገድ ላይ የማድርባቸው አጋጣሚዎችም ነበሩ። በተደጋጋሚ የእናቶችን ከፍተኛ የሆነ ሲቃይ አይቻለሁ። በዚህኛው ግን በጣም ተስፋ ቆርጨ ከዚህ በሗላ መኪና ላለማሽከርከር አስቤ ነበር። በፌስቡክ የእኔን ምስል ብዙዎች ሲቀባበሉት ስመለከት እና ብዙዎች ለእናቶች ያላቸውን ፍቅር ሲገልፁ ሳይ ግን በጣም ደስ ብሎኛል።

ሁሌም በመንገድ ጉዳይ እንደተሰቃየን ነው፣ ችግሩ ጫፍ የወጣ ነው። የእናቶችን እና የህፃናቶችን ሞት ለማቆም ሁሉም ሰው ለመሎ ጋዳ መንገድ ትኩረት ሊሰጥ ይገባል " ሲል ተናግሯል በማለት
ዘግቧል።

" ሰላምን እንሻለን ! " - የትግራይ ኃይል አባላት➡️ " የኛን ጥያቄ መመለስ ከማይችል አመራር የሌላው ህዝብ ጥያቄ ሊመልስ አይችልም ! "የትግራይ ኃይል አባላት ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 3/201...
13/10/2025

" ሰላምን እንሻለን ! " - የትግራይ ኃይል አባላት

➡️ " የኛን ጥያቄ መመለስ ከማይችል አመራር የሌላው ህዝብ ጥያቄ ሊመልስ አይችልም ! "

የትግራይ ኃይል አባላት ዛሬ ሰኞ ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም ከጥዋቱ 2:30 ጀምረው የመብት ጥያቄ አንስተው በከተማዋ ዋና ዋና መንገዶች ሰላማዊ ሰልፍ አካሂደዋል።

ሰልፈኛቹ ቁጣን ባዘለ ድምፅ ፦

- " የደመወዝና ጥቅማጥቅም ጥያቄያችን ይመለስ ! "
- " የሰራዊት ጥያቄ የማይመልስ አመራር የሌላው ህዝብ ጥያቄ መመለስ አይችልም ! "
- " የሰራዊት ድምፅ ይሰማ ! "
- " ሰላምን እንሻለን ! "
- " ክብር ለሰራዊትና ለተሰው ቤተሰብ አባላት ! "
የሚሉና ሌሎች መፈክሮች አሰምተዋል።

ሰላማዊ ሰልፈኞቹ መፈክራቸው እያሰሙ ወደ ትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅህፈት ቢያመሩም ፕሬዜዳንቱ ማግኘት አልቻሉም።

ጥያቄያቸው ስምቶ መልስ የሚሰጥ ሃላፊ በማጣታቸው የተቆጡት ሰልፈኛቹ ከቀኑ 7:00 እስከ 11:00 ከመቐለ ወደ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ የሚወስደው ዋናው የመኪና መንገድ በድንጋይና በአካል ዘግተውት ውለዋል።

ይህንን መረጃ ከተዘጋጀበት ጥቂት ደቂቃዎች በፊት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮቹ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች ጋር ለውይይት መቀመጣቸው ተከትሎ የተዘጋው መንገድ መከፈቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አረጋግጧል።

በተጀመረው ውይይት የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) መገኘታቸውና አለመገኘታቸው ማረጋገጥ አልቻልንም።

የውይይቱን ውጤት ተከታትለን እናቀርባለን።

- በአሁኑ ሰዓት የሰላማዊ ሰልፈኞቹ ተወካዮች የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀ) ከሚገኙባቸው ከፍተኛ ወታደራዊና የስቪል አመራሮች በመነጋገር ላይ ይገኛሉ።
FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

via Tikvah

ቀደም ብለን ባወጣነው የአፋልጉኝ ማስታወቂያ በውስጥ መስመር ከደረሰን መረጃዎች አድራሻው:- በሲዳማ ክልል ሐዋሳ ከተማ ኮንዶሚኒየም ሳይት 4 ሲሆን።  አቶ ተአምራት ሞርኮ ይባላል።የቀድሞ ደቡ...
09/10/2025

ቀደም ብለን ባወጣነው የአፋልጉኝ ማስታወቂያ በውስጥ መስመር ከደረሰን መረጃዎች
አድራሻው:- በሲዳማ ክልል ሐዋሳ ከተማ ኮንዶሚኒየም ሳይት 4 ሲሆን። አቶ ተአምራት ሞርኮ ይባላል።የቀድሞ ደቡብ ክልል ፖሊስ ባልደረባ የነበረ ነው።ግለሰቡ በሙስና እና በወንጀል በማስቸገሩ ከዚህ ተቋም የተባረረ ሲሆን።
በአብሮነት እና በመቻቻል እየኖረ ያለ ህዝብን ለማጋጨት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል።
ይህ ውንብድና የተፈጸመባቸው አባት የሀዋሳ መካነ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ ካህን መምህር ሞገስ ናቸው!
ካህኑ ከአገልግሎት ሲመለሱ በካህኑ አካል ላይ በመነካካት (ትከሻ እና እጅ) እና በመሳለቅ ሲያላግጥ በቪድዮ ተስተውሏል።
ድርጊቱ ሃይማኖታዊ ክብርን የሚጎዳ እና የሰውን ግላዊ ድንበር የሚጥስ መሆኑን ተስተውሏል።
በዚህም የግለሰቡ ድርጊት መላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች አስቆጥቷል።

የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር እ*ር*ም*ጃ እንዲወስድ በጥብቅ እንጠይቃለን ::

አስቸኳይ ፓስተሩ መንገድ ላይ ያለ ካህኑ ፍቃድ ለመስበክ ሲሞክር ካህኑ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ካህኑን ሲገፋና በግድ "እየሱስ ጌታ ነው ይበሉ በማለት ሲያስጨንቅ በማህበራዊ ሚዲያ የታየው "የዚህ...
09/10/2025

አስቸኳይ

ፓስተሩ መንገድ ላይ ያለ ካህኑ ፍቃድ ለመስበክ ሲሞክር ካህኑ ፍቃደኛ ባለመሆናቸው

ካህኑን ሲገፋና በግድ "እየሱስ ጌታ ነው ይበሉ በማለት ሲያስጨንቅ በማህበራዊ ሚዲያ የታየው "የዚህን ፓስተር አድራሻ የምታውቁ በመጠቆም ተባበሩ

ይሄ ስብከት ሳይሆን ትንኮሳ ነው!!
መከባበር እና ጨዋነት ከሌለ ወንጌል ሳይሆን ወንጀል ነው

በህግ መጠየቅ የሚገባው ፓስተር ስለሆነ አድራሻውን በማፈላለግ
ለጥቆማ :-
ስሙን______
የሚያገለግልበትን የእምነት ተቋም______
አሁን የት እንደሚገኝ _______
የማታቁት ሼር በማድረግ ተባበሩ !

ኤርትራ መልስ ሰጠች‼️ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የድርድር ጥያቄ ኤርትራ መልስ ሰጥታለች፡፡ ጠቅላዩ በሳምንቱ መጀመሪያ አዲሱን መጽሀፋቸውን ባስመረቁበት ወቅት ‹‹አምስት አመት ሙሉ የቆየነው ው...
19/09/2025

ኤርትራ መልስ ሰጠች‼️

ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የድርድር ጥያቄ ኤርትራ መልስ ሰጥታለች፡፡

ጠቅላዩ በሳምንቱ መጀመሪያ አዲሱን መጽሀፋቸውን ባስመረቁበት ወቅት ‹‹አምስት አመት ሙሉ የቆየነው ውጊያን ለማስቀረት ነው፤ ወንድም እህቶቻችን በአስቸኳይ እራሳቸውን ለድርድር አዘጋጁ›› ብለው ነበር፡፡ ለዚህ የአብይ ንግግር ኤርትራ የመልስ ምት ሰጥታለች፡፡ ‹‹ብልጽግና ሊወረኝ እያኮበኮበ ነው›› ሲልም የድርድሩን ጥሪ ገፍቶታል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የመደመር መንግስት የተሰኘውን አዲስ መጽሀፋቸውን ባስመረቁበት ወቅት ስለ ባህር በር ጉዳይ ንግግር ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ በንግግራቸውም፣ ለድርድር ተዘጋጁ፣ በፍጹም ኢትዮጵያ መውጫ መግቢያ በሯን ዝግ አይሆንም፣ ባህር በሩ ይመጣል እናሳካዋለን›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

ለዚህ የአብይ ንግግር ኤርትራ በማስታወቂያ ሚኒስትሩ በኩል እንደተለመደው የተቃውሞ መልስ ሰጥቷል፡፡

የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ በኤክስ ገፃቸው ባሰራጩት መልእከት፣ ብልጽግና ሉአላዊነታችንን ለመጣስ እያኮበኮበ ነው በማለት ከሰዋል፡፡ የብልጽግና ባለሥልጣናት ዘምተውብናል ሲሉ የወነጀሉት ሚኒስትሩ፤ የብልጽግና ባለሥልጣናት በባለቤትነት የሚቆጣጠሩት የባህር በር ለማግኘት ያላቸውን መሻት አጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በተለይም አሰብን ማስመለስ እንዳለባት ኤርትራ ከተገነጠለች ማግሥት ጀምሮ የአጀንዳነት ሚዛኑ ከፍ ዝቅ ቢልም ሲነሳ እንደነበር ይታወቃል፡፡

(FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ)

Inbox:-  #ሸርእባካችሁ ድምፅ እንሁነው የተከበሩ የፓርላማ አባል ክርስቲያን ታደለ በማረሚያ ቤት ህመማቸው ተባብሶባቸዋል፤ እንደሚታወቀው ባለፈው በመቅረዝ ሆስፒታል ቀዶ ህክምና ተደርጎላቸ...
17/09/2025

Inbox:- #ሸርእባካችሁ ድምፅ እንሁነው የተከበሩ የፓርላማ አባል ክርስቲያን ታደለ በማረሚያ ቤት ህመማቸው ተባብሶባቸዋል፤ እንደሚታወቀው ባለፈው በመቅረዝ ሆስፒታል ቀዶ ህክምና ተደርጎላቸው ህክምናውን በአግባቡ ሳይጨርሱ ወደ ቂሊንጦ መልሰው በመወሰዳቸው ህመሙ አሁን ላይ ከባድ ሁኔታ ላይ ይገኛል።

ስለዚህ መላው ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ድምፅ ሁኑት ይፈታ ሳይሆን በአግባቡ ህክምናውን ይከታተል ሰብዓዊ መብቱ ይከበርለት ዘንድ ፍትህ እንጠይቅለት።

ዝም አንበል በሶሻል ሚድያ #ሸር በማድረግ በመንሸራሸር ለኢትዮጵያ ሰበአዊ መብት ኮሚሽን እና ለሚመለከታቸው አካላት ይደርስ ዘንድ ተባበሩን🙏

የሚጎድልባቸው ነገር የለም #ሸር በግሩፑ በየአካውንታችሁ #ሸር አድርጉት ሚዲያ አቅም አለው

የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ በጠና ታመሙ::አዲስ አበባ፤ መስከረም 7 ቀን 2018 በእስር ላይ የሚገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ በጤና እ...
17/09/2025

የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ
በጠና ታመሙ::

አዲስ አበባ፤ መስከረም 7 ቀን 2018 በእስር ላይ የሚገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ በጤና እክል ምክንያት በጠና መታመማቸውን ቤተሰቦቻቸው እና ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።

ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ እንዳሉት፣ ሰኞ ዕለት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ውስጥ አግኝተዋቸው የነበረ ሲሆን፣ አቶ ክርስቲያን ከቅርብ ጊዜ በፊት ካደረጉት ቀዶ ሕክምና በኋላ ተገቢው ክትትል ባለማግኘታቸው ሕመማቸው እየተባባሰ መምጣቱን ገልጸዋል።

አንድ የቤተሰባቸው አባልም እንደተናገሩት፣ አቶ ክርስቲያን ከወራት በፊት በመቅረዝ ሆስፒታል ቀዶ ሕክምና ካደረጉ በኋላ፣ በቂ ክትትል ሳይደረግላቸው ወደ ማረሚያ ቤት እንዲመለሱ መደረጉ ለዚህ ሁኔታ እንደዳረጋቸው ተናግረዋል።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) ወክለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እንዲሁም በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የነበሩት አቶ ክርስቲያን፣ በአማራ

ክልል በተፈጠረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ በኋላ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ከዚያም ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ ላለፉት ሁለት ዓመታት በእስር ላይ ይገኛሉ።

Via BBC Amharic

እኔም ክርስቲያን ታደለ ነኝ!! የመታከም መብቱ ይከበር! የሚል ህዝባዊ ንቅናቄ ተጀምሯል በንቅናቄው ከተስማሙ ሼር በማድረግ ድምፅ ይሁኑ
14/09/2025

እኔም ክርስቲያን ታደለ ነኝ!! የመታከም መብቱ ይከበር! የሚል ህዝባዊ ንቅናቄ ተጀምሯል

በንቅናቄው ከተስማሙ ሼር በማድረግ ድምፅ ይሁኑ

በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች በሙሉ እንኳን ለ2018 የዘመን መለወጫ በአል አደረሳችሁ  የሚል መልእክቴን እያስተላለፍኩ በዓሉ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆን...
10/09/2025

በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች በሙሉ እንኳን ለ2018 የዘመን መለወጫ በአል አደረሳችሁ የሚል መልእክቴን እያስተላለፍኩ በዓሉ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።

መልካም አዲስ አመት!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፍቅር ያሸንፋል!
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)
#ላይክ #ሸር #አይረሳ

ወገኖችየጦርነት ዜና አልሰለቻችሁም? አንድ መኪና ሰው ታገተ፣ ተገደለ፣ እከሌ ታግቶ ለአጋቾች ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው የሚል ጩኸት አልሰለቻችሁም? ከክልል ክልል፣ ከከተማ ከተማ በሰላም እጦት...
10/09/2025

ወገኖች

የጦርነት ዜና አልሰለቻችሁም? አንድ መኪና ሰው ታገተ፣ ተገደለ፣ እከሌ ታግቶ ለአጋቾች ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው የሚል ጩኸት አልሰለቻችሁም?

ከክልል ክልል፣ ከከተማ ከተማ በሰላም እጦት እንደ ልባችሁ ተንቀሳቅሳችሁ መስራት አልተቸገራችሁም? በዚህ የተነሳስ ኑሮ አልከበዳችሁም?

አቦ አዲሱ ዓመት የዚህ ሁሉ ችግር ምንጭ ደርቆ በሰላምና በፍቅር የምንኖርበት አመት ይሁንልን።

ድል በዲኘሎማሲ ትግል…🇪🇹🔥✌️ግብፅ ዛሬ ማበድ ይዛለች አል-ሲሲ ጉዳዩን ወደ ፀጥታው ም/ቤት በመውሰድ ኢትዮዽያ ላይ አለም አቀፍ  እርምጃ ይወሰድልኝ ብልዋል…😂😂😂  ከእንዲህ የአባይ ጉዳይ ...
09/09/2025

ድል በዲኘሎማሲ ትግል…🇪🇹🔥✌️

ግብፅ ዛሬ ማበድ ይዛለች አል-ሲሲ ጉዳዩን ወደ ፀጥታው ም/ቤት በመውሰድ ኢትዮዽያ ላይ አለም አቀፍ እርምጃ ይወሰድልኝ ብልዋል…😂😂😂

ከእንዲህ የአባይ ጉዳይ አብቅቷል ።በኔ ግምት አል ሲሲ ሀገራችን የኀዳሴ ግድብ ማስመረቋን ተከትሎ ከግብፅ ህዝብ ከፍተኛ የሆነ ህዝባዊ ተቃውሞ ይጠብቀዋል ተቃውሞው ደግሞ ሲሲን ስልጣን እስከ ማሳጣት ይሆናል ኢትዮዽያ ግብፅን በአለም አደባባይ ዘርራለች … ሁሌም ከፍ በይ ሀገሬ 🇪🇹🔥🇪🇹🔥🇪🇹🎊🇪🇹🎊🇪🇹

𝐁𝐑𝐄𝐀𝐊𝐈𝐍𝐆: 𝐄𝐠𝐲𝐩𝐭 𝐬𝐞𝐧𝐝𝐬 𝐥𝐞𝐭𝐭𝐞𝐫 𝐭𝐨 𝐔𝐍 𝐒𝐞𝐜𝐮𝐫𝐢𝐭𝐲 𝐂𝐨𝐮𝐧𝐜𝐢𝐥 𝐨𝐯𝐞𝐫 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚’𝐬 𝐮𝐧𝐢𝐥𝐚𝐭𝐞𝐫𝐚𝐥 𝐨𝐩𝐞𝐫𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐨𝐟 𝐆𝐄𝐑𝐃

Egypt’s Foreign Minister Badr Abdelatty on Tuesday sent a letter to the President of the UN Security Council (UNSC), stating that despite all futile attempts to grant the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) a false veneer of legitimacy, it remains a unilateral act in violation of international law and norms with no consequences affecting the legal regime of the Eastern Nile Basin.

Minister Abdelatty indicated that Ethiopia’s recent actions constitute a new breach added to a long list of its violations of international law.

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ:

Share