FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ ፋኖስ ሚዲያ ወቅታዊ ዜናዎችን፣ ተዓማኒነት ያላቸው መረጃዎች በሳል የፖለቲካ ተንታኞች አተያዮች ከኢትዮጵያና ከአለም ዙሪያ በፍጥነት ይቀርቡበታል

ኤርትራ መልስ ሰጠች‼️ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የድርድር ጥያቄ ኤርትራ መልስ ሰጥታለች፡፡ ጠቅላዩ በሳምንቱ መጀመሪያ አዲሱን መጽሀፋቸውን ባስመረቁበት ወቅት ‹‹አምስት አመት ሙሉ የቆየነው ው...
19/09/2025

ኤርትራ መልስ ሰጠች‼️

ለጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የድርድር ጥያቄ ኤርትራ መልስ ሰጥታለች፡፡

ጠቅላዩ በሳምንቱ መጀመሪያ አዲሱን መጽሀፋቸውን ባስመረቁበት ወቅት ‹‹አምስት አመት ሙሉ የቆየነው ውጊያን ለማስቀረት ነው፤ ወንድም እህቶቻችን በአስቸኳይ እራሳቸውን ለድርድር አዘጋጁ›› ብለው ነበር፡፡ ለዚህ የአብይ ንግግር ኤርትራ የመልስ ምት ሰጥታለች፡፡ ‹‹ብልጽግና ሊወረኝ እያኮበኮበ ነው›› ሲልም የድርድሩን ጥሪ ገፍቶታል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ የመደመር መንግስት የተሰኘውን አዲስ መጽሀፋቸውን ባስመረቁበት ወቅት ስለ ባህር በር ጉዳይ ንግግር ማድረጋቸው ይታወሳል፡፡ በንግግራቸውም፣ ለድርድር ተዘጋጁ፣ በፍጹም ኢትዮጵያ መውጫ መግቢያ በሯን ዝግ አይሆንም፣ ባህር በሩ ይመጣል እናሳካዋለን›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

ለዚህ የአብይ ንግግር ኤርትራ በማስታወቂያ ሚኒስትሩ በኩል እንደተለመደው የተቃውሞ መልስ ሰጥቷል፡፡

የማስታወቂያ ሚኒስትሩ አቶ የማነ በኤክስ ገፃቸው ባሰራጩት መልእከት፣ ብልጽግና ሉአላዊነታችንን ለመጣስ እያኮበኮበ ነው በማለት ከሰዋል፡፡ የብልጽግና ባለሥልጣናት ዘምተውብናል ሲሉ የወነጀሉት ሚኒስትሩ፤ የብልጽግና ባለሥልጣናት በባለቤትነት የሚቆጣጠሩት የባህር በር ለማግኘት ያላቸውን መሻት አጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በተለይም አሰብን ማስመለስ እንዳለባት ኤርትራ ከተገነጠለች ማግሥት ጀምሮ የአጀንዳነት ሚዛኑ ከፍ ዝቅ ቢልም ሲነሳ እንደነበር ይታወቃል፡፡

(FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ)

Inbox:-  #ሸርእባካችሁ ድምፅ እንሁነው የተከበሩ የፓርላማ አባል ክርስቲያን ታደለ በማረሚያ ቤት ህመማቸው ተባብሶባቸዋል፤ እንደሚታወቀው ባለፈው በመቅረዝ ሆስፒታል ቀዶ ህክምና ተደርጎላቸ...
17/09/2025

Inbox:- #ሸርእባካችሁ ድምፅ እንሁነው የተከበሩ የፓርላማ አባል ክርስቲያን ታደለ በማረሚያ ቤት ህመማቸው ተባብሶባቸዋል፤ እንደሚታወቀው ባለፈው በመቅረዝ ሆስፒታል ቀዶ ህክምና ተደርጎላቸው ህክምናውን በአግባቡ ሳይጨርሱ ወደ ቂሊንጦ መልሰው በመወሰዳቸው ህመሙ አሁን ላይ ከባድ ሁኔታ ላይ ይገኛል።

ስለዚህ መላው ኢትዮጵያዊያን እባካችሁ ድምፅ ሁኑት ይፈታ ሳይሆን በአግባቡ ህክምናውን ይከታተል ሰብዓዊ መብቱ ይከበርለት ዘንድ ፍትህ እንጠይቅለት።

ዝም አንበል በሶሻል ሚድያ #ሸር በማድረግ በመንሸራሸር ለኢትዮጵያ ሰበአዊ መብት ኮሚሽን እና ለሚመለከታቸው አካላት ይደርስ ዘንድ ተባበሩን🙏

የሚጎድልባቸው ነገር የለም #ሸር በግሩፑ በየአካውንታችሁ #ሸር አድርጉት ሚዲያ አቅም አለው

የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ በጠና ታመሙ::አዲስ አበባ፤ መስከረም 7 ቀን 2018 በእስር ላይ የሚገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ በጤና እ...
17/09/2025

የምክር ቤት አባል የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ
በጠና ታመሙ::

አዲስ አበባ፤ መስከረም 7 ቀን 2018 በእስር ላይ የሚገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ በጤና እክል ምክንያት በጠና መታመማቸውን ቤተሰቦቻቸው እና ጠበቃቸው ለቢቢሲ ተናገሩ።

ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ እንዳሉት፣ ሰኞ ዕለት ቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ውስጥ አግኝተዋቸው የነበረ ሲሆን፣ አቶ ክርስቲያን ከቅርብ ጊዜ በፊት ካደረጉት ቀዶ ሕክምና በኋላ ተገቢው ክትትል ባለማግኘታቸው ሕመማቸው እየተባባሰ መምጣቱን ገልጸዋል።

አንድ የቤተሰባቸው አባልም እንደተናገሩት፣ አቶ ክርስቲያን ከወራት በፊት በመቅረዝ ሆስፒታል ቀዶ ሕክምና ካደረጉ በኋላ፣ በቂ ክትትል ሳይደረግላቸው ወደ ማረሚያ ቤት እንዲመለሱ መደረጉ ለዚህ ሁኔታ እንደዳረጋቸው ተናግረዋል።

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄን (አብን) ወክለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል እንዲሁም በምክር ቤቱ የመንግሥት ወጪ፣ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የነበሩት አቶ ክርስቲያን፣ በአማራ

ክልል በተፈጠረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ከታወጀ በኋላ በቁጥጥር ስር ውለዋል። ከዚያም ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቶ ላለፉት ሁለት ዓመታት በእስር ላይ ይገኛሉ።

Via BBC Amharic

እኔም ክርስቲያን ታደለ ነኝ!! የመታከም መብቱ ይከበር! የሚል ህዝባዊ ንቅናቄ ተጀምሯል በንቅናቄው ከተስማሙ ሼር በማድረግ ድምፅ ይሁኑ
14/09/2025

እኔም ክርስቲያን ታደለ ነኝ!! የመታከም መብቱ ይከበር! የሚል ህዝባዊ ንቅናቄ ተጀምሯል

በንቅናቄው ከተስማሙ ሼር በማድረግ ድምፅ ይሁኑ

በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች በሙሉ እንኳን ለ2018 የዘመን መለወጫ በአል አደረሳችሁ  የሚል መልእክቴን እያስተላለፍኩ በዓሉ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆን...
10/09/2025

በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖች በሙሉ እንኳን ለ2018 የዘመን መለወጫ በአል አደረሳችሁ የሚል መልእክቴን እያስተላለፍኩ በዓሉ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።

መልካም አዲስ አመት!

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ፍቅር ያሸንፋል!
ቴዎድሮስ ካሳሁን
(ቴዲ አፍሮ)
#ላይክ #ሸር #አይረሳ

ወገኖችየጦርነት ዜና አልሰለቻችሁም? አንድ መኪና ሰው ታገተ፣ ተገደለ፣ እከሌ ታግቶ ለአጋቾች ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው የሚል ጩኸት አልሰለቻችሁም? ከክልል ክልል፣ ከከተማ ከተማ በሰላም እጦት...
10/09/2025

ወገኖች

የጦርነት ዜና አልሰለቻችሁም? አንድ መኪና ሰው ታገተ፣ ተገደለ፣ እከሌ ታግቶ ለአጋቾች ገንዘብ እየተሰበሰበ ነው የሚል ጩኸት አልሰለቻችሁም?

ከክልል ክልል፣ ከከተማ ከተማ በሰላም እጦት እንደ ልባችሁ ተንቀሳቅሳችሁ መስራት አልተቸገራችሁም? በዚህ የተነሳስ ኑሮ አልከበዳችሁም?

አቦ አዲሱ ዓመት የዚህ ሁሉ ችግር ምንጭ ደርቆ በሰላምና በፍቅር የምንኖርበት አመት ይሁንልን።

ድል በዲኘሎማሲ ትግል…🇪🇹🔥✌️ግብፅ ዛሬ ማበድ ይዛለች አል-ሲሲ ጉዳዩን ወደ ፀጥታው ም/ቤት በመውሰድ ኢትዮዽያ ላይ አለም አቀፍ  እርምጃ ይወሰድልኝ ብልዋል…😂😂😂  ከእንዲህ የአባይ ጉዳይ ...
09/09/2025

ድል በዲኘሎማሲ ትግል…🇪🇹🔥✌️

ግብፅ ዛሬ ማበድ ይዛለች አል-ሲሲ ጉዳዩን ወደ ፀጥታው ም/ቤት በመውሰድ ኢትዮዽያ ላይ አለም አቀፍ እርምጃ ይወሰድልኝ ብልዋል…😂😂😂

ከእንዲህ የአባይ ጉዳይ አብቅቷል ።በኔ ግምት አል ሲሲ ሀገራችን የኀዳሴ ግድብ ማስመረቋን ተከትሎ ከግብፅ ህዝብ ከፍተኛ የሆነ ህዝባዊ ተቃውሞ ይጠብቀዋል ተቃውሞው ደግሞ ሲሲን ስልጣን እስከ ማሳጣት ይሆናል ኢትዮዽያ ግብፅን በአለም አደባባይ ዘርራለች … ሁሌም ከፍ በይ ሀገሬ 🇪🇹🔥🇪🇹🔥🇪🇹🎊🇪🇹🎊🇪🇹

𝐁𝐑𝐄𝐀𝐊𝐈𝐍𝐆: 𝐄𝐠𝐲𝐩𝐭 𝐬𝐞𝐧𝐝𝐬 𝐥𝐞𝐭𝐭𝐞𝐫 𝐭𝐨 𝐔𝐍 𝐒𝐞𝐜𝐮𝐫𝐢𝐭𝐲 𝐂𝐨𝐮𝐧𝐜𝐢𝐥 𝐨𝐯𝐞𝐫 𝐄𝐭𝐡𝐢𝐨𝐩𝐢𝐚’𝐬 𝐮𝐧𝐢𝐥𝐚𝐭𝐞𝐫𝐚𝐥 𝐨𝐩𝐞𝐫𝐚𝐭𝐢𝐨𝐧 𝐨𝐟 𝐆𝐄𝐑𝐃

Egypt’s Foreign Minister Badr Abdelatty on Tuesday sent a letter to the President of the UN Security Council (UNSC), stating that despite all futile attempts to grant the Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) a false veneer of legitimacy, it remains a unilateral act in violation of international law and norms with no consequences affecting the legal regime of the Eastern Nile Basin.

Minister Abdelatty indicated that Ethiopia’s recent actions constitute a new breach added to a long list of its violations of international law.

ዘመናዊ ከተሞች‼️በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ከተሞች ማስተር ፕላን እየተዘጋጀ ነው ተባለ።ዘመናዊ የመኖሪያና የቱሪዝም ከተሞች ይመሰረታሉ ተብሏል።በሕዳሴው ግድብ በተፈጠረው "ንጋት" 24...
08/09/2025

ዘመናዊ ከተሞች‼️
በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ከተሞች ማስተር ፕላን እየተዘጋጀ ነው ተባለ።
ዘመናዊ የመኖሪያና የቱሪዝም ከተሞች ይመሰረታሉ ተብሏል።
በሕዳሴው ግድብ በተፈጠረው "ንጋት" 246 ኪ.ሜ ባህር ዙሪያ ለሚመሰረቱ ዘመናዊ ከተሞች ማስተር ፕላን የማዘጋጀት ሥራ መጀመሩ ተገለጸ፡፡

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ዙሪያ ለሚመሰረቱ ዘመናዊ የመኖሪያና የቱሪዝም ከተሞች ማስተር ፕላን የማዘጋጀት እንዲሁም የአሶሳ ከተማ የማስፋፊያ ፕሮጀክት ሥራ፤ 'ሲቲስ አሊያንስ' በተሰኘ ድርጅት አማካኝነት በይፋ መጀመሩን የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ አስታውቋል።

ወደፊት በአካባቢው ብዙ ከተሞች ይመሰረታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የተገለጸ ሲሆን፤ አካባቢው የዓለም አቀፍ ባለሀብቶችን ትኩረት መሳቡ ተነግሯል።

ቀደም ሲልም የኢንቨስትመንት ፈቃድ የወሰዱ አልሚዎች እንዳሉ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ የሐይቁን መሃል በተመለከተ ከፌደራል መንግሥት ጋር በትኩረት የሚሰራ መሆኑ የተጠበቀ ቢሆንም፣ ብዙ ደሴቶች በመኖራቸው ጥናት እንደሚፈልግ ተናግረዋል።
FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

Make the nation Proud ❤ 🇪🇹ይቅናሽ ሀገሬ ❤ይቅናሽ እምዬ ጦቢያ 🇪🇹
05/09/2025

Make the nation Proud ❤ 🇪🇹
ይቅናሽ ሀገሬ ❤
ይቅናሽ እምዬ ጦቢያ 🇪🇹

የቻይና ወፍ መሰል ድሮኖች ለመሰለል እየተዘጋጁ ነው ተባለቻይና ከእውነተኛ ወፎች ለመለየት እጅግ በጣም አስቸጋሪ የሆኑ፣ ሰው ሰራሽ ወፎችን የሚመስሉ አዲስ የድሮን ቴክኖሎጂ እየሰራች መሆኑ ተ...
05/09/2025

የቻይና ወፍ መሰል ድሮኖች ለመሰለል እየተዘጋጁ ነው ተባለ

ቻይና ከእውነተኛ ወፎች ለመለየት እጅግ በጣም አስቸጋሪ የሆኑ፣ ሰው ሰራሽ ወፎችን የሚመስሉ አዲስ የድሮን ቴክኖሎጂ እየሰራች መሆኑ ተገለጸ። እነዚህ ድሮኖች ክንፋቸውን በማንቀሳቀስና በተፈጥሯዊ ሁኔታ በመንሳፈፍ በቀላሉ ከእውነተኛ ወፎች ጋር ሊዋሃዱ ይችላሉ ተብሏል።

የአሜሪካ የቴክኖሎጂ ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፣ ይህ አዲስ ግኝት ለዕይታ ብቻ የተሰራ ሳይሆን፣ በዋናነት ለምስጢር ክትትልና ለመሰለል አገልግሎት እንዲውል ታስቦ ነው ተብሏል። ወደፊትም ለወታደራዊ አገልግሎትና እንደ ጦር መሳሪያ ሊያገለግሉ እንደሚችሉ መረጃዎች ያሳያሉ።

ይህ ቴክኖሎጂ የሳይንስና ቴክኖሎጂን ድንበር የገፋ ቢሆንም፣ በሌላ በኩል ደግሞ አዲስ የስጋት ስሜት ፈጥሯል። ብዙዎች ይህ ግኝት በሰማይ የምናያቸው ወፎች እንኳን እውነተኛ ስለመሆናቸው እንድንጠራጠር የሚያደርግ እና የዓለማችንን ገጽታ የሚቀይር እንደሆነ እየገለጹ ነው።
FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

ኔይማር ከባለሀብቱ ውርስ ድርሶታል.....አንድ ብራዚላዊ ቢሊየነር ለ33 አመቱ ኮከብ ኔይማር ሀብቱን እንዳወረሰው ዴሊሜል አስነብቧል::በብራዚል የሚገኘው ይህ ቢሊየነር ያለውን ሀብት ኔይማር ...
04/09/2025

ኔይማር ከባለሀብቱ ውርስ ድርሶታል.....

አንድ ብራዚላዊ ቢሊየነር ለ33 አመቱ ኮከብ ኔይማር ሀብቱን እንዳወረሰው ዴሊሜል አስነብቧል::

በብራዚል የሚገኘው ይህ ቢሊየነር
ያለውን ሀብት ኔይማር እንዲወርሰው ተናዞ መሞቱ ተገልጿል።

ባለሀብቱ አጠቃላይ ያለው ሀብት 1.2 ቢልዮን ዶላር እንደሚገመት የተነገረ ሲሆን ትዳርም ይሁን ልጅም እንደሌለው ተነግሯል::

እስካሁን ድረስ ኔይማር በጉዳዩ ላይ አስተያየት ከመስጠት ተቆጥቧል::

ግለሰቡ ለኔይማር ማውረስ የፈለገበት ጉዳይ ለእሱ ያለውን ክብር እና አድናቆት ለመግለጽ እንደሆነ ታውቋል::

ፍርድቤቱም ነገሮችን ካጣራ በሗላ ውርሱን ለተጨዋቹ ያስተላልፋል ተብሎ ይጠበቃል::
FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ:

Share