Public News Ethiopia /P.N.E

Public News Ethiopia /P.N.E Focusing on socioeconomic and political aspects.

" የቼልሲ እና ዩናይትድ ትልቅ ጨዋታ አይደለም " ፖል ሜርሰን የቀድሞ የመድፈኞቹ እና የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ፖል ሜርሰን የዛሬው የቼልሲ እና ማንችስተር ዩናይትድ ጨ...
04/04/2024

" የቼልሲ እና ዩናይትድ ትልቅ ጨዋታ አይደለም " ፖል ሜርሰን

የቀድሞ የመድፈኞቹ እና የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ፖል ሜርሰን የዛሬው የቼልሲ እና ማንችስተር ዩናይትድ ጨዋታ ትልቅ ጨዋታ አለመሆኑን ገልጿል።

ከዚህ በፊት የማንችስተር ዩናይትድ እና ቼልሲ ጨዋታ በጉጉት የሚጠበቅ እንደነበር የገለፀው ፖል ሜርሰን " ጨዋታው በአሁኑ ሰዓት ትልቅ ጨዋታ እንኳን አይደለም " በማለት ተናግሯል።

" ከሁለቱ አንዱ ቡድን ከብሬንትፎርድ ጋር ባደረገው ጨዋታ ከባድ ፈተና ገጥሞት ነበር ሌላኛው ደግሞ አስር ተጨዋቾች የያዘው በርንሌይን ተቆጣጥሮ መጫወት አልቻለም።"
n.e

21/02/2024

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! እግዜአብሄር መልካም ነው, Mohammed Jafer, Fife Bmlke

20/02/2024

አቢ----ይይይ!!🤔😎🤔😎

" ይሄ ' የአማራ አዋሳኝ ' የሚባለው ቀልድ መቆም ያለበት ነው " - አቶ ረዳዒ ኃለፎምየትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ረዳዒ ሀለፎም ሰሞኑን ስለነበረው የተኩስ ልውውጥ...
17/02/2024

" ይሄ ' የአማራ አዋሳኝ ' የሚባለው ቀልድ መቆም ያለበት ነው " - አቶ ረዳዒ ኃለፎም

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ረዳዒ ሀለፎም ሰሞኑን ስለነበረው የተኩስ ልውውጥ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

አቶ ረዳዒ ሀለፎም ምን አሉ ?

- ግጭቱ ራያ አላማጣ ሳይሆን ጨርጨር አካባቢ ነው። ይሄ የአማራ አዋሳኝ የሚባለው #ቀልድ ደግሞ መቆም ያለበት ነው።

- የትግራይ መሬት ነው ጨርጨር። ጨርጨር ትግራይ እንጂ አማራ ሆኖ አያውቅም። አሁንም አይደለም። እዚያው የአማራ ታጣቂዎች አሉ። እነዛ የአማራ ታጣቂዎች በእኛ ሚሊሻዎች ላይ የፈጸሙት ጥቃት ነው። የአጭር ጊዜ ተኩስ ልውውጥ ነበር ቁሟል አሁን ግጭቱ የለም።

* ጉዳዩን በተመለከተ ምን እየተሰራ እንደሆነ ለቀረበ ጥያቄ ፦ " በእኛ በኩል (በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደርም) ከላይ ከሚመለከታቸው የፌደራሉ መንግሥትም የተወሰነ ንግግር እየተደረበት ነው " ብለዋል።

* የመፍትሄ ሀሳብን በተመለከተ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተነሳው ጥያቄ ፦

" የመጀመሪያው ነገር ሕገ መንግሥቱን ማክበር ነው። የአዋሳኝ ጉዳይ አይደለም መሀል ትግራይ ላይ ነው ችግሩ እየተፈጠረ ያለው። ወረው በኃይል ከያዙት መሬት ላይ ነው አሁን ደግሞ መልሰው ጥቃት እየፈጸሙ ያለት። ይሄ ትክክል አይደለም። ለማናችንም የሚጠቅም ነገር አይደለም።

መሆን ያለበት ጥያቄ ያለው አካልም በሕጉ መሠረት ካልሆነ በቀር የሆነ አጋጣሚ ተጠቅሞ ‘ጉልበት አለኝ፣ ይጠቅመኛል’ ብሎ ባሰበ ጊዜ የኃይል አማራጭ የሚወስድ ከሆነ፣ ቢያንስ የሕዝቦች ዘላቂ ወዳጅነትና መቀራረብ የሚያረጋግጥ አይደለም። ከዚህ መቆጠብ ነው ያለብን " ብለዋል።

- የፌደራል መንግሥት ሲቪሊያንን የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ድሮም ቢሆን በውሉም በተመሳሳይ ፤ ይህ እንደተጠበቀ ሆኖም ከመከላከያ ሰራዊት ውጪ ያሉ ታጣቂዎች ከትግራይ ክልል እንዲወጡ ውሉም ያስገድዳል። አለመውጣታቸውም ብቻ ሳይሆን በየትኛውም የአማራ ታጣቂዎች ባሉበት አካባቢ ሴቶች እየተደፈሩ ናቸው። ሰብዓዊ መብቶች እየተረገጡ ናቸው። ብዙ ጥፋቶች እየተፈጸሙ ናቸው። ስለዚህ ውሉን በአግባቡ ተግባሪዊ ማድረግና በቁጥጥር ሥር መስራት ከተቻለ ብቻ ነው ወደ ሰላም ማምራት የምንችለው።

- በአማራ ክልል እየተፈጸሙ ያሉት ትክክል ስላልሆኑ አደብ መያዝ ያስፈልጋል።

ፐ.ኒ.ኢ
የካቲት 8/2016 ዓ/ም
መቐለ

.n.e

አሜሪካ 5 የጦር ሰፈሮችን ለሶማሊያ ለመገንባት ስምምነት አደረገች!በሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በሞቃዲሾ በተካሄደው ስነ ስርዓት ሁለቱ ሀገራት ለሶማሊያ ብሔራዊ ጦር አምስት ወታደ...
17/02/2024

አሜሪካ 5 የጦር ሰፈሮችን ለሶማሊያ ለመገንባት ስምምነት አደረገች!

በሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በሞቃዲሾ በተካሄደው ስነ ስርዓት ሁለቱ ሀገራት ለሶማሊያ ብሔራዊ ጦር አምስት ወታደራዊ ካምፖችን ለመገንባት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።

የዩናይትድ ስቴትስ እና የሶማሊያ መንግስት የጸጥታ ሃላፊነቱን ለመረከብ እና ከአልሸባብ ታጣቂዎች ጋር ለመዋጋት የሚያስችል ተግባራዊ የሆነ የሶማሊያ ጦር ለመገንባት እንደ ፍኖተ ካርታ ያቀረቡትን የደህንነት ስምምነት ከሰሞኑ መፈራረማቸዉ የተነገረዉ።እነዚህ የጦር ሰፈሮች የሚገነቡት በባይዶዋ፣ ዱሳማረብ፣ ጁሃር፣ ኪስማዮ እና ሞቃዲሾ ላይ ነው ተብሏል።

[Capital]n.e

የሩሲያ ተቃዋሚ መሪ አሌክሲ ናቫልኒ በእስር  ቤት ውስጥ መሞታቸው ተገለፀ!የሩሲያ ተቃዋሚ መሪ አሌክሲ ናቫልኒ ለዓመታት በቆዩበት የአርክቲክ እስር ቤት ዛሬ አርብ ህይወታቸው ማለፉን የሩሲያ ...
16/02/2024

የሩሲያ ተቃዋሚ መሪ አሌክሲ ናቫልኒ በእስር ቤት ውስጥ መሞታቸው ተገለፀ!

የሩሲያ ተቃዋሚ መሪ አሌክሲ ናቫልኒ ለዓመታት በቆዩበት የአርክቲክ እስር ቤት ዛሬ አርብ ህይወታቸው ማለፉን የሩሲያ የፌደራል ማረሚያ ቤት አስታውቋል።የሩሲያ ተቃዋሚ መሪ አሌክሲ ናቫልኒ “ከእግር ጉዞ በኋላ መጥፎ ስሜት ተሰምቶት ነበር” ሲሉ የእስር ቤቱ ባለስልጣናት ተናግረዋል።ስለሞቱ ምክንያት ግን ምንም ማረጋገጫ እንደሌላቸው ገልፀዋል።

የአውሮፓ ህብረት፣ ኔቶ እና አብዛኛዎቹ የምዕራባውያን ሀገራት ሩሲያን ለናቫልኒ ሞት ተጠያቂ አድርገዋል።የጀርመኑ መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልስ በበኩላቸው የሩሲያ ተቃዋሚ መሪ አሌክሲ ናቫልኒ በእስር ቤት በመሞታቸውን “በጣም ማዘናቸውን” ገልፀው፤ ከቅርብ አመታት ወዲህ ሩሲያ እንደ ሀገር እንዴት እንደተቀየረች የሚያሳይ “አሰቃቂ” ምልክት ነው ብለዋል።የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪም ለተቃዋሚው መሪ አሌክሲ ናቫልኒ ግድያ የሩስያውን መሪ ቭላድሚር ፑቲንን ከሰዋል።

ናቫልኒ ከደረሰባቸው የነርቭ መመረዝ ችግር ጀርመን ውስጥ ካገገሙ በኋላ ወደ ሩሲያ ሲመለሱ በጎርጎሪያኑ ጥር 2021 ዓ/ም ነበር በቁጥጥር ስር የዋሉት።ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ህይወታቸው እስካለፈበት እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ የ19 ዓመታት እስር ተፈርዶባቸው በማረፊያ ቤት ቆይተዋል።

Via DWn.e

ከትናንት በስትያ በንፋስ ስልክ ክ/ከተማ የእሳት አደጋ የደረሰበት ያ ቴሌቪዥን ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የተገመተ የንብረት ጉዳት ድርሶብኛል አለ፡፡ ያ ቲቪ የተቃጠለው ሁለተኛው ስቱዲዮ በመሆ...
16/02/2024

ከትናንት በስትያ በንፋስ ስልክ ክ/ከተማ የእሳት አደጋ የደረሰበት ያ ቴሌቪዥን ከ15 ሚሊየን ብር በላይ የተገመተ የንብረት ጉዳት ድርሶብኛል አለ፡፡

ያ ቲቪ የተቃጠለው ሁለተኛው ስቱዲዮ በመሆኑ ከአየር ላይ ስጭቱ አለመቋረጡን ተናግሯል፡፡ የቴሌቪዥን ጣቢያው ከትናንት በስቲያ የካቲት 6፣2016 ዓ.ም ከምሽቱ 1:00 ነፋስ ስልክ አካባቢ በቀድሞው በአጎና ሲኒማ ላይ ሁለተኛው ስቱዲዮው ላይ የእሳት አደጋ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ያ ቲቪ አደጋ ያጋጠመው ቁጥር ሁለት ስቱዲዮው ስለሆነ ወሎ ሰፈር የሚገኘው ቁጥር አንዱ ስቱዲዮው ስርጭቱን ቀጥሏል ተብሏል፡፡

Via Shegern.e

ወይዘሮ አስቴር ሰይፉ ለ23 አመታት ያስገነቡት ህንፃ ቤተክርስቲያን ሊመረቅ ነው። .n.eታላቅ የምሥራች  በመላው አለም ለምትገኙ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በሙሉ።የለኩ ኢየሱስ ቤተክርስቲ...
16/02/2024

ወይዘሮ አስቴር ሰይፉ ለ23 አመታት ያስገነቡት ህንፃ ቤተክርስቲያን ሊመረቅ ነው።
.n.e
ታላቅ የምሥራች በመላው አለም ለምትገኙ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች በሙሉ።የለኩ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ከ23 ዓመት ድካም በኋላ ተጠናቆ የካቲት 10 ቀን 2016 ዓ/ም ብፁአን አባቶች መዘምራንና ሰባኪያን በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።

"ይህቺ ሴት ግን ከአቋሟ ሳታፈገፍግ ጸናች። ስንዝር በሆነው ዕድሜዋ አግኝታ ከምትለዬው የልጅ ፍቅር ይልቅ በሰማይ የሚጠብቃት ሙሽራዋ ክርስቶስን አስባ እና ተስፋ አድርጋ ሁሉንም ትታ ቤተክርስቲያኒቷን ማነጽ ብቻ ሐሳቧ አደረገች ።

በትግስት ዓመታትን በተማጽኖ ውስጥ ሆነ ከሰነበተች በኃላ እንደ አጋጣሚ ሀገረስብከቱ የብጽአን አበው ሊቃነጳጳሳት ለውጥ በማድረግ ብጽኡ አቡነ ፋኑኤል ወደ ሲዳማ ሀገረስብከት ይመደባሉ።

ይህቺ ብርቱ ሴት ለዓመታት የተከለከለችውን ህንጻ መቅደስ የማነጽ ቡራኬ እና ፍቃድ ብጽኡ አቡነ ፋኑኤል በቀናት ውስጥ ጨርሰው "አይዞሽ በርቺ" ብለው ሸኝዋት ።

እነሆ ከእዛች ቀን በኃላ 21 ዓመታትን ስለኢየሱስ እያለች በበዓላት በአዘቦት ቀናት ለ21 ዓመታት የአድባራትን ደጅ እየጠናች ከማህበረ ምዕመኑ ባሰባሰበችው ገንዘብ እዚህ ደረጃ ላይ አደረሰች።

ሲቃ ባነቀው እንባ ባጀበው የስስት ምኞቷ "የአምላኬ ስጋና ደም ሲፈተት፣በስፍራው ህጻናት ተሰብስበው ምስጋና ለሥላሴ ሲያቀርቡ፣ቅዱሳን ተወድሰው መላእክት ከብረው የምመለከትበትን ቀን እናፍቃለው" ትለናለች። "n.e

 #ማስታወሻለአዲስ አበባ ከተማ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ፦1ኛ. የሞተር ባለንብረቶች እንዲሁም በሞተር እየተንቀሳቀሳችሁ ስራችሁን ለምትሰሩ አባላቶች ከነገ አርብ የካቲት 8 /2016...
15/02/2024

#ማስታወሻ

ለአዲስ አበባ ከተማ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት ፦

1ኛ. የሞተር ባለንብረቶች እንዲሁም በሞተር እየተንቀሳቀሳችሁ ስራችሁን ለምትሰሩ አባላቶች ከነገ አርብ የካቲት 8 /2016 ዓ/ም ከጠዋቱ 12:00 ጀምሮ እስከ ሰኞ የካቲት 11/2016 ዓ.ም ጠዋት 2:00 ሰአት ድረስ ሞተር ማሽከርከር ፍፁም ተከልክሏል። የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ ክልከላውን በሚተላለፉ ላይ " ጥብቅ እርምጃ እወስዳለሁ " ብሏል።

__

2ኛ. ለአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ #መሪዎች ወደ አዲስ አበባ እየመጡ ይገኛሉ። በዚህ ምክንያት መሪዎች እስኪያልፉ ድረስ መንገዶች ለሌሎች ተሽከርካሪዎች ሊዘጉ ይችላሉ።

ፖሊስ አማራጭ / ተለዋጭ መንገዶችን ተጠቀሙ ብሏል።

➡ ከፓርላማ መብራት-በውጭ ጉዳይ ሚ/ር - መስቀል አደባባይ ፍላሚንጎ - ኦምሎፒያ - ወሎ ሰፈር - ጃፓን ኤምባሲ - ፍሬንድ ሺፕ -ቦሌ ቀለበት መንገድ - ኤርፖርት

➡ ከፓርላማ መብራት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር - በብሔራዊ ቤተ - መንግስት - በፍልውሃ - በብሔራዊ ቴአትር- ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ህብረት አዳራሽ ዙሪያ

➡ ከፓርላማ መብራት -ብሔራዊ ቤተ-መንግስት - ወዳጅነት ፓርክ - ንግድ ማተሚያ ቤት - ሞናርክ ሆቴል-ቴዎድሮስ አደባባይ-ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል- ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን- ብሔራዊ ቴአትር - ሜክሲኮ አደባባይ - አፍሪካ ህብረት መንገዶች እንግዶች የሚያልፉባቸው ናቸው።

ከዚህ ባለፈ ፦

☑ ከፓርላማ መብራት-በሸራተን ሆቴል ቁልቁለቱን-ፍልውሃና አምባሳደር ቴአትር ዙሪያውን

☑ ከንግድ ምክር ቤት ጀምሮ በሱዳን ኤምባሲ - አፍሪካ ህብረት ዋናው በር - ሳርቤት ድረስ በሁለቱም አቅጣጫዎች እንግዶች ተጠቃለው እስኪመለሱ ግራና ቀ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ተከልክሏል።

__

3ኛ. 37ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባዔ የካቲት 9 እና 10 ቀን 2016 ዓ.ም ይካሄዳል። የ2024 መሪ ቃል ፤ " ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚመጥን አፍሪካዊ ማስተማር፤ የማይበገሩ የትምህርት ስርዓቶች በመገንባት በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ፣ የሕይወት ዘመን፣ ጥራትና አግባብነት ያለው የትምህርት ተደራሽነትን ማስፋት " የሚል ነው።
n.e

ከ 20 በላይ የሆኑ የማዕድን አዉጪዎች ከተዋጡበት ፍርስራሽ ለማዳን ሲደረግ የነበረዉ የነፍስአድን ጥረት ከአቅሜ በላይ ሆኗል ሲል የደላንታ ወረዳ አስታወቀ ባሳለፍነዉ ሀሙስ ጥር 27 ቀን 20...
15/02/2024

ከ 20 በላይ የሆኑ የማዕድን አዉጪዎች ከተዋጡበት ፍርስራሽ ለማዳን ሲደረግ የነበረዉ የነፍስአድን ጥረት ከአቅሜ በላይ ሆኗል ሲል የደላንታ ወረዳ አስታወቀ

ባሳለፍነዉ ሀሙስ ጥር 27 ቀን 2016 ዓ.ም ከሌሊቱ 6 ሰዓት ገደማ ላይ በደላንታ ወረዳ 018 ቀበሌ ልዩ ስሙ ቆቅ ዉሃ ተብሎ በሚጠራዉ አካባቢ በባህላዊ መንገድ የኦፓል ማዕድንን በማዉጣት ላይ የነበሩ ወጣቶች ባጋጠማቸዉ የመሬት መደርመስ አደጋ በፍርስራሽ ዉስጥ እንደሚገኙ የደላንታ ወረዳ ማዕድን ልማት ጽ/ት ቤት ሀላፊ አ/ቶ ተስፋ ሰማሁን ዋቢ በማድረግ ብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን ዘግቧል።

ወጣቶቹ ላለፉት ሰባት ቀናት በፍርስራሽ ዉስጥ ተዉጠዉ የቆዩ ሲሆን የነፍስ አድን ቁፋሮዉ በማህበረሰቡ ትብብር ሲከናወን ቆይቶ ነበር። ሆኖም አሁንም በቁፋሮዉ ወቅት የመሬት መደርመስ እና መንሸራተት እያጋጠመ ስራዉን ፈታኝ አድርጎት እንደነበር ብስራት በትናንትናው እለት ዘግቦ ነበር።

ይሁንና የደላንታ ወረዳ ማዕድን ልማት ጽ/ት ቤት ሀላፊ አ/ቶ ተስፋ ሰማሁ ለብስራት ራዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት አሁን ላይ በሰዉ ሀይል ሲከናወን የነበረው ቁፋሮ ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ነዉ።

"በነፍስ አድን ስራዉ ወቅት ተጨማሪ የሰዉ ህይወት እንዳናጣ በሚል ስራዉን አቋርጠናል" ሲሉ ገልጸዋል። ወረዳዉም ሆነ የደቡብ ወሎ ዞን ጉዳዩን ለክልሉ እና የፌዴራል መንግስት ማሳወቃቸዉንም ነግረዉናል።

አቶ ተስፋ " ቁፋሮዉ ከሰዉ አቅም በላይ በመሆኑ ከህብረተሰቡ በድማሚት እና ከባድ መሳሪያ ፈንጂዎች ቢመታ የሚል ጥያቄ እያቀረበ ነዉ" ያሉን ሲሆን ይህንንም ለማከናወን ቦታዉ በጂኦሎጂስት ባለሙያ መታየት ያለበት በመሆኑ የክልሉ መንግስት ባለሙያዉን ለመላክ መስማማቱን አስታዉቀዋል።

ከዚህ በተጨማሪም ጉዳዩ ከአቅም በላይ መሆኑን ሪፖርት በማድረግ ለማዕድን ሚኒስቴር ያሳወቁ ሲሆን ተጨማሪ ድጋፍ ለማግኘት ጥያቄ ማቅረባቸውንም ጠቅሰዋል።
n.e

በአዲስ አበባ በስድስት ወራት ከሁለት ሺህ 800 በላይ የትዳር ፍቺ ተመዝግቧል!በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት ሁለት ሺህ 813 ፍቺዎች እና 16 ሺህ 933 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአ...
15/02/2024

በአዲስ አበባ በስድስት ወራት ከሁለት ሺህ 800 በላይ የትዳር ፍቺ ተመዝግቧል!

በአዲስ አበባ ከተማ ባለፉት 6 ወራት ሁለት ሺህ 813 ፍቺዎች እና 16 ሺህ 933 ጋብቻዎች መመዝገባቸውን የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ።

የአዲስ አበባ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ዓለማየሁ ለኢፕድ በላኩት መግለጫ እንደገለጹት፤ ዘንድሮ በ6 ወራት ብቻ ከተመዘገበው ጠቅላላ ኩነት 181 ሺህ 983 ልደት፣ 16 ሺህ 933 ጋብቻ፣ 2 ሺህ 813 ፍቺ እና 8 ሺህ 761 ሞት ተመዝግቧል።

Via EPAn.e

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Public News Ethiopia /P.N.E posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Public News Ethiopia /P.N.E:

Share