Gamo times

Gamo times Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo times, Media/News Company, Addis Ababa.

መንገድ አሳዮታለሁ በማለት ከ70 ዓመት አዛዉንት  ላይ 14ሺ ብር ሰርቆ የተሠወረው ግለሰብ ተያዘ።ወላይታ ሶዶ መስከረም 6/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ) በወላይታ ሶዶ ከተማ በአራዳ ቀበሌ ክልል በ...
16/09/2025

መንገድ አሳዮታለሁ በማለት ከ70 ዓመት አዛዉንት ላይ 14ሺ ብር ሰርቆ የተሠወረው ግለሰብ ተያዘ።

ወላይታ ሶዶ መስከረም 6/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ) በወላይታ ሶዶ ከተማ በአራዳ ቀበሌ ክልል በዋጃ ቄሮ ቀጠና ላይ ተጠርጣሪው ግለሰብ ነዋሪነታቸው ዋጃ ቄሮ የሆነው አዛውንት 14000/አሥራ አራት ሺህ /ብር ይዘው ሲጓዙ አይቶ መንገድ ልምራዎት በማለት ከተጠጋቸው በኋላ በኪሳቸው ያለውን ገንዘብ ሰርቆ ልብስና ጫማ ገዝቶ ቀሪዉን 4000/አራት ሺህ /ብር በእጁ ይዞ እያለ ግል ተበዳዩ ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ እየተጣራበት መሆኑን የሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያደረሰን መረጃ አመላክቷል።

ይድረስ ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ #ጂንካ
14/09/2025

ይድረስ ለደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ትምህርት ቢሮ
#ጂንካ

05/09/2025

የጥንካሬ ምልክት ናት ለሴቶች 💪

አንዳንድ ሴቶች ልብ አላቸው ቅዳሜና እሁድ ፍቅረኛቸው ቤት ገብተው ልብሱን አጥበው ምግብ ሰርተውለት የሚያስፈልገውን ሁሉ ሰጥተውት ሰኞ ብር ሳይጠይቁ ይሄዳሉ እና ዋጋቸው ምን ያህል ዋጋ እንደ...
05/09/2025

አንዳንድ ሴቶች ልብ አላቸው ቅዳሜና እሁድ ፍቅረኛቸው ቤት ገብተው ልብሱን አጥበው ምግብ ሰርተውለት የሚያስፈልገውን ሁሉ ሰጥተውት ሰኞ ብር ሳይጠይቁ ይሄዳሉ እና ዋጋቸው ምን ያህል ዋጋ እንደሚከፍሉ አታውቅም።

ጊዜህን፣ ታማኝነትህን፣ እና ፍቅርህን ነው የሚፈልጉት

እንደዚህ አይነት ሴቶች እዚህ ካሉን ፈጣሪ ይባርካችሁ፡፡

የህወኃት ዳግም የደቡብን ሀብት በሞግዝትነት የመቆጣጠር ቅዤት መቼም አይሳካም።የህወኃት ዳግም የደቡብን ሀብት በሞግዝትነት የመቀራመት ቅዤት በብርሃነ መስቀል ክንፌ አጽብሃበህወኃት የሥልጣን ዘ...
04/09/2025

የህወኃት ዳግም የደቡብን ሀብት በሞግዝትነት የመቆጣጠር ቅዤት መቼም አይሳካም።

የህወኃት ዳግም የደቡብን ሀብት በሞግዝትነት የመቀራመት ቅዤት በብርሃነ መስቀል ክንፌ አጽብሃ

በህወኃት የሥልጣን ዘመን በሁሉም የአገርቱ ክፍሎች ኔትወርክ በመዘርጋት የአገርቱን አንጡራ ሀብት ጥቂት ራሱ አሰልጥኖ ባሰማራቸው ዘራፍ ነጋዴዎች በስሜ ኢንበስትሜንት ስዘርፍና ሲያዘርፍ ቆይተዋል፡፡

የጋምቤላ መሬት፣ የቤንሻጉል መሬትና ወርቅ፣ የደቡብ ምዕራብ መሬትና ወርቅ፣ የደቡብ መሬት፣ የኦሮሚያ መሬትና ወርቅ እንዲሁም የተለያዩ ማዕድናትን በትዕዛዝ ላደራጃቸው የኔትወርክ አባላት አከፋፍለው አዘርፈዋል ፡፡

ከክልሎች በኢንበስትመንት ስም በነጻ የወሰዱትን መሬት ምንም ሳያለሙ አስይዘው በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከባንኮች በብድር ስም ዘርፈዋል፤ለተበላሸ ብድር ባንኮችን ዳርገዋል፡፡ በአገርቱ አዋጭ ነው ተብለው በተለዩ ዘርፎች ሁሉ ለማጭበርበር እንዲያመቻቸው የንግድ ፈቃድ ታድሎላቸው ያለከልካይ በጨረታ ሥም ያለውድድር በሁሉም የንግድና የኢንበስትሜንት ዘርፍ ተሰማርተው ዘርፈዋል፤ አዘርፈዋል ፡፡

ዛሬ የህወኃት የደቡብ የአገርቱ ክፍል የኔትወርኩ አስተባባሪና መሪ ስለሆነው የብርሃነመስቀል ክንፌ አጽብሃ ዳግም የደቡብን ሐብት በሞግዝትነት የመቀራመት ቅዤት በጥቂቱ ለማንሳት ወደድን፡፡ የሌሎችም በቀጣይነት በተደራጀ መልክ የሚቀርብ ይሆናል፡፡ ህወኃት የምዝበራውና የማፊያ ቡድኑን እንዲመራው በደቡብ የአገርቱ ክፍል ተልዕኮ የተሰጠው ለብርሃነመስቀል ክንፌ አጽብሃ ፣ በጡረታ ሰበብ ከመከላከያ ለተቀነሱ መኮንኖችና በደቡብ መስመር በወቅቱ ለተሰማሩ የፌደራል ኬላዎች ተቆጣጣሪዎች ነበር፡፡

በዚህም ሰፋፍ የእርሻ መሬቶች፣ በክልሉ በሚወጡ የትኞቹን የመንግስት ጨረታዎችን ፣ የማዕድን ቦታዎችንና ከሞያሌ እስከ አዲስ አበባ የተዘረጋውን የኮንትሮባንድ ንግድ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋር አስፈጻሚና መሪ ተዋኒያን ብርሃነመስቀል ክንፌ አጽብሃ ነበረ ፡፡

ህገ ወጥ የገንዘብ ዝውውርና የህገ ወጥ የጦር መሣሪያ ዝውውር የደቡብ ምድብ ተልዕኮ የተሰጠውም ለእሱና በስሩ ላደራጀው ማፊያ ቡድን ነው፡፡ በዚህም የአገርቱን ሃብት ዘርፈዋል አስዘርፈዋል፤ ብርሃነ መስቀል ክንፌ አጽብሃ አሁን በአገርቱ በተለያየ ቦታዎች ላፈራቸው የሃብቱ ምንጭ የዚህ ዘረፋ ውጤት ነው ፡፡

የገንዘብ ጡንቻውን ያፈረጠመው የህወኃት ዋናው ቀኝ እጅ ብርሃነ መስቀል ክንፌ አጽብሃ በለውጡ ወቅትም በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከወላይታ ወጣቶችን መልምሎ ስያደራጅና ወደ ጦርነት ስያሰማራ እንደነበር በወቅቱ ሚዲያን የሚከታተል ሁሉ የሚያውቁት ሀቅ ነው ፡፡

አሁን አሁን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ ሃብትዋ እንዳትጠቀም በውጭ ተደራጅተው አገራችንን በተለያየ መልክ እየወጉ ካሉ ሃይሎች ተልዕኮ በመቀበል በዘረፈው ገንዘብ አገርቱ እንዳትረጋጋ ቅጥረኞች አሰማርቶ እያስወጋን ይገኛል፡፡ በገንዘብ እያማለለ ወጣቶችን ለጸረ ሰላም ሃይሎች የመመልመልና የማሰማራቱን ሥራ ዛሬም አጠናክሮ ቀጥሏል

በዝርፍያና በማጭበርበር በሰበሰበው ገንዘብ በአገር ውስጥና በውጭ አገር ሆነው ቀጠናውን ፣ ሀገርቱና ክልሉ እንዳይረጋጋ የሚሠሩ ህገ ወጥ የሚዲያ ቡድን በማደራጀት ከውጭ ባንዳዎች ጋር ከመሥራቱም በላይ በብርቱ ትግል ተንኮታኩቶ የነበረውን የደቡብ የኮንትሮባንድ ኔት ወርክ ለመዘርጋት ላይ ታች እየባዘነ እንደሆነ ተጨባጭ መረጃዎች ወደ እጃችን እየደረሱ ናቸው ፡፡

ሰሞኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በወሰደው ድንገተኛ ፍተሻ በብርሃነ መስቀል ክንፌ አጽብሃ የሚመራው የደቡብ ቀጠና ተልዕኮ ተቀባይ ቤት ሃሰተኛ የገንዘብ ማተሚያ ማሽንና ሀሰተኛ የብር ኖቶች ተይዘው ተጨማሪ ምርመራ እየተካሄደ ይገኛል፡፡

ብርሃን መስቀል ክንፌ አጽብሃ በህገ ወጥ የሰዎች ዝውውር እጁ እንዳለበት እና በአሜሪካና አውሮፓ ሆነው በህገ ወጥ አገራችን እንዳትረጋጋ ከምሰሩ ቅጥረኞች ጋር በመመሳጠር በወንጀል የተገኘ ገንዘብ ወደ ውጭ አገር ባንክ በማሸሽ ሥራ ላይ ተሰማርቶ እንደቆየ አሁን አሁን ለፍትህ መዋቅር እየቀረቡ ያሉ የምርመራ ጥያቄዎች ያሳያሉ ፡፡ የተደራጀ መረጃ በቅርቡ እናደርሳለን፤

በአሁኑ ሰዓት ለማጭበርበርና ለዝርፍያ የምጠቀመው በተለያየ ዘርፍ 18 የንግድ ፈቃድ በእጁ ይገኛል ፡፡ በቀድመው ሥርዓት ያለ ማንም ከልካይ ስዘርፍና ሲያዘርፍ የነበረው ብርሃነ መስቀል ክንፌ አጽብሃ ከአስራ ስምንቱ የንግድ ፈቃድ አንዱ በሆነው በማዕድን ዘርፍ ፈቃድ እንደ ልማዱ የህወኃት ዳግም የደቡብን ሀብት በሞግዝነት የመቆጣጠር ዕቅዱን ወደ መሬት ለማውረድ ያልፈነቀለው ድንጋይ ያልቆፈረው ጉድጋድ የለም ፡፡

ለዛሬ ከብዙ ጥቂቱን ለማንሳት ፈለግን፤ በቀድመው ደቡብ ክልል ውስጥ በነበረው ኔትወርኮች ጋር በመመሳጠር ከአገርቱ ማዕድን አዋጅና ደንብ ውጭ 600 ሄክታር የማዕድን ቦታ ለምርመራ ተሰጠው ፡፡

ያለ አግባብ ለምርመራ የተሰጠውን የማዕድን ቦታ ፈቃድ ለማምረት እንደተሰጠ ፈቃድ መጠቀም አለብኝ የሚል የቀድሞ የገዢነት መንፈስ መጣበትና ይህንን ያህል የማዕድን መሬት የተሰጠበት መንገድና አንተም እያደረክ ያለሄው ትክክል አይደለም ያለ ባለሙያና አመራር ካገኘሁ በተደራጀው ህገ ወጥ ቡድን ካላጠፋሁ ቤት አልገባም አለ፤ አልተሳካለትም እንጅ የሚችለውነወ ሁሉ አድርገዋል ፡፡

ከብዙ መረጃና ማስረጃ ማሰባሰብ ቦኃላ የገዢነት ወኔ የመጣበትን ምክንያትና በየትኛውም ህገ ወጥ መንገድ (አመጽን ያካትታል) የማዕድን መሬት ካልወሰድኩኝ ሞቸ እገኛለሁ ያለበትን መረጃዎችን በእጃችን ማስገባት ችለናል ፡፡

የጋምቤላ ፣የቤንሻጉል ፣የኦሮሚያ ፣የደቡብና የደቡብ ምዕራብ ክልሎች መሬትና የማዕድናት ቦታዎችን በቀጭን ትዕዛዝ ወስዶ ላደራጀቸው የኔት ወርክ ቡድን አባላት አከፋፍሎ የመንግስትን መሬት አስይዞ በቢሊዮን የሚቆጠር ብር ከባንኮች ወስዶ ባንኮችን የተበላሸ ብድር አሸክሞ የጠፋውን አሠራር በደቡብ የማዕድን መሬት ላይ ለመፈጸም እጅግ ቋምጠዋል ፡፡

በኔትወርኮቹ በኩል ለምርመራ የተሰጠውን 600 ሄክታር የማዕድን ቦታ አለኝና ብዙ ሳይለፋ ማእድን ማምረት የሚፈልግና ተጫርቶ በቂ ገንዘብ ሊከፍል የሚችል ካለ ከብርሃነ መስቀል ክንፌ አጽብሃ ጋር እንዲደራደሩ በጀሌዎች በኩል የጨረታ ማስታወቂያ መነገር ተጀመረ ፡፡

በጨረታውም ሰላሳ የሚሆኑ የማዕድን አልም ባለሀብቶችን አግኝቶ ከአስራ አራቱ ጋር የውል ስምምነት ፈጽሞ ለመጀመሪያ ዙር ቀብድ ብቻ አራት መቶ ስድሳ ሁለት ሚሊዮን አምስት መቶ ሃያ ሺህ ብር የተቀበለበት ሠነድ ኮፒዎች በእጃችን ይገኛሉ፡፡

በህዝቦች መራራ ትግል ከጫንቃችን የተወገደው በሞግዝትነት የአገርቱንና የክልሉን ሀብት የመቀራመት ቅዤት ምስጥሩ እየጠራ መጥተዋል፡፡ በቀጣይ የገጠርና የከተማ መሬት ጉዳይ፣ የኮንትሮባንድ ኔት ወርክ ጉዳይ ፣ የህገ ወጥ የሰዎችና ህገ ወጥ የመሳሪያ ዝውውር እንዲሁም በህገ ወጥ መንገድ የተገኘውን ገንዘብ ወደ ውጭ የማሸሽ ወንጀሎችን በሚመለከት በእጃችን የገቡ ማስረጃና መረጃዎችን አስደግፈን እናቀርባለን ፡፡

የህወኃት ዳግም የደቡብን ሀብት በሞግዝትነት የመቆጣጠር ቅዤት መቼም አይሳካም

 #ሌባዉ ገ/መስቀል ሴራው ተጋለጠ 'በግልጽ አነጋገር ለWt media መረጃ መስጠት የእናንተ ግዴታ ነው!' የሼባው ገብረመስቀል ለአመራሩ የተናገረው ድምጽ ቅጂ ደርሶናል። አጠቃላይ የወላይታ ...
31/08/2025

#ሌባዉ ገ/መስቀል ሴራው ተጋለጠ

'በግልጽ አነጋገር ለWt media መረጃ መስጠት የእናንተ ግዴታ ነው!' የሼባው ገብረመስቀል ለአመራሩ የተናገረው ድምጽ ቅጂ ደርሶናል።

አጠቃላይ የወላይታ ተወላጅ አመራሩ በተገኘበት ለWT Media መረጃ የማይሰጥ እና የማይተባበርን አመራር በመቀስ እቆርጣለሁ በማለት ሲዝት መዋሉን ከታማኝ ምንጫችን በድምጽ ጭምር መረጃ ደርሶናል።

መረጃም ሆነ ሽርሙ*ናውን መደበቅ በማይችልበት ቦታ የሚውለው ጨቅላው ሼባ ገብረመስቀል መድረክ ላይ በግልፅ እየዛተና በወላይታ ተወላጅ አመራሮች ላይ ጫና እያደረገ መሆኑን ሰላም እና አንድነትን የሚወዱ አመራሮች ሹክ ብለውናል።

በተለይ አቶ ጥላሁን ቦታ ላይ እንዳልቀመጥ እንቅፋት የሆናችሁት እናንተ ናችሁ በማለት ሲናዘዝ ያመሸ ሲሆን የክልሉ ፖሊስ ምርመራ የጀመረው የሀሰተኛ መረጃ ቡድን ለማቋረጥ የክልል ፖሊሶችን ለማስፈራራት ያደረገው ሙከራ አልተሳካለትም።
ከዚህ ጋር ተያይዞ ሼባው ገብረመስቀል እና ዶ/ር መሪሁን የጀመርነውን የመረጃ ስርጭት በማያደናቅፍ መልኩ በውስጥ መስመር መረጃ በWhatsapp መለዋወጥ አለባችሁ ይህ ካልሆነ ግን በየጊዜዉ ለየዘመዶቻችሁ የምናመቻቸው ቁልፍ ቦታ የምናሳጣችሁ ይሆናል ብለው በአካል መገኘት ላልቻሉ አመራሮች በስልክ ሲዝቱ ውለዋል።

ሼባው ገብረመስቀል ከወላይታ ውሃ ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር የፈጸመውን ውንብድና በቀጣይ ይዘን እንቀርባለን። እስከዛው Like, share ,follo እየያደረጋችሁ ጠብቁን
Nuso WT Media Wolayta Media Network Gamo Zone Holistic Media Gammo Midea @

 #የገብሬ የሚዲያ ሠራዊትየገብረመስበል ጫላ እና ጴጥሮስ ኃይለማሪያም ገመና ከሰሞኑ በተጀመረው የአመራር ግምገማ የሼባው ገብረመስቀል ጫላ የሴራ አካሄድ በተከዳው የቀድሞ አጋሩ ገሀድ ወጥቷል።...
31/08/2025

#የገብሬ የሚዲያ ሠራዊት

የገብረመስበል ጫላ እና ጴጥሮስ ኃይለማሪያም ገመና ከሰሞኑ በተጀመረው የአመራር ግምገማ የሼባው ገብረመስቀል ጫላ የሴራ አካሄድ በተከዳው የቀድሞ አጋሩ ገሀድ ወጥቷል።

ሼባው ገብረመስቀል በወላይታ ዞን ያለውን ፖለቲካ ለመቆጣጠር እንዲመቸው እና በዞኑ በአረካ ስም አደረጃጀቱን የሚጠብቁለትን 100 የfacebook ሠራዊት አሰማርቶ እየሰራ እንደነበር የቀድሞ የወላይታ ዞን አስተዳዳሪ ጴጥሮስ ወልደማሪያም በግምገማ አዳራሽ በማስረጃ የተግፎ የቀረበውን አምኖ ወላይታን ለመከፋፈል ሲሰራ እንደነበር አምኗል።

እነዚህ አፍራሽ ኃይሎች በሁለት ምድብ የተከፈሉ ሲሆን ግማሹ የዞኑን ፖለቲካ ለማወክ ገሚሱ ደግሞ በጎፋ ዞን፣ በጋሞ ዞን፣ በአሪ እና ጌዴኦ ዞኖች ላይ ትኩረት በማድረግ ከገብረመስቀል ጫላ የሚፈበረኩ የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨት እና ሰላም መንሳት ተልዕኮ ይዘው እየተንቀሳቀሱ ነው።

ይህን ብቻ ሳይሆን ለእያንዳንዱ የሚዲያ ጥፋት ኃይል Samsung a26 ስልክ በዞኑ በጀት ገዝቶ ከመስጠቱም ባሻገር ወርሃዊ ጉርሻከ1000 እስከ 5000 ሺህ ብር ይሰጥ እንደነበር አረካ ታይምስ በደረገችው ማጣራት አረጋግጣለች።

ናትናኤል ጌቾ ለተባለው አክቲቪስት ከወላይታ ዞንና ከተለያዩ ተቋማት የሚላከውን ገንዘብ በሚመለከት በሌላ ጽሑፍ እንመለሳለን።

ወደ ግምገማው ስንመለስ አቶ ጴጥሮስ ኃይለማሪያም ህዝብን የሚያውክ ሠራዊት አደራጅቶ በበጀት እየደገፈ መስራቱን በአደባባይ ቢያምንም በጡት አባቱ ገብረመስቀል ቀጥተኛ ትዕዛዝ እና በዘረፋ ተባባሪው ዶ/ር መሪሁን ጫና አቶ ጴጥሮስ 'C' ተሸልሞ በወኝጀል ቀመጠየቅ እንድያመልጥ ሆኗል።

በአንፃሩ ለገብረመስቀል በሳምንት 200 ሺህ ብር የሚያግዙና በእንስሳት መድኃኒት እና መኖ ግዥ ስም በአራት ወራት ውስጥ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ የተቀራመቱ የገብረመስቀል ቤተሰቦች A ሲያገኙ ጥሩ አፈጻጸም ያላቸው እና ወላይታ ያልሆኑ የጌዴኦ፣ ደራሼ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ፣ እና ጎፋ ዞን ተወላጆች ሰዓት አርፍደዋል በሚል ከአቶ ጴጥሮስ እኩል 'c, ተሰጥቷቸው እንደወንጀለኛ ራሳቸውን እያዩ ነው።

በክልሉ ያለው ፍትሓዊነት ጥያቄ ውስጥ ነው በማለት ነውራቸው እንዳይገለጥ በርካታ ተግባራትን አከናውነዋል። ነገር ግን በዲላ ክላስተር ያለው የረቀቀ አደረጃጀት፣ የምዝበራ እና ዝርፊያ ቡድን በረቀቀ መንገድ ክልሉን እያዳከመ መሆኑ ግልጽ እየወጣ ነው።

አቶ ገብረመስቀል ጫላ ወደ ፓርቲ አመራርነት ከመጡ ወዲህ ዶክተር መርሁን በምክትል ር/መስተዳድር ማዕረግ የዝርፊያ እና ሠራ ቡድኑን እየመሩ በርካታ የዘረፋ እና የመዝበራ ተግባር ማከናወኑን በትላንትናው እለት መዘገባችን ከፍተኛ ድንጋጤ ውሰጥ የከተታቸው ሲሆን አንዳንድ የማደናገሪያ ስራ ለመስራት ሙከራ እያደረጉ መሆኑን ደርሰንበታል።

የወላይታ ተወላጁን ዶ/ር አዲሱን ፈራሚነት በክልሉ የዓሳ ዝርያ ለማሻሻል እና የእንስሳት ምርማነት ለማረጋገጥ የተመደበውን በጀት ለገብረመስቀል ጫላ፣ ፍሬዘር እና መሰል ሙሰኛ ስራ አስፈጻሚዎች በየሳምንቱ አበል የማመላለስ ተግባሩ እስኪቆም ድረስ ትግላችን ይቀጥላል።

ሼባው ገብረመስቀል ጫላ ከተለያዩ ፕሮጀክቶች የነዳጅና አበል በሳምንት 200 ሺህ ብር እየተላከለት አዲስ አበባ ከሚገኙ አስመጪ እና ላኪዎች ጋር እቁብ እየጣለ መሆኑን ከትላንትናው ጽሁፍ በኋላ በinbox የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ትግላችን ይቀጥላል

እውነት ታሸንፋለች!
WT Media Nuso Gamo News Network Fikadu Abate Aliye Wolayta Media Network

ህይወቱ ሊታደግ አልተቻለም  በዛሬው ዕለት ነሐሴ 23/2017 ዓ,ም በጂንካ ዩኒበርስቲ የመብራት ሀይል አደጋ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተስምቷል ። የጂንካ ዩኒበርስቲ ማስመረቂያ አደራ...
30/08/2025

ህይወቱ ሊታደግ አልተቻለም

በዛሬው ዕለት ነሐሴ 23/2017 ዓ,ም በጂንካ ዩኒበርስቲ የመብራት ሀይል አደጋ በሰው ህይወት ላይ ጉዳት ማድረሱ ተስምቷል ።

የጂንካ ዩኒበርስቲ ማስመረቂያ አደራሹን ከጅማሪው እስኬ ፍፃመው ድረስ ስገነባ የነበረው እንጂነር መብራት ስገጣጥም በተፈጠረው የተክኒክ ችግር ህይወቱ አልፏል ።

ግለሰቡን ለማዳን ጥረት የተደረገ ብሆንም ልሳካ ባለመቻሉ ፣ አርፏል :: ሟቹ የአዲስ አበባ ከተማ ተወላጅ መሆኑ ተረጋግጦ በዩንበርስቲው አማካኝነት ወደ አከባቢው ድረስ ለማድረስ ሙከራ እየተደረገ ይገኛል ።

ጣቢያችን በስራ ላይ በገጠመው የመብራት አደጋ ህይወት በማለፉ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለፀ ለወዳጅ ዘመዶች መጽናናትን ይመኛል ::

ሁልጊዜ ጥንቃቄ እንደ መስፈርት እንያዘው ።

#ጂንካ #ሀዘን #መብራትሃይል

‎ ‎‎ነሐሴ 20/12/2017 በአራዳ ቀበሌ  በኪዳነ ምህረት ቀጠና ልዩ ስሙ በተለምዶ ላሾ ታክስ ተራ ተብሎ በሚጠራበት ቦታ ከኬንያ የተላከለትን ፎርጅድ ብር ባለ  #200   #31ሺህ  ብር...
26/08/2025



‎ነሐሴ 20/12/2017 በአራዳ ቀበሌ በኪዳነ ምህረት ቀጠና ልዩ ስሙ በተለምዶ ላሾ ታክስ ተራ ተብሎ በሚጠራበት ቦታ ከኬንያ የተላከለትን ፎርጅድ ብር ባለ #200 #31ሺህ ብር/ከሱቅ ዕቃ ለመግዛት ገብቶ እ ብር ሲያወጣ እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ እየተደረገ ይገኛል ።

‎የ "WT MEDIA" ባለቤት ናትናኤል ጌቾ የገንዘብ ምንጭ የሆነው አቶ ብርሃኔ መስቀል ክንፈ በመታሰሩ በስደተኞች ካምፕ ውስጥ ተቀምጦ ገንዘብ በማጣቱ ለወንድሙ በኩል ፎርጅድ ገንዘብ ማሰራጨት መጀመሩ ተደርሶበታል ።

‎ ።

WT Media
Nuso Dicha Media

መልካም ዜና  ለጤና ባለሙያዎች 🤲 ለጤና ባለሙያዎች ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ምቹ የሥራ ቦታ እና ወጥ የሆኑ የጥቅማጥቅም ፓኬጆች ተግባራዊ እንደሚደረጉ ጤና ሚኒስቴር ለአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔ...
26/08/2025

መልካም ዜና ለጤና ባለሙያዎች 🤲

ለጤና ባለሙያዎች ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ምቹ የሥራ ቦታ እና ወጥ የሆኑ የጥቅማጥቅም ፓኬጆች ተግባራዊ እንደሚደረጉ ጤና ሚኒስቴር ለአለርት ኮምፕሪሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በላከው ደብዳቤ ለማወቅ ተችሏል።

የጨለምተኛ ኃይሎች የስካር ድርግት!በ"Nuso" እና በ"WT Media" ፌክ አካዉንቶች ጀርባ ተሸፍነዉ የዉሼት መረጃ አሰራጭ ቡድኖች ህቡዕ ዓላማቸዉ ግልጽ ነዉ፤ ግቡም በረጅሙ የታቀደ ነዉ። ...
26/08/2025

የጨለምተኛ ኃይሎች የስካር ድርግት!

በ"Nuso" እና በ"WT Media" ፌክ አካዉንቶች ጀርባ ተሸፍነዉ የዉሼት መረጃ አሰራጭ ቡድኖች ህቡዕ ዓላማቸዉ ግልጽ ነዉ፤ ግቡም በረጅሙ የታቀደ ነዉ።

ስልታቸዉም ዝም ካልን ዓላማችን አይሳካም፤ ነጩን ጥቁር፣ ዳቦን ድንጋይ እያልን እንዳልረካና ሁሌም ችግር እንዳለ አስመስለን በማወናበድ እንጠቀማለን ያሉ የዉጥን ኃይሎች ፋሽኑ ያለፈበት እርካሽ አካሄድ ነዉ።

ሁሉም ሰዉ ማወቅ ያለበት አሁን ክልሉ እየተመራበት ባለዉ አካሄድ ህልናቸዉ የሚያዉቀዉ ችግር ስላለ አይምሰላችሁ።

ነጋ ጠባ በክልሉ ፕረዝዳንት እና በሌሎች የክልሉ አመራሮች ላይ የተከፈተዉ የስም ማጥፋት ዘመቻን ስናይ ሁሉም ነገር እኛዉ ካልጋገርንና ካልቀደስን ትክክል መሆን የለበትምና ታልፎ እስክሰጠን ድረስ ይህንን አዉቆ አበደነት ስታይልን ተደራጅተን መምራት ይኖርብናል ብለዉ የተማማሉ ወሮ በላዎች እንቅስቃሴ ነዉ።

በዚህ አካሄድ በዛ ብባል ሁላችንም እንጎዳለን እንጅ የተለየ ጉዳት የሚያስተናግድ አካል ልኖር እንደማይችል በጥልቀት ተንትኖ ካለማየት የሚመነጭ የጨለምተኛ ኃይሎች የስካር ድርግትም ነዉ።

እነዚህ አካላት በወላይታ ህዝብ ስም የሚነግዱ ግን ለወላይታ ህዝብም ይሁን ለሌሎች ክልሉ ህዝቦች ክብር የሌላቸዉ ግልበተኛ ቡድኖች ስለሆኑ መላዉ የክልላችን ህዝቦች ልያወግዛቸዉ ይገባል።
WT Media Wolayta Media Network Gamo Zone Holistic Media Gamo News Network
Gamo times Gammo Midea
Gamo News Network
Degu Desalegn Damota

አቶ Mekonen Moges

አቶ ብርሃነመስቀል ክንፈ አፅባሃ የሚባል ሰው ያኔ ለጁንታው ቡድን ከወላይታ 15ሺህ ሰራዊት ከቀድሞው ዞኑ አመራሮች ጋር ተባብረው ጁንታው ሀገርን እንዲያምስና እንዲያፈርስ መልምለው ስልክ የነ...
24/08/2025

አቶ ብርሃነመስቀል ክንፈ አፅባሃ የሚባል ሰው ያኔ ለጁንታው ቡድን ከወላይታ 15ሺህ ሰራዊት ከቀድሞው ዞኑ አመራሮች ጋር ተባብረው ጁንታው ሀገርን እንዲያምስና እንዲያፈርስ መልምለው ስልክ የነበረን በሀገር ክህደት ወንጀል ልጠየቅ የሚገባ ባንዳ ነው!!!!
Degu Desalegn Damota
Gamo times
Gammo Midea
Gamo News Network
WT Media
Wolayta Media Network
Nuso

Address

Addis Ababa
00111111

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gamo times:

Share