GECH MEDIA

GECH MEDIA GECH ጌች ሚዲያ ወቅታዊ ዜናዎችን፣ ተዓማኒነት ያላቸው መረጃዎች በሳል የፖለቲካ ተንታኞች አተያዮች ከኢትዮጵያና ከአለም ዙሪያ በፍጥነት ይቀርቡበታል

15/05/2025

እንኳን ደስ አላችሁ የማክሮ- ኢኮኖሚ ማሻሻያ አድርገናል ከተባለ ጊዜ ጀምሮ ...

* ኢትዮ-ቴሌኮም ከፍተኛ የታሪፍ ማሻሻያ ጭማሪ አደረገ
* መብራት ሃይል ሶስት እጥፍ የዋጋ ጭማሪ አደረገ
* የውሃ አገልግሎት የክፍያ ታሪፉን እላይ ሰቀለው

* የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለአገልግሎት ተጨማሪ እሴት ታክስ ማስከፈል ጀመረ
* ነዳጅ በሊትር በየወሩ ከሃያና ከአስር ብር በላይ ይጨምራል
* የትኛውም የመንግስት አገልግሎቶች እንደ ቀልድ የሚጨምሩት ክፍያ የማይቀመስ ሆነ

* መሰረታዊ የፍጆታ ሸቀጦች ሆነ የትኛውም ምርት በየቀኑ የዋጋ ተመናቸው ከፍ እያለ አስቸገረ .
* ከውጭ የሚገቡ ምርቶች በየወሩ ከእጥፍ በላይ ይጨምራሉ

* አገልግሎት ሰጪ ተቋማት የሰው ኪስ መግባት እስኪቀራቸው ድረስ ህብረተሰቡን አማረሩ ..

* መንግስት በታክስ ሀንግ መስራት ጀመረ ... ወዘተረፈ

ነገር ግን የሰራተኛው ደሞዝ ባለበት ደርቋል። ደሞዝ ቢጨመርም እንኳን ለአንድ ቀን ምሳ የማትበቃ 700 ብር ጠብ ትደረጋለች። የገንዘባችን የመግዛት አቅም ተመናምኖ እርቃኑን ቀርቷል። ህዝቡ በተአምርና በአስማት ሌላውን ነገር ትቶ ትንፋሹን ለማስቀጠል ብቻ ህይወቱን ይገፋል።

በጎን በኩል ደግሞ ሚዲያው ፣ ካድሬው ፣ የገፅታ ግንባታ ባለሞያው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ መላው አለም እየተደመመበት እንደሆነ ይነግሩናል። አስፓልት ፣ መብራት ፣ ዘንባባ በባዶ ሆዶችሁ እያያችሁ ተደመሙ ይሉናል።

የኢኮኖሚ እድገት ማለት .. በየቀኑ የሚጨምር የዋጋ ንረት እንደሆነ አስበው ነው መሰለኝ ... የሸቀጦች ፣ የአገልግሎት ዋጋ በጨመረ ቁጥር የኢኮኖሚ እድገቱን ቁጥር እየጨመሩ በአውራው መንግስታቸው ተደመሙ።

እኛ ኢትዮጵያ የምናላት ሀገር ... ለእነሱ ኖርዌይ ሆና ትታያለች። እኛ ግን የተወደደውን ኑሮዬን እንጂ የካድሬውን ኖርዌይ አናውቅም 😃 !!

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሊጠናቀቅ 1.34% ብቻ ነው የቀረው   | ግንባታው የተጀመረው መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ነበር። የኢትዮጵያዊያን አንድነትና የይቻላል መንፈስ የታየበት ሀገ...
28/04/2025

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሊጠናቀቅ 1.34% ብቻ ነው የቀረው

| ግንባታው የተጀመረው መጋቢት 24 ቀን 2003 ዓ.ም ነበር።

የኢትዮጵያዊያን አንድነትና የይቻላል መንፈስ የታየበት ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው። ለመጪው #ትውልድም የይቻላል መንፈስን ሲያንጸባርቅ የሚኖር ፕሮጀክት ነው።

👉 የዓባይ ግድብ በአሁን ላይ ኃይል በማመንጨት ላይ ነው፣

👉 74 ቢሊዮን ኪዮቢክ ሜትር ውሃ በመያዝ ትልቁ ሰው ሰራሽ ሀይቅ ይሆናል፣

👉 ግድቡ ሲጠናቀቅ 78 ደሴቶች ይፈጠራሉ፤

👉 ግድቡ በዓመት ከ10 እሰከ 15 ሺህ ቶን አሳ ማምረት የሚያስችል ነው፣

👉 የዓባይ ግድብ የኤሌክትሪክ ኃይልን በማመንጨት ከአፍሪካ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፣

👉 ለቀጠናው ህዝቦች ትስስር፣ ለአፍሪካ ሀገራት ተሞክሮ ቁልፍ ሚና አለው፣

👉 የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሽፋንን 75 በመቶ ያሳድጋል፣

👉 ለአፍሪካ ሀገራት በራስ አቅም ልማት መነቃቃት ተምሳሌት የሆነ ፕሮጀክት ነው፣

✍️ ብእሩ የሚናፍቅን ልጅታዴ ❓ታደለ ጥበቡ  ባህርዳር ካፈራቻቸው አንዱ ጀግና ነው::ለወገኖቹ እና ላመነበት ዓላማ የቆመ ልጅ ነበርነገር ግን ከ1 ዓመት ከ10 ወር በፊት ነበር በዚህ በሶሻል...
26/04/2025

✍️ ብእሩ የሚናፍቅን ልጅ

ታዴ ❓ታደለ ጥበቡ ባህርዳር ካፈራቻቸው አንዱ ጀግና ነው::

ለወገኖቹ እና ላመነበት ዓላማ የቆመ ልጅ ነበር

ነገር ግን ከ1 ዓመት ከ10 ወር በፊት ነበር በዚህ በሶሻል ሚዲያ ብቅ ብሎ የነበረው አሁን ሙሉ ለሙሉ ጠፍቷል::

ሁሌም በአእምሮችን ውስጥ
የሚመላለስ ልጅ ነው
#ለተቸገሩት ደራሽ
#ታሪክ አዋቂ
Tadele tibebu - ታደለ ጥበቡ

የት ነው ግን ❓

ምን ውስጥ ነህ ጏዴ ?
ከ ጉርሻ page

ትልቅ አቅሙን ራሱን ለማጥፋት የሚጠቀመው የአማራ የሳይበር ሰራዊት ከዚህ ምን ይማራል?ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ለነልጅ ያሬድና ለተለያዩ ፌስቡክ ብሎገሮች የተደረገ ህዝባዊ አቀባበል ነው። እንደአጋ...
21/04/2025

ትልቅ አቅሙን ራሱን ለማጥፋት የሚጠቀመው የአማራ የሳይበር ሰራዊት ከዚህ ምን ይማራል?

ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ለነልጅ ያሬድና ለተለያዩ ፌስቡክ ብሎገሮች የተደረገ ህዝባዊ አቀባበል ነው። እንደአጋጣሚ ቪዲዮውንም ተመልክቼ ነበር። ወጣቱ በነቂስ ወጥቶ የክብር አቀባበልና ድጋፉን ሲያሳያቸው ነበር። በተለያዩ ከተሞች ተመሳሳይ ቱር እያደረጉ መሆኑንም ገልፀዋል።

የኔ ትኩረት ግን የእነሱ አቀባበል መደረግን መግለጽ ወይም ለህዝቡ አወንታዊም ሆነ አሉታዊ አበርክቶዎቻቸውን መተንተን አይደለም።

በሳይበር ሚዲያው ላይ ከፍተኛ አቅም ያለውም ፣ ተፅዕኖ መፍጠርና መቆጣጠር የሚችለው የአማራ የሳይበርና የአክቲቫዝም ሀይል በጠባብ ሰርክል እየተከፋፈለ እርስበርሱ ሲጠለሻሽና ሲዘራጠጥ መመልከት የተለመደ ነገር ሆኗል። እምቅ አቅሙን የህዝቡን የህልውና ትግል ለማገዝ ብሎም ተቋም ለመገንባትና የህዝቡን ሁለንተናዊ ችግሮች አመላክቶ መፍትሔ ለማዋለድ ሳይሆን ልዩነትን ለመስበክ ፣ ተቋማትን ለማፍረስ ፣ እርስበርስ ለመጠለሻሸትና ደም ለማፋሰስ እየተጠቀመበት ይገኛል❗️

ከዚህ ተነስተን የአማራ አክቲቪስት አይደለም እንዲህ ተሰባስቦ አካባቢዎቹን መጎብኘትና ህዝቡ ጋር መገናኘት ቀርቶ እርስበርሱ ቢገናኝ ሊጨፋጨፍ እንደሚችል በቀላሉ መገመት አያዳግትም። ''ቆይ አባክ እዚህ አካባቢ ትመጣና'' እየተባባለ ሲዛዛት የሚውለውን ስታይ ሁሉም አካባቢዎች ላይ በተመሳሳይ ቅቡልነት ያላቸው አንቂዎችን ፣ ጦማሪዎችንና የሚዲያ ሰዎችን ፈልጎ ማግኘት ዘበት ይሆናል❗️

ታዲያ የኦሮሚያ ህዝብ የሌሎችን እምነት በማጠልሸት ግጭት ሲቀሰቅሱና በህግ ተፈርዶባቸው የነበሩት እነልጅ ያሬድን ሳይቀር በየደረሱበት ከተማ በዚህ መልኩ በህብረት ወጥቶ ሲደግፋቸው መመልከትና እነሱም ለሌሎች ተሞክሮ በሚሆን መልኩ በክልላቸው እንዲህ የተደራጀ ጉብኝት ማድረጋቸው የሚያስደንቅና መንፈሳዊ ቅናት የሚያሲዝ ነው❗️

@ተዋቸው ዘ አምሓራ

♦ ይህ'ም ይመዝገብ!የሞራል ጥያቄ ?!እነኚህ የመንግስት ሹመኞች ፤ አንዴ አይደለም በተደጋጋሚ ጊዜ "ወክለነዋል" በሚሉት አማራው ላይ እየደረሰ ላለው ማንነት ተኮር በደል እና ግፍ በሥልጣን ...
28/03/2025

♦ ይህ'ም ይመዝገብ!

የሞራል ጥያቄ ?!

እነኚህ የመንግስት ሹመኞች ፤ አንዴ አይደለም በተደጋጋሚ ጊዜ "ወክለነዋል" በሚሉት አማራው ላይ እየደረሰ ላለው ማንነት ተኮር በደል እና ግፍ በሥልጣን ዘመናቸው ....

ልክ እንደዚህ በአደባባይ ወጥተው ምን ያህል ጊዜ ለምን ብለው ጠይቀው ይሆን ?! ግፍና በደል ፈጻሚዎችን ምን ያህል ጊዜ አውግዘዋል ?!

ይድነቃቸው ከበደ

እህቶቼ ሆይ በደላችሁን እና ስቃያችሁን ስትናገሩ ቦታውን ባህር ዳር ወይም ጎንደር ወይም ደሴ ወይም ደብረ ብርሃን አድርጉት። አፋኞቹ እና ደፋሪዎቹም አሸናፊ ወይም አየለ ወይም ተመስገን እንደ...
25/03/2025

እህቶቼ ሆይ በደላችሁን እና ስቃያችሁን ስትናገሩ ቦታውን ባህር ዳር ወይም ጎንደር ወይም ደሴ ወይም ደብረ ብርሃን አድርጉት። አፋኞቹ እና ደፋሪዎቹም አሸናፊ ወይም አየለ ወይም ተመስገን እንደሆነ ተናገሩ። ያን ጊዜ ለእናንተ ተሰምቷቸው ሳይሆን የሚጠሉትን አማራ የሚያዋርድላቸው ስለሚመስላቸው
1. ከንቲባዋ በብርሃን ፍጥነት አቅፈው የአዞ እንባቸውን እያነቡ ቤት ይሰጧችኋል።
2. ሚንስትሮች ማህበራዊ ሚዲያዉን በውግዘት ያደምቁታል።
3. ሴት ሚንስትሮች በቲቪ መስኮት ቀርበው ስለ ሴት ልጅ ጥቃት በእንባ ታጅበው ይነግሩናል።
4. ታዋቂ ሰዎች መድረግ ያዘጋጅላችኋል። ቲክቶኩን ይሞሉታል።
5.የእምነት አባቶች መጽሀፍ እያጣቀሱ አደባባይ ይወጣሉ

የእዚህ ሁሉ ግርግር ዓላማ ግን ስቃይሽን በደልሽን መጋራት አይደለም። ህግና የሞራል ተጠየቅ ለማቅረብም አይደም። የእነሱ ዓላማ በጠላትነት የፈረጁትን፣ መጥፋቱን የሚመኙትን፣ ዘመኑ ባፈራው መሳሪያ ሲጨፈጭፉት የሚውሉትን የመጣችሁበትን አማራን ለማውገዝ ነው።
እውነተኛ እህት ወንድሞቻችሁ ግን እንባችሁን ለማበስ የበደላችሁን ሰው በፍርድ አደባባይ ለማቅረብ በዱር በገደሉ ውድ ህይወታቸውን እየሰጡላችሁ ነው። በቅርቡ ሁሉም የእጁን ያገኛል::

የ13 ዓመት ልጅ ከመደብር ዳቦ ሲሠርቅ እጅ ከፍንጅ ተያዘ። ከተያዘበት ሊያመልጥ ሲሞክር የመደብሩ መደርደሪያ ወድቆ ተሰበረ።ዳኛው የወንጀሉን ዝርዝር ሰማና ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀው!👨‍⚖️"...
26/12/2024

የ13 ዓመት ልጅ ከመደብር ዳቦ ሲሠርቅ እጅ ከፍንጅ ተያዘ። ከተያዘበት ሊያመልጥ ሲሞክር የመደብሩ መደርደሪያ ወድቆ ተሰበረ።
ዳኛው የወንጀሉን ዝርዝር ሰማና ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀው!
👨‍⚖️"የሆነ ነገር፥ ማለትም ዳቦ ሰርቀህ ነበር?"
🧑‍🦲ልጁ - (እያፈረ) "አዎን ሰርቄአለሁ"
👨‍⚖️ዳኛው - "ለምን?"
🧑‍🦲ልጁ - "አስፈልጎኝ"
🧑‍⚖ዳኛው - "መግዛት አትችልም ነበር?"
🧑‍🦲ልጁ - "ገንዘብ አልነበረኝም"
🧑‍⚖ዳኛው - "ከቤተሰብህ ለምን አትወስድም?"
🧑‍🦲ልጁ - "እናት ብቻ ናት ያለችኝ፥ እሷም በጠና ታምማ እቤት ተኝታለች"
🧑‍⚖ዳኛው - "ምንም ስራ የለህም?"
🧑‍🦲ልጁ - "መኪና እጥበት እሰራ ነበር፥ ነገር ግን እናቴን ለማስታመም አንድ ቀን ከስራ ስቀር አባረሩኝ"
🧑‍⚖ዳኛው - "ሌሎች እንዲረዱ አልጠየቅኽም?"
🧑‍🦲ልጁ - "በጧት ነው ከቤት የወጣሁ፥ እንዲረዱኝ 50 የሚሆኑ ሰዎች ጋ ሄጄ ነበር፤ አንድም የሚረዳኝ ሰው ግን አላገኘሁም፤ በቃ መጨረሻ ላይ ይህንን መጥፎ ውሳኔ ወሰንሁ"።
ጥያቄው ሲጠናቀቅ #ዳኛው ውሳኔ ማስተላለፍ ጀመረ።
#ውሳኔ🧑‍⚖
"ዳቦ መስረቅ፥ በተለይ የተራበ ልጅ ዳቦ መስረቅ እጅግ በጣም አሳፋሪ ወንጀል ነው፤ እናም እኛ ሁላችንም የዚህ ወንጀል ተጠያቂ ነን። እኔን ጨምሮ በዚህ ቤት ውስጥ ያላችሁ በሙሉ ወንጀለኛና ተጠያቂ ነን። ስለዚህ እያንዳንዱ በዚህ ችሎት ላይ የታደመና እዚህ ቤት ውስጥ ያለ አስር (10) አስር ዶላር$ እንዲከፍል ፍርድ ቤቱ ወስኗል።
ማንም ሰው ሳይከፍል መውጣት አይችልም በማለት
👉አስር ዶለር ከኪሱ አውጥቶ ወረቀት ላይ መመዝገብ ጀመረ።
👉በተጨማሪ ዳቦ ቤቱ የተራበ ልጅ ለፖሊስ አሳልፎ በመስጠቱ 1000 ዶላር እንዲከፍል ውሳኔ አስተላለፈ።
👉ይህ በ24 ሰአት ውስጥ ካልተፈጸመ ፍርድ ቤቱ ዳቦ መደብሩን ያሳሽጋል።
👉ፖሊስም የተራበ ልጅ ፍርድ ቤት በማቅረቡ 1000 ዶላር እንዲቀጣለት ወሰነ።
👉የተወሰነለትን ገንዘብ ለልጁ ካስረከበ በኋላ ፍርድ ቤቱ ልጁን ህዝብ ፊት ይቅርታ ጠየቀው!
የዳኛውን ውሳኔ ከሰሙ በኋላ በችሎቱ ላይ የነበሩ ታዳሚዎች ሁሉ በእንባ ተራጩ።
👉የልጁ እጅ ላይ የነበረው ሰንሰለት ተፈታለት። ዳኛው እንባ እየተናነቀው ሲያወራ ልጁ ያይ ነበር።
---------------------------------------
በኛ ማህበረሰብ ውስጥ ያለው የፍትህ ስርዓት ግን ምን ይመስላል? የተራበ ልጅ ዳቦ ሰርቆ ቢያዝ ወንጀሉም እፍረቱም ለህዝቡ ነው ይህ መልዕክት ልብህን ከነካ እባክህን ለአንድ ሰው ዳቦ ግዛ።
👉አንተ እያለ ሌላው ጾም ማደር የለበትም።
👉በዙሪያህ ካሉ ከብዙዎች አንድ መካከል ቢያንስ ለ አንድ ሰው የአቅምህን አድርግ!
!
👉ከብዙዎች ትሻላለህና ካለህ ጥቂት ነገር ላጡት አካፍል!
ይህንን ከባድ ጊዜ ተጋግዘን እንለፈው
ይህንን በማረጋችሁ ፈጣሪ ያስብልናልና!
(Source: Facebook)

በአዲስ አበባ ከተማ 100 ኪሎ ጤፍ 19.000 ብር እየተሸጠ ነው።  በአካባቢያችሁ ባሉ ከተሞች ስንት እየተሸጠ  ነው  ?
31/07/2024

በአዲስ አበባ ከተማ 100 ኪሎ ጤፍ 19.000 ብር እየተሸጠ ነው።
በአካባቢያችሁ ባሉ ከተሞች ስንት እየተሸጠ ነው ?

የ "ጉማ አዋርድ" አዘጋጅ ዮናስ ብርሃነ ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ከተካሄደው የሽልማት ስነ ስርአት በኋላ ለእስር ተዳርጓል። በስፍራው ከነበሩ ሰዎች በደረሰኝ መረጃ መሰረት ዮናስን ...
10/06/2023

የ "ጉማ አዋርድ" አዘጋጅ ዮናስ ብርሃነ ትናንት ምሽት በስካይ ላይት ሆቴል ከተካሄደው የሽልማት ስነ ስርአት በኋላ ለእስር ተዳርጓል።

በስፍራው ከነበሩ ሰዎች በደረሰኝ መረጃ መሰረት ዮናስን ሲቪል የለበሱ ደህንነቶች ከምሽቱ 5 ሰአት ገደማ ከነባለቤቱ አስረው ወስደዋቸዋል። ባለቤቱ ከጥቂት ቆይታ በኋላ ብትፈታም ዮናስ አንበሳ ጋራዥ አካባቢ በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ እንደሚገኝ ታውቋል።

በትናንትናው ፕሮግራም ላይ "ልጅ ማኛ" በሚል የምትታወቀው ቲክቶከር ባደረገችው ሜካፕ ምክንያት "ልጅቷን አምጡ" በሚል አዘጋጆቹ ተጠይቀው እንደነበር እና እስሩም ከእሱ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል በስፍራው የነበሩ ግለሰቦች እና ሌሎች ምንጮች አረጋግጠውልኛል።

የኔ ጥያቄ:

- ሜካፕ ተቀብቶም ይሁን ፒካፕ ተኮናትሮ ሀሳብን ሰላማዊ በሆነ መንገድ መግለፅ በቃ ተከልክሏል?

- የፕሮግራሙ አዘጋጅ የተለያየ ልብስ ለብሶ እና ሜካፕ ተቀብቶ ለሚመጣው የሀገር ህዝብ ሁሉ ሀላፊነት አለበት?

ለህግ ማቅረብ ከተፈለገ አንዱ ማስረጃ ይሄ ነው!ያውም የፀጥታ አካላትን የደንብ ልብስ በለበሱ ሰዎች የሚፈፀም እንዲህ አይነት የጭካኔ ድርጊት ሊቆም ይገባል። #አሸባሪ መንግስት እንጂ ፋኖ አይ...
05/06/2023

ለህግ ማቅረብ ከተፈለገ አንዱ ማስረጃ ይሄ ነው!

ያውም የፀጥታ አካላትን የደንብ ልብስ በለበሱ ሰዎች የሚፈፀም እንዲህ አይነት የጭካኔ ድርጊት ሊቆም ይገባል።
#አሸባሪ መንግስት እንጂ ፋኖ አይደለም

 !አርበኛ ዘመነ ካሴ አራት አይና በሆኑ ፋኖዎች እጀባ እየተደረገለት ከሰባታሚት ማረሚያ ቤት ወጥቷል። የፋኖዎቹ ጥንቃቄ የሚገርም ነበር።እንቅስቃሴያቸውና ቅኝታቸው የሰለጠኑ ሪፐብሊካን ጋርድ ...
04/06/2023

!

አርበኛ ዘመነ ካሴ አራት አይና በሆኑ ፋኖዎች እጀባ እየተደረገለት ከሰባታሚት ማረሚያ ቤት ወጥቷል። የፋኖዎቹ ጥንቃቄ የሚገርም ነበር።

እንቅስቃሴያቸውና ቅኝታቸው የሰለጠኑ ሪፐብሊካን ጋርድ ይመስሉ ነበር።

ግንቦት 27 ቀን 2015 ዓ.ም.
GECH MEDIA

 #መገደል   #መገደል  አሳምነው ፅጌ በህይወት መያዝ ሳይሆን መገደል ነው ያለብት ብሎ ትዕዛዝ የሰጠው አብይ አህመድ እስክንድር ነጋ ባለበት ይገደል የሚል ትዕዛዝ ማስተላለፉ የሚደንቅ አይደ...
04/06/2023

#መገደል #መገደል
አሳምነው ፅጌ በህይወት መያዝ ሳይሆን መገደል ነው ያለብት ብሎ ትዕዛዝ የሰጠው አብይ አህመድ እስክንድር ነጋ ባለበት ይገደል የሚል ትዕዛዝ ማስተላለፉ የሚደንቅ አይደለም:: እስክንድር ነጋ ወይም ሌሎች ቢሰው በዋናነት ተጠያቂው የአማራ ወጣት እንጂ የጠላት ወታደር ወይም ዘረኛው አብይ አህመድ አይደለም:: እነሱማ አንዴ ጠላት ናቸው እኮ::

ማንኛውም ለህዝብ ትግል ሲል የተደራጀ ሀይል የጠላቱን የመንግስትን ሪሶርስ መጠቀም መጀመር አለበት:: የመንግስት ንብረቶች:- መኪናዎች:- ገንዘብ:- መድሃኒቶች እንዲሁም መሳሪያዎችን መጠቀም ትክክለኛው ፍትሃዊ መንገድ ነው::
አማራ የነቁ ልጆቹን እያስበላ ትግሉን ከዐ መጀመር ሊበቃው ይገባል።

Address

Addis Ababa
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when GECH MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to GECH MEDIA:

Share