Ethio News Tube

Ethio News Tube Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethio News Tube, Media/News Company, Addis Ababa,Ethiopia, Addis Ababa.

የተፈጥሮ ጥርስን እንደገና ማብቀል የሚችል መድኃኒት በሰው ላይ መሞከር ተጀመረ ጃፓን ሰው ሰራሽ ጥርሶችን (Dentures) እና የጥርስ ተከላዎችን (Implants) ወደ ታሪክ የሚሰድ አዲስ ...
05/11/2025

የተፈጥሮ ጥርስን እንደገና ማብቀል የሚችል መድኃኒት በሰው ላይ መሞከር ተጀመረ

ጃፓን ሰው ሰራሽ ጥርሶችን (Dentures) እና የጥርስ ተከላዎችን (Implants) ወደ ታሪክ የሚሰድ አዲስ ዘመን ሊከፍት የሚችል አብዮታዊ መድኃኒት በሰዎች ላይ መሞከር መጀመሯን አስታወቀች። ይህ ግኝት የተፈጥሮ ጥርስን በሰውነት ውስጥ እንደገና ማብቀል የሚቻልበትን መንገድ ያመላክታል።

የጃፓን ተመራማሪዎች፣ በተለይም በኪዮቶ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ሳይንቲስቶች፣ USAG-1 የተሰኘውን ፕሮቲን የሚገታ መድኃኒት አዘጋጅተዋል። ይህ ፕሮቲን በተፈጥሮ የሰው ልጅ ሦስተኛ ዙር ጥርስ እንዳያበቅል የሚከላከል "ብሬክ" እንደሆነ ይታመናል።

አዲሱ መድኃኒት (TRG-035) ይህን ብሬክ በማስወገድ፣ በሰውነት ውስጥ ያሉትን የተኙ የጥርስ "ቡቃያዎች" እንዲነቃቁ እና አዲስ፣ ተፈጥሯዊ ጥርስ እንዲያበቅሉ ያስችላል ተብሎ ይጠበቃል።

የመድኃኒቱ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሙከራ የተጀመረው በአዋቂ በጎ ፈቃደኞች ላይ ሲሆን፣ ዋና ዓላማው የመድኃኒቱን ደኅንነት ማረጋገጥ ነው። በአይጦችና ፈረሶች ላይ በተደረጉ ቀደምት ሙከራዎች መድኃኒቱ ስኬታማ ውጤት አስመዝግቧል ነው የተባለው።

ሙከራው በተሳካ ሁኔታ ከቀጠለ፣ መድኃኒቱ ጥርስ በማጣት ለሚሰቃዩ ሕፃናትና ለአረጋውያን መፍትሔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ሳይንቲስቶች መድኃኒቱ በ2030 ገበያ ላይ እንዲውል ለማድረግ አቅደዋል።

ይህ ግኝት በዓለማቀፍ የጥርስ ሕክምና ታሪክ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣና ሰዎች የተፈጥሮ ጥርሳቸውን መልሰው እንዲያገኙ ተስፋ የሚሰጥ አዲስ ምዕራፍ ነው።

04/11/2025

ህክምና ባህላዊ እና ዘመናዊ ብሎ መደብ የለም ይለናል ኢትዮጵያዊ ሳይንቲስት ወንድማችን ዮሐንስ ሽፈራው #ኢትዮጵያ #ጤናችን

አስደንጋጭ ግኝት📌አዲስ የአንድሮይድ ተጋላጭነት የባለ ሁለት እርከን መለያ ቁጥሮችን (2FA ኮዶችን) ያለፍቃድ ሊሰርቅ ይችላል ተባለ   | የሳይበር ደህንነት ተመራማሪዎች በአንድሮይድ ስልኮች...
31/10/2025

አስደንጋጭ ግኝት

📌አዲስ የአንድሮይድ ተጋላጭነት የባለ ሁለት እርከን መለያ ቁጥሮችን (2FA ኮዶችን) ያለፍቃድ ሊሰርቅ ይችላል ተባለ

| የሳይበር ደህንነት ተመራማሪዎች በአንድሮይድ ስልኮች ላይ የተገኘ አዲስ እና አደገኛ የደህንነት ጉድለት ይፋ አድርገዋል።

ይህ ግኝት፣ ጠላፊዎች የባለ ሁለት እርከን የማረጋገጫ (2FA - Two-Factor Authentication) ኮዶችን ጨምሮ ሚስጥራዊ መረጃዎችን ያለተጠቃሚው እውቅና እና ያለምንም ልዩ ፍቃድ እንዲሰርቁ ያስችላል።

"Pixnapping" ወይም "Pixel Stealing" የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ የጥቃት ዘዴ፣ አንድሮይድ አፕሊኬሽኖች ምስሎችን በስክሪኑ ላይ እንዴት እንደሚያሳዩ ያለውን ሂደት ይጠቀማል።

ተንኮል አዘል አፕሊኬሽን (Malicious App) በማይታይ ሁኔታ የስክሪን ላይ መረጃን "በመለካት" እና ቀለሞችን "በማወዳደር" መረጃውን ያወጣል።

ይህ አዲስ ጥቃት ከዚህ ቀደም ከነበሩት የተለየ የሚያደርገው፣ እንደ ስክሪን ሾት ማንሳት ወይም ልዩ የስርዓት ፍቃድ (Special Permissions) በፍጹም አያስፈልገውም። በቀላሉ አፕሊኬሽኑ በስልኩ ላይ ተጭኖ መገኘቱ ብቻውን በቂ ነው ተብሏል።

በሙከራዎች ይህን ዘዴ በመጠቀም እንደ Google Authenticator ባሉ አፕሊኬሽኖች የሚፈጠሩትን ባለአንድ ጊዜ የይለፍ ቁጥሮች (OTP) በአጭር ጊዜ ውስጥ መውሰድ እንደሚቻል ተረጋግጧል።

የሳይበር ደህንነት ቡድኖች ይህን ከባድ ተጋላጭነት ለጉግል ሪፖርት ያደረጉ ሲሆን፣ ኩባንያው ለፒክሰል (Pixel) እና ለሌሎች የአንድሮይድ ስልኮች የደህንነት ማሻሻያዎችን (Security Patches) እየለቀቀ ነው።

ሁሉም የአንድሮይድ ተጠቃሚዎች የደህንነት ስጋት ውስጥ እንዳይገቡ የስልካቸውን ሲስተም ሶፍትዌር በአፋጣኝ ወደ የቅርብ ጊዜው ስሪት እንዲያሳድጉ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

እንደ መናኸሪያ ኤፍ ኤም ዘገባ ተጠቃሚዎች ከታመነበት Google Play Store ውጪ ከሌሎች ምንጮች አፕሊኬሽን ከመጫን እንዲቆጠቡ ተመክሯል።

  የአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ ቀንና ማታ ተግታችሁ በመስራት አገልግላቿልና ላበረከታችሁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ልባዊ ምስጋናችንን እያቀረብን በሄ...
31/10/2025



የአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ ህዝብን በቅንነትና በታማኝነት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትሉ ቀንና ማታ ተግታችሁ በመስራት አገልግላቿልና ላበረከታችሁ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ልባዊ ምስጋናችንን እያቀረብን
በሄዳችሁበት ሁሉ ቸር እንድገጥማችሁ መልካም ምኞቴ ነው
በርቱልን የኛ አምባሳደሮች ሁለም ከጎናችሁ ነን ....❤❤❤🙏

በመጨረሻም የጠ/ሚ አብይ በይፋ "አሰብ" የኢትዮጵያ መሆኑንና የተወሰደበት መንገድ ህገወጥነትን ፤ በማነኛውም አማራጭ የሚመለስ መሆኑን ማወጅ  በሻዕቢያ  መንደር እጅግ እጅግ ከፍተኛ ነውጥና ...
30/10/2025

በመጨረሻም የጠ/ሚ አብይ በይፋ "አሰብ" የኢትዮጵያ መሆኑንና የተወሰደበት መንገድ ህገወጥነትን ፤ በማነኛውም አማራጭ የሚመለስ መሆኑን ማወጅ በሻዕቢያ መንደር እጅግ እጅግ ከፍተኛ ነውጥና ፍራቻ ፈጥሯል ።

"የፈሩት ይደርሳል የጠሉት ይወርሳል" እንደሚባለው ሻዕቢያዊያን ለ34 ዓመታት ሲፈሩ ሲሰጉ ወጣቱን በሳዋ በረሃ በባዶ ሆድ ስልጠና ሲያሰቃዩ የኖሩበት የዘረፉት የ130ሚሊየን ህዝብ ባህር አሁን ላይ ሳተናው የኢትዮጵ አዲስ ትውልድ ተነስቶለታል።

የኛ ምክር ለሻዕቢያ በሰላም መልሱ ! አልያም ምፅዋና አስመራንም ታጣላቹ ነው ! በአሁኑ የነቃ የበቃ የኢትዮጵያ ትውልድ ላይ ባህር በሩን ዘርፎ በሰላም ቆሞ መሄድ አይቻልም ሰዓቱ እየደረሰ ነው እንላለን ።

በገዛቹት 100 የማይሞላ የዩቱዩብ ባንዳ አትሸወዱ በሚሊዮኖቹ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን ለዚህ ቅዱስ አላማ ፊሽካ እየተጠባበቁ ይገኛሉና ።

ፎርጅድ ሰነዶችን በማዘጋጀት መንግሥት እና ህብረተሰብን ሲያጭበረብር የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ።ዎላይታ ሶዶ  ጥቅምት 20/2018 ዓ.ም (ደኢፖኮ)በዎላይታ ሶዶ ከተማ ውስጥ አራዳ ቀበ...
30/10/2025

ፎርጅድ ሰነዶችን በማዘጋጀት መንግሥት እና ህብረተሰብን ሲያጭበረብር የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ።

ዎላይታ ሶዶ ጥቅምት 20/2018 ዓ.ም (ደኢፖኮ)

በዎላይታ ሶዶ ከተማ ውስጥ አራዳ ቀበሌ የተለያዩ ተቋማት ማህተም እና ሃላፊዎች ፊርማ በማስመሰል ፎርጅድ ሰነዶችን አዘጋጅቶ መንግሥት እና ህብረተሰብን ሲያጭበረብር የነበረ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን የአራዳ ቀበሌ ፖሊስ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ደርጉ አሳሌ ገለፁ።

ማቱሳል ፊሊጶስ የተባለ ይህ ተጠርጣሪ በመርካቶ ዩሿዋ ቀበሌ ልዩ ስሙ ገበያ አካባቢ ነዋሪ ሲሆን በርካታ ዓመታትን የተለያዩ ሰነዶችን በማስመሰል ህብረተሰቡን ሲያጭበረብር የነበረ መሆኑን ነው አዛዡ የጠቆሙት።

በመሆኑም በቁጥር 19 ለሚሆኑ ሰዎች በፎርጅድ የተለያዩ ወረዳዎችና ከተማ አስ/ር እንዲሁም የት/ት ጽ/ቤቶች ኃላፊ ፊርማ በማስመሰል እየፈረመ ፤ የቅጥር ፎርሞችንም አስመስሎ በመስራት ብር እየተቀበለ የቆዬ ቢሆንም ህብረተሰቡ ባደረሰው ጥቆማ መሠረት ሊያዝ ችሏል።

ግለሰቡ በድምሩ 2,280,00/ሁለት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰማንያ ሺህ /ብር በህገወጥ መንገድ መሰብሰቡንም ተናግረዋል።

ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሎ ተጨማሪ ምርመራ እየተደረገ መሆኑንም የአራዳ ቀበሌ ፖሊስ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ደርጉ አሳሌ ጨምረው ገልጸዋል።

በአጠቃላይ ህብረተሰቡ መሰል አጨበሮባሪዎች ራሱን መከላከል እና ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት የዎላይታ ሶዶ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር ሀብታሙ አሰፋ አሳስበዋል ።

በጀግንነት መጠበቅ በሰብዓዊነት ማገልገል!

 #የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ ኣፍወርቂ የዩኒቨርስቲ መግቢያቸው ማመልከቻ (ፎርም)፤ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ - 1957 ዓ.ም በእኛ የትምህርት ስርዓት ተምሮ ነው እንግዲህ አገር ለ...
29/10/2025

#የኤርትራው ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ ኣፍወርቂ
የዩኒቨርስቲ መግቢያቸው ማመልከቻ (ፎርም)፤
ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ - 1957 ዓ.ም
በእኛ የትምህርት ስርዓት ተምሮ ነው እንግዲህ አገር ለመገንጠል የበቃው።

የማዳበሪያ ጉዳይ‼️የማዳበሪያ አቅርቦት ላይ የሚደረገዉ  ቁጥጥር ከግብርና ሚኒስቴር ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ተዛወረ።የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከቻይና የገባውን ደረጃውን ያ...
21/10/2025

የማዳበሪያ ጉዳይ‼️
የማዳበሪያ አቅርቦት ላይ የሚደረገዉ ቁጥጥር ከግብርና ሚኒስቴር ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢሮ ተዛወረ።
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከቻይና የገባውን ደረጃውን ያልጠበቀ ማዳበሪያ ተከትሎ፣ ወሳኝ በሆነው የግብርና ግብዓት አቅርቦት ላይ ቀጥተኛና ወሳኝ ቁጥጥር መውሰዱን አስታወቀ። ጽሕፈት ቤቱ የማዳበሪያ ቅሌቱን በጥልቀትና በግልጽ ለመመርመር ልዩ ከፍተኛ ደረጃ ኮሚቴ ማቋቋሙን ተሰምቷል።

በዚህ አዲስና የተጠናከረ አመራር፣ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽሕፈት ቤት የአገሪቱ ዋነኛ የግብርና ግብዓት አቅራቢ የሆነውን የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ኢግሥኮ) ሥራዎችን በበላይነት ይመራል።

ይህን ተከትሎ የኢግሥኮ እና የኢትዮጵያ ባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎት (ኢባትሎ) ከፍተኛ ሥራ አስፈጻሚዎች እንዲሁም የቦርድ ሰብሳቢዎች ሙሉ ለሙሉ ተቀይረዋል።

ባለፉት ጊዜያት ማዳበሪያ ወደ ሀገር ዉስጥ መግባቱን የሚቆጣጠረው የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ቦርድ ሊቀመንበር የግብርና ሚኒስትር የነበረ ሲሆን ሌሎች ማለትም የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና ኢባትሎ የመሳሰሉ ቁልፍ ባለድርሻ አካላት አባላት ነበሩ።

ይሁን እንጂ፣ በቅርብ ጊዜ ማዳበሪያ የጫኑ መርከቦች ጅቡቲ ከደረሱ በኋላ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የካቢኔያቸው ኃላፊ ቦርዱን በቀጥታ እንዲመሩ ሾመዋል።

በአዲሱ መዋቅር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ እና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር የሆኑት ወይዘሮ ዓለምፀሐይ ጳውሎስ የኢግሥኮ የዳይሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ መሆናቸውን ለመረዳት ትችሏል።
“ዓለምፀሐይ የቀድሞው ቦርድ አባል ነበረች፣ ግን አሁን ያለችበት ቦታ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ የፖለቲካ ትኩረት በሚያሻው ምርት ላይ ቀጥተኛ ቁጥጥር መውሰዳቸውን ያመለክታል” ብለዋል።

አዲሱ የኢግሥኮ ቦርድ የግብርና ሚኒስትሩን አቶ አዲሱ አረጋን እንደ ምክትል ሰብሳቢ፣ የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታከለ ኡማን እና የግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሤን እንደ አባላት አካቷል።

Via Inbox የወላይታ ፖለቲከኞች ግጭት ጠማቂዎች ሆነዋል።እውነት አንተ ለእውነት የምትታገል ከሆነ ይህችን ጽሁፍ ሳትቀንስ ሳትጨምር ፖስት አድርግ።የማልማት አቅም የትግል አቅጣጫ ያጡት የወ...
21/10/2025

Via Inbox የወላይታ ፖለቲከኞች ግጭት ጠማቂዎች ሆነዋል።

እውነት አንተ ለእውነት የምትታገል ከሆነ ይህችን ጽሁፍ ሳትቀንስ ሳትጨምር ፖስት አድርግ።

የማልማት አቅም የትግል አቅጣጫ ያጡት የወላይታ ፖሌቲከኞች ህዝቦችን መከፋፈል እንደ ትግል አቅጣጫ ተያይዘዋል።

ከሲዳማ፣ ከከንባታ፣ ከጋሞ፣ ከጎፋ እና ወንዝ ተሻግረው ከዳውሮ ጋር ግጭት ውስጥ የሚገኙት የወላይታ እንጭጭ ፖሌቲከኞች የግጭት አጀንዳ ክልሉን ከማተራመስ በቀር ለወላይታ ህዝብ አንዳች የሚፈይድ አይደለም።
ወላይታ ፖለቲከኞች ግጭት ጠማቂዎች መሆናቸውን ከዚህ በላይ ምን ያረጋግጣል?

አንድነት በመሸርሸር ልዩነትን በመካብ የሚታወቁት የወላይታ ፖለቲከኞች በኮንሶ እና ሙርሲ፣ ደራሼን ከአሌ፣ ኮሬን ከኮንሶ፣ በጋሞ እና ወላይታ፣ በኮንሶ እና በጸማይ፣ በባስኬቶ እና ጎፋ፣ በአሪ እና በና እንዲሁም በአሪ እና ማሌ ብሔረሰቦች ዘንድ ጥርጣሬ፣ ግጭት እና እርስ በርስ ጦ።re*ነt በመቀስቀስ በአከባቢው ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ጉዳት ማድረሳቸው አይዘነጋም።

የወላይታ ፖለቲከኞች ግጭት ጠማቂዎች መሆናቸውን ከዚህ በላይ ምን ያረጋግጣል?

በሌላ በኩል አንድ ብሔር የሆኑ ህዝቦችን በጎፋ ዞን ኡባ ደብረጸሓይ ወረዳ፣ በጋሞ ዞን ቁጫና አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳዎች ላይ አዲስ ብሔር ለመፍጠር ከፍተኛ በጀት መድበው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ።

ይህ ደግሞ በእምነት ተቋማት እና ለህዝብ ልማት እሰራለሁ ብለው በገቡ NGO አስተባባሪነት ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በወላይታ ፖለቲከኞች የተስፋፊነት ልክፍት የተጀመረ መሆኑ የአደባባይ ሀቅ ነው።

በተለይ በጎፋ ጋዜ ብሔረሰብ ብለው የጀመሩት መርዝ የኡባ ደብረጸሓይ ወረዳ እስከአሁን እንዳይረጋጋ አድርጎታል። በተመሳሳይም በጋሞ ዞን ላይ የጀመሩት መጠነሰፊ የመከፋፈል አጀንዳ ላይ የወላይታ ልሂቃን በስፋት የተሳተፉበት በመሆኑ ስር የሰደደ የጥላቻ እና የመጠፋ_⛔️ፋት ነጋሪት እየጎሰመ ነው።

ከዚህ ቀደም በፖለቲካው መድረክ የተሸነፈው የተስፋዬ ይገዙ ቡድን በ Excellency Center አሁን ደግሞ ገብረመስቀል ጫላ wolaita times (wt media) admin በመሆን በተመሳሳይ መልኩ ክልሉን እየበጠበጡ ይገኛሉ።

ለምን ተስፋዬ ይገዙ ፌዴራል ሲሄድ Excellency ጠፋ Wt እንዴት አሁን አንሰራራ? በድርቅና እኔ አይደለሁም ካላለ በቀር WT Media የገብረመስቀል እና ጌታሁን ጋረደው የሚመሩት ነው።
⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️⛔️
እና እንደምትልልን ከዚህ በኋላ እንደ ህዝብ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ፣ ጎፋ እና አሪ ዞን ህዝቦች ግልጽ እርምጃ እንወስዳለን ብለውሃል በልልኝ። ማንም ማንንም አክስሞ መኖር አይችልም!!!
ብራይሌ ላይ በ10 ሺህ ዘላይታ እየኖረ 5000 ኮንሶ ሰላማጎ ስለመኖሩ ወላይታ ግጭት እየቀሰቀሰ በሰላም የሚኖር ከሆነ የዋህነት ነው!!!

ሰላም በለው!
እውነት ያሸንፉል!

መንገድ አሳዮታለሁ በማለት ከ70 ዓመት አዛዉንት  ላይ 14ሺ ብር ሰርቆ የተሠወረው ግለሰብ ተያዘ።ወላይታ ሶዶ መስከረም 6/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ) በወላይታ ሶዶ ከተማ በአራዳ ቀበሌ ክልል በ...
16/09/2025

መንገድ አሳዮታለሁ በማለት ከ70 ዓመት አዛዉንት ላይ 14ሺ ብር ሰርቆ የተሠወረው ግለሰብ ተያዘ።

ወላይታ ሶዶ መስከረም 6/2018 ዓ/ም(ደኢፖኮ) በወላይታ ሶዶ ከተማ በአራዳ ቀበሌ ክልል በዋጃ ቄሮ ቀጠና ላይ ተጠርጣሪው ግለሰብ ነዋሪነታቸው ዋጃ ቄሮ የሆነው አዛውንት 14000/አሥራ አራት ሺህ /ብር ይዘው ሲጓዙ አይቶ መንገድ ልምራዎት በማለት ከተጠጋቸው በኋላ በኪሳቸው ያለውን ገንዘብ ሰርቆ ልብስና ጫማ ገዝቶ ቀሪዉን 4000/አራት ሺህ /ብር በእጁ ይዞ እያለ ግል ተበዳዩ ለፖሊስ በሰጡት ጥቆማ እጅ ከፍንጅ ተይዞ ምርመራ እየተጣራበት መሆኑን የሶዶ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ያደረሰን መረጃ አመላክቷል።

Address

Addis Ababa,Ethiopia
Addis Ababa
00111111

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio News Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethio News Tube:

Share