Gamo times

Gamo times Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo times, Media/News Company, Addis Ababa.

ምናልባትም ከባድ ሁኔታ ውስጥ ሁነሽ ይሆናል ያመንሽው ከድቶሽ ተስፋ ቆርጠሽ ይሆናል ግን ያንን የህመም የድካም ስሜት ያሳለፍሽበትን ጊዜ የ 9 ወራትን ህመም መርሳት አልነበረብሽም ::ዋናውን ...
26/05/2026

ምናልባትም ከባድ ሁኔታ ውስጥ ሁነሽ ይሆናል ያመንሽው ከድቶሽ ተስፋ ቆርጠሽ ይሆናል ግን ያንን የህመም የድካም ስሜት ያሳለፍሽበትን ጊዜ የ 9 ወራትን ህመም መርሳት አልነበረብሽም ::

ዋናውን ክፉውን ጊዜ አልፈሽ ወልደሽ አቅፈሽ ስመሽዋል ጠረንሽን ጠረኑን አይተሻል ካሁን በኋላ የከፉ ግዚያት አይመጡም ነበር ምናለ ትንፋሽ ወስደሽ በነበር አድጓል እኮ አልችልም ካልሽም አሁን የኛ ጊዜ የቱንም ክፉ ነው ቢባልም ተስፋ ላጡት ተስፋ እየሰጠን ነበር እርዱኝ ብለሽ በነበር ::!

ይህ ህፃን በጉጂ ዞን ኦዶ ሻኪሶ ወረዳ ሳዊና መንደር ዉስጥ ተጥሎ የተገኘ ነዉ😭💔

 ! !የመንግስት ሠራተኞች 15% የግብር ቅናሽ ተፈቅዶ በሥራ ላይ ውሏል የሚለው ከእውነት የራቀ ሀሰተኛ መረጃ ነው!  : የገንዘብ ሚኒስቴር የተቋሙን ስምና መለያ በመጠቀም " ለክልሎችና ከተ...
21/05/2026

!
!

የመንግስት ሠራተኞች 15% የግብር ቅናሽ ተፈቅዶ በሥራ ላይ ውሏል የሚለው ከእውነት የራቀ ሀሰተኛ መረጃ ነው!

: የገንዘብ ሚኒስቴር የተቋሙን ስምና መለያ በመጠቀም " ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ስለ ስራ ግብር ቅናሽ እና የደመወዝ መጠን መሰረት ያደረገ ማሻሻያ " ተብሎ እየተሰራጨ የሚገኘ መረጃ ሀሰተኛ ነው ሲል አሳውቋል።

ግጭት ተቀስቅሷል‼️ከትናንት በስተያ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም በኦሮሚያ እና በሲዳማ ድንበር በምስራቅ ሲዳማ ዞን በጭሬ ወረዳ ጉበ ሔማ ቀበሌ በገበያ ቦታ ላይ በተነሳ አለመግባባት ምክንያት ...
21/05/2026

ግጭት ተቀስቅሷል‼️
ከትናንት በስተያ ግንቦት 10/2018 ዓ.ም በኦሮሚያ እና በሲዳማ ድንበር በምስራቅ ሲዳማ ዞን በጭሬ ወረዳ ጉበ ሔማ ቀበሌ በገበያ ቦታ ላይ በተነሳ አለመግባባት ምክንያት በሲዳማ እና በኦሮሞ ማኅበረሰብ አባላት መካከል ግጭት ተቀስቅሷል። በዚህም ምክንያት የሰው ሕይወት የጠፋ ሲሆን፣ በርካታ ወገኖቻች ጉዳት እንደደረሰባቸው የአካባቢው ምንጮች ለአዩዘሀበሻ ገልፀዋል።
እስካሁን ባለው መረጃ የአንድ ሰው አስከሬን እና 7 የቆሰሉ ሰዎች ወደ ጤና ጣቢያ የገቡ ሲሆን፣ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ሌሎች ሰዎችም መጎዳታቸው ታውቋል።
ግጭቱ አድማሱን አስፍቶ በሰብሎች ላይ ጭፍጨፋ ተፈፅሟል፣ ቤቶች ተቃጥለዋል።
(አዩዘሀበሻ)
=====================

  በክልል ምክር ቤት በአድሱ አዋጅ ከአንድ ምርጫ ክልል አምስት ሰዎች ይወከላሉ የጋሞ ዞን የወከላቸውን ሰዎች የስም ዝርዝር ከታች ይገኛል በሰዎች ላይ ያላችሁት አስተያየት በኮሜንት አሳውቁን...
31/12/2025

በክልል ምክር ቤት በአድሱ አዋጅ ከአንድ ምርጫ ክልል አምስት ሰዎች ይወከላሉ የጋሞ ዞን የወከላቸውን ሰዎች የስም ዝርዝር ከታች ይገኛል በሰዎች ላይ ያላችሁት አስተያየት በኮሜንት አሳውቁን የስምንቱ የምርጫ ክልል ተወካዮች አሉ !!
ውስጥ ብልፅግና ለኢፌደሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለ 2018 ዓ.ም ምርጫ በዕጩነት የቀረቡ ግለሰቦች ለብልፅግና ፓርቲ ተብሏል።

ሥነምግባራዊ ትውልድ ለዲሞክራሲ፣ ለሰላም እና ለልማት። ሚንስትር/ሚ ንስተር፣ ዴታ እና ቋሚ ኮሚቴ አባል እና ሰብሳቢ የመሆን ዕድል አላቸው።

‎1. 🇧🇪.አቶ ታገሰ ጫፎ
‎2. 🇧🇪 .ወ/ሮ አለምፀሃይ ጰዉሎስ
‎3 .🇧🇪 .አቶ . እስያስ እንድሪያስ
‎4. 🇧🇪.ፕሮፈሰር ይስሃቅ ኮቾሬ
5. 🇧🇪 ወ/ሮ አዘብ ዘውዴ
‎6. 🇧🇪. ዶ/ሮ ኤዞ እማቆ
‎7. 🇧🇪 .ዶ/ር አዳነ አልቶ
8. 🇧🇪 .ወ/ሮ ልሳነወርቅ ካሳዬ

‎1 ለክልል ምክር ቤት ዕጩዎች

‎አቶ . ሐክሜ አየለ
‎ዶር . አንተነህ ካሳዬ
ወ/ሮ. አለምነሽ ደመቀ
አቶ . በረጋ ጋንችሬ
ዶ/ር ቦርሴ ቦሼ

‎2. ክልል ለክልል ምክር ቤት ዕጩዎች

አቶ .ገዛኸኝ ጋሞ
‎አቶ . ውበ ከድር
‎ወ/ሮ ታርኩ ኦይቻ
ወ/ሮ . ምትክነሽ ጨለቀ
አቶ . እድሬ እርኮ

‎3. ለክልል ምክር ቤት ዕጩዎች

ዶ/ሮ አሸናፊ ኦይዳ
‎ወ/ሮ አንቃሬ አሰኔ
‎አቶ .ሰፉ ዋናቃ
አቶ .እልጎ እንጄ
አቶ . መስፍን ሞላ

‎4. ለክልል ምክር ቤት ዕጩዎች

‎አቶ ይስማ ከተማ
‎ዶ/ር ብርሃኑ ገመዳ
‎አቶ. አየለ ቱንጄ
አቶ ማሔ ቦዳ
አቶ እንዳልካቸው አስራት

‎5. ለክልል ምክር ቤት ዕጩዎች

ዶ/ር . ታረቀኝ ማርካ
‎አቶ. ወርቁ ወልደ
‎አቶ .አሸናፊ ሻሌ
አቶ .አብርሃ አይካ
አቶ .ሻምበል ቦኩ

‎6. ለክልል ምክር ቤት ዕጩዎች

‎አቶ . መኮንን ሞጎስ
‎ዶ/ር . መስፍን ማንዛ
‎አቶ . ዳርዛ ደምሴ
አቶ ዳንኤል ደሳለኝ
አቶ አስፋው አልኤና

‎7. ለክልል ምክር ቤት ዕጩዎች

አቶ . ጥላሁን ከበደ
‎ዶር .ደምስ አድማሱ
‎ወ/ሮ .ትማም አለሙ
አቶ. ሰብስበ ቡናበ
አቶ . ዳዊት ታደሰ

‎8. ለክልል ምክር ቤት ዕጩዎች

ዶ/ር . አለኔ አበጀ
ዶ/ር ታርኩ ዘካርያስ
አቶ . አይሱጼ ህሎታ
‎አቶ . ሙናዬ ሞሶሌ
‎አቶ . አዴ አለሙ

ገንቢ አስተያየታችሁ ይጠበቃል።

በጋሞ ዞን በገረሴ ዙሪያ ወረዳ 4 ክላሽንኮብ መሣርያ ከ90 ጥይት ጋር ወደ ዛይሴ ልሻገር የነበረ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋለ።ታህሳስ 8/2018 ዓ.ም (የገረሴ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽ...
17/12/2025

በጋሞ ዞን በገረሴ ዙሪያ ወረዳ 4 ክላሽንኮብ መሣርያ ከ90 ጥይት ጋር ወደ ዛይሴ ልሻገር የነበረ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ዋለ።
ታህሳስ 8/2018 ዓ.ም (የገረሴ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉ/ጽ/ቤት)
የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ የማህበረሰብ አቀፍ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ረዳት እንስፔክተር እንግዳ ሞኮኒን እንደገለጹት ከደራሼ ወደ ጋቶ አካባቢ ከዚያ ወደ ኤልጎ ሉዳ አካቢብ በሦስት እግር ባጃጅ አምጥተው ካስረከቡ በኃላ ወንጀለኛው በራሱ ሞተር ተቀብሎ ወደ ገረሴ ዙሪያ ወረዳ ስገባ በኬላ አካባቢ ያሉ ፖሊሶችን ጥሶ አልፎ ወደ ዳንብሌ አቶራ ስገባ ህብረተሰቡና ፖሊስ በመተባበር ስያሳድዱ ጫካ ውስጥ በመግባት የያዘውን ሞተርና መሣሪያ ጥሎ ስፈረጥጥ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መደረጉን አስታውቋል።

የገረሴ ዙሪያ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ አስተዳዳር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታረቀኝ ፀጋዬ በበኩላቸው ዛሬ በቀን 8/4/2018 በ12:00 ሰዓት ላይ አራት የክላሽኮብ መሣርያ ከ90 ጥይት ጋር በህብረተሰቡ ጥቆማና ክትትል መያዙን አስታውቋል።

ወንጀለኛው በገረሴ ዙሪያ ወረዳ በኮይራ ሙኩላ ቀበሌ በሻሌ ቀበሌ ነዋሪና ሞተረኛ ሆኖ ሳለ በዘይሰ አካባቢ ለሽብርተኞች መሣሪያ አቀባይ መሆኑ የሚያሳዝን ቢሆንም በሕዝቡ ትብብር ልያዝ ችሏል ብለዋል።

በሕዝብ ወስጥ ሆነው ሕዝብን ለማሸበር የሚሠሩት ስላሉ ህብረተሰቡ አስሶ እንዲያጋልጥ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን የራስን ሰላም በራስ ለማስጠበቅ ማህበረሰቡ ጠንክረው እንድሠሩ አሳስቧል።
የማህበራዊ ድህረገጻችንን follow

ሃይለማርያም ደሳለኝ፤  አትሞክረው !አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን በዲንነት እንዲመራ ተመድቦ አቅቶት ፊቱን ወደ ፖለቲከኝነት ያዞረው፤ በፖለቲከኝነት የደቡብ ክልልን በፕሬዝዳንትነት እንዲመራ ተመር...
16/12/2025

ሃይለማርያም ደሳለኝ፤ አትሞክረው !

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲን በዲንነት እንዲመራ ተመድቦ አቅቶት ፊቱን ወደ ፖለቲከኝነት ያዞረው፤ በፖለቲከኝነት የደቡብ ክልልን በፕሬዝዳንትነት እንዲመራ ተመርጦ አንድም የሚጠቀስ መልካም ነገር ሳይሰራ የተሰናበተው፤ በመጨረሻም የመለስ ዜናዊ ሞት በሰጠው የጠቅላይ ሚኒስትርነት ስልጣን እድል ሃገሪቱን ቀውስ ውስጥ ከቶ ከቀውስ ማውጣት ሲያቅተው ስልጣኑን አስረክቦ የሸሸው ሃይለማርያም ደሳለኝ አሁን የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ለመምራት ሊወዳደር ነው በሚል እየተወራለት ነው። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለሃገራቸው ባከናወኑት ተግባር ስኬት አስመዝግበው ብቃታቸው የተመሰከረላቸው ሰዎች የሚታጩበት እንጂ የውዳቂዎች መጠራቀሚያ አይደለም። ሃይለማርያም ባይሞክረው መልካም ነው!
WT Media Nuso Wolayta Media Network Gamo News Network

‎" ተማሪው ከዋናዉ ቤተ መጽሐፍ ሰገነት ላይ ወድቆ ወደ አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ነው ህይወቱ ያለፈው " - የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ‎➡️ ‎" አስክሬኑ ዛሬ ወደ...
12/12/2025

‎" ተማሪው ከዋናዉ ቤተ መጽሐፍ ሰገነት ላይ ወድቆ ወደ አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ነው ህይወቱ ያለፈው " - የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች

➡️ ‎" አስክሬኑ ዛሬ ወደ ቤተሰቦቹ ተሸኝቷል፤ የሻማ ማብራት መርሃግብር ይደረጋል " - የተማሪዎች ሕብረት

‎በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዓመት የአካውንቲንግ እና ፋይናንስ ትምህርት ክፍል ተማሪ የነበረው ጥላሁን ባዘዘዉ ትላንት ምሽት በጫሞ ካምፓስ ከዋናዉ ቤተ መጽሐፍ ጣሪያ ሰገነት ላይ ወድቆ ወደ አርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ከደረሰ በኋላ ሕይወቱ ማለፉን ጉዳዩን በቅርበት እናዉቃለን ያሉ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጫሞ ካምፓስ ተማሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

‎" ተማሪው ባሳለፍነዉ ዐርብ ለሕክምና ወደ አዲስ አበባ ሄዶ እሁድ መመለሱን አረጋግጠናል " ያለን የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አንድ የተማሪዎች ሕብረት አመራር ትላንት ማምሻውን በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ጫሞ ካምፓስ ከሚገኘዉ ዋናው የተማሪዎች ቤተመጽሐፍ ጣሪያ ላይ ወድቆ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ በዚያው ሕይወቱ ማለፉን አብራርቷል።

‎ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሳውላ ካምፓስ በመስከረም ወር የአካውንቲንግ እና ፋይናስ የትምህርት መስክ በመምረጥ ወደ ጫሞ ካምፓስ መምጣቱን የገለፁት ተማሪውን በቅርበት የሚያዉቀው አንድ የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ " የተለየ ሕመምና ባህሪ አይቸበት አላዉቅም " ሲል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

‎'' አስክሬኑ ማድረቂያ እንዳይወጋ የተማሪዉ ቤተሰብ ፈቃደኛ ባለመሆናቸውና 'አስክሬን እናስመረምራለን' በማለታቸው ወደ አዲስ አበባ በፖሊስ እና የተማሪዉ አብሮአደግ ጓደኛ ተልኳል " ያሉት የተማሪ ሕብረት አመራሮች በሚቀጥሉት ቀናት የሻማ ማብራት ስነስርዓት በዩኒቨርሲቲዉ ግቢ ዉስጥ እንደሚከናወን ገልፀዋል።

‎ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተማሪው አሟሟት ጋር በተያያዘ ከጋሞ ዞን ፖሊስ እና ከዩኒቨርሲቲዉ የበላይ አመራሮች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ሙከራ አድርጓል።

የዞኑ ፖሊስ አዛዥ " በአካል ካልተገኛችሁ መረጃ አልሰጠም " በማለታቸው የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት በበኩላቸው ስብሰባ ውስጥ መሆናቸውን በመግለፃቸዉ በዚህ መረጃ አልተካተተም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ

11/12/2025

የዚህን ዱሪዬ ምክር ስሙልኝ.🤔

የጋሞ ሕዝብን ወክላችሁ ከፌዴራልና ከክልል ጀምራችሁ ያላችሁ የጋሞ አመራሮች ታሪክ ይፋረዳችኃል ።የጋሞ አጥንት ወንበራችሁን እሾክ ያድርግላችሁ!
11/12/2025

የጋሞ ሕዝብን ወክላችሁ ከፌዴራልና ከክልል ጀምራችሁ ያላችሁ የጋሞ አመራሮች ታሪክ ይፋረዳችኃል ።
የጋሞ አጥንት ወንበራችሁን እሾክ ያድርግላችሁ!

Address

Addis Ababa
00111111

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share