Wariye Najiib Dayiib

Wariye Najiib Dayiib ku sodhawaada bogeena si aad wararkena ula.socotaan iyo warbixinada like follow saara aad nala socotaane

01/01/2022

በመላው ዓለም የምትኖሩ ወዳጆቻችን እና ዳያስፖራ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ2022 አዲስ ዓመት አደረሳችሁ"ጠ/ሚ አቢይ አህመድ

ታህሳስ 23 ቀን 2014 - ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ዛሬ የገባውን የ2022 የጎርጎሳውያን አዲስ ዓመት በማስመልከት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስት አቢይ በመልካም ምኞት መግለጫቸው "በመላው ዓለም የምትኖሩ ወዳጆቻችን እና ዳያስፖራ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለ2022 አዲስ ዓመት አደረሳችሁ" ብለዋል በትዊተር ገፃቸው።

31/12/2021
31/12/2021

መንግሥት ከአሸባሪዎች ጋር እንደማይደራደር አስታወቀ

: አገር ዐቀፍ ምክክሩ በሕዝቦች መካከል ብሔራዊ መግባባት ለመፍጠር እንጂ ከአሸባሪዎች ጋር መደራደርን ታሳቢ ያደረገ አይደለም ሲሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን አስታወቁ።

ሚኒስትር ዴኤታው በጎርጎሮሳዊያኑ 2021 የተከወኑ ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮችና በቀጣይ 2022 የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ ከ"ሆርን ሪቪው" ጋር ቃለ ምልልስ አድርገዋል።

በዚህም የውስጥ ችግሮችን መፍታት የውጭ ጫናዎችን ለመቋቋም እንደሚያስችል በማስገንዘብ ብሔራዊ መግባባት በሚለው ሐሳብ ላይ ግልጽነት ሊኖር ይገባል ብለዋል።

የታሰቡት አገራዊ የምክክር መድረኮች በሕዝቡ እና በፖለቲካ ልሂቃኑ መካከል የጋራ መግባባት ማስፈንን ታሳቢ ያደረጉ እንጂ አሸባሪ ከተባሉ አካላት ጋር መደራደር ማለት እንዳልሆነ አሳውቀዋል።

አሸባሪው ትሕነግ አፈጣጠሩ ለአመጽ እንጅ ለሰላም የሚመች እንዳልሆነ አስታውሰው የየትኛውም አገር መንግሥት ከአሸባሪ ድርጅት ጋር ሲደራደር አይተን አናውቅም እኛም አንደራደርም ማለታቸውን ከብልፅግና ፓርቲ የፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል።

30/12/2021

በአዲሱ "ጉንፋን" መሳይ በሽታ ዙርያ ለህዝብ መረጃ ሊሰጥ ይገባል!

ከሰሞኑ ጉንፋን መሰል በሆነ በሽታ እጅግ በርካታ ሰዎች ተይዘዋል። በሽታው በሀገራችን እንዲሁም በአንዳንድ ጎረቤት ሀገራት ተከስቷል፣ በርካታ ሰዎችም በዚህ ዙርያ ማህበራዊ ሚድያ ላይ መረጃ እያጋሩ ይገኛሉ።

ትናንት ዶ/ር ፋሲል መንበረ በተባሉ የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ባልደረባ ከተሰጠ አንድ መረጃ ውጪ ይህ ጉዳይ በሚመለከታቸው የጤና ሚኒስትርም ሆነ የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እስካሁን በሽታው ዙርያ የተሰጠ ማብራርያ የለም።

እየሰማነው ያለው አስደንጋጭ ነው፣ በቢሮዎች እና የስራ ቦታዎች በግምት ከ50% በላይ የሚያስል፣ የሚያስነጥስ እና በህመም ላይ የሚገኝ ሰው እየተገኘ ነው። ይባስ ብሎ አንዳንድ መስሪያ ቤቶች ማንም ሰው በዚህ ሰበብ ከስራ እንዳይቀር እያስጠነቀቁ ይገኛሉ።

ታድያ ይህ ሁሉ ሲሆን ሰፊ ምርመራ ተደርጎ የበሽታው ምንነት ለህዝብ ሊነገር አይገባም? ምልክቱ ከኮቪድ-19 ጋር የሚመሳሰል ስለሆነ የላብራቶሪ ማረጋገጫ ሊደረግ ግድ አይልም?

በሌሎች ሀገራት እንዲህ አይነት ወረርሽኝ ሲከሰት በፍጥነት ምርመራ ተደርጎ የመከላከያ እና መጠንቀቂያ እርምጃዎች ይወሰዳሉ። ይህን ማድረግ ጊዜ ሊሰጠው አይገባም፣ ስለዚህ ለህዝብ መረጃ ይሰጥ።

30/12/2021

አሜሪካ ወደ ቱርክ:ግብጽ: የተባበሩት አረብ ኤሜሬትና ወደ ጎረቤት ሃገሮች ተመላልሳ ኢትዮጵያ ላይ ተጽእኖ ለመፍጠር ከምትሞክር በቀጥታ ከኢትዮጵያ ጋር ብትነጋገር የተሻለ ነዉ።

የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዱና ሙፍቲ

የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሳምንታዊ መግለጫ ሰጥተዋል።

አምባሳደሩ ትኩረት ሰጥተዉ መግለጫ ከሰጡባቸዉ ጉዳዮች መካከል ወደ ሃገር እየገቡ ያሉ የዲያስፖራዎች ጉዳይ ዋንኛዉ ነዉ።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ወደ ሃገር የገቡ ዳያስፖራዎችን በወዳጅነት አደባባይ ደማቅ አቀባበል እንዳደረጉላቸዉ ቃል አቀባዩ በመግለጫቸዉ ጠቅሰዋል።

የአሸባሪዉ ህወሃትን ሴራ ስታጋልጥ የነበረችዉ ጋዜጠኛ ሄርሜላ አረጋዊን ጨምሮ በርካታ ዲያስፖራዎች በቀጣይነት ወደ ሃገር እንደሚገቡ የተናገሩት ቃል አቀባዩ በቆይታቸዉም በተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ እንደሚሳተፉ ገልጸዋል።

በፊንፊኔ ከተማ የሚገኙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን መጎብኘት: የኢትዮጵያን ይግዙ በሚል አላማ በኢግዚቢሽንና ባዛር ላይ እንዲሳተፉ ማድረግ: በግጭቱ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎችን መርዳት: በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ መሳተፍ: የሚሊዮኖች ጉዞና ደም ልገሳ: የኢንቨስትመንት ፎረምና ሲምፖዚየም : የዲያስፖራ አማካሪ ምክር ቤት መሠየም: ዲያስፖራን እንደወላጅ በሚል አላማ ወላጅ አልባ ህጻናትን መርዳት: አርት:ሲኒማና ስፖርት ዳያስፖራዎቹ በቆይታቸዉ የሚሳተፉባቸዉ ዋና ዋና መርሃ ግብሮች መሆናቸዉን አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገልጸዋል።

ዲናስፖራዉ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ወደ ኦሮሚያና ሲዳማ ክልሎች እንደሚንቀሳቀሱም አምባሳደሩ ጠቅሰዋል።

ፐብሊክ ዲፕሎማሲን ከማጠናከር ረገድ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ዉስጥ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ ማዕከል እንደሚከፈትና በመከፈት ላይ እንደሚገኝ ቃል አቀባዩ ገልጸዋል።

የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመቶ ቀናት የስራ አፈጻጸም መገምገሙ: የተቋሙ የመዋቅር ለዉጥ ዉጤታማ መሆኑ : ሚኒስቴሩ ዲያስፖራዉንና የኢትዮጵያን ወዳጆች በማንቀሳቀስ የተሻለ ስራ መስራቱ በመግለጫዉ ተጠቅሷል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሃፊ በተወካያቸዉ በኩል ደቡብ ሱዳን ለሚገኘዉ የኢትዮጵያ ሰላም አስከባሪ ሃይል ምስጋና ማቅረቡም በመግለጫዉ ተጠቅሷል።

አምባሳደሩ ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸዉ የተለያዩ ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡ ሲሆን አሜሪካ ወደ ቱርክ: ግብጽ: የተባበሩት አረብ ኤሜሬትና ወደ ተለያዩ ጎረቤት ሃገራት ተመላልሳ በእጅ አዙር ተጽእኖ ለመፍጠር ከምትሞክር በቀጥታ ከኢትዮጵያ ጋር ብትነጋገር የተሻለ ነዉ ብለዋል።

አሜሪካኖች ወደ ቱርክ ሲሄዱ ኢትዮጵያን አትደግፉ ወደ ግብጽ ሲሄዱ ደግሞ በርቱ ከማለት እንደማይቆጠቡም አምባሳደሩ ጠቅሰዋል።

ሱዳንን አስመልክቶ ለቀረበላቸዉ ጥያቄ ሱዳኖች በነጻ እየተጣሉ አይደለም: በግጭቱ ዉስጥ በርካታ እጆች አሉበት ኢትዮጵያ ግን የሱዳናዊያን ችግር በሱዳናዊያን እንዲፈታ ትፈልጋለች ድጋፍም ታደርጋለች ብለዋል።

ወንድማገኝ አሰፋ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ፌስቡክ፡ http://facebook.com/OBNAmharic
ዩትዩብ፦ Youtube.com/OBNoromiyaa
ቴሌግራም፦ https://t.me/OBN_VoiceOfthepeople
ትዊተር፦ https://twitter.com/OBNoromiyaa
የአፋን ኦሮሞ ፌስቡክ፡ http://facebook.com/OBNAfaanoromo
OBN English ፌስቡክ: http://facebook.com/OBNEnglish.
https://zeno.fm/radio/obnradio/
በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

29/12/2021
29/12/2021

የኬንያ ፕሬዝዳንት እና የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር “በኢትዮጵያ በአፋጣኝ ግጭት የማቆም አስፈላጊነት” ላይ መስማማታቸው ተነገረ

የኬንያው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ እና የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን “በኢትዮጵያ በአፋጣኝ ግጭት የማቆም አስፈላጊነት” ላይ ከስምምነት ላይ መድረሳቸውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታወቀ። አሁሩ እና ብሊንከን ከዚህ ስምምነት ላይ የደረሱት፤ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያ ሁኔታን ጨምሮ በክፍለ አህጉሩ የጸጥታ ጉዳይ ላይ ትላንት ማክሰኞ በስልክ ከተነጋገሩ በኋላ ነው ተብሏል።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ ትላንት ማክሰኞ ምሽት ባወጡት መግለጫ፤ ኡሁሩ እና ብሊንከን በኢትዮጵያ ያልተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ሊኖር፣ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ሊቆም እንደሚገባ ከስምምነት መድረሳቸውን ገልጸዋል።

ዝርዝሩን ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ፦ https://ethiopiainsider.com/2021/5442/

28/12/2021

| Ezema questions national dialogue lawmaking process


The Ethiopian Citizens for Social Justice Party (Ezema) criticized the speed in the law making process of the newly drafted national dialogue bill, which is under discussion at the House of Peoples’ Representatives (HoPR), The Reporter has learnt.
Read More: https://bit.ly/3sTy5Hl

----------||----------
Follow Us:
Facebook ↠ https://bit.ly/3fmc8YE
Twitter ↠ https://bit.ly/3nJLRpR
Telegram ↠ http://bit.ly/37OFEnC
Youtube ↠ https://bit.ly/3namddM
----------||----------
Reporter Jobs ↠ https://bit.ly/3FHb6Ts

27/12/2021

የሰላም አማራጩ የማይሰራ ከሆነ የትግራይ ህዝብ በረሀብ እየረገፈ ዝም ብሎ የማይመለከት ግዙፍ ሰራዊት አለን

—ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል

የትግራይ መንግስት እየወሰደው ያለው የሰላም አማራጭ መልካም ቢሆንም በአብይ አህመድ በኩል ግን ተመሳሳይ ፍላጎት እየታየ አለመሆኑን ፕሮፌሰር ሸትል ትሮንቮል ተናገሩ።

ፕሮፌሰር ሸትል ትሮንቮል ዴሞክራሲ ኢን አፍሪካ ላይ ባሰፈሩት ፅሁፋቸው አብይ አህመድ የሰላም አማራጩን ቢቀበለው እንኳን ኢሳያስ አፍወርቂ እና የአማራ ሀይሎች እንቅፋት ሊሆኑት ይችላሉ ብለዋል።
የኢትዮጵያው ጦርነት በ2021 ትልቁ የዓለማችን ጦርነት ሆኖ አልፏል አሁንም የትግራይ መንግስት የከፈታተ ትንሽ የሰላም መስኮት መጠቀም ካልተቻለ በ2022ም የዓለማችን ትልቁ አውዳሚ ጦርነት ሆኖ እንድሚቀጥል ተናግረዋል።

ፕሮፌሰር ሸትል ትሮንቮል ከትግራይ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል አገኘሁት ባሉት መረጃ የሰላም አማራጩ የማይሳካ ከሆነ የትግራይ ህዝብ በረሀብ እየረገፈ ዝም ብሎ የማይመለከት ግዙፍ ሰራዊት አለን ብልውኛል ይላሉ።

ታህሳስ18/2014ዓ/ም
Pres. Debretsion Gebremichael
Dimtsi Weyane
Digital Weyane ዲጂታል ወያነ

27/12/2021

#ሰበር ዜና!
#ከተከዜ ግንባር

ደባርቅ፡ ታህሳስ 18/2014 ዓ.ም
(የሰሜን ጎንደር ኮሙዩኒኬሽን)

አሸባሪዉ የትግሬ ወራሪ ሃይል ሲተማመንበት የነበረዉ #የአምባጉላይ ኮንክሪት ምሽግ በጀግኖች የኢትዮጵያ ልጆች ፈርጣማ ክንድ ተደርምሷል፡፡

ጀግናዉ የኢትዮጵያ ሰራዊት ጥምር ጦርም #የጨዉ በርንና #በርማርያምን እያስለቀቀና ነጻ እያዎጣ ወደ #አዲአርቃይ ገስግሷል፡፡

#ኢትዮጵያ ታሸንፋለች!
ድል ለጀግኖቻችን!
ዘላለማዊ ክብር በትግሉ ለተሰዉ ሰማእታት!

26/12/2021

አሸባሪው ሸኔ የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ ቤተሰብን ጨምሮ 8 ሰላማዊ ሰዎችን ገደለ
****************

አሸባሪው ሸኔ በጅማ ዞን የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ 3 ወንድሞችን ጨምሮ 8 ሰላማዊ ሰዎችን ጭካኔ በተሞላበት መንገድ መግደሉን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።

የሽብር ቡድኑ ይህን ግፍ የፈፀመው በጅማ ዞን ኖኖ ቤንጃ ወረዳ ኮንቺ ቀበሌ ታኅሣሥ 15 ቀን 2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 3:30 አካባቢ መሆኑ ተገልጿል።

በአሸባሪው ቡድን የተገደሉት የአቶ ዓለማየሁ አቶምሳ ቤተሰብ አባላት አቶ አደባ አቶምሳ፣ አቶ ቲሊንቲ አቶምሳ እና አቶ ሙላቱ አቶምሳ የተባሉ ወንድሞቻቸው መሆናቸውን የቤንጃ ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪ አቶ በሬቻ ተኩ ለኦቢኤን ተናግረዋል።

የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ የኦሮሞ ሕዝብ የነፃነት ትግልን ካቀጣጠሉት እና የአሸባሪው ህወሓት ውድቀት እንዲፋጠን ምክንያት ከሆኑ ሰዎች መካከል አንዱ ናቸው።

የደረሰብን ኀዘን ከባድ ነው ያሉት አቶ በሬቻ ተኩ፣ ከአቶ ዓለማየሁ ቤተሰብ በተጨማሪ ሌሎች ሰላማዊ ሰዎችም በጭካኔ መገደላቸውን እና ከእነዚህም መካከል ሁለቱ ሴቶች መሆናቸውን ተናግረዋል።

አሸባሪው ሸኔ የአርሶ አደሩን ሀብት ንብረት ማቃጠሉን እና የተረፈውም ጥቅም ላይ እንዳይውል መበታተኑን ተናግረዋል።

17 የአርሶ አደሮች ቤት በዚሁ ቡድን በመቃጠሉ ምክንያት የተፈናቀሉ ሰዎች መኖራቸውን ገልጸዋል።

ካቃጠሉት የአርሶ አደሩ ሰብል መካከል 9 ጎተራ በቆሎ እና በርካታ የጤፍ ክምር እንደሚገኝ የገለጹት ምክትል አስተዳደሩ፣ በሚያሳዝን መልኩ ጥገት ላምን እና ጥጆችን ጨምሮ ወደ በረት አስገብተው አቃጥለዋል ብለዋል።

የኖኖ ቤንጃ ወረዳ ነዋሪዎች የአሸባሪው ሸኔን ድርጊት በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ መውጣታቸውም ተገልጿል።

የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት ትክክለኛውን የዩቲዩብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/c/EBCworld/
የመዝናኛ ቻናላችን የቪዲዮ መረጃዎችን ለማግኘት የዩቲዩብ የመዝናኛ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ
https://www.youtube.com/channel/UCp9pS23Vw1n8WpcpZBDJNmA
በምስል የሚገኙ መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የኢንስታግራም ገፃችንን ይከተሉ
https://www.instagram.com/ebcnews1/
አጫጭርና ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት የትዊተር ገፃችንን ይከተሉ
https://twitter.com/ebczena
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/EBCNEWSNOW

Address

Addis Ababa

Opening Hours

09:00 - 17:00

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Wariye Najiib Dayiib posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share