Enor Muslims media

Enor Muslims media This is Anor Muslim Media, by the will of Allah! Fast and reliable daily information will be provided

በጉራጌ ዞን ከ2000 በላይ የእኖር ሙስሊም ተማሪዎችን በአለባበሳቸው ሳቢያ ከትምህርት ገበታቸው እንዲርቁ በማድረግ ረገድና ከዚያም በኋላ ያሻውን ሙስሊም ሲያሳስር፣ ሲያስገርፍና ሲያሰቃይ የነ...
18/05/2023

በጉራጌ ዞን ከ2000 በላይ የእኖር ሙስሊም ተማሪዎችን በአለባበሳቸው ሳቢያ ከትምህርት ገበታቸው እንዲርቁ በማድረግ ረገድና ከዚያም በኋላ ያሻውን ሙስሊም ሲያሳስር፣ ሲያስገርፍና ሲያሰቃይ የነበረው የዞኑ የጸጥታ ኃላፊ አቶ ያዕቆብ ግርማ ከኃላፊነቱ ተነስቷል።

ለእኖር ሙስሊሞች የሚጠቅመው፤ የግለሰቡ ከኃላፊነቱ መነሳት ብቻ ሳይሆን እስካሁን በፈጸማቸው ዘግናኝ ወንጀሎች ተጠያቂ መደረግ አለበት። ከዞኑ ጀምሮ እስከ ጉንችሬ ድረስ እንዲሁም እስከ ፌዴራልና ክልሉ ድረስ ያለው ሰንሰለቱ ተጣርቶ ግብረ አበሮቹም ላይ ተገቢው እርምጃ ሊወሰድ ይገባል።

የእኖር ሙስሊም ተማሪዎችና ቤተሰቦቻቸውም የሞራል ካሳ ተክሰው፤ ተማሪዎቹ የእምነት ነፃነታቸው ተከብሮ በክብር በኒቃባቸው ሊማሩ ይገባል።

ተገቢው መፍትሄ እስኪ ገኝ ድረስ እስከ ድል ደጅ በአላህ ፈቃድ ትግላችን ይቀጥላል።

⚠️⚠️⚠️ የጉንችሬ ጉዳይ የሚመለከተው ለጉንችሬ ሙስሊሞች ብቻ ነው ወይስ አጠቃላይ  የሙስሊሞች ግዳይ ነው ???    ጀመዓውን የሚያንቀሳቅሱት የጉንችሬ ሙስሊም ወጣቶች  በሙሉ ታስረዋል ። ...
18/05/2023

⚠️⚠️⚠️ የጉንችሬ ጉዳይ የሚመለከተው ለጉንችሬ ሙስሊሞች ብቻ ነው ወይስ አጠቃላይ የሙስሊሞች ግዳይ ነው ???



ጀመዓውን የሚያንቀሳቅሱት የጉንችሬ ሙስሊም ወጣቶች በሙሉ ታስረዋል ። አሉን የምንላቸው ጀግና አባቶቻችንም ተመርጦ ታስረዋል። የታሰሩት ወጣቶችና አባቶች ቁጥር ከ40 አልፈዋል። የተቀሩት ከእስራት ያመለጡት ከመታሰር ከተማውን መልቀቅ መርጠዋል። አሁን ላይ ወጣቱን ጨረስሰው አስረው ከከተማ አባረው ሲያበቃ ተማሪዎችን ለማሰር የእስራት ትዛዝ አውጥተው ማሰደድ ጀምረውታል።

#ከጉንችሬ ውጭ የምንገኝ _ሙስሊሞች የኛ ሚና ምንድ ነው ። ለዲኑ የሚታገሉት ጀግና ወጣቶችና አባቶች በሙሉ ታስረዋል። አሁን ያሉ ወጣቶች ከቤት ከወጡ ይታሰራሉ።

ትግሉን ለማክሸፍ ሙስሊም ወጣቱን በማሰርና በመደብደብ ለዲኑ የሚታገል ወጣት እንዳይኖር ትግሉን አቀጭጮታል።

ላይ የጉንችሬ ሙስሊሞች ጉዳዩ ከቁጥራቸው ወጥቶ እጃቸው ወደ አላህ ከመዘርጋት ውጭ ምንም አይነት እርምጃ ወደ ፊት የሚሄዱበት አቅማቸው ተማጠዋል።

በላይ አካል መሄድ ያለበቸው በሙሉ በተደጋጋሚ ሄደዋል ጠይቀዋል ማንም መልስ የሚሰጣቸው አጥተዋል። አቤቱታ ካቀረቡባቸው ተቃማቶች ለምሳሌ ከዞን መጅሊስ እስከ ፊደራል መጅልስ ብዙ ግዜ ተመላልሰዋል ምን ያተረፉት ነገር የለም ። ከመንግስት ተቃማቶች መካከል ከጉንችሬ ከተማ ከንቲባ ቢሮ አንስቶ እሰከ ፈደራል ያሉ ሙሉ ተቃማት በሙሉ እስከ ጠቅላይ ሚኒስተር ፅፈት ቤት ድረስ አቤቶታቸውን ቅሬታቸውን አሳውቀዋል። ነገር ግን ድካምን እንጂ መልስ የሚሰጣቸው አንድም የበላይ አካል አላገኙም።

ከጉንችሬ ውጭ የምንገኝ የአዲስ አበባና ሌሎች ከተሞች የምንገኝ ሙስሊሞች ምንድ ነው የኛ ሚናችን‼

ይህ በአላህ ፍቃድ እኖር ሙስሊሞ ሚዲያ ነው‼ አሁን ላይ በእኖር ሙስሊሞች እየደረሰ ያለውን ግፍና ጭቆና አስቾካይ መፍትሄ ይመጣ ዘንድ ፈጣንና ታማኝ ዕለታዊ መረጃዎች በዚህ ሚዲያ የሚቀ.....

 ‼᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗  የጆካ ሽማግሌዎች የሽንገላ ቀናቸው ነው። እንደምታውቁት ከሁለት ሳምንት በፊት ለ10 ቀን ተይዞ የነበረው የሸምግልን ጉደይ ዛሬ ...
18/05/2023


᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗
᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗᎗

የጆካ ሽማግሌዎች የሽንገላ ቀናቸው ነው። እንደምታውቁት ከሁለት ሳምንት በፊት ለ10 ቀን ተይዞ የነበረው የሸምግልን ጉደይ ዛሬ ሀሙስ 9/8/2015 ይቀጥላል።

ቢሆን ሽማግሌዎች የመንግስትን የሴራ ፖለቲካ እያስፈፀሙ እንጂ ጉንችሬ ላይ ምንም አይነት ሰላም እንዲመጣ እየሰሩ አይደለም።

ሳምንት ሽማግሌዎች ቀጠሮ ከያዙባቸው ጉዳዮች አንድ ከሁለቱም ወገን ስለወደመባቹ ጉዳይ የሚያስረዳ ሁለት ሽማግሌ መርጠው በቀጠይ ውይይታቸው ከኑሱ ጋር መሆኑና ሽምግልናው ስለንብረት መሆኑ ገልፀዋል።

ያቶኮረው በወደመው ንብረት እንጂ አንድ አመት ከትምህርት ለተፈናቀሉት የጉንችሬ ሙስሊም ተማሪዎች ጉዳይ እንዳልሆነ የጆካ ሽማግሌዎች በግልፅ "የትምህርት ቤቱ ጉዳይ እኛ አይመለከተንም መንግስት የራሱን ተቃም መምራት ያለበት እሩሱ ነው።" በማለት ስለሙስሊም ተማሪዎች ትምህርት ማጣት ጉዳይ ሽምግልናውን ምንም እንደማይመለከት ተናግረዋል።

ከጎን ትምህርት ቤቱ በአንድ ወር ውስጥ ትምህርት እንዲያጠናቅቅ መግለጫ ሰጥተዋል። የትምህርቱ መጠናቀቅ አለማ ካፊር ተማሪዎች ወደ ቀጣይ ክፍል እንዲሸጋገሩ ለማመቻቸትና ሙስሊሙ ተማሪዎች አንድ አመት የቀጡት ትምህርት ምንም አይነት መፍትሄ ሳያገኙ ከትምህርት እንደተገለለ ለማስቀረት የታሰበት ሴራ ነው።

ደሞ የመንግስትን ሴራ ለማስፈፀም በሽምግልና ስም ቀነ ቀጠሮ እያበዙ ትምህርቱ እንዲቀጥልና የመንግስትን አላማ ለማሳካት ትልቅ አስተዋፆ እያደረጉ ይገኛል ።

⚠️ ማወቅ ያለብን ነገር‼

ጉዳይ ዘንድሮ ካልተፈታ የመብታችን መከበር ጉዳይ ጥያቄ ስር ይገባል።

ተማሪዎች ዘንድሮ መፍትሄ ካለገኙ ቀጣይ አመት ለመማራቸው ምንም አይነት ዋስትና የለንም።

ጉዳይ ዘንድሮ መንግስት ትምህረት ሳያጠናቅቀወ እኛ መፍትሄ ካልፈለግን ቀጣይ አመት ሙተነቂብ እህቶቻችን ወደ ትምህርት መመለሳቸው አለመመለሳቸው ምንም አይነት ዋስትና የለንም።

አገኛለሁ ብሎ አንድ አመት ቤቱ ለተቀመጠው ሙስለም ተማሪ ቀጠይ አመት በዚህ ፅናቱ ለመቀጠሉ ምንም አይነት ዋስትና የለንም።

መንግስት ትምህርቱን ከጠናቀቀ በሃለ ስለሙስሊም ተማሪዎች ብለን ብንጮህ ምንም አይነት መፍትሄ እንደማናስገኝ ጠንቅቀን ማወቅ ይኖርብናል።

………ይቀጥላል።

ይህ በአላህ ፍቃድ እኖር ሙስሊሞ ሚዲያ ነው‼ አሁን ላይ በእኖር ሙስሊሞች እየደረሰ ያለውን ግፍና ጭቆና አስቾካይ መፍትሄ ይመጣ ዘንድ ፈጣንና ታማኝ ዕለታዊ መረጃዎች በዚህ ሚዲያ የሚቀ.....

18/05/2023

This is enor Muslim Media, by the will of Allah! Fast and reliable daily information will be provided to you through this media.

ይህ በአላህ ፍቃድ እኖር ሙስሊም ሚዲያ ነው‼ አሁን ላይ በእኖር ሙስሊሞች እየደረሰ ያለውን ግፍና ጭቆና አስቾካይ መፍትሄ ይመጣ ዘንድ ፈጣንና ታማኝ ዕለታዊ መረጃዎች በዚህ ሚዲያ የሚቀርብላቹህ ይሆናል‼

Address

Addis Ababa
Addis Ababa
6249

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Enor Muslims media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share