Ijjoolle Shaggar

Ijjoolle Shaggar Alaaf keessi shaggaris teenya

24/07/2024

ሰላምም ጦርነትም የማይችል ወለፈንዲ ጠላት ነው የገጠመን!

Danielkibret

01/04/2024

ያ ቀን!!

መች ነበር እሱ ቀን: ኢህአዴግ ዶክተር አብይ አህመድን ልቀ-መንበር አድርጎ የመረጠብትና እኛ መግልጫ ለመጠበቅ ውጭ ያደርንበት!?

The difference is visible!
11/02/2024

The difference is visible!

24/01/2024

#60ቀናት በላፍቶ

ላፍቶ፣ጥር 15/2016:-በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሁለተኛ ዙር የ60 ቀን እቅድ ዛሬ ይፋ ሆኗል::

በእቅዱ መሰረት በሚቀጥሉት 60 ቀናት ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ላይ በልዩ ትኩረት የሚሰራ ይሆናል::

በዚህም:-

- የህብረተሰብ ተሳትፎን ከፍ በማድረግ ለተለያዩ ልማት የሚውል ከ4 መቶ ሚሊዮን ብር በላይ ሀብት ከህብረተሰቡ መሰብሰብ

- የክፍለ ከተማ ምድረ ግቢ ምቹ ማድረግ እና ሞደል የከተማ ግብርና በግቢው ውስጥ መስራት

- በክ/ከተማ ህንፃ ላይ 4 ወለሎችን ማደስ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማደራጅትና ለአገልግሎት ምቹና ሳቢ ማድረግ

- እስከ 600 ቤተሰብ ተጠቃሚ የሚያደርግ የአቅመ ደካሞች ቤት እድሳት

- የመንገድና ሰብ ቤዝ መሰረተ ልማት ዝርጋታና እድሳት

- የመንግስት ቤትና መሬት አካባቢ ያሉትን ህገ ወጥነት መቆጣጠር በህገ ወጥ የተያዙትን ማስለቀቅ

- የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት

- የከተማ ስታንዳርድ ማስጠበቅ

- የከተማ ፅዳትና ደረቅ ቆሻሻ ማስወገድ

- የህፃናት ፕሌይ ግራውንድ

- የከተማ ግብርና ማስፋፋት

- የኑሮ ውድነት የሚያረጋጉ ስራዎች

- መሬት ነክ አገልግሎቶችን ማዘመን

- ደንብ መተላለፎችን በጥብቅ መቆጣጠር

- የግንባታ ፕሮጀክቶች (ከ40 በላይ ፕሮጅክቶች)

- የፀጥታ ስራን ማጠናከር

- የመልካም አስተዳደር ችግሮችን መፍታትና ተጠያቂነት ማረጋገጥ

- የስራ እድል ፈጠራ

- ማህበረሰብ አቀፍ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ

- የገቢ አሰባሰብ ማሻሻል

- ለህዳሴ ግድብ ገቢ ማሰባሰብ

- የቴክኖሎጂና ኢንተርኔት መሰረተ ልማት ዝርጋታ

- የነዋሪዎች አገልግሎት አሰጣጥ ማዘመን

የክፍለ ከተማ አስተዳደሩ በትኩረት የሚሰራባቸው ይሆናል::

22/01/2024

Kanaa akka naaf Gootan waan beekuf dursee ULFAADHA jechuu barbaada. 🙏🙏🙏

Link kana tuquudhaan Follow naa godhaa namoota kaanis invite naa godhaa.

ሰላም ቤተሰብ ይሄ ፔጅ አካወንቴ 5 ሺ በመሟላቱ ምክንያት የተከፈተ ነው:: እስከሁን ግን 5.3k 🤔🤔 አዛ ነው የምር::

ልንኩን አስቀምጫለው Follow, like and invite your friends please 🙏

https://www.facebook.com/profile.php?id=100068180716524&mibextid=LQQJ4d

what you can find here is only Abdurazak's personal view and stand

ከአዲስ አበባ 0 Km ርቀት ላይ ቆሜ...✍በአብዲ ኬጠዋት ነበር ቀጠሯችን 1:00 ሰዓት። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፅህፈት ቤት ተገናኝተን ጉብኝታችን ልንጀምር ነው:: ጉብኝቱ ...
20/12/2023

ከአዲስ አበባ 0 Km ርቀት ላይ ቆሜ...
✍በአብዲ ኬ

ጠዋት ነበር ቀጠሯችን 1:00 ሰዓት። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ፅህፈት ቤት ተገናኝተን ጉብኝታችን ልንጀምር ነው:: ጉብኝቱ ብዙ ዘመናትን በትዝታ የሚያስቃኝ፣ የትውልዶችን ትስስር፣ የኢትዮጵያዊያንን ዘመን ተሻጋሪ አንድነትና አንጸባራቂ ጀብድ የሚታይበት አድዋ ነው። አድዋ-የጥንቱ፣ የትናንቱ፣ የዛሬውና የነገው ታሪካችን፡፡

ታሪካዊው አድዋ ሰሜን ድረስ አልራቀም። እዚሁ መሀል አዲስ አበባ ከንቲባ ጽህፈት ቤት ፊት ለፊት ጉብ ብሏል። ጉብኝታችንን እንጀምር። የትም ሳንራመድ 00 km ላይ እንገኛለን። በዚህ ስፍራ ያለው ነገር ተነግሮ የሚያልቅ ታሪክ አይደለም፤ ለመግለጽ ቃላት የሚያጥሩህ ከባድ ታሪክ ነውና ይህን በልባችን እንያዝ።

ጠዋት አንድ ሰዓት ቢሆንም ቀጠሯችን ያው የባህላችን ነገር ሆኖ ሁሉ እኩል ተሟልቶ አልመጣምና እየተጠባበቅን ነበር፤ በዚህ ሰዓት የረዥም ጊዜ ትዝታ የሚቀሰቅሱ ከተገናኘን የቆየን ጋዜጠኞች ጓደኞቼ ብቅ ብቅ ማለት ጀመሩ። ኦኦ እገልዬ ጠፋህ/ጠፋሽ! ወፈርክ/ወፈርሽ! አቤት አረጀህ! .... እየተባባልን ቆይተን የጉብኝታችን ማስጀመሪያ ገለፃ ሊጀመር ወደ አዲስ አበባ ባህል አዳራሽ ገባን፤ ገለፃው ተጀመረ፡፡

የከንቲባ ጽህፈት ቤት ሃላፊው አቶ ጥላሁን ወርቁ ወደ መድረኩ ብቅ ብሎ፤ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን ካስተላልፉ በኋላ፤ ‘’የዛሬ ቆይታችን የሚሆነው የፕሮጅክት ጉብኝት ነው’’ አሉ፡፡ ቀጠል አድርገውም ‘’ይህ ዛሬ የምንጎበኘው ፕሮጀክት እንደ ዜጋም የዚህ ትውልድ አካል በመሆኔ፤ እንደ አመራርም በዚህ ፕሮጀክት ላይ የራሴን አስተዋጽዖ በማበርከቴ በጣም ያኮራኛል’’ አሉ፡፡

እኔም ውስጤ ለመስማት ቢጓጓም፤ የትኛው ፕሮጀክት ሊሆን እንደሚችል መገመቴ አልቀረም፡፡ እንድንጎበኝ ቀጠሮ ተይዞልን በስፍራው የተሰባሰብነው ፕሮጀክት ‘የአድዋ ዜሮ ኪሎሜትር’ ፕሮጅክት ነው፤ ጎብኚዎች ደግሞ በአገሪቱ ካሉ ሁሉም የአገር ውስጥና የውጭ ሚዲያ የተውጣጡ ጋዜጠኞችና የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች ናቸው። ፖ! ጥሩ አጋጣሚ ነው አልኩኝ በውስጤ፡፡

ይህን ፕሮጀክት ከውጭ ከመመልከትና በየቀኑ የሚያሳየውን ለውጥ እያየው በፍጥነቱ ከመገረም ውጭ፤ ቅርቤ ሆኖ ሳለ ገብቼ አላየሁም ነበር፤ የመጀመሪያ ጉብኝቴ ነው፡፡ እንደ ግንባታው ፍጥነት ሁሉ የስሙም ስያሜ ሁሉ ይገርመኛል፤ ...’አድዋ ዜሮ ኪሎሜትር’... ፡፡
ወደ ጉብኝታችን ከመግባታችን በፊት እስኪ ጥቂት ስለስያሜና ስለፕሮጀክቱ ምንነት ግልጽ አድርጌ ልጀምር፡፡ የአድዋ ዜሮ ኪሎሜትር ፕሮጀክት፦ የመዲናችንና አገራችን አምብርት የሆነችው የአራዶቹ መንደር ፒያሳ ላይ፤ የኢትዮጵያና የአፍሪካ ዋና ከተማ የሆነች አዲስ አባባ ከተማ አስተዳድር ከንቲባ ጽህፈት ቤት በር ላይ፤ የአገራችን ከተሞች ርቀት መለኪያ መነሻ የሆነ ስፍራ ላይ እየተገናባ የሚገኝ የጥቁር ህዝብ ኩራት የሆነው የአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም ነው፡፡

አድዋ ዜሮ ዜሮ የተባለበትም ምክኒያት የሚገኝበትን ርቀት ለመግለጽ ታስቦ ነው፤ የአገራችን ከተሞች ከአዲስ አበባ ያላቸውን ርቀት ሲለካ የሚጀምርበት ቦታ ላይ የሚገኝ ፕሮጀክት በመሆኑ የሱ ርቀት ሲለካ 00 ነው ኪሎሜትሩ፡፡ የፕሮጀክቱ ብቻ አይደለም የአድዋ ታሪክም፤ ስፍራውም ከእያንዳንዱ ኢትዮጵያዊና ጥቁር ህዝብ ልብ ያለው ርቀት ሲለካ ርቀቱ 00 ነው ባይ ነኝ፤ ምክንያቱም ከታሪካችን ከማንነታችን በጥቅሉ ከእኛነታችን ተለይቶ አያውቅምና፡፡

ታሪኩ ብዙ ነውና እሱን ትተን ወደ ጉብኝታችን ልመልሳችሁ፤ ጉብኝቱን ስንጀምር እያወጋን ጎን ለጎን ስንራመድ ለነበሩት ወዳጆቼ እንዲህ አልኳቸው... ‘’ ዜሮ ኪሎሜትር ተጉዘን አድዋን ልናያው ነዋ’’... አዎ እውነቴን እኮ ነው፤ ከአዲስ አባባ ምንም ኪሎሜትር ሳንጓዝ የአድዋ ተራሮች ላይ የተፈጠረው ገድል ከነ ሙሉ ክብሩ ተሰይሞ ነው ያገኘሁት፡፡ ለዚያም ነው እኔ እንደዚህ ያስገረመኝ አድዋን የሚመጥን ሌላ አድዋን የሚያክል ገድል የተፈጸመበት ድንቅ ስራ 00 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ቆሜ ለማስጎብኘት የፈለኩት፡፡

ከንቲባ ጽህፈት ቤትና አድዋ ዜሮ ኪሎሜትር ሙዚየምን ባገናኘው ድልድይ ተሻግረን ጉብኝቱ ስንጀምር አቶ ጥላሁን የሜጋ ፕሮጀክቶች ጽህፈት ቤት ስራ አስኪያየጅ ለሆኑት ለኢንጂነር ደቦል አስተዋውቆ ወደርሱ አሸጋገረን፡፡ ኢንጂነሩ ስለ ፕሮጀክቱ ሲያብራሩ ‘’ይህ ፕሮጀክት ያረፈበት 3.3 ሄክታር ላይ ሲሆን ከ3 እስከ 5 ወለሎች አሉት፤ ለግንባታውም 4.3 ቢሊዮን ወጪ ተደርጓል ’’ ብሎ ሲጀምሩ በጣም ገረመኝ፣ መገረም ብቻ ሳይሆን ስለ ፕሮጀክቱ ብዙም እንደማላውቅ ገባኝ። እንደኔ ስለ ፕሮጀክቱ በጥልቀት ያልተረዳ ብዙ ሰው እንደሚኖር በማሰብም ይህን ጽሁፍ ለመጻፍ ወሰንኩ፡፡

ይህ ፕሮጀከት ከውጭ ሳየውና ሳስበው የሚወከለው ታሪክ ቢገዝፍብኝም፤ ግንባታው ሳየው ቀለል ያለ፤ ሰማይ ጠቀስ ህንጻ አለመሆኑን ነበር ማስበው፡፡ የሚገርማችሁ ነገር ግን በጣም ግዙፍ ግንባታ ነው፤ ከአድዋ ጋር የተያዘው የህዝቡ ገድልና የነበረው ወኔና መነሳሳት፤ የነበረውን ትብብርና አንደነት፤ የጦርነቱ አመራር፤ በዚህ ውስጥ የአንበሳውን ሚና የተጫወቱ ንጉሰ ነገስቱ፤ ንግስቲቱንና የጦር መሪዎችን በሃውልትና በተለያየ መንገድ በሚደንቅ ሁኔታ ተቀምጧል፡፡ የአድዋ ብቻ ሳይሆን የመቀሌ ጦርነትና የአምባላጌንም ታሪክ በአግባቡ ለማካትተ ታስቧል፡፡

በዚህ ጉዳይ ላይ የሚገርም ቅደመ ዝግጅትና ጥንቃቄ እየተደረገ መሆኑን የተገነዘብኩበትም አንድ ነገር በአቶ ጥላሁን ተጠቅሶ ነበር፤ እሱም በውስጡ የሚካተቱትን ነገሮች የሚለይ ቅርስና የሚጎበኝ ቁሳቁሶችን የሚያሰባስብ እና ሙዚየም ውስጥ መንፀባረቅ የሚገባ ታሪኮችን የሚለይ የታሪክ ባለሙያዎች ቡድን ተቋቁሞ ስራ መጀምሩን ሰምቻለው፡፡

ከሙዚየምነት በተጨማሪ ዘርፈ ብዙና መልከ ብዙ አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጎ ነው የተገነባው፤ የተወሰኑትን በአሃዛዊ መረጃ አስደግፈን ስንመለከት፦ ከላይ የጠቀስኩላችሁን ከከንቲባ ጽ/ቤት ጋር የሚያስተሳስረውን በር ጨምሮ 5 በሮች አሉት፤ ከዋናው ሙዚየም በተጨማሪ 400 ሰዎችን በነፍስወከፍ የመያዝ አቅም ያላቸው 2 የስብሰባ አዳራሾችና 250 ሰዎችን የሚያስተናግድ ሌላ አዳራሽና 3 የተለያዩ የመሰብሰቢያ አዳራሾች ይኖሩታል፡፡

ሌላኛው የፕሮጀክቱ አካል የተለያዩ ቢሮዎችና የመመገቢያ አዳራሽን የሚያካትተው ክንፍ ይሆናል፡፡ በዚህኛው የፕሮጀክቱ ክፍል ዘመኑ በደረሰባቸው መሳሪያዎች የተደራጀውና 2000 መቀመጫዎች የሚኖሩት ግዙፍና በዘመናዊ ግብዓቶች የተደራጀ አዳራሽ /City Hall/ ይኖሩታል፡፡

በአንድ ጊዜ 1000 መኪኖችን ማቆም የሚያስችል የመኪና ማቆሚያ ፣የታክሲ እና የአውቶቡስ ተርሚናል በዚሁ ውስጥ ይገኛል፡፡ ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውልና 4000 መቀመጫ የሚይዝ ግዙፍ ሁለገብ አዳራሽ፣ የቤት ውስጥ ስፖርት ሜዳ፣ ህፃናት የሚጫወቱበት ሜዳ፣ በዘመናዊ መሳሪያ የተደራጀ ጂምናዚየም፣ሀገራዊ የዕደጥበብ ውጤቶች እና ሌሎችም የሚሸጡባቸው ሱቆች በፕሮጀክቱ ሌላኛው ክንፍ የሚገኙ አገልግሎቶች ናቸው፡፡

ከዚህም በተጨማሪ 2 ዘመናዊ ሲኒማዎች፤ ካፌ እና ሬስቶራንት፤ ግዙፍ ቤተ-መፅሀፍት፤ አምፊ ቲያትር፤ ከቤት ውጪ የሚዘጋጅ ኤግዚቢሽን ማሳያ ቦታ አሉት፡፡ ከህንጻው ውጭ የአካባቢውን ገጽታ የሚቀየሩ ሁለት ፕላዛዎች በግራና በቀኝ እየተገነቡ ነው፤ ይህም ከሙዚየሙና በውስጡ በተካተቱ አገልገሎቶች ጨምሮ የአካባቢውን የቱሪስት መዳረሻነትና ሳቢነት ከፍ የሚያደርግ ነው፡፡

የፕሮጀክቱ ግንባታ እየተጠናቀ ነው፤ ከዚህ በኋላ ቢበዛ አንድ ወር ቢወስድ ነው፡፡ ይህ ተጠናቆ ለአገር፤ ለመላው ጥቁር ህዝብ ኩራት ሆነው ማየት እንኳን ያላያችሁን እኔ በዚህ ሰሞን ያየሁትን እራሱ ያጓጓኛል፡፡ ይህን ስራ ቀድሞ በምናባቸው ቀርጾ ሃሳብ ያመነጩ ጭንቅላቶች እና ሰርቶ እውን ያደረጉ እጆች ይባረኩ፡፡

በዚህ ስራ ውስጥ፤ የሃሳቡን አመንጪ ጠ/ሚ አብይ አህመድንና ይህን ስራ አቅዶ በጀትና የሰው ሀይል አስመድበው ሌትተቀን ተከታትሎ በዚህ ደረጃ ያደረሱትን ከንቲባ አዳነች አቤቤን ጨምሮ መላው አመራሩንና የግንባታ ስራው ላይ የተሳተፉትን አለማመስገን ንፉግነት ነው፡፡ እነርሱም እንደ አባቶቻችን ሌላ አድዋን የሚያክል ገድል ነው የፈጸሙት ባይ ነኝ።

ቸር እንሰንብት!!

ጂግጂጋ ነው ያለው ጀምዓው!! #የኢትዮጵያልጆች ቀን #የብሄርብሄረሰቦች ቀን
08/12/2023

ጂግጂጋ ነው ያለው ጀምዓው!!

#የኢትዮጵያልጆች ቀን
#የብሄርብሄረሰቦች ቀን

25/11/2023
14/11/2023

ነጠላ ትርክት ሀገር አይገነባም!!

04/05/2023

☑️☑️ የሽግግር መንግስት ሳይሆን የሚያሻግር ሃሳብ ነው የሚያስፈልገን!
🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ከማጡ ወጥተን እንደ ሀገር ብቻ ሳይሆን እንደ አሁጉርም ተምሳሌት ሆነን ቆመናል‼️✌️ አሁን ላይ የሚያስፈልገን ክፉውን ጊዜ ላሻገረን እና ለቀጣዩ ዘመን ተስፋ ለሆነን የሚበጅ ሃሳብ ማዋጣት ነው‼️👌 ሃሳብ ሲደመር ታላቅነትን ይፈጥራል‼️👌 እኔ ያልኩት ብቻ ማለት አንሶ ያሳንሰናል‼️‼

02/04/2023

ሰውዬው ሃሳብ አለው ብታግዘው ታተርፋለህ‼️

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ijjoolle Shaggar posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share