ኦፍና ሚዲያ ማዕከል - ofna media center

ኦፍና ሚዲያ ማዕከል - ofna media center Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ኦፍና ሚዲያ ማዕከል - ofna media center, Media/News Company, ADISABEBA, Addis Ababa.

የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታ ዝግጅቱ ተጠናቋል።አዲሱ የከተራና የጥምቀት ማክበሪያ ቦታ ዝግጅቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።አደባባዩ የዝግጅት ሁኔታ በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓ...
18/01/2025

የጥምቀት በዓል ማክበሪያ ቦታ ዝግጅቱ ተጠናቋል።

አዲሱ የከተራና የጥምቀት ማክበሪያ ቦታ ዝግጅቱ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

አደባባዩ የዝግጅት ሁኔታ በብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ተጎብኝቷል።

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ሁላችንም ከውኃና ከመንፈስ ዳግም የተወለድንበት የዲያብሎስ ሥራ የፈረሰበት አንድነታችን የታወጀበት መለያየት የተወገደበት ማያት የሚቀደሱበት በአጠቃላይ ምድራችን በቃል ኪዳኑ ታቦታት ኪደተ እግር የምትባረክበት ዕለት ነው።

ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ እንደተባለው ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ከአደባባይ ጽኑስ እስከ ዙፋን ንጉሥ በነቂስ በመውጣት የቤተ ክርስቲያናችንን ታላቅነትና የሀገራችንን ታሪካዊነት የምናሳይበት የሕዝባችንን ፍቅር አንድነት የምንገልጽበት የሰላም የፍቅርና የአንድነት በዓላችን መሆኑን ዓለም ያወቀው ፀሐይ የሞቀው የአደባባይ በዓላችን ነው።

በመሆኑም ይኽንን ታሪካዊና ዓለም አቀፋዊ የጥምቀት በዓል በነገሥታቱ መናገሻ በዐፄዎቹ መንደር በንጉሡ ቅን ፍርድ ከሰማይ ብርሃን በወረደባት ዘወትርም የክርስቶስ የፍቅር ብርሃን እንደ ፈሳሽ ውኃ በሚፈስባት በዓለ ጥምቀት በአዲስ ታሪካዊ አደባባይ በማክበር ሌላ ታሪክ ሊመዘገብ ጥቂት ሰአታት ቀርተውታል።

ለመጀመሪያ ጊዜ በዚህ ታሪካዊ አደባባይ በዓሉን ለማክበር የበቃችሁ ውድ ሕዝበ ክርስቲያን የታሪኩ ተካፋይ በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ።

አቡቀለምሲስ ሚዲያ በመላው ዓለም ለምትገኙ ኢትዮጵያዊያን በዩቲዩብ ፣ በፌስቡክና በሌሎችም አማራጮች በቀጥታ ስርጭት ወደ እናንተ የሚያደርሳችሁ ይሆናል።

"የጥምቀት ክብረ በዓልን ስናከብር የጥምቀት መስራች እና ምሳሌ የሆነውን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሕይወት በመለማመድ መሆን ይኖርበታል!" ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ          ...
17/01/2025

"የጥምቀት ክብረ በዓልን ስናከብር የጥምቀት መስራች እና ምሳሌ የሆነውን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሕይወት በመለማመድ መሆን ይኖርበታል!" ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ሊቀ ጳጳስ

#ኦሚማ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ
-------------------------------------------------------------------------------

የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ፣ የአዲስ አበባ ሃይማኖት ተቋማት ዋና ሰብሳቢ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የ 2017 ዓ.ም በዓለ ጥምቀትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው እኔ ለንስሐ በውሃ አጠምቃችኋለሁ: ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል" (ማቴ.3:11) የሚለውን ቅዱስ ቃል ጠቅሰው ሕዝበ ክርስቲያኑ የጥምቀት በዓልን ሲያከብር የጌታን መንገድ አቅኑ እያለ በምድረ በዳ የጮኸውን የንስሐ ድምፅ በማሰብ ያለ ልክ የኖርንበትን ያለፈውን ዘመን ንስሐ በመግባት እንዲሁም የጥምቀት መስራች እና ምሳሌ የሆነውን የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሕይወት በመለማመድ መሆን እንደሚገባው ገልጸዋል።

በዓሉ በሀገሪቱ ርዕሰ መዲና በአዲስ አበባ ከተማ የቅዱስ ሲኖዶስ ርዕሰ መንበር ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በተገኙበት በጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀት የሚከበር ሲሆን በጠቅላላ ከተማው ከ 64 ባላነሱ ቦታዎች እንደሚከበር ገልጸዋል።

በበዓሉ ወቅት በሁሉም ቦታዎች ስብከተ ወንጌል ተደራሽ እንደሚሆን ጠቅሰው በዓለም አቀፍ ደረጃ የተመዘገበ እንደመሆኑ ይዘቱን በጠበቀ እና ሰላማዊ በሆነ መልኩ በአንድ ዓይነት የወንጌል ድምፅ እንዲከበር ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የተሰጠውን አቅጣጫ ሁሉም በመተባበር እንደመተገበር አሳስበዋል። በመሆኑም

1. ለበዓሉ የሚመጥን ነጭ ልብስ እና የአገልግሎት ልብስ ከመልበስ ጀምሮ፣ የጋራ ኅብረ ዝማሬ በማቅረብ እና የጉዞ ቅደም ተከተላችንን በመጠበቅ ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ማዕከል ያደረገ እና ለበዓሉ ድምቀት የሚስጥ አሰላለፍ እንዲኖረን፤

2. ወደ ባሕረ ጥምቀቱ የሚደረገው ናዞ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ I ከልዕልና ወደ ትህትና መውረዱን የሚያሳይ መንፈሳዊ እሴት ያለበት እንደሆነ የታወቀ በመሆኑ በየትኛውም ጉዞ ዋዛ ፈዛዛ ሳይታይና ከቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና ጋር የሚጣረስ ድርጊት ሳይፈጸም በተቀመጠው አቅጣጫ ብቻ እንዲፈጸም!

3. የጉዞ ሰዓትን በተመለከተ

- ጥር 10 ቀን 2017 ዓ.ም የጥምቀት ዋዜማ የከተራ በዓልን የመነሻ ሰዓቱ እንደዓቢያተ ቤተ ክርስቲያናቱ ርቀት ሆኖ ወደ ባሕረ ጥምቀት የሚደርሱበት ሰዓት ግን ከ9 - 11 ሰዓት እንዲሆን ::

- የጥር 11 የጥምቀት በዓልና የጥር 12 የቃና ዘገሊላ በዓልን በተመለከተም መነሻ ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ከባሕረ ጥምቀት ተነሥተው ሁሉም ታቦታት እንደየርቀታቸው ከ 8-11 ሰዐት ወደ መንበረ ክብራቸው እንዲመለሱ፣ በዚሁ ጉዳይ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ቤትክህነት ጋር በመናበብ የወጣው መመሪያ ተግባራዊ እንዲደረግ ፣ ለተግባራዊነቱም ከሀገረ ስብከቱ ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የሥራ ኃላፊዎችና አስተባባሪ ኮሚቴዎች በጋራ በመቀናጀት ሰዓቱን የማስከበር ሥራ እንዲሠሩ

4. አገልግሎታችን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን የተከተለ መሆን ስለሚገባው አስፈላጊውን ግብዓት ከማቅረብ በቀር ከአበው ካህናት ውጭ በየትኛውም መልኩ በሌሎች አካላት የሚደረግ ማዕጠንት ተገቢነት የሌለው እና ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጪ በመሆኑ እንዳይፈጸም የሚመለከታቸው አካላትም ተገቢውን ክትትል እንዲያደርጉ እንዲሁም የማዕጠንት አገልግሎቱ በካህናት አባቶች በሰፊው እንዲሰጥ ይሁን ፤

5. በረከተ ጥምቀቱን የማድረስ እና የመርጨት ክንውን የሚፈጸመው በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን መሠረት በካህናት ብቻ መሆኑ ይታወቃል በዚሁ መሠረት ቀኖና ቤተ ክርስቲያን ባለማወቅ ምክንያት እንዳይፈርስ ወጣት ልጆቻችንም ይህን አውቃችሁ ሥርዓቱን እንድትጠብቁና አገልጋዮች ካህናትም ድርሻችሁን እንድትወጡና ሕዝቡን እንድታገለግሉ እናሳስባለን ።

6. ከልክ ያለፉ እና በተደጋጋሚ የተስተዋሉ ከሥርዓት ውጭ በሆነ መልኩ ለታቦታቱ ክብር በማይመጥኑ ሥፍራዎች ላይ እንዲቆሙ የሚደረገው ልምድ እንዲታረምና ሁሉም በሕግና በሥርዓት እንዲመራ።

7 . ምእመናን እንደተለመደው ራሳችሁን ከሁከትና አላስፈላጊ ነገሮች በማራቅ በትዕግሥት እና በሆደ ሰፊነት በዓሉን እንድናከብር እያሳሰብን ችግሮች ቢፈጠሩ እንኳን ከሚመለከታቸው ከበዓሉ አስተባባሪዎችና የጸጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት በተናበበ መልኩ እልባት እንዲሰጣቸው ሊደረግ ይገባል፡፡

በዓለ ጥምቀትን ስናከብር በፍጹም ወንድማዊ ፍቅር የተራቡትን በማብላት ፣ የተጠሙትን በማጠጣት ፣ የታረዙትን በማልበስ ፣ በተለያዩ ምክንያቶች ከቀያቸው የተፈናቀሉ ወገኖችን በመርዳትና በመደገፍ የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ትህትና አብነት በማድረግ በመተሳሰብና በመደጋገፍ እንዲሆን እናሳስባለን በማለት አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል ሲል የዘገበው ተዋህዶ ሚዲያ ማዕከል ነው።

በዓሉ ፍፁም ትህትና የተሰበከበት በዓል እንደመሆኑ መጠን በትህትና ሆነን ልናከብረው ይገባል።                                                  ዲያቆን ጌታው በቀለ...
17/01/2025

በዓሉ ፍፁም ትህትና የተሰበከበት በዓል እንደመሆኑ መጠን በትህትና ሆነን ልናከብረው ይገባል።
ዲያቆን ጌታው በቀለ

#ኦሚማ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ
"""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
በኢትዮጵያ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በመርሐቤቴ ላይ ቤት ወረዳ የማኅደረ ሰላም ኦፍና ቅዱስ አማኑኤል ሰንበት ትምህርት ቤት ሰብሳቢ የሆኑት ዲያቆን ጌታው በቀለ ለመላው ህዝበ ክርስቲያን ለብርሃነ ጥምቀቱ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

በዓሉ የትህትና በዓል ነው ያሉት ሰብሳቢው ሁሉም ህዝበ ክርስቲያን በፍፁም ትህትና ሆኖ ሊያከብረው የሚገባ በዓል ነው ሲሉ አስገንዝበዋል። እንደ ማኅደረ ሰላም ቅዱስ አማኑኤል ሰንበት ትምህርት ቤት ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመነጋገር የበዓል ዝግጅት ቅድመ ሁኔታዎች ተጠናቀዋልም ብለዋል።

እንደ ሰብሳቢው ገለጻ በርካታ ታቦታት ከቅርብም ከሩቅም የሚሰበሰቡበት እንዲሁም በርካታ የከተማውና ታቦታቱን እጅበው የሚመጡ የገጠሪቱ ቤተክርስቲያን ምእመናንን የሚታደሙበት በዓል ስለሆነ የታቦታት ማደሪያውን ስፍራ ምቹ በማድረግ አካባቢውን በማጽዳት ሰንበት ት/ቤታችንና በአካባቢያችን ያሉ ልዩልዩ ማኅበራት በጋራ እየሰሩ ይገኛሉም ነው ያለው።

በመጨረሻም ምእመናን በዚህ ታላቅ በዓል በበጎ ሥና በትሩፋት ችግረኞችን በማሰብ ማሰለፍ እንደሚገባ ጠቁመዋል። በዚህ በዓል በብዙ የተቸገሩ ወገኖች እንዳሉ በማስታወስ እነዚህን የማይዘነጋ በዓል መሆን ይጠበቅበታልም ሲሉ አስገንዝበዋል።

በአብ ስም በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ ስም አንድ አምላክ አሜን!በዓለ ጥምቀትን በደብረ ብርሃን ከተማ ያሉ ገዳማትና አድባራት በሙሉ በአንድ ላይ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራው  መጠናቀቁን ...
16/01/2025

በአብ ስም በወልድ ስም በመንፈስ ቅዱስ ስም አንድ አምላክ አሜን!

በዓለ ጥምቀትን በደብረ ብርሃን ከተማ ያሉ ገዳማትና አድባራት በሙሉ በአንድ ላይ ለማክበር የቅድመ ዝግጅት ሥራው መጠናቀቁን አስመልክቶ ከሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ።

ወአስተኃለፉ ለሕዝብ ወይቤልዎሙ እምከመ ርኢክሙ ታቦተ ሕጉ ለእግዚአብሔር አምላክነ ወካህናተኒ ወሌዋውያነኒ እንዘ ይጸውርዋ ገዐዙ አንትሙኒ እመካናቲክሙ ወትልዉ ድኅሬሃ።

ሕዝቡን ፦ የአምላካችሁ የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ሌዋውያንና ካህናት ተሸክመውት ባያችሁ ጊዜ ከሰፈራችሁ ተነሥታችሁ ተከተሉት መጽ ኢያ ፫ ÷ ፫
ጥንታዊቷ ፣ ታሪካዊቷ ፣ ሐዋርያዊቷ ፣ ኲላዊቷና ኢትዮጵያዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአደባባይ ከምታከብራቸው ታላላቅ በዓላት መካከል አንዱና ፊተኛው መንፈሳዊው ፣ ብሔራዊውና ዓለም አቀፋዊው በዓለ ጥምቀት መሆኑ ይታወቃል።

የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ምሳሌ አበው ትንቢተ ነቢያት የተፈጸመበት ምሥጢር የተደላደለበት የፈጣሪና የፍጡር ትሕትና የተገለጸበት ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ በዮርዳኖስ ወንዝ የቀበረው የእዳ ደብዳቤ የተደመሰሰበት የሥላሴ አንድነትና ሦስትነት የተገለጸበት የአንድነትና የነጻነት በኲረ በዓላት ነው።

ምንም እንኳን ሀገራችን ኢትዮጵያ የጌታን ጥምቀት በጃንደረባው አካኝነት ከዓለም አስቀድማ የሰማችና አምና የተቀበለች ቢሆንም በመንፈሳዊነቱ ፣ በውበቱና በኅብረ ብሔራዊነቱ የታላቋ ቤተ ክርስቲያናችን ዓለም አቀፋዊነት ከፍታ የሚታይበትና የሀገራችን ኢትዮጵያ መገለጫ የሆነው የበዓለ ጥምቀት አከባበር ሥርዓት ግን በአንድ ጀንበር ተሠርቶ ያለቀ አለመሆኑን የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ።

በአከባበሩ ሥነ ሥርዓት ላይ በየዘመናቱ የነበሩ ሕዝብ እየመሩ ሀገር የሚያስተዳድሩ በርካታ የእግዚአብሔር ወዳጆች ጉልህ አሻራቸውን ያኖሩ ሲሆን በተለይም ደገኛው መፍቀሬ እግዚአብሔር ርቱዐ ሃይማኖት ቆስጠንጢኖስ ዘኢትዮጵያ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ታቦተ ጽዮን በእስራኤል ከተማና አካባቢ በካህናቱና በሌዋውያኑ አማካኝነት ተንቀሳቅሳ ሀገራቸውንና ሕዝባቸውን ትባርክ እንደነበረ በማሰብ ለበዓለ ጥምቀት የቃል ኪዳኑ ታቦታት ጥር አስር የከተራ ዕለት ውኃ ወደ ተከተረባቸው ወንዞች ወርደው በማደር አካባቢውንና ሕዝቡን ባርከው እንዲመለሱ ዘመን የማይሽረው ታሪክ ማኖራቸውን ዛሬ ከምናከብረው የበዓል አከባበር ሥርዓት የምንረዳው እውነት ነው።

በዚህ ሥርዓት በርካታ የቃል ኪዳን ታቦታት ርቀት ሳይገድባቸው ድካመ ሥጋ ሳይገታቸው በአንድ ላይ ተሰባስበው በተለያየ የሀገራችን ክፍል እንደሚያከብሩ ይታወቃል ። በሀገረ ስብከታችንም በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በኢራንቡቲና በኤፍራታና ግድም ወረዳ በጋዲሎ ሜዳ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት በኅብረት የሚያከብሩ ሲሆን በመዲናችን በደብረ ብርሃን ከተማ ግን አድባራቱ በተለያየ ምክንያት በተለያየ ቦታ ሲያከብሩ ቆይተዋል።

በመሆኑም ከሁለት ሺህ አስራ ሦስት ዓም ጀምሮ በደብረ ብርሃን ከተማ ያሉ ገዳማትና አድባራት በሙሉ በአንድ ላይ እንዲያከብሩ የሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አባታችን አቡነ ቀሌምንጦስ በሰጡት አባታዊ መመሪያ መሠረት አብሮ ለማክበር ከፍተኛ ጥረት ቢደረግም በዋናነት በዓለ ጥምቀትን የምናከብርበት ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ አደባባይ የሁሉንም ገዳማትና አድባራት ሕዝብለማስተናገድ የተጣበበ በመሆኑ በአንድ ላይ ማክበር ላለመቻላችን በምክንያትነት ሲጠቀስ የቆየ ጉዳይ ነው።

በመሆኑም አብሮ ለማክበር እንቅፋት የሆነብንን የበዓለ ጥምቀት ማክበሪያ የቦታ ችግር ለከተማ አስተዳደራችን አቅርበን ከተማ አስተዳደራችንም ጉዳዩን በትኩረት ተመልክቶ በደብረ ብርሃን ከተማ የሚገኙ ገዳማትና አድባራት በሙሉ አብረው በዓለ ጥምቀትን የሚያከብሩበት መቶ ሺህ ካሬ ቦታ በክልል አጸድቆ አስረክቦን በሁለት ሺህ አስራ ሰባት ዓም ከመንግሥት በተረከብነው አዲሱ ቦታ ላይ በከተማው ያሉ አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ አብረው ለማክበር በተደረሰው ስምምነት መሠረት የበዓሉ አዘጋጅ ዐቢይ ኮሚቴና ንዑሳን ኮሚቴዎች በየዘርፉ ተዋቅረው የቅድመ ዝግጅት ሥራው በመጠናቀቅ ላይ የሚገኝ ሲሆን አብረው ማክበር የሚገባቸው አብያተ ክርስቲያናትም ተለይተው በውይይት ስምምነት ላይ በመደረሱ ሰርኩላር ደብዳቤ ለአብያተ ክርስቲያናቱ መተላለፉ ይታወቃል ።

አብረው የሚያከብሩት የአብያተ ክርስቲያናት ስም ዝርዝር
1 ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴና በሥሩ ያሉ አንሳስ መንበረ ብርሃን ቅድስት ማርያም ፣ ደብረ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና ፈለገ ዮርዳኖስ ቅዱስ ሩፋኤል
2 ጠባሴ ደብረ ሰላም ቅዱስ መድኃኔ ዓለምና በሥሩ ያሉ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ፣ ደብረ ምሕረት ሽፍኑ ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ተክለ ሃይማኖት
3 ደብረ ጽባህ ቅዱስ ጊዮርጊስና መካነ ሰማዕት ቅዱስ ቂርቆስ
4 ደብረ ገነት ቅዱስ ዑራኤልና አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል
5 ደብረ ፀሐይ ቅዱስ እግዚአብሔር አብና ምዕራፈ ቅዱሳን ቅዱስ ዮሐንስ
6 ሐመረ ኖኅ ልደታ ለማርያም ፣ ደብረ ታቦር ቅዱስ ገብርኤልና አቡነ አረጋዊ
7 ደብረ እንቊ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ
8 አቦ ገዳም አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
9 ደብረ ማዕዶት ቅድስት አርሴማ
10 አታክልት ደብረ ኅሩያን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ
11 ታዕካ ነገሥት ሊቼ ኢየሱስና እምቢ ለዐፄ ቅዱስ ዮሐንስ
12 ደብረ ሰላም በርዮ በዓለ ወልድ
13 ቦራሌ ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሲሆኑ እነዚህ በስም የተዘረዘሩት 25 የሚደርሱ አብያተ ክርስቲያናት ከወትሮው በተለየ በዓለ ጥምቀቱ የአንድነት በዓል እንደመሆኑ መጠን በአንድነት በማክበር ደብረ ብርሃንን እንደስሟ በጥምቀቱ ብርሃን ለማድረግ ጫፍ ላይ እንገኛለን።

ስለሆነም ፦
1 ስማችሁ ከላይ የተዘረዘረው ገዳማትና አድባራት ካህናቱንና ሕዝቡን በማስተባበርና በመምራት በበዓሉ ሥራ አስፈጻሚ ዐቢይ ኮሚቴ በወጣው የበዓሉ መርሐ ግብር መሠረት በሰዓቱ በተለመደው የታቦታቱ መሄጃ መንገድ ታቦታቱን አክብራችሁ እንድትመጡ በአጽንኦት መልእክታችንን እናስተላልፋለን ።
2 በከተማችን ደብረ ብርሃን ከተማ የምትገኙ ሕዝበ ክርስቲያን በሙሉ ዘንድሮ በከተማችን ያሉ አብያተ ክርስቲያናት በሙሉ በዓለ ጥምቀቱን የምናከብረው ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ አዲስ በተረከብነው ቦታ ላይ መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የቃል ኪዳኑን ታቦታት አጅባችሁ ታከብሩ ዘንድ በአክብሮት እንገልጻለን።

3 በከተማችን የምትገኙ ወጣቶች በሙሉ ልዩ ልዩ መንፈሳውያን ማኅበራት ግቢ ጉባኤያት በዓሉ በአንድ ላይ የሚከበር እንደመሆኑ መጠን አገልግሎታችሁን በኅብረት በማዘጋጀት በዓሉ ታሪካዊ ድባቡን ጠብቆ ይከናወን ዘንድ የድርሻችሁን ትወጡ ዘንድ ማሳሰብ እንወዳለን።

4 ከተማ አስተዳደራችን በዓሉ የሚከበርበትን አካባቢ ከትራስፖርት እንቅስቃሴ ነጻ እንዲያደርግልንና የጸጥታ ሁኔታውንም ከወጣቶቻችንና ከሕዝቡ ጋር በመናበብ የድርሻውን ይወጣልን ዘንድ እንጠይቃለን ።

5.ሚዲያዎችና የሚዲያ ባለሙያዎች የዞንድሮው በዓለ ጥምቀታችን ከእስከ ዛሬው በተለየ ሁኔታ ሁሉም አብያተ ክርስቲያናት አብረው የሚያከብሩ በመሆኑ ከማስታወቂያ ሥራው ጀምራችሁ አስፈላጊውን የሚዲያ ሽፋን ትሰጡልን ዘንድ በአክብሮት እናሳስባለን ።
6 በመላው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያን ፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያንና ቱሪስቶች በሙሉ ታሪካዊውን የጥምቀት በዓል በታሪካዊቷ ደብረ ብርሃን ከተማ መጥታችሁ ታከብሩ ዘንድ በክርስቶስ ፍቅር ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።

በመጨረሻም የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት ሁላችንም ከውኃና ከመንፈስ ዳግም የተወለድንበት የዲያብሎስ ሥራ የፈረሰበት አንድነታችን የታወጀበት መለያየት የተወገደበት ማያት የሚቀደሱበት በአጠቃላይ ምድራችን በቃል ኪዳኑ ታቦታት ኪደተ እግር የምትባረክበት ለጥምቀት ያልሆነ ቀሚስ ይበጣጠስ እንደተባለው ከልኂቅ እስከ ደቂቅ ከአደባባይ ጽኑስ እስከ ዙፋን ንጉሥ በነቂስ በመውጣት የቤተ ክርስቲያናችንን ታላቅነትና የሀገራችንን ታሪካዊነት የምናሳይበት የሕዝባችንን ፍቅር አንድነት የምንገልጽበት የሰላም የፍቅርና የአንድነት በዓላችን መሆኑን ዓለም ያወቀው ፀሐይ የሞቀው የአደባባይ በዓላችን ነው።

በመሆኑም ይኽንን ታሪካዊና ዓለም አቀፋዊ የጥምቀት በዓል በነገሥታቱ መናገሻ በዐፄዎቹ መንደር በንጉሡ ቅን ፍርድ ከሰማይ ብርሃን በወረደባት ዘወትርም የክርስቶስ የፍቅር ብርሃን እንደ ፈሳሽ ውኃ በሚፈስባት በዓለ ጥምቀት በዚህ ደረጃ እንዲከበር በንጉሡ ሥርዓት በተሠራባት በደጋማዋ ፣ በነፋሻማዋና በብርሃናማዋ ደብረ ብርሃን ከተማ ተገኝተን በከተማችን ከሚገኙ ገዳማትና አድባራት ጋር በዓሉን በኅብረት በታላቅ ክብርና በድምቀት እናከብር ዘንድ በታላቅ አክብሮት ሁላችሁም ተጋብዛችኋል ።

እግዚአብሔር ሀገራችን ኢትዮጵያን ሕዝቦቿን ይባርክ !
ጸግዋ ሰላመ ለሀገሪትነ ኢትዮጵያ
አዘጋጅ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ጽ/ ቤት ከአድባራትና ገዳማቱ ጋር በመተባበር
ቀን ፮/ ፭ /፳፻ ፲፯ ዓም
ሸዋ ደብረ ብርሃን ኢትዮጵያ

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከ1 ሺህ 4መቶ በላይ ለሚሆኑ ዲያቆናትና ቀሳውስት ሥልጣነ ክህነት ሰጡ።             #ኦሚማ ጥር 8 ቀን 2017 ዓ.ም አ...
16/01/2025

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከ1 ሺህ 4መቶ በላይ ለሚሆኑ ዲያቆናትና ቀሳውስት ሥልጣነ ክህነት ሰጡ።

#ኦሚማ ጥር 8 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ
++++ +++++ +++++ ++++++ +++++ ++++

ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከ1 ሺህ 4መቶ በላይ ለሚሆኑ ዲያቆናትና ቀሳውስት ሥልጣነ ክህነት ሰጥተዋል።

ብፁዕነታቸው ለ1 ሺህ 3 መቶ የአብነት ደቀ መዛሙርት የዲቁና ፣ ለ1 መቶ 60 ቀሳውስት የቅስና እና ለ6 መነኮሳት የቁምስና ሥልጣነ ክህነት ሰጥተዋል።

ብፁዕነታቸው በሀገረ ስብከታቸው በሚገኙ በተለያዩ አድባራትና ገዳማት የመደቧቸው የአብነት መምህራን ላፈሯቸው ለመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው ከሌሊቱ 7 ሰዓት ተኩል ጀምረው ሥልጣነ ክህነት ሲሰጡ አድርዋል።

ክህነት ለተቀበሉ ዲያቆናትና ቀሳውስት ስለክብረ ክህነት ፣ ስለአምስቱ አዕማደ ምሥጢራት ፣ ስለ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን እና ካህናት በጾም ፣ በጸሎት ፣ በስግደትና በምጽዋት ለሚመሯቸው ምእመናን ምሳሌና አርዓያ መሆን አለባችሁ ሲሉ ባስተላለፉት አባታዊ ቃለ በረከት አስገንዘበዋል።
©አቡቀለምሲስ

“እውቀት ይስፋ ድንቁርና ይጥፋይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ”  | የመጀመሪያው ብሔራዊ የተማሪዎች ሽልማት 2017  #ልዩ ተሸላሚ   Recognition Award ተስፋ ገብረሥላሴ፣ ዘብሔረ ቡልጋ...
16/01/2025

“እውቀት ይስፋ ድንቁርና ይጥፋ
ይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ”

| የመጀመሪያው ብሔራዊ የተማሪዎች ሽልማት 2017 #ልዩ ተሸላሚ Recognition Award ተስፋ ገብረሥላሴ፣ ዘብሔረ ቡልጋ ሆነዋል።

“እውቀት ይስፋ ድንቁርና ይጥፋ
ይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ”

በታላቁ የፊደል ገበታ አባትና አርበኛ ቀኝ አዝማች ተስፋ ገብረ ሥላሴ፣ ዘብሔረ ቡልጋ

"ሀ... ሁ...ዕውቀት ይስፋፋ ፤ ድንቁርና ይጥፋ፤ ይህ ነው የኢትዮጵያ ተስፋ" በማለት የፊደል ገበታን በማዘጋጀትና የዕውቀት ማነስ የኢትዮጵያውያንም ሆነ የመላው የዓለም የሰው ልጆች ሁሉ ጠላት እንደሆነ በመናገር የሚታወቁት ሐኪምና የፊደል አባት የኢትዮጵያ ባለውለታ ቀኝ አዝማች ተስፋ ገብረሥላሴ ዘብሔረ ቡልጋ ነበሩ።

የፊደል ገበታ አባትና አርበኛ ቀኝ አዝማች ተስፋ ገብረ ሥላሴ ከ120 ዓመታት በፊት ታኅሣስ 24 ቀን 1895 ዓ.ም የተወለዱ ሲሆን ከ360 በላይ መጻሕፍትን በማተሚያ ድርጅታቸው ያሳተሙ ታላቅ የሀገርና ባለውለታ ናቸው፡፡

የቡልጋ ከተማ በቀኝ አዝማች ተስፋ ገብረ ሥላሴ ስም አደባባይ በስማቸው ሰይማለች።

16/01/2025

ብጹእ አቡነ ቀውስጦስ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ህዝቡን በእንባ አራጩት😭

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በቀወት ወረዳ የአብነት ተማሪዎች የምገባ መርሐ ግብር በሸዋሮቢት ከተማ ተካሄደ።           #ኦሚማ ጥር 8 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ ++++++ +++++...
16/01/2025

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በቀወት ወረዳ የአብነት ተማሪዎች የምገባ መርሐ ግብር በሸዋሮቢት ከተማ ተካሄደ።

#ኦሚማ ጥር 8 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ
++++++ ++++++ ++++++ ++++++ ++++++ ++++++

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ቀወት ወረዳ በሸዋሮቢት ከተማ ከተለያዩ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ለተሰባሰቡ የአብነት ተማሪዎች የክርስቶስን ልደት አስመልክቶ በጥር ፭ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም የምገባ መርሐ ግብር ተካሂዷል ።

በምገባ መርሐ ግብሩ ላይ ላይ ከ450 በላይ የአብነት ተማሪዎች የተመገቡ ሲሆን የቀወት ወረዳ ቤተክህነት ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ካህናት በላይ መክቴ ሰፊ ድርሻውን ወስደዉ መርሐግብሩን መርተዋል ።

ይህ ምገባ ለክርስቶስ ልደት እና ለበዓለ ፋሲካ በዓመት ሁለት ጊዜ የሚደረግ እንደሆነ አንስተዉ የአብነት ተማሪዎቹም ከተለያዩ አጥቢያ ቤተክርስቲያን ተሰባስበዉ በቀወት ቤተ ክህነት እንደሚያከብሩ ተገልጿል ።

በተጨማሪ ቦታዉም ድረስ በመሄድ የተለያዩ እርዳታዎችን እንደሚያደርጉ ተናግረዉ በመርሐ ግብሩ ላይ ደከመን ሳይሉ ሲያስተምሩ ለነበሩ 8 የቅኔ እና የአቋቋም መምህራን ስጦታ ያበረከቱ ሲሆን ወደፊትም ተጠናክሮ እንዲቀጥል መልእክት አስተላለፈዋል።

"የተሰጠኸዉን አደራ ጠብቅ" በሚል ኃይለ ቃል በመጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ አብርሃም ሙሉጌታ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን አብነት ትምህርት ቤቶች የሊቃዉንት መፍለቂያ እንደሆኑና ሁሉም ተማሪዎች ይህን ከቤተክርስቲያን የተሰጠዉን አደራ እንዲወጡ እና ጠንክረዉ የቤተክርስቲያንን አደራ እንዲጠብቁ ሀገረ ስብከቱም ለዚህ አይነት ተግባር ከጎናቸዉ እንደሚቆም ገልጸዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የቅኔ ተማሪዎች የተማሩትን ቅኔ ተቀኝተዋል ወረብም ከመምህራኖቻቸዉ ጋር በመሆን አቅርበዋል።

ሊቀ ካህናት በላይ መክቴ ለዚህ መርሐግብር መሳካት ትልቁን ድርሻ የወሰዱትን በመጀመሪያ ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ እና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም በገንዘብም ሆነ በጉልበት ለዚህ ፕሮግራም የበኩላቸዉን ላደረጉ ከሀገር ዉጪ ና ሀገር ዉስጥ ለሚገኙ ሕዝበ ክርስቲያኖች የምስጋና ፕሮግራም አድርገዋል ።

ጥሪ የተደረገላቸዉም እንግዶች እና የዚህ በጎ ተግባር ባለድርሻ አካሎች ወደ ፊትም ከጎናቸዉ እንደሚቆሙ እንዲሁም የአብነት ተማሪዎቹ ፕሮግራሙ በመዘጋጀቱ የተሰማቸዉን ደስታ ገለፀዋል መርሐ ግብሩ በአባቶች ፀሎት ተጠናቋል።

በምገባ መርሐ ግብሩ ላይ ቆሞስ አባ ወልደ ማርያም፣ የሸዋሮቢት ከተማ ፍርፍር ደብረ ልዑል አስተዳዳሪ መልአከ ልዑል መምህር ሳሙኤል ዉድዬ እንዲሁም የአጥቢያ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎች፣ የቅኔ እና የአቋቋም መምህራን፣ የአብነት ተማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተገኝተዋል።
©አቡቀለምሲስ

መንፈሳዊ ክብር ከሚገኝበት ከዚህ አደባባይ አትራቁ በሰማይ ደጅ በቤታችሁ ተሰብሰቡ በየደረጃችሁ በአገልግሎት ትጉ።                              መላከ ምሕረት ቆሞስ አባ ኃይለ...
16/01/2025

መንፈሳዊ ክብር ከሚገኝበት ከዚህ አደባባይ አትራቁ በሰማይ ደጅ በቤታችሁ ተሰብሰቡ በየደረጃችሁ በአገልግሎት ትጉ።

መላከ ምሕረት ቆሞስ አባ ኃይለሚካኤል

#ኦሚማ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ
=======================================

ቤተክርስቲያን የቅዱሳን በዐት የድሆች መጠጊያ የችግረኞችም ስንቅ ናት ቤተክርስቲያን የሩሁባን ቀለብ የምስኪናንም እናት ናት ታሪክ ጠባቂ የሀገር መልክና ውበት ናት ምእመናን በዚህች ሁሉ ባላት ባለፀጋ እመቤት ከሆነቸው ከቅድስት ቤተክርስቲያን ስላላችሁ ደስ ይበላችሁ። ብዙ ዓለማትን ያስደነቁ እጆች የነ ቅዱስ ላሊባላ መቅደስ ያነፁ ብርቱ ክንዶች ከዚችው መንፈሳዊት እናት የተገኙ ናቸው።

ምእመናን በርቱ የቀደሙ አባቶቻችሁን ፈለግ ተከተሉ እነሱ ሀገር መርተዋል ሀገር ሰርተዋል አጽንተዋልም በሃይማኖታቸው ጽኑአን ናቸው እነሱ የእምነት አርበኞች ናቸው እኛም የእነሱ ልጆች ነን ዛሬ የቅድስት ሥላሴ በዓል ሲከበር የመጣችሁ መልካም አደረጋችሁ በሥላሴ ክብር ከብራችኋልና በበዓሉ ያልተገኛችሁም ቀረባችሁ ያጣችሁት ብዙ ነውና። አጥማቂ፣ ተአምር አድራጊ፣ ትንቢት ተናጋሪ መጣ ቢባል የቤተክርስቲያኒቱ ቅጽር ሞልቶ ከተማይቱ በህዝብ ትጨናነቅ ነበር።

ምእመናን በስህተት ጎዳና አትረማመዱ ከሁሉም ወንጌል ይቀድማል ሁልጊዜ ተአምራት የሚገለጥባት ቤተክርስቲያን ተአምር አድራጊ መጣ በሚል እንግዳ ነገር አትወሰዱ እያጠመቀች መንፈሳዊ ልጅነትን የምትሰጥ ቤተክርስቲያን በጥምቀት ድኅነተ ስጋ ድኅነተ ነብስ ፈውስ መንፈሳዊን ለሁሉ የምታጎናጽፍ ቤተክርስቲያን ፤ ትምህርቷም መልኳም ባልሆነ አጥማቂ ነን በሚሉ ሐሳውያን ምክንያት የሚሸወድ ትውልድ ሊኖር አይገባም።

ይሄው መንፈሳዊው መሰናዶ ከሁሉ በላይ ነው ወንጌሉን ቅረቡና ተማሩት መምህራኑ ይህንን ምግብ አቅርበው ብሉ ይሏችኋል በቅድስት ቤተክርስቲያን በውስጧ ያለውን እውነተኛ መብልና መጠጥ ቅረቡና ተመገቡት ጠጡትም ይህ የሕይወት እንጀራ ሁልጊዜ ይቀርባል ይህ የሕይወት ውኃ ዘወትር ይቀዳል ለምን ትሩቁታላችሁ በርቱ እንጂ እርሱን ስትመገቡ ትጠግባላችሁ እርሱን ስትጠጡት ትረካላችሁ በበዓሉ መሰበሰባችሁ ይህንን በማድረግ ሊቋጭ ይገባል።

ምእመናን አስተውሉ እውነቱን ነው የምንነግራችሁ ከዚህ ውጭ የሚገኝ ሕይወት የለም እኔ የዚህ መንፈሳዊ ቤት አስተዳዳሪ የሆንኩት እናንተን ለመንግሥተ እግዚአብሔር ለማብቃት ነው የዚህ ቤት መሠራት እናንተን በነብስ ለመጥቀም ነው ነብሳችሁ እንዳትጎሳቆል እንዳትራብ ቤቱ ለሁሉ የሚበቃ ዘለዓለማዊ ሕይወት የሚገኝበት ድግስ ያለበት ነው ይህን ምግብ ቅረቡና ብሉት።

መንፈሳዊ ክብር ከሚገኝበት ከዚህ አደባባይ አትራቁ በሰማይ ደጅ በቤታችሁ ተሰብሰቡ በየደረጃችሁም በአገልግሉት ትጉ ለእናታችሁ ስሩላት በረከትም አግኙ ምእመናን የትም አትባክኑ መምህራን እየዞሩ ከጥንት ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ያስተምራሉ የመምህራን መንገላታት እኛ እንጠቀም ዘንድ ነው እንጂ የዙረት ልማድ አይደለም። እግዚአብሔር ሁልጊዜ ይናገራል እዝነ ልቡናን ከፍቶ መስማት ይገባል ዛሬም በሰደድ እሳት በመሬት መንቀጥቀጥ በልዩልዩ ነገሮች እየተናገረን ይገኛል እኛም አመፃችን ዋዛ ፈዛዛችን እንደበረታ ነው ለእያንዳንዳችን ማስተዋልን ያድለን ብለው የመከሩት የቡታጅራ ደብረ ምሕረት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል አስተዳዳሪ ክቡር መላከ ምሕረት ቆሞስ አባ ኃይለሚካኤል ናቸው።

የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታሪካዊውና ጥንታዊው ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከብሮ ዋለ።          #ኦሚማ ጥር 7 ቀን...
16/01/2025

የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታሪካዊውና ጥንታዊው ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከብሮ ዋለ።

#ኦሚማ ጥር 7 ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም አዲስ አበበባ
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++

የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታሪካዊውና ጥንታዊው ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን አቡነ ቀሌምንጦስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያና የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።

በተመሳሳይ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መጋቤ ሐዲስ ነቅዓጥበብ አባቡ ፣ የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ሓላፊዎች ፣ የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ መልአከ ብርሃናት ቆሞስ አባ ይትባረክ መኮንን ፣ የአዲስ አበባየተለያዩ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ተገኝተዋል።

በዓሉ በማስመልከት ሊቀ ጉባኤ ቆሞስ አባ ተክለ ሃይማኖት ወልዱ "ኑ እንውረድ የከለዳውያንን ቋንቋቸውን እንደባልቀው" በሚል ኃይለ ቃል ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።

በኖኅ ዘመን ከተፈጸመው የጥፋት ያልተማሩት ከለዳውያን ናምሩድ በሚባል ሰው ስም ከፍተኛ ሕንጻ ገንብተው በፈጣሪያቸው ላይ በማመፃቸው እግዚአብሔር ነፋስ አስነስቶ ሕንጻውን እንዳፈራሰውና ቋንቋቸውንም እንደገለባበጠባቸው አስተምረዋል።

ከለዳውያን አንድ መግባቢ ቋንቋ የነበራቸው ቢሆን
በሠሩት ኃጢአት ምክንያት የነበራቸው 1 ቋንቋ ላይ 71 ቋንቋ ጨምሮ መግባባት ሳይችሉ መቅረታቸውን ሊቀ ጉባኤ አስተምረዋል።

የገነት በር ተዘግቶበት በሱራፌልና በኪሩቤል በምትገለባበጥ ሰይፍ ትጠበቅ ወደ የነበረችው ኤደን ገነት አዳም እንዳይገባ ተከልክሎ እንደነበረ ሊቀ ጉባኤ ገልጸዋል።

ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰናዖርን ግንብ ካፈረሱት ከሦሰቱ አካል መካከል ወልድ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግ ልማርያም በድንግልና ተወልዶ ወደዚህ ዓለም በመጣበት ወቅት አዳም ወደ ኤደን ገብቷል ፣ ሰውና መላእክት በአንድ ላይ ዘምረዋል ፣ነፍስና ሥጋ ፣ሕዝብና አሕዛብ ታርቀዋል ብለዋል።

መምህሩ በአስተምህሯቸው ተለያይተው የነበሩት ኢየሱስ ክርስቶስ ለ12ቱ ደቀ መዛሙርት 72 ቋንቋ በመገለጽ ዓለምን በሚያግባባ ቋንቋ አስተምረዋል ዛሬም በሀገራችን የሚታየውን የዘረኝነትና የቋንቋ የልዩነት ግንብ አፍርሰው ቅድስት ሥላሴ የፍቅርና የአንድነት ግንብ ያጽኑልን ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ባስተላለፉት መልእክት ኃጢአትን የሚያደርግ የዲያብሎስን ሴራ ይሠራልና ይኸንን የዲያብሎስን ሴራ ያፈርስ ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ ስለዚህ በልደቱ ወልደ እግዚአብሔር የጠላትን ሴራ ተደምስሷልና ዛሬም በምድራችን የምናየውን ጠብ መከራና መለያየትን ይደምስስልን ብለዋል።

ብፁዕ ቡነ ቀሌምንጦስ በሰጡት ቃለ ምዕዳን በዓለማዊያን ክፋትና ኃጢአት ምክንያት እየተንቀጠቀች ነውና እንደየግል ሀሳባችን ሳይሆን እንደ እግዚአብሔር ቃልና ፈቃድ ልንኖር ይገባናል ሕንጻ ሰናዖር ያፈረሰ እግዚአብሔር ለሕዝባችንና ለሀገራችን አንድነት መሰናክል የሆኑ ግንቦችን አምላካችን ያፍርስልን ለሀገራችንና ለሕዝባችን ሰላምና ፍቅር ያድልልን ብለዋል።

በዓሉ ከዋዜማው ጀምሮ በሊቃውንት ስብሐተ እግዚአብሔር ፣ በደብሩ ሰንበት ትምህርት ቤት ዘማርያን ወረብ ፣ በምእናን ዝማሬና እልልታ አምሮና ተውቦ በሰላም ተጠናቋል ሲል የዘገበው አቡቀለምሲስ ሚዲያ ነው

15/01/2025
15/01/2025

ከቡታጅራ ደብረ ምሕረት ቅድስት ሥላሴ

ቡታጅራ የደብረ ምሕረት ቅድስት ሥላሴ ገዳም የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በፎቶ!! #ኦሚማ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ቡታጅራ
15/01/2025

ቡታጅራ የደብረ ምሕረት ቅድስት ሥላሴ ገዳም የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በፎቶ!!
#ኦሚማ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ቡታጅራ

የአጋዝተ ዓለም የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳስት በተገኙበት እየተከበረ ነው።
15/01/2025

የአጋዝተ ዓለም የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳስት በተገኙበት እየተከበረ ነው።

የአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከብሯል !             #ኦሚማ   ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም አዲ...
15/01/2025

የአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በድምቀት ተከብሯል !

#ኦሚማ ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""

የአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በእንጦጦ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ወቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በድምቀት የተከበረ ሲሆን በበዓሉም ላይ የጎንደር ደብረ ኃይል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያም የታች ቤት አቋቋም ምስክር ጉባኤ ቤት መምህር መጋቤ አእላፍ የኔታ ክቡር ጥላሁንን ጨምሮ በርካታ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ምእመናን ተገኝተዋል።

በቡታጅራ ከተማ የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።         ኦፍና ሚዲያ ማዕከል ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ቡታጅራ ===================...
15/01/2025

በቡታጅራ ከተማ የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል በታላቅ መንፈሳዊ ድምቀት ተከብሮ ዋለ።

ኦፍና ሚዲያ ማዕከል ጥር 7 ቀን 2017 ዓ.ም ቡታጅራ
=======================================

በኢትዮጵያ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በምስራቅ ጉራጌና ማረቆ ልዩ ወረዳ ሀገረ ስብከት በቡታጅራ ከተማ የቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል የደብረ ምሕረት ቅድስት ሥላሴ ገዳም አስተዳዳሪ ክቡር መላከ ምሕረት ቆሞስ አባ ኃይለሚካኤልና የገዳማት የአድባራት አስተዳዳሪዎች የወረዳ ቤተክህነቱ ሰራተኞች እንዲሁም በርካታ የአካባቢው ምእመናን በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ስርዐት ተከብሮ ዋለ።

የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል ሰባኬ ወንጌል የሆኑት መምህር ፈቃዱ ሳኅሌ ዕለቱን በማስመልከት ሰፊ ትምህርት ሰጥተዋል የደብሩ ሊቃውንትና የገዳሙ ሰንበት ት/ቤት መዘምራንም ዕለቱን የሚዘክር ያሬዳዊ ዝማሬ አቅርበዋል።

በመጨረሻም የገዳሙ አስተዳዳሪ መላከ ምሕረት ቆሞስ አባ ኃይለሚካኤል ለማኅበረ ምእመናኑ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን ቤተክርስቲያንም ሀገርም መስቀል ላይ ናቸው ብለዋል ስለዚህ በመጠን ኑሩ በጸሎት በርታ ወቅቱ እርጋታና ስክነት የሚያጠይቅ ነው ሲሉ በመልእክታቸው አክለዋል። እንደ መልአከ ምሕረት ገለፃ በዚህ ወር የዛሬውን በዓል ጨምሮ መጪው ጥምቀትና በርካታ ሰርጎች ሃይማኖታዊና ባህላዊ ኩነቶች የሚስተናገዱበት ወር በመሆኑ ሁሉን በስርዐት ማስኬድና ችግረኞችን በመጎብኘት የምናሳልፈው መሆን ይጠበቅበታል ሲሉ አስገንዝበዋል።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ፡፡ አሜን፡፡እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ  በዓል አደረሰን አደረሳችሁ!!አጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወልድ መንፈስ ቅ...
15/01/2025

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ፡፡ አሜን፡፡

እንኳን ለቅድስት ሥላሴ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ!!
አጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ

ሥሉስ ቅዱስ (አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ) ማለት በሦስነት ዓለምን ካለመኖር ወደ መኖር አምጥተው የፈጠሩ ለዘመናቸው ኀልፈት በመንግሥታቸው ሽረት የሌለበት ዓለምን ፈጥረው የሚመግቡ እነሱ ዓለሙንና በውስጧ ያለውን ሲያስገኙ አስገኝ የሌላቸው በባሕር በየብስ በሰማይ በምድር ምሉኣን የኾኑ ናቸው፡፡ ባሕርያቸው ባሕርያቸውን ያመሰግነዋል፡፡

ሥላሴ በስም በአካል ፫ በባሕርይ በህልውና በመለኮት ፩ አንድ ናቸው፡፡ በስመ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ይባላሉ፡፡ በግብር አብ ወላዲ ወልድ ተወላዲ መንፈስ ቅዱስ ሠራፂ፤ አብ መውለድ ማሥረፅ ፤ ወልድ መወለድ መንፈስ ቅዱስ መሥረፅ ግብራቸው ነው፡፡

አካል ማለት ከራስ ጠጉር እስከ እግር ጥፍር ድረስ ሲኾን እንደ አንድ ሰው አካል ፈራሽ በስባሽ አይደለም፡፡ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ለየራሳቸው ፍጹም አካል ፍጹም ገጽ ፍጹም መልክ አላቸው፡፡ አብ ልብ ወልድ ቃል መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ ሲኾኑ በአብ ልብነት ወልድ መንፈስ ቅዱስ ያስባሉ፡፡ በወልድ ቃልነት አብ መንፈስ ቅዱስ ይናገራሉ፡፡ በመንፈስ ቅዱስ እስትፋስነት አብ ወልድ ሕያዋን ናቸው፡፡

ይህም የኩነት ስም ነው ይባላል፡፡ የአንድነት ስማቸው እግዚአብሔር፣ አምላክ ፣ጸባኦት፣ ኤልሻዳይ፣ አዶናይ፣ መለኮት፣ ፈጣሪ፣ መሓሪ የመሳሰለው በነጣለ ግስ የሚነገረው ስም ነው፡፡ አብ ወላዲ አሥራፂ ወልድን ተወላዲ መንፈስ ቅዱስን ሠራፂ ብለን ፫ቱን አንድ አምላክ አንላለን እንጅ ፫ አምላክ አንልም ይህም ሲባል አንድነታቸው ሦስትነታቸውን አይጠቀልለውም ሦስትነታቸው አንድነታቸውን አይለያውም፡፡ በባሕርይ በፈቃድ በሥልጣን ፩ድ ናቸው፡፡

ጥቅመ ሰናኦር
ዛሬ ጥር 7 የሚከበረው በዓል ታሪክ በአጭሩ ከጥፋት ውኃ በኋላ በምድር ላይ ከተራቡት ከካም ዘሮች ናምሩድ በምድር ላይ ኀያል መኾን ጀመረ፡፡ ዘፍ ፲፥፱ ከምሥራቅ ተነሥተው ሰናኦር በምትባል ሜዳ ላይ ስማችንን እናስጠራው ዘንድ ወደ ሰማይ የሚደርስ ግንብ እንሥራ ተባባሉና በእሳት ተኮሰው መሥራት ጀመሩ፡፡

ወርዱ ፫ ክንዱ ቁመቱ ፲ ክንድ ፩ ወገን የሚኾን አቈልቋዩ ፫ ክንድ ቁመቱ ፭ ሺህ ፬፻፴፫ ክንድ ከ፪ ስንዝር በአንድ ጎን አቈልቋዩ ፲፭ ምዕራፍ የሚኾን ግንብ በ፵፭ ዓመት ሠሩ፡፡ በዚህ ጊዜ ሥላሴ “ንዑ ንረድ ወንዝርዎ (ወንክዐዎ) ለነገሮሙ” ይላል፡፡ ኦ.ዘፍ. ፲፩፥፩ ትርጉም ኑ ወርደን ቋንቋቸውን እንደባልቅ ብለው በዐሳብ ለዩአቸው፡፡ ይህም የኾነበት በትዕቢታቸው ነው፡፡ ጦር ወደ ሰማይ እየወረወሩ አኹን አብን ወጋነው አኹን ወልድን ወጋነው አኹን መንፈስ ቅዱስን ወጋነው እያሉ ሲዘብቱ ባቢል የሚል ጥልቅ ነፋሰ ተልኮ ሕንጻቸውን ንዶታል፡፡ እነሱንም ተበታትነዋል፡፡ ስለዚህ ሰናኦር ባቢል ባቢሎን ተብላለች፡፡ ዝሩት (የተበተነች) ማለት ነው፡፡

የአጋዕዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ በረከት ረድኤት አይለየን፡፡

ምንጭ፡- መድበለ ታሪክ ዘሐምሌ 7

15/01/2025

ከቡታጅራ ደብረ ምሕረት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን

Address

ADISABEBA
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኦፍና ሚዲያ ማዕከል - ofna media center posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share