FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ ፋኖስ ሚዲያ ወቅታዊ ዜናዎችን፣ ተዓማኒነት ያላቸው መረጃዎች በሳል የፖለቲካ ተንታኞች አተያዮች ከኢትዮጵያና ከአለም ዙሪያ በፍጥነት ይቀርቡበታል

ጋና በሄሊኮፕተር አደጋ መሪዎቿን አጣች!‎‎በጋና የአየር ሃይል ሄሊኮፕተር ተከስክሶ የሀገሪቱ ቁልፍ ባለስልጣናት መሞታቸው ተሰማ ።‎‎የጋና ኮሚኒኬሽን እንደገለፀው ከሆነ ረቡዕ ከጠዋቱ 9፡00...
07/08/2025

ጋና በሄሊኮፕተር አደጋ መሪዎቿን አጣች!

‎በጋና የአየር ሃይል ሄሊኮፕተር ተከስክሶ የሀገሪቱ ቁልፍ ባለስልጣናት መሞታቸው ተሰማ ።

‎የጋና ኮሚኒኬሽን እንደገለፀው ከሆነ ረቡዕ ከጠዋቱ 9፡00 ሰዓት ከአክራ ተነስቶ ከዋና ከተማው በስተሰሜን ምዕራብ ወደምትገኘው ወደ ኦቡአሲ ከተማ በማምራት ላይ የነበረ ሶስት የበረራ ሰራተኞችን እና አምስት የሀገሪቱን ከፍተኛ ባለስልጣናት የያዘ ዜድ-9 ሄሊኮፕተር
‎በገጠመው የመከስከስ አደጋ በአውሮፕላኑ ውስጥ የነበሩ ሁሉም ሰወች ህይወት ማለፉን ገልጿል ።

‎በአደጋዉም የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር ኤድዋርድ ኦማን ቦአማህ እና የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሩ ኢብራሂም ሙርታላ መሐመድ ከብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ኮንግረስ ገዥ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር፣ የብሔራዊ ደህንነት ከፍተኛ አማካሪ እና የበረራ አባላት በጥቅሉ አስር ሰዎች ህይወታቸው ወዲያውኑ ማለፉን አረጋግጧል ።

‎የሄሊኮፕተሯ ስብርባሪ በአሻንቲ አዳንሲ አካባቢ መገኘቱን የገለፀው መግለጫው የአደጋው መንስኤ እስካሁን ያልታወቀ ሲሆን፥ ወታደራዊ ሃይሉም ምርመራ እየተካሄደ ነው ብሏል።

‎ከአደጋዉ በኋላ ባለስላጣናቱ በቦአማህ መኖሪያ እና በፓርቲው ዋና ፅህፈት ቤት የተሰበሰቡ ሲሆን የጋና መንግስት አደጋውን “ሀገራዊ አሳዛኝ” ሲል ገልጿል።

‎"ፕሬዝዳንቱ እና መንግስት ለጓዶቻችን ቤተሰቦች እና ለሀገር በማገልገል ላይ ለሞቱት አገልጋዮች ሀዘናችንን እና ሀዘናችንን እንገልፃለን" ሲሉ የማሃማ ዋና ሰራተኛ ጁሊየስ ዲብራህ ተናግረዋል ።

‎በሁሉም የመንግስትና የግል መስርያ ቤቶች ባንዲራዎች ዝቅ ብለዉ እንዲውለበለቡ ያሉት ፕሬዚዳንቱ በበኩላቸው ማሃማ የዕለቱን ይፋዊ እንቅስቃሴያቸውን መሰረዛቸውን ተናግረዋል።

‎የረቡዕ አደጋ ከአስር አመታት በላይ በጋና ካጋጠሙት አስከፊ የአየር አደጋዎች አንዱ ነው።

‎ለዘገባው ፍራንስ 24 ቢቢሲ አፍሪካ ኒዉስን ተጠቅመናል ።
FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

‎በኢትዮጵያዊቷ እህታችን የተፈፀመዉን ግፍ በማጋለጡ‎ የሳውዲ ደህንነት ክትትል እያደረገበት ይገኛል !‎‎ቪዲዮ የቀረጸው ወንድም በደህንነት ይፈለጋል ‎ግፍን ማጋለጥ ሊሸለም እንጅ ሊታሰር አይ...
04/08/2025

‎በኢትዮጵያዊቷ እህታችን የተፈፀመዉን ግፍ በማጋለጡ
‎ የሳውዲ ደህንነት ክትትል እያደረገበት ይገኛል !

‎ቪዲዮ የቀረጸው ወንድም በደህንነት ይፈለጋል
‎ግፍን ማጋለጥ ሊሸለም እንጅ ሊታሰር አይገባም የኢትዮጵያ መንግሦት ከጎኑ ሊቆም ይገባል

‎============================
‎ የዛሬ አንድ ወር አካባቢ የብዙዎቻችን ልብ የሰበረ ድርጊት በአንዲት ኢትዮጵያ ላይ ሲፈጽም በቪዲዮ የተደገፈ የመብት ገፈፋ ተሰራጨ ። ልብ ሰባሪውን ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ተመልክተን " ፍትህ ለእህታችን " ብለን ሁነኛ አጀንዳ አድርገነው በዳይ ተፈበዳይ ሪያድ ላይ በሳውዲ ፖሊስ ክትትል መገኘታቸው ይታወሳል።

‎ ኢትዮጵያዊቷ እህት መካ ሙሐመድ በሳውዲ ሪያድ በአሰሪዎቿ በአውራ ጎዳና እየተጎተተች ወደ መኪና ሲያስገቧት ድንገት ደርሶ ቪዲዮ የቀረጸው ወደ መኪና ወንድም ከሶስት ቀናት ወዲህ በሳውዲ አረቢያ ሲቢል ለባሽ ደህንነቶች እየተፈለገ ስለመሆኑ ጭብጥ የሆነ መረጃ ደርሶኛል ። በወገኑ ላይ ግፍ ሲፈጸም አላስችል ብሎት እህታችን ያለችበት ሁኔታ እንዲታወቅ በዳዮቿ ተፈለገው እንዲያዙ ትልቁን ኃላፊነት የተወጣውን ወንድማችን ለመያዝ የተሰማሩ ሲቪል የለበሱ ስውር የደህንነት አባላት የሚሰራበትን ኩባንያን ድረስ ሄደው እንደነበር የመረጃ ምንጮቸ አስረድተውኛል ። ክትትል ያደረጉ ደህንነቶች ስ ተፈላጊው ወንድም በቂ መረጃ ማሰባሰባቸው ሪፖርት ስለ መቅረቡ ለፍትህ የቆሙ ለጉዳዩ ቅርብ ያላቸዎ የሳውዲ ዜጋ አሾልከው ካደረሱኝ መረጃ ለመረዳት ችያለሁ ።

‎ ይህ በእንዲህ እንዳለ የሪያድና ኢንባሲና የሪያድ ኮሚኒቲ ስለ ደህነት ክትትሉ ሪፖርት እንደደረሳቸው ከሪያድ ኢንባሲ ምንጮቸ አረጋግጫለሀ ። ወደ ተፈላጊው ወንድማችን ስልክ የ።ወልኩ ቢሆንም ስልኩ እየጠራ ባለመነሳቱ ከእሱ በኩል ስላለበት ሁኔታ ማወቅ አልቻልኩም ። የተፈላጊውን ወንድም አንድ የቅርብ ጓደኛ በስልክ አግኝቸው በደህንነት ስለመፈለጉ መረጃ የደረሰው ቢሆንም ድንጋጤ እንዳላየበት አስረድቶኛል ። " ወንጀል ሲፈጸም እንጅ ወንደል አልፈጸምኩምና አላህ ለክፉ አይሰጠኝም ። "
‎ብሎ ከአንድ ሰዓት በፊት እንዳጫዘተው ነግሮኘኛል።

‎ ከወንድማችን ጎን እንቁም
‎======================
‎ ወንድማችን አስፈላጊውን ጥበቃ በማድረግ ረገድ ቸውጭ ጉዳይ ሚር እና የሪያድ ኢንባሲ ሊደረግለት ከሚችለዎ አደጋ አስፈላጊውን ጥበቃ ሊደረግለት ይገባል እላለሁ ። ስለ ደረሰኝ ጭብጥ ሁነኛ መረጃ ዘርዘር አድርጌ በነገው የማለዳ ወጌ የማቀርብ ይሆናል።

‎ቸር ያሸማን ...

‎FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ
ጉርሻ page
Human Rights Commission
Abiy Ahmed Ali
‎ሐምሌ 28 ቀን 2017 ዓም

የሀዘን መግለጫ💔በየመን በደረሰው የመርከብ መስመጥ ለሞቱት ከ68 በላይ ኢትዮጵያውያን ሞት የተሰማንን ሀዘን እንገልፃለን!''ህገወጥ ስደት ስናስብ የነገ ተስፋችንን እናስብ''| FANOS MED...
04/08/2025

የሀዘን መግለጫ💔

በየመን በደረሰው የመርከብ መስመጥ ለሞቱት ከ68 በላይ ኢትዮጵያውያን ሞት የተሰማንን ሀዘን እንገልፃለን!

''ህገወጥ ስደት ስናስብ የነገ ተስፋችንን እናስብ''| FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ ሐምሌ-28-2017🕊

(ዘ-ሐበሻ ዜና) ታሪኩ ሁለት ገጽታዎች አሉት። በአንደኛው ገጽታ፣ ዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም.፣ የአዲስ አበባው ሚሊኒየም አዳራሽ በደማቅ መብራቶችና በሺዎች በሚቆጠሩ ሰዎች ተሞልቷል።...
02/08/2025

(ዘ-ሐበሻ ዜና) ታሪኩ ሁለት ገጽታዎች አሉት። በአንደኛው ገጽታ፣ ዛሬ ሐምሌ 26 ቀን 2017 ዓ.ም.፣ የአዲስ አበባው ሚሊኒየም አዳራሽ በደማቅ መብራቶችና በሺዎች በሚቆጠሩ ሰዎች ተሞልቷል። ፓስተር ትዝታው ሳሙኤል "ለኢየሱስ" በተሰኘው ታላቅ "የአምልኮ ድግስ" ላይ መድረኩን ተቆጣጥሮታል። በሌላኛው ገጽታ ደግሞ፣ የፌደራል ፖሊስ፣ ይኸው መድረክ ላይ በይፋ የሚታየውን ግለሰብ "ፈልጌ አጣሁት" በማለት እጁን ማጣጣፉን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስታውቃለች።

🔴 የህግ ጥያቄ እና የእግድ ትዕዛዝ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የህግ ክፍል ኃላፊ የሆኑት አፈ መምህር አባ ገብረሥላሴ ጌትነት ከማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ፣ ቤተክርስቲያኗ በአቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ መመስረቷንና ማስረጃዎችንም አያይዛ ማቅረቧን ገልጸዋል።

ይህንን ክስ ተከትሎም፣ የፍትህ አካላት ግለሰቡ ከሀገር እንዳይወጣ እግድ እንደጣሉበት የገለጹ ሲሆን፣ በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውልም ትዕዛዝ መሰጠቱን አፈ መምህሩ አስረድተዋል።

🔴 የፖሊስ እንቆቅልሽ የሆነው ምላሽ

የቤተክርስቲያኗ የህግ ክፍል ኃላፊ እንደሚሉት፣ ይህ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ቢኖርም፣ የፌደራል ፖሊስ የሰጠው ምላሽ አስገራሚ ነበር። "ፖሊስ፣ ግለሰቡን ለመያዝ እየፈለገው እንደሆነና በዚህ የፍለጋ ተግባር ላይ የትኛውም ኢትዮጵያዊ ጥቆማ እንዲያደርግለት ጥሪ አቅርቧል" ብለዋል አፈ መምህሩ።

ይህ የፖሊስ ምላሽ፣ በማህበራዊ ሚዲያ እና በአስተያየት ሰጪዎች ዘንድ ከፍተኛ መነጋገሪያ ሆኗል። ምክንያቱም፣ "የጠፋው" ግለሰብ፣ ለወራት ያህል በሚዲያዎች በግላጭ ሲቀሰቅስበት የነበረውንና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የታደሙበትን ዝግጅት፣ በሀገሪቱ ትልቁ አዳራሽ እያካሄደ ባለበት ወቅት፣ "ፈልጌ አጣሁት" መባሉ እጅግ አስገራሚ ሆኗል።

አስተያየት ሰጪዎች እንደሚሉት፣ አንድ ሰው በይፋ በሚታወቅበት ቦታ፣ በአደባባይ መድረክ ላይ እያለ፣ "የት እንዳለ አላውቅም" መባሉ፣ የህግ የበላይነትን የማስከበር ሂደቱን ጥያቄ ውስጥ የሚከት ነው።

ይህ ዜና እየተሰራጨ ባለበት ወቅት፣ በሚሊኒየም አዳራሽ መድረክ ላይ ያለው ፓስተር እና እርሱን "እየፈለገ ያለው" ፖሊስ ጉዳይ፣ የብዙዎችን ትኩረት የሳበና በቀጣይ ምን ሊፈጠር ይችላል የሚል ጉጉትን የፈጠረ አነጋጋሪ ክስተት ሆኖ ቀጥሏል።
FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

የሩሲያን ምድር በድሮን እያደባየሁት ነዉ ! /ዩክሬን /‎‎ዩክሬን የሩሲያን ቁልፍ ስፍራዎች ላይ መብረቃዊ ጥቃት መድረሷን ተናገረች ።‎‎የዩክሬን ጦር ዛሬ ቅዳሜ ዕለት ባወጣው መግለጫ በሩሲያ...
02/08/2025

የሩሲያን ምድር በድሮን እያደባየሁት ነዉ ! /ዩክሬን /

‎ዩክሬን የሩሲያን ቁልፍ ስፍራዎች ላይ መብረቃዊ ጥቃት መድረሷን ተናገረች ።

‎የዩክሬን ጦር ዛሬ ቅዳሜ ዕለት ባወጣው መግለጫ በሩሲያ ውስጥ የነዳጅ ማምረቻዎችን ዋና ዋና ማጣሪያ ፋብሪካን እንዲሁም የድሮኖችን እና የኤሌክትሮኒክስ ፋብሪካን ወታደራዊ አየር ማረፊያን ጨምሮ መምታቱን ተናግሯል።

‎በቴሌግራም ላይ በሰጠው መግለጫ የዩክሬን ሰው አልባ ሲስተም ሃይሎች ከሞስኮ በስተደቡብ ምስራቅ 180 ኪሜ (110 ማይል) ርቀት ላይ በምትገኘው ሪያዛን የሚገኘውን የነዳጅ ማጣሪያ በመምታቱ በግቢው ላይ የእሳት ቃጠሎ ዳርገዋል ብሏል።

‎መግለጫው በሰሜን ምስራቅ ዩክሬን በሚያዋስነው በቮሮኔዝ ክልል የሚገኘው የአናኔፍቴፕሮዶክት ዘይት ማከማቻ ቦታ መመታቱን ቢገልፅም ተቋማቱ እንዴት እንደተመቱ ባይገልፅም ከዚህ በተጨማሪ የዩክሬን ኤስቢዩ የስለላ ድርጅት ሰው አልባ አውሮፕላኖቹ በዩክሬን ዒላማዎች ላይ የረዥም ርቀት ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ለማጥቃት ያገለገለውን የሩሲያ ፕሪሞርስኮ-አክታርስክ ወታደራዊ አየር መንገድን መምታቱን አስታውቋል።

‎የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር በየእለቱ በሚያወጣዉ ዘገባ እንዳስታወቀው የመከላከያ ክፍሎቹ በአንድ ጀምበር 338 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መውደቃቸውን አስታውቋል።

‎ከዚህም በተጨማሪ በዩክሬን ምስራቃዊ ጦር ግንባር ላይ ቅዳሜ ዕለት የሩስያ ጦር እየገሰገሰ መሆኑን የገለፀዉ የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር በዶኔትስክ ክልል የሚገኘውን ኦሌክሳንድሮ-ካሊኖቭን መንደር መያዙን አስታውቋል።
ሲል የዘገበው ሮይተርስ ነዉ ።

‎FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ

የሀምሣ አመታ ባለዉለታ ናትና እናመሰግናለን !በሃይቁ ላይ ለበርካታ ዓመታት እንዳሻት ሁናለች ። ከባህር ዳር ተነስታ ደቅ፣ ቁንዝላ፣ ደልጊ፣ እሰይ ደብር፣ዘጌ እና ጎርጎራ ወደሚባሉ መዳረሻዎች...
02/08/2025

የሀምሣ አመታ ባለዉለታ ናትና እናመሰግናለን !

በሃይቁ ላይ ለበርካታ ዓመታት እንዳሻት ሁናለች ። ከባህር ዳር ተነስታ ደቅ፣ ቁንዝላ፣ ደልጊ፣ እሰይ ደብር፣ዘጌ እና ጎርጎራ ወደሚባሉ መዳረሻዎች መንገደኞችን አጓጉዛለች።

‎ሀምሳ ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ በጣና ሀይቅ ያገለገለችው የጣናነሽ ዕድሜዋን እና አበርክቶዋን የተመለከቱት ነዋሪዎች "የጣና-አድባር" ይሏታል የጣናነሽ ጀልባን።

‎የጣናነሽ በ1957 ዓ.ም በጀርመን ሀገር እንደተሰራችና በ1960 ዓ.ም መጀመሪያ ወደ ሀገር ወስጥ እንደገባች በኢትዮጵያ እንደተገጣጠመች ይነገራል።
‎ከ1960 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ዓመታት ያህል መኖሪያዋ እና እንቅስቃሴዋ አርባ-ምንጭ ከተማ እንደነበር ታሪኳ ይገልጻል።

‎በወቅቱ ግዙፍ የሆነችውን የጣናነሽ አርባ ምንጭ ያለው የውሃ መጠን ማንቀሳቀስ ባለመቻሉ ከጣና ሀይቅ አንዲት አነስተኛ ተመሳሳይ ስያሜ ያላት የጣናነሽ የምትባል ጀልባ ወደ አርባ ምንጭ ተልካ በምትኩ የጣናነሽ ከሰባት ተቆራርጣ ወደ ጣና ሀይቅ መጣች።

‎በ1970 ዓ.ም ከሰባት ተቆራርጣ የመጣችው የጣናነሽ በጣና ሀይቅ ጎርጎራ ወደብ በነበረው ትልቅ “ወርክሾፕ” ተገጣጥማ አገልግሎት መስጠት ጀመረች።( በወቅቱ በጎርጎራ በተቋቋመው ንጋት እና ሌሎች በተሰሩበት የጀልባ ጥገናና መገጣጠሚያ ነበር )
‎እንዲህ የተገጣጠመችዉ የጣናነሽ በጣና ሀይቅ ላይ በሰጠችው አገልግሎት ለበርካታ ዓመታት የውጭ ሀገር ካፒቴኖች እንደነበሯት ይወሳል።

‎የጣናነሽ አንድ መቶ ቶን (ወደ 90,718.5 ኪ.ግ) የምትመዝን ስትሆን ይህም ጣና ኃይቅ ላይ ሊነሳ የሚችል ማዕበል በቀላሉ አያንቀሳቅሳትም።

‎በሀይቁ ካሉ ጀልባዎች ግዙፏ የጣናነሽ 27 ሜትር ስፋት እና 8 ሜትር ቁመት ሲኖራት አራት መቶ ሰው እና ስምንት መቶ ኩንታል የመጫን አቅም ያላት ሲሆን ዕቃ ሳትጭን እስከ አንድ ሺህ ሰው የመጫን አቅም አላት ።

‎ የጣናነሽ ባለሁለት ፎቅ ቁመና ሲኖራት፣ በሁለተኛው ፎቅ እየተዝናና መሄድ የፈለገ መንገደኛ ያለምንም ተጨማሪ ክፍያ መጓጓዝ የሚችልበት ክፍል አላት። በውስጧም ሁለት መፀዳጃ-ቤቶች እና የሠራተኞች ማደሪያ መኝታ ክፍሎች ይዛለች።

‎ ወደ ጀልባዋ መሾፈሪያ ክፍል ስንዘልቅ ሁለት መሪ ያላት ሲሆን፤ ሦስት ሰዎችን አደላድላ የምታስቀምጥበት ቦታን ይዛለች። ታሪካዊቷ ጀልባ ገመድ አልባ ስልክ እና የጂፒኤስ መሳሪያም ተገጥሞላታል። በተጨማሪም ለመንገደኞች የሻይ ቡና መስተንግዶ የምትሰጥበት ካፌም በዉስጧ ይገኛሉ ።

‎የጣናነሽ በትልቁ የጣና ሀይቅ ላለፉት 50 ዓመታት ተመላልሳበታለች። በሃይቁ ላይ ለበርካታ ዓመታት ከባህር ዳር ተነስታ ደቅ፣ ቁንዝላ፣ ደልጊ፣ እሰይ ደብር ፣ዘጌ እና ጎርጎራ ወደሚባሉ መዳረሻዎች መንገደኞችን አጓጉዛለች።
‎የጣናነሽ በጉዞዋ በጣና ሀይቅ የሚገኙ ሰባት ወደቦችን ታዳርሳለች።

‎ ዘወትር መነሻዋን ከባህርዳር ወደብ በለሊት አድርጋ ወደ ዘጌ ታቀናለች። በታሪካዊቷ ዘጌ ከተማ ስትደርስ መንገደኛ እና የጫነችውን ዕቃ ታራግፋለች። ጉዞዋን ቀጥላ መዳረሻዋን ወደ ደቅ-ደሴት ታደርጋለች በደቅ ደሴት ለራሷም ለመንገደኞቿም መጠነኛ እረፍት ትሰጣለች። የጣናነሽ መንገዷን ቀጥላ ምሽት ላይ አዳሯን ቁንዝላ ላይ ታደርጋለች። ደግም በንጋት ከቁንዝላ ተነስታ ሁለት መዳረሻዎችን ካለፈች በኋላ በመጨረሻ ከበርበራ ወደብ ተነስታ ወደ ቤቷ ውቢቱ ባህርዳር ትመለሳለች።

‎የጣናነሽ ረጅሙ የጉዞ መዳረሻዋ በበርበሬ ምርት የሚታወቀው ደልጊ ሲሆን እዚያ ለመድረስ ግማሽ-ቀን ይፈጅባታል። ደልጌ ስደርስም ረጅም መልህቋን ትጥላለች።

‎የጣናነሽ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ካፒቴን አቶ ስራው አስፋው ይባላሉ።

በጣና ነሽ 2 ላይ የተሰራውን የፕሮፖጋንዳ ስራ አይታችሁ ብልፅግና ምን አይነት ሀይል እንደሆነ መረዳት ይቻላል። አዲት አሮጌ ጀልባን ለማስገባት (ለመገጣጠም አይደለም ፣ ከ45 ዓመት በፊት በ...
01/08/2025

በጣና ነሽ 2 ላይ የተሰራውን የፕሮፖጋንዳ ስራ አይታችሁ ብልፅግና ምን አይነት ሀይል እንደሆነ መረዳት ይቻላል።

አዲት አሮጌ ጀልባን ለማስገባት (ለመገጣጠም አይደለም ፣ ከ45 ዓመት በፊት በባህር ዳር የተገጣጠመችው ጣና ነሽ አንድን ልብ ይሏል ) የተሰራው ፕሮፖጋንዳና ህዝብን የማታለል ምንጩ የአብይና አዕምሮ ነው።

ይሄ ሀይል የኢትዮጵያ አየር መንገድን ቢመሰረት ኑሮ ፣ የህዳሴ ግድብ ግንባታን ቢያስጀምር ኑሮ ፣ ከአዲስ አበባ መተማ ፣ ከአዲስ አበባ ዛላንበሳ ፣ ከአዲስ አበባ ጋምቤላ ፣ ከአዲስ አበባ ሞያሌ ፣ ከአዲስ አበባ ቶጎ ውጫሌ አስፓልት ቢሰራ ...ወይም የመቀለን ፣የባህር ዳር፣ የሀዋሳን የላሊበላን ፣ የጎንደርን ወዘተ ኤርፖርትና ዩኒቨርሲቲዎች ቢገነባ ኑሮ... ጥቁር አንበሳይ ወይም ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታልን ወዘተ ቢገነባ ኑሮ ምን ያደርግ ነበር?
ኢትዮጵያውያንን ምን ያደርጋቸው ነበር?

ሳስሰበው ይጨንቀኛል😀
Alamirew

የዛሬ ሳምንት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ኮከብ ተጫዋች የነበረው አለልኝ አዘነን የገ*ደሉ 16 አመት ነበር የተፈረደባቸው። ከእንጦጦ ፓርክ የመብራት ገመድ የሰረቁ ደግሞ 23 አመታት ተፈርዶባቸ...
31/07/2025

የዛሬ ሳምንት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ኮከብ ተጫዋች የነበረው አለልኝ አዘነን የገ*ደሉ 16 አመት ነበር የተፈረደባቸው። ከእንጦጦ ፓርክ የመብራት ገመድ የሰረቁ ደግሞ 23 አመታት ተፈርዶባቸዋል።

እኛ ሳናውቅ የሰው ነብስ ማጥ*ፋ*ት ... የኮሪደር ልማት ማበላሸት የወንጀል መቅጫ አንቀፃቸው ተቀያየረ እንዴ 🤔 ... ወዴት እየሄድን ነው ወገን ...

በረሮዎችን ለወታደራዊ ስለላ #ቢዝነስሚዲያ l በረሮዎችን ለወታደራዊ ስለላ ለማሰማራት ምርምር እያደረገ ያለው የጀርመን ኩባንያ ምርምሩን ወደማጠናቀቁ መቃረቡን ይፋ አድርጓል።ስዋርም ባዮታክቲክ...
27/07/2025

በረሮዎችን ለወታደራዊ ስለላ

#ቢዝነስሚዲያ l በረሮዎችን ለወታደራዊ ስለላ ለማሰማራት ምርምር እያደረገ ያለው የጀርመን ኩባንያ ምርምሩን ወደማጠናቀቁ መቃረቡን ይፋ አድርጓል።

ስዋርም ባዮታክቲክ የተባለውና ከጀርመን መንግሥት ወታደራዊ የቴክኖሎጂ ተቋም ጋር በቅርበት የሚሰራው ኩባንያ በበረሮዎች ላይ ጥቃቅን ካሜራዎች በመግጠምና ወደ ወታደራዊ ስፍራዎች በህብረት ወይም በተናጠል አስርጎ በማስገባት ወቅታዊ መረጃዎችን እንዲልኩ ለማድረግ መቻሉን አስታውቋል።

ከፍተኛ ወጪ ተመድቦ ሲካሄድ የነበረው ይህ ምርምር በበረሮዎች ላይ ምስጢራዊና ደህንነቱ የተጠበቀ ሊጠለፍ የማይችል መገናኛ መሳሪያ እንዲሁም ትናንሽ ዘመናዊ ካሜራ በመግጠም በርቀት ሆኖ በመቆጣጠርና በመምራት የስለላ ድሮን ማሰማራት ከማይቻልባቸው ቦታዎች መረጃዎችን ለማግኘት ያስችላል ተብሏል።

በቅርቡም ምርምሩ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቆ ወደ ተግባር እንደሚገባ የኩባንያውን ምንጮች ዋቢ በማድረግ ሮይተርስ ዘግቧል።

ይሄ ህዝብ ይጫወታል አይገልፀውም 🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣comment ተጨፋጨፉ አሏቸሁ
09/07/2025

ይሄ ህዝብ ይጫወታል አይገልፀውም 🤣🤣🤣🤣🤣🤣🤣
comment ተጨፋጨፉ አሏቸሁ

ኢራን ጥቃቱን አስቀድማ ለአሜሪካ ማሳወቋ ታወቀ!!መካከለኛው ምስራቅ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ባለበት በአሁኑ ሰዓት፣ ኢራን በአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ ጥቃት ከመፈጸሟ ከሰዓታት በፊት በሁለት የተ...
23/06/2025

ኢራን ጥቃቱን አስቀድማ ለአሜሪካ ማሳወቋ ታወቀ!!

መካከለኛው ምስራቅ በከፍተኛ ውጥረት ውስጥ ባለበት በአሁኑ ሰዓት፣ ኢራን በአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ ጥቃት ከመፈጸሟ ከሰዓታት በፊት በሁለት የተለያዩ ዲፕሎማሲያዊ መስመሮች ለአሜሪካ ማሳወቋ ተገለጸ። ይህ አስገራሚ መረጃ የወጣው፣ እስራኤል በበኩሏ በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ላይ ከግጭቱ መጀመር ወዲህ ትልቁን የአየር ጥቃት መፈጸሟን ካስታወቀች በኋላ ነው።

የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፣ ኢራን ሚሳኤሎቿን ከመተኮሷ በፊት ማስጠንቀቂያ በመስጠቷ በጦር ሰፈሩ ውስጥ የነበሩ የኳታር እና የውጭ ሀገር ወታደሮች አስቀድመው ለቀው እንዲወጡ ተደርጓል። የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር (ፔንታጎን) በበኩሉ፣ በኢራን ጥቃት በአሜሪካ ወታደሮች ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰ አረጋግጧል። ይህም የኢራን ጥቃት የሰው ህይወት ከማጥፋት ይልቅ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ለማስተላለፍ ያለመ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት እንዲያጭር አድርጓል።

ሲኤንኤን (CNN) የፔንታጎን ቃል አቀባይን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፣ ኢራን በአል-ኡደይድ ጦር ሰፈር ላይ ጥቃት የፈጸመችው መካከለኛ እና አጭር ርቀት ተምዘግዛጊ ሚሳኤሎችን (ballistic missiles) በመጠቀም ነው። የኢራን የጸጥታው ቢሮ ጥቃቱ "ስኬታማ" እንደነበር ያምናል ሲል አስታውቋል። ይህን ተከትሎም በኢራን ዋና ከተማ ቴህራን ውስጥ ህዝቡ ደስታውን ሲገልጽ የሚያሳዩ እና የሚሳኤል ማስወንጨፉን የሚያሳዩ ቪዲዮዎች በማኅበራዊ ሚዲያ ተሰራጭተዋል።

ይሁን እንጂ፣ የኢራን ጥቃት ጉዳት አለማድረሱ የፈጠረው ጊዜያዊ የመረጋጋት ስሜት በፍጥነት ተቀይሯል። የእስራኤል መከላከያ ሠራዊት (IDF)፣ ከሰዓታት በፊት በቴህራን ከተማ በሚገኙ ኢላማዎች ላይ "ከግጭቱ መጀመሪያ አንስቶ ትልቁን ተከታታይ ጥቃት" መፈጸሙን አስታውቋል። ይህ የእስራኤል እርምጃ፣ ግጭቱን ወደ አዲስና ከፋ ምዕራፍ ያሸጋገረው ሲሆን፣ የኢራን ቀጣይ ምላሽ ምን ሊሆን ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት ፈጥሯል።

የግጭቱ መባባስ በመላው መካከለኛው ምስራቅ ከፍተኛ መደናገጥን ፈጥሯል። የኢራንን ጥቃት ተከትሎ ኢራቅ፣ ባህሬን ፣ ዩኤይ ኢ እና ኩዌት የአየር ክልላቸውን ሙሉ በሙሉ ዘግተዋል። የሩሲያ የአቪዬሽን ባለሥልጣን (Rosaviatsia) በበኩሉ፣ አየር መንገዶች በእስራኤል፣ በዮርዳኖስ፣ በኢራቅ፣ በኢራን እና በኳታር የአየር ክልል እንዳይጠቀሙ ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላልፏል።

በአሁኑ ሰዓት፣ ኢራን የሰጠችው ቅድመ ማስጠንቀቂያ ሊከፍት ይችል የነበረው የመነጋገሪያ በር በእስራኤል ከባድ የአጸፋ ጥቃት የተዘጋ ይመስላል። የቀጠናው የአየር ክልል በመዘጋቱና የጥቃትና የመልሶ ማጥቃት ዑደቱ ከቁጥጥር ውጪ በሆነ መንገድ እየተሽከረከረ በመሆኑ፣ መላው ዓለም ቀጥሎ የሚመጣውን ክስተት በከፍተኛ ስጋትና ጭንቀት እየተከታተለ ይገኛል።

የ13 ዓመት ልጅ ከመደብር ዳቦ ሲሠርቅ እጅ ከፍንጅ ተያዘ። ከተያዘበት ሊያመልጥ ሲሞክር የመደብሩ መደርደሪያ ወድቆ ተሰበረ።ዳኛው የወንጀሉን ዝርዝር ሰማና ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀው!👨‍⚖️"...
26/12/2024

የ13 ዓመት ልጅ ከመደብር ዳቦ ሲሠርቅ እጅ ከፍንጅ ተያዘ። ከተያዘበት ሊያመልጥ ሲሞክር የመደብሩ መደርደሪያ ወድቆ ተሰበረ።
ዳኛው የወንጀሉን ዝርዝር ሰማና ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀው!
👨‍⚖️"የሆነ ነገር፥ ማለትም ዳቦ ሰርቀህ ነበር?"
🧑‍🦲ልጁ - (እያፈረ) "አዎን ሰርቄአለሁ"
👨‍⚖️ዳኛው - "ለምን?"
🧑‍🦲ልጁ - "አስፈልጎኝ"
🧑‍⚖ዳኛው - "መግዛት አትችልም ነበር?"
🧑‍🦲ልጁ - "ገንዘብ አልነበረኝም"
🧑‍⚖ዳኛው - "ከቤተሰብህ ለምን አትወስድም?"
🧑‍🦲ልጁ - "እናት ብቻ ናት ያለችኝ፥ እሷም በጠና ታምማ እቤት ተኝታለች"
🧑‍⚖ዳኛው - "ምንም ስራ የለህም?"
🧑‍🦲ልጁ - "መኪና እጥበት እሰራ ነበር፥ ነገር ግን እናቴን ለማስታመም አንድ ቀን ከስራ ስቀር አባረሩኝ"
🧑‍⚖ዳኛው - "ሌሎች እንዲረዱ አልጠየቅኽም?"
🧑‍🦲ልጁ - "በጧት ነው ከቤት የወጣሁ፥ እንዲረዱኝ 50 የሚሆኑ ሰዎች ጋ ሄጄ ነበር፤ አንድም የሚረዳኝ ሰው ግን አላገኘሁም፤ በቃ መጨረሻ ላይ ይህንን መጥፎ ውሳኔ ወሰንሁ"።
ጥያቄው ሲጠናቀቅ #ዳኛው ውሳኔ ማስተላለፍ ጀመረ።
#ውሳኔ🧑‍⚖
"ዳቦ መስረቅ፥ በተለይ የተራበ ልጅ ዳቦ መስረቅ እጅግ በጣም አሳፋሪ ወንጀል ነው፤ እናም እኛ ሁላችንም የዚህ ወንጀል ተጠያቂ ነን። እኔን ጨምሮ በዚህ ቤት ውስጥ ያላችሁ በሙሉ ወንጀለኛና ተጠያቂ ነን። ስለዚህ እያንዳንዱ በዚህ ችሎት ላይ የታደመና እዚህ ቤት ውስጥ ያለ አስር (10) አስር ዶላር$ እንዲከፍል ፍርድ ቤቱ ወስኗል።
ማንም ሰው ሳይከፍል መውጣት አይችልም በማለት
👉አስር ዶለር ከኪሱ አውጥቶ ወረቀት ላይ መመዝገብ ጀመረ።
👉በተጨማሪ ዳቦ ቤቱ የተራበ ልጅ ለፖሊስ አሳልፎ በመስጠቱ 1000 ዶላር እንዲከፍል ውሳኔ አስተላለፈ።
👉ይህ በ24 ሰአት ውስጥ ካልተፈጸመ ፍርድ ቤቱ ዳቦ መደብሩን ያሳሽጋል።
👉ፖሊስም የተራበ ልጅ ፍርድ ቤት በማቅረቡ 1000 ዶላር እንዲቀጣለት ወሰነ።
👉የተወሰነለትን ገንዘብ ለልጁ ካስረከበ በኋላ ፍርድ ቤቱ ልጁን ህዝብ ፊት ይቅርታ ጠየቀው!
የዳኛውን ውሳኔ ከሰሙ በኋላ በችሎቱ ላይ የነበሩ ታዳሚዎች ሁሉ በእንባ ተራጩ።
👉የልጁ እጅ ላይ የነበረው ሰንሰለት ተፈታለት። ዳኛው እንባ እየተናነቀው ሲያወራ ልጁ ያይ ነበር።
---------------------------------------
በኛ ማህበረሰብ ውስጥ ያለው የፍትህ ስርዓት ግን ምን ይመስላል? የተራበ ልጅ ዳቦ ሰርቆ ቢያዝ ወንጀሉም እፍረቱም ለህዝቡ ነው ይህ መልዕክት ልብህን ከነካ እባክህን ለአንድ ሰው ዳቦ ግዛ።
👉አንተ እያለ ሌላው ጾም ማደር የለበትም።
👉በዙሪያህ ካሉ ከብዙዎች አንድ መካከል ቢያንስ ለ አንድ ሰው የአቅምህን አድርግ!
!
👉ከብዙዎች ትሻላለህና ካለህ ጥቂት ነገር ላጡት አካፍል!
ይህንን ከባድ ጊዜ ተጋግዘን እንለፈው
ይህንን በማረጋችሁ ፈጣሪ ያስብልናልና!
(Source: Facebook)

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to FANOS MEDIA ፋኖስ ሚዲያ:

Share