Ethio Christian Post

Ethio Christian Post ክርስቲያናዊ ዜናዎችን በየጊዜው እያገኙ ለዳግም ምጽአት ይዘ?

ቢትዬ በሕይወት እስካለሽና በሕይወት እስካለሁ ድረስ  ላንቺ መደረግ ያለበትን ሁሉ አደርጋለሁ። አንድም ቀን እንደ ልጆች ተጫዉተሽ; ቦረቀሽ ሳታውቂ ይኸው ድፍን ስድስት አመት ቆዘምሽ። አባትሽ...
08/06/2024

ቢትዬ በሕይወት እስካለሽና በሕይወት እስካለሁ ድረስ ላንቺ መደረግ ያለበትን ሁሉ አደርጋለሁ። አንድም ቀን እንደ ልጆች ተጫዉተሽ; ቦረቀሽ ሳታውቂ ይኸው ድፍን ስድስት አመት ቆዘምሽ። አባትሽንና እናትሽን አባ; እማ ብለሽ ሳትጠሪ; ከወንድምሽና ከእህትሽ ሳትጫወቺ; የጠፈጠሽንና የወደድሽውን ምግብ መርጠሽ ሳትበይ; ውሃ ጠማኝ; ሽንቴ መጣ;... ሳትይ አመታት ነጎዱ።ትምህርት ቤት ብትገቢ ኖሮ በዚህ ሰኔ ከኬጂ ትመረቂ ነበር። ስድስት ጊዜ ልደትሽ ስናከብርልሽ Happy Birthday ብለሽ ሳትዘምርና ሳትደሰቺ... በቃ... ከሥራ ተመልሼ ወደ ቤት ሲገባ በአልጋ ተኝተሽ እጄን ጥብቅ አርገሽ አይን አይኔን ሲታይኝ የማደርገው ይጠፋኛል። ምን እያልሽኝ እንደሆነ አይገባኝም። ቢቲዬ ምን ላድርግ?... በምን ቋንቋ ፍላጎትሽን ልረዳ? የኔ ሕይወት ተቋርጦ ያንቺ ይጀመራል ቢባል ደስ ባለኝ። ተስፋ... ከቀን ወደ ቀን እየራቀን መጣ። የምችላቸው ነገሮች የማልችላቸው ሆኑ። የማውቃቸው ነገሮች የማላውቃቸው ሆኑ። እስከ ዛሬ ብቻችንን ሞክረናል። አሁን ደግሞ በአደባባይ በሕዝብ ፊት እንሞክረው። ላንቺ ይሆናል የተባለውን ሁሉ ከመሞከር ወደኋላ አንልም።

Help 6-Year-Old Bithia Get the Care and Support She Needs Bith… Amanuel Tadesse Heboto needs your support for Support Bithia's Journey Towards Better Care

27/09/2023

TikTok

የንስሐ ጊዘ
24/09/2023

የንስሐ ጊዘ

Watch, follow, and discover more trending content.

የኃጢአት License
24/09/2023

የኃጢአት License

Watch, follow, and discover more trending content.

ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን
23/09/2023

ከእግዚአብሔር ጋር ቃል ኪዳን

Watch, follow, and discover more trending content.

Dormant እምነት
23/09/2023

Dormant እምነት

Watch, follow, and discover more trending content.

እውነተኛ ክርስቲያናዊ ትምህርቶችን ለማግኘት  ሊንኩን ይጫኑ
22/09/2023

እውነተኛ ክርስቲያናዊ ትምህርቶችን ለማግኘት ሊንኩን ይጫኑ

TikTok

You can get free books download from
03/09/2023

You can get free books download from

Z-Library Project | Z-Library. Download books for free. Find books

ኢየሱስ ይመጣል!=========ይህ ሐይማኖት አይደለም!=============ኢየሱስ የጴንጤዎች ብቻ አይደለም!===================የአንተም፤ የአንቺም ነው! ሊያድንህ፤ ሊያድንሽ ይወዳ...
11/08/2023

ኢየሱስ ይመጣል!
=========
ይህ ሐይማኖት አይደለም!
=============
ኢየሱስ የጴንጤዎች ብቻ አይደለም!
===================
የአንተም፤ የአንቺም ነው! ሊያድንህ፤ ሊያድንሽ ይወዳል!
==============================
ኢየሱስ ይመጣል ስንል በቃ ጅል የምንመስላቸው ሰዎች ብዙ ናቸው። እነዚህ በፎቶው ላይ የሚታዩአቸው ይመጣል የሚል ጽሑፍ አትመው ትልቅ በሚባለው ፕሮግራማቸው ላይ ትልቅ የሆነውን ጉዳይ አተልቀው መታየታቸው ዝም ብለው እንዳይመስሏችሁ። ልባሞች ናቸው።
ኖኅ የጥፋት ውሃ ይመጣል እያለ መርከብ ሲሰራ ለዘመኑ ሰዎች በጣም ሞኝ ሆኖባቸው፣ አንዳንዴ እንደ እብድ ይቆጥሩት ነበር። 120 ዓመት ሙሉ የጥፋት ውሃ ይመጣል። እግዚአብሔር ተናግሮኛል ስላቸው መሳቂያ፣ መዝናኛ፣ መቀለጃ ያደርጉት እንደነበር የእግዚአብሔር ቃል ያስተምረናል። በመጨረሻም ኖኅ ያለው አልቀረም ዝናቡ መጣ፣ ምንጮች ፈለቁ፣ ጎርፍ መጣ፣ ውሃው ሞላ፣ ተራሮችን ሸፈነ፣ ኖኅ እና የአባታቸውን እብደት የተቀበሉ፣ አባታቸው ሲሳለቁበት አብረው ከአባታቸው ጋር የቆሙ እና ከእንስሳት የተመረጡ ከመርከቡ ገብተው ተረፉ።
ዛሬ ኢሱስ ይመጣል የሚሉ ሰዎች መርከባቸውን በመስራት ላይ ናቸው። የኖኅ 120 አመት እንደፈጀ ሁሉ የዘገየባችሁ አትሞኙ ይመጣል። የዘገየ ቢመስልም አይቀርም። ይልቁንስ መርከባችሁን ብትሰሩ ይሻላችኋል። ኋላ ይቆጫችኋል። ማለት ዝም ብላችሁ ሞታችሁ ደብዛችሁ የሚጠፋ እንዳይመስላችሁ። ትሞታላችሁ ግን ደግሞ ሰላም የሌለው ሕይወት ከሞት በኋላ ትቀጥላላችሁ። እዚያ ሆናችሁ ወይኔ ምን ነካኝ። ተሸወድኩኝ ማለታችሁ አይቀርም። ስቃዩ ዘላለማዊ ነው፣ የማያቋርጥ ነው፣ መጨረሻ የለውም። በአንጻሩ መርከባቸውን የሰሩ ሰዎች አሁን ለእናንተ ሞኞች የሚመስሉ በዚያን ጊዜ በቃ ከጌታቸው ጋር በተዘጋጀላቸው ስፍራ ይንደላቀቃሉ፣ በማያልፍ ደስታ፣ በማይለመድ ሀሴት ደስ እየተሰኙ ከበጉ ጋር ለዘላለም ይኖራሉ።
በእርግጥ ኢየሱስ ይመጣል??????
የማቴዎስ ወንጌል 24፡14፣ 24፡44፣ 24፡50። የሉቃስ ወንጌል 12፡40፣ 12፡46። የዮሐንስ ወንጌል 5፡28-29፣ 6፡45። የሐዋሪያት ሥራ 1፡11፣ ዕብራዉያን 10፡37። 2ኛ ጴጥሮስ መልዕክት 3፡10፣ የዮሐንስ ራዕይ 1፡7። ስለዚህ ወገኖች መምጣቱ እውን ነው። እነዚህን ጥቅሶች ብቻ ሳይሆን እግዚአብሔርን ቃል በደንብ አንብቡ። ማንም አያታልላችሁ።
ይመጣል የተባለው ኢየሱስ ለምን ዘገየ????
2ኛ ጴጥሮስ 3፡1-15። ሰዎች ወደ እርሱ እንዲመለሱ ነው የዘገየው። ነገር ግን ይመጣል። አሁን በትዕግሥት ነው የሚጠብቀው። ሲመጣ ግን እንደለባ ነው የሚመጣው። የሚመጣበትን ቀን ከእግዚአብሔር በቀር ማንም አያውቅም። ስለዚህ ለአንዳንዶች በቃ አስደንጋጭ ይሆናል። አመጣጡ እንደኖኀ በዝግጅት ላይ ለሚሆኑ ግን አዲስ አይሆንባቸውም። ማቴዎስ 24:3, 7-14፤ ሉቃስ 21:10, 11 ምልክቶችን ስለተናገረ በዝግጅት ውስጥ ያሉት አዲስ አይሆንባቸውም። እንዲያውም እርሱ ሲመጣ ይነጠቃሉ። አይደነግጡም ይደሰታሉ። የመምጣቱ ቀንና ሰዓት ባይታወቅም በሚመጣበት ሰዓት በዓለም ሁሉ እየታየ በታላቅ ክብር ይመጣል። ግን ብዙዎች ይጮሃሉ። ያ ቀን ላልተዘጋጁ ዋይታ ነው። በምድነው መዘጋጀት ያለብን ለሚትሉኝ ይህን ክፍል አንብባችሁ ስትጨርሱ ይገባችኋል። ብቻ በጌታ አንብቡት፣ ቀላል ነው።
ታድያ ሰዎች ምን ማድረግ አለባቸው?????
1ኛ ኢየሱስን በመቀበል እና በስሙ በማመን የእግዚአብሔር ልጅ መሆን። የዮሐንስ ወንጌል 1፡12
2ኛ ንስሐ መግባት፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም መጠመቅ፣ የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ መቀበል ሐዋ 2፡38፣ 3፡ 19-20፣ 17፡30
3ኛ ተዘጋጅቶ መኖር። ማለት ቃሉን ማንብ፣ መጸለይ፣ በቅድስና መኖር፣ ከሌሎች አማኞች ጋር ህብረት ማድረግ፣ ለሌሎች እንዲድኑ ወንጌልን/ኢየሱስን መናገር፣ ወዘተ.... የማቴዎስ ወንጌል 25፡1-46 ሙሉውን አንብቡ።
እስኪ አንድ ጥያቄ መልሱልኝ፡፡ ገነት መግባት የማይፈልግ ሰው አለ?????? እርግጠኛ ነን ፈጣሪን የማያምን/እግዚአብሔር/አላህ/ፈጣሪ የለም የሚል ሰው ካልሆነ፣ አለ የሚል ሁሉም ሰው ገነት መግግባት ይፈልጋል።
ይህ ከሆነ ደግሞ ወደ ገነት/ወደ እግዚአብሔር መንግስት/ወደ መንግስተሰማያት/ወደ ህይወት መግቢያ መንገድ አንድና አንድ ነው።
ሌላ መንገድ የለም!!!!! በእግዚአብሔር እምላለሁ ሌላ መንገድ የለም!። የመዳን መንገድ አንድ ነው። እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!!!!! የዮሐንስ ወንጌል 14፡6 ። የሐዋሪያት ሥራ 4፡6። “ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉ” 1ኛ ቆሮንቶስ 15፡22። ኤፌሶን 2፡8-9።ኢየሱስ “እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ የሚከተለኝ የሕይወት ብርሃን ይሆንለታል እንጂ በጨለማ አይመላለስም” ብሏል። ዮሐንስ 8:12።ኢየሱስ እንዲህ አለ፡- “እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የእግዚአብሔርን መንግሥት ሊያይ አይችልም” (ዮሐንስ 3፡3)። "ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም" (ዮሐ. 3:5)። በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዷልና። የዮሐንስ ወንጌል 3፡16።
በመሆኑም በአንድያ ልጁ በማመን ብቻ ነው ሕይወትን የምናገኘው። አለቀ!
ታዲያ ምን ትጠብቃላችሁ። ይህ ሐይማኖት አይደለም። የህይወትህ/ሽ የመዳን ጉዳይ ነው። ወደ ዘላለም ሕይወት የመግባት ጉዳይ ነው። የእግዚአብሔርን መንግስት የመውረስ ጉዳይ ነው። ከሞት የማምለጥ ጉዳይ ነው። ከገሐነመ እሳት የማምለጥ ጉዳይ ነው።
የመዳን ቀን ደግሞ ዛሬ ነው። 2ቆሮንቶስ 6፡2
ኢየሱስን መቀበል ከባድ አይደለም። በልብህ ነው የሚትቀበለው፣ በአፍህ ነው የሚትመሰክረው።
ሮሜ 10፡9 ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህ።
ተባረኩ!!!።

አንተ አትሳሳትም በሥራህ
01/08/2023

አንተ አትሳሳትም በሥራህ

Check out Osias Amanuel Tadess's video.

ለምን? ለምን?
25/07/2023

ለምን? ለምን?

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Christian Post posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio Christian Post:

Share