መረጃ ከሁሉም

መረጃ ከሁሉም እውነተኛ እና ምንጭ ያላቸው መረጃዎች ብቻ ይቀርባሉ

መረጃ ከሁሉም 20-09-13የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ ሮበርት ጎዴክ  አሜሪካ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ላይ ተጨማሪ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል አስጠነቀ...
28/05/2021

መረጃ ከሁሉም 20-09-13
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ ሮበርት ጎዴክ አሜሪካ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ላይ ተጨማሪ እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል አስጠነቀቁ።
***********************************************
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ ሮበርት ጎዴክ በትግራይ ክልል ያለው ግጭት ተሳታፊዎች አካሔዳቸውን ካልቀየሩ አገራቸው በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ላይ ተጨማሪ እርምጃ ልትወድ እንደምትችል አስጠነቀቁ። ኃላፊው በአሜሪካ ሴኔት የውጭ ግንኙነት ኮሚቴ ፊት ትናንት ቀርበው በኢትዮጵያ ቀውስ ላይ አገራቸው እየተከተለች ያለችውን የምላሽ አሰጣጥ አስረድተዋል።
ኃላፊው በቅርብ ሳምንታት የከፋ ደረጃ ላይ ደርሷል ያሉት የጸጥታ ሁኔታ የሰብዓዊ ቀውሱን እንዳባባሰም ተናግረዋል። «የአሜሪካ እና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ትንተና የቀጠለው ግጭት ወደ ጠኔ የሚጠጋ ሁኔታ መፍጠሩን ያሳያል» ያሉት ጎዴክ በተመጣጠነ ምግብ እጦት እና በረሐብ ሰዎች ለመሞታቸው የተረጋገጠ መረጃ አለ ብለዋል። ውጊያ፣ የፍተሻ ኬላዎች፣ ሥርዓተ አልበኝነት እና በተዋጊ ኃይሎች ወከባ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅራቢዎች እንቅስቃሴ ችግር እንደገጠመው የተናገሩት ሮበርት ጎዴክ ለዚህም የዩስኤይድ አጋር ባልደረባ እና ሌሎች ሰባት የእርዳታ ድርጅቶች ሠራተኞች መገደላቸውን በምሳሌነት አንስተዋል።
«ሙሉ የተኩስ አቁም፣ ሙሉ እና ያልተገደበ የሰብዓዊ እንቅስቃሴ፣ የሰላማዊ ሰዎች ደህንነት ጥበቃ እንፈልጋለን» ያሉት ኃላፊው የኤርትራ ወታደሮች እና የአማራ ክልል ኃይሎች ለቀው ሊወጡ ይገባል ብለዋል። ቀውሱ በፖለቲካዊ መንገድ መፍትሔ እንዲበጅለት በትግራይ ተፈጽመዋል የተባሉ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች፣ በደሎች እና የጭካኔ ድርጊቶች ላይ ገለልተኛ ዓለም አቀፍ ምርመራ እንዲደረግ እና ፈጻሚዎች ተጠያቂ ሊሆኑ እንደሚገባም ተናግረዋል።
የአሜሪካ ባለሥልጣናት እንዲህ አይነት ውትወታ ሲያቀርቡ የመጀመሪያቸው አይደለም። በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ አሜሪካ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ባለሥልጣናት፣ በጸጥታ ተቋማት አመራሮች፣ በአማራ ክልል ኃይል እና በህውሓት አባላት ላይ የቪዛ ማዕቀብ መጣሏን የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። አሜሪካ ከቪዛ ማዕቀብ ተጨማሪ ለኢትዮጵያ የምትሰጣቸውን ዕገዛዎች ከልክላለች።
የኢትዮጵያ መንግሥት የአሜሪካ እርምጃ አጥብቃ ተቃውሟል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የአሜሪካ መንግሥት እርምጃውን መለስ ብሎ እንዲያጤን በጠየቁበት መግለጫ «የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት በገንዘብ፣ በዓለም የገንዘብ ድርጅት፣ በዓለም ባንክ የሚቀየር» አይደለም ብለዋል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ ሮበርት ጎዴክ ግን የትግራይ ግጭት ማቆሚያ ካልተበጀለት አገራቸው ተጨማሪ እርምጃ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ ላይ ልትወስድ እንደምትችል ተናግረዋል።

DW Amharic

መረጃ ከሁሉም 19-09-13“በትግራይ ክልል የሚገኙ ተፋላሚዎች አስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ሊደርሱ ይገባል”- ፕሬዝደንት ባይደን*********************************...
27/05/2021

መረጃ ከሁሉም 19-09-13
“በትግራይ ክልል የሚገኙ ተፋላሚዎች አስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ሊደርሱ ይገባል”- ፕሬዝደንት ባይደን
***********************************************
አሜሪካ በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ የሁሉንም ሀገሮች ፍላጎት ያማከለ ስምምነት እንዲደረስ መሻቷ መሆኑንም ገልጸዋል

የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን ትናንት ምሽት በሰጡት መግለጫ በትግራይ የሚደረገው ጦርነት ያስከተለው ስብዓዊ ቀውስ አሳሳቢ መሆኑን አስታውቀዋል።

በትግራይ ክልል እየተፋለሙ ያሉ ሁሉም ወገኖች በአስቸኳይ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ሊደርሱ እንደሚገባ ማሳሰባቸውንም ኋይት ሀውስ ባወጣው መግለጫ አመላክቷል።

ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በመግለጫቸው አክለውም “የኤርትራ ወታደሮችና የአማራ ኃይሎች ከትግራይ ክልል በአስቸኳይ እንዲወጡ” ጠይቀዋል።

በክልሉ ጾታዊ ጥቃትን ጨምሮ የሚስተዋሉ “መጠነ ሰፊ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች” ተቀባይነት የሌላቸው መሆኑን እና ሊቆሙ እንደሚገባም አሳስበዋል።

የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ በያዝነው ሳምንት እንዳስታወቀው ፣ እየተካሄደ ባለው ግጭት ሳቢያ በትግራይ ያለው የሰብዓዊ ቀውስ አሳሳቢ መሆኑንና በኢትዮጵያ ከ1970ዎቹ ወዲህ ከፍተኛ የረሀብ አደጋ እንዳንዣበበ ማስታወቁን የጠቀሰው መግለጫው ፤ ሁሉም ተፋላሚ ኃይሎች የሰላም መንገድ እንዲከተሉ፣ ዕርዳታ ያለምንም መስተጓጎል ለተቸገሩት እንዲደርስ መንግስት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ፕሬዝደንቱ መጠየቃቸውን ጠቁሟል።

የኢትዮጵያ መሪዎችና ተቋማት ለብሔራዊ እርቅና መግባባት ቅድሚያ ሰጥተው በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ያሉ ግጭቶችን በማቆም ለውይይት እና ለጋራ ሀገራዊ ጉዳይ እንዲሰሩ አሜሪካ ጥሪ ታቀርባለችም ብለዋል ፕሬዝደንቱ።

በኢትዮጵያ ላለው ችግር መፍትሄ ለማፈላለግ በሚደረገው ጥረት ውስጥ አሜሪካ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ ነች ያሉት ፕሬዚዳንት ባይደን፤ ሀገራቸው ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ከአፍሪካ ህብረት ጋር በቅርበት የምትሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

በአፍሪካ ቀንድ የአሜሪካ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ጄፍሪ ፌልትማን ፣ አሜሪካ በቀጠናው የምታካሂደውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ለማጠናከር በዚህ ሳምንት ወደ ቀጠናው እንደሚጓዙም ጠቁሟል።

ፕሬዚዳንት ባይደን በመግለጫቸው አክለውም አሜሪካ በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ የሁሉንም ሀገሮች ፍላጎት ያማከለ ስምምነት እንዲደረስ ፍላጎት እንዳላት በመግለጽ፤ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ በዚህ ጉዳይ ላይ ከሁሉም አካላት ጋር እንደሚመክሩም አስታውቀዋል።

አል-ዐይን

መረጃ ከሁሉም 19-09-13 የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ወደ ጅቡቲ አቀኑ***********************************************ግብፅ ከሱዳን ጋር ለ 6 ቀናት...
27/05/2021

መረጃ ከሁሉም 19-09-13

የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ወደ ጅቡቲ አቀኑ
***********************************************
ግብፅ ከሱዳን ጋር ለ 6 ቀናት የሚቆይ ሁለገብ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ ትናንት ጀምራለች

የግብፁ ፕሬዝደንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ ከጂቡቲ ሪፐብሊክ ፕሬዝደንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር ለመወያየት ዛሬ ማለዳ ወደ ጅቡቲ አቅንተዋል፡፡

የፕሬዝደንት አል ሲሲ ቃል አቀባይ እንደተናገሩት የፕሬዚዳንቱ የጅቡቲ ጉብኝት በዓይነቱ የመጀመሪያ ነው፡፡

የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በጋራ ትብብር እና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩም ነው ቃል አቀባዩ የገለፁት፡፡ በተለይም በፀጥታ ፣ በወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች የሁለቱን ሀገራት ትብብር ማጠናከር የውይይቱ ዓላማ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

በተጨማሪም የግብፅና የጅቡቲ መሪዎች የጋራ በሆኑ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ለመወያየት እና ሀሳቦችን ለመለዋወጥም አቅደዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ግብፅ እና ኬንያ በትናንትናው እለት ወታደራዊ ስምምነት ተፈራርመዋል፡፡ በናይሮቢ የተፈረመው ስምምነት ዓላማ የሁለቱን ሀገራት የጋራ ጥቅም ለማስጠበቅ የሚደረገው የሁለትዮሽ ትብብር አካል ነው ተብሏል፡፡

ግብፅ ከኬንያ ጋር ያደረገችው ወታደራዊ ስምምነት እ.ኤ.አ. በ2021 በምስራቅ አፍሪካ ከሚገኙ ሀገራት ጋር ያደረገችው አራተኛ ስምምነት ነው፡፡ ከኬንያ በተጨማሪ ከሱዳን ፣ ከኡጋንዳ እን ከብሩንዲ ጋርም ግብፅ ወታደራዊ ስምምነት ፈርማለች፡፡

በተያያዘ ዜና ግብፅ እና ሱዳን በትናንትናው ዕለት ለ 6 ቀናት የሚቆይ ሁለገብ የጋራ ወታደራዊ ልምምድ በሱዳን ጀምረዋል፡፡ ኢትዮጵያ በሕዳሴው ግድብ ጉዳይ ከሁለቱ ሀገራት ጋር ውጥረት ውስጥ በምትገኝበት ወቅት የሚካሔደው ይህ ልምምድ ፣ የናይል ጠባቂዎች (Nile Protectors/ናይል ፕሮቴክተርስ) የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ከግድቡ በተጨማሪ ኢትዮጵያና ሱዳን በድንበር ጉዳይም ከፍተኛ አለመግባባት ውስጥ የሚገኙ መሆኑ ይታወቃል፡፡

አል-ዐይን

መረጃ ከሁሉም 18-09-13ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም በተጠረጠሩበት ወንጀል በድጋሜ እንዲጠየቁ ተወሰነ***********************************************ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራ...
26/05/2021

መረጃ ከሁሉም 18-09-13
ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም በተጠረጠሩበት ወንጀል በድጋሜ እንዲጠየቁ ተወሰነ
***********************************************
ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም ክስ በቀረበባቸው የህወሓት አመራሮች ላይ ምስክር ለመሆን ከጠቅላይ ዓቃቤ ህግ ጋር የገቡትን ስምምነት በማፍረሳቸው በሕግ አግባብ ያገኙት የምስክርነት ጥበቃ እንዲቋረጥና በተጠረጠሩበት ወንጀል ክስ እንዲመሠረትባቸው ዓቃቤ ሕግ ወሰነ።

ወይዘሮኬርያ ምስክር ለመሆን ስምምነት ገብተው ዝርዝር የምስክርነት ቃላቸውን ሰጥተው የጥበቃ ተጠቃሚ ከሆኑ በኋላ ሐሳባቸውን በመቀየር ስምምነቱን ስለጣሱ የምስክርነት ጥበቃው ተቋርጧል፣ ተጠርጣሪዋ ምስክር የመሆን ሐሳባቸውን የተው በመሆኑም መጀመርያ በተጠረጠሩበት ወንጀል ክስ እንደሚቀርብባቸው ነው የተገለጸው፡፡

በወንጀል ተጠርጥሮ የተያዘ ወይም ክስ ቀርቦበት በክስ ክርክር ሒደት ላይ ያለ ሰው ስለቀረበው ክስና ሁኔታዎች ጉዳይ የሚታመን ዝርዝር መግለጫና ጥቆማ ከሰጠ ከተጠርጣሪው ወይም ከተከሳሹ ጋር በመስማማት ክሱን መተው ወይም ምስክር በማድረግ፤ የሕዝብን ጥቅም ማስከበር በሕግ የተፈቀደ አሠራር መሆኑን ሪፖርተርጋዜጣዘግቧል ይህ አሠራርም የቆየና በተለያዩ አገሮች የሕግ ሥርዓት የሚተገበር መሆኑን ነው ጋዜጣው ያተተው፡፡

በዚሁ መሠረት የምስክር ጥበቃ የተሰጣቸው ወይዘሮ ኬሪያ በርካታ ጠቃሚ መረጃና ማስረጃዎችን እጃቸውን ከሰጡበት ቀን ጀምሮ በፍላጎታቸው ለምርመራ ቡድኑ መስጠታቸውን፣ ምስክር ለመሆን መስማማታቸውን እንዲሁም በራሳቸው ፍላጎት እጅ መስጠታቸውን ከግምት በማስገባት የምስክርነት ጥበቃ እንደተሰጣቸው ነው የተገለጸው።

ወ/ሮ ኬሪያ በትላንትናው ዕለት በፌደራል የመጀመርያ ፍርድቤት አራዳ ምድብ ችሎት በነበራቸው ቀጠሮ በእነ አቶ ስብሓት ነጋ እንደማይመሰክሩ ለፍርድቤቱ ገልጾ እስካሁን ብቻየን በአንድ ክፍል ታስሬ ብመሰክርም ወደ ቃሊቲ እስርቤት እንወስድሻለን አዛው ፍትህ ታገኛለሽ በማለት፤ በማስፈራራት፤ ቪድዮ በመቅረጽ መብቴ ተጥሶ ነው ያለሁት በማለት ለፍርድቤቱ ማስረዳታቸው ይታወሳል፡፡

አውሎ ሚድያ

መረጃ ከሁሉም 18-09-13 ጀነራል ብርሃኑ ጁላ የኤርትራ ወታደሮች ከትግራይ እንዲወጡ መጠየቃቸው ተሰማ*******************************የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር...
26/05/2021

መረጃ ከሁሉም 18-09-13

ጀነራል ብርሃኑ ጁላ የኤርትራ ወታደሮች ከትግራይ እንዲወጡ መጠየቃቸው ተሰማ
*******************************
የኢፌዴሪ ጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄነራል ብርሃኑ የኤርትራ ጦር ከትግራይ ክልል ሙሉ ለሙሉ ለቆ እንዲወጣ ጠየቁ ተባለ፡፡

ጀነራል ብርሃኑ ጁላ የኤርትራ ጦር ሙሉ ለሙሉ ትግራይ ክልልን ለቆ እንዲወጣ ለኤርትራ አመራሮችን በደብዳቤ መጠየቃቸው ነው የተገለጸው፡፡

ጠቅላይ ኢታማዡር ሹሙ ከቀናት በፊት ለኤርትራ የጦር አዛዥ ጀነራል ፍሊጶስ ወ/ዮሃንስ በጻፉት ደብዳቤ የኤርትራ ጦር ትግራይን ለቆ እንዲወጣ የሚጠይቅ ቢሆንም ደብዳቤዉ የደረሳቸዉ አመራሮች ስለ ጉዳዩ በይፋ እንዲያወሩ እንደማይፈቀድላቸዉ አሳዉቀዋል ሲል ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡

በኢትዮጵያ በኩል ኤርትራ ወታደሮች እንዲወጡ የቀረበዉ ጥያቄ ባለፈዉ ሳምንት አሜሪካ በሀገሪቷ ያስቀመጠችዉን የኢኮኖሚና የጸጥታ መዕቀብና የጉዞ ዕቀባን ተከትሎ ሊሆን እንደሚችል ዘገባዉ ያትታል፡፡

ብሉምበርግ ከኢትዮጵያ የጦር አዛዥ ወደ ኤርትራ ስለተጻፈዉ ደብዳቤ አስተያየታቸዉን ለመቀበል ለብርሀኑ ጁላ፣ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል አቀባይ ቢልለኔ ስዩምና ለኤርትራ የመረጃ ሚኒስቲር አቶ የማነ ገብረመስቀል ጥያቄ በማቅርብ ያደረገዉ ጥረት እንዳልተሳካለት በዘገባዉ አካትዋል፡፡

አሜሪካና የአዉሮፓ ህብረት የኤርትራ ጦር ከትግራይ እንዲወጣ በተደጋጋሚ መጠየቁን ሚዘነጋ ጉዳይ አይደለም፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት በመጋቢት ወር የኤርትራ ሰራዊት የትግራይ ክልል ለቀዉ ወደ ሀገራቸዉ እንደሚመለሱ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

አውሎ ሚድያ

መረጃ ከሁሉም 17-09-13 ከ500 በላይ ወጣቶች በኤርትራና በኢትዮጵያ ወታደሮች በግዳጅ ተወሰዱ  – ሮይተርስ***********************************************የኤር...
25/05/2021

መረጃ ከሁሉም 17-09-13

ከ500 በላይ ወጣቶች በኤርትራና በኢትዮጵያ ወታደሮች በግዳጅ ተወሰዱ – ሮይተርስ
***********************************************
የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ወታደሮች በትናንትናው ዕለት ምሽት በትግራይ ሰሜናዊ ክልል ሽረ ከተማ በአራት ካምፖች የነበሩ ቁጥራቸው ከ500 በላይ የሚሆኑ ወጣት ሴቶችና ወንዶች በግዳጅ መያዛቸው ሶስት የእርዳታ ሰራተኞች እና አንድ ዶክተር ለሮይተርስ ተናግረዋል፡፡

ወታደሮቹ ሰኞ ዕለት 5 ስዓት ምሽት ገደማ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች በጭነት መኪና መወሰዳቸው ነው የተነገረው፡፡

እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች እና ሐኪሙ በቦታው የነበሩ የአይን ምስክሮችን ቃል በመጥቀስ ብዙ ወጣቶች እንደተወሰዱ ነው የተናገሩት፡፡ ከእርዳታ ሰጪ ሠራተኞች መካከል አንዱ እንዳሉት ከሆነ በርካታ ወንዶች ተደብድበዋል ፣ ስልካቸው እና ገንዘባቸው ተወስዷል ነው ያሉት፡፡

የኢትዮጵያ ወታደራዊ ቃል አቀባይ ፣ በትግራይ ላይ የመንግስት ግብረ ኃይል ሀላፊ እና የትግራይ ክልላዊ ሀላፊ አስተያየት ለመጠየቅ በተደረገው ጥረት መልስ አልተሰጠንም ነው ያለው ሮይተርስ ፡፡

የሽረ ሰሜን ምዕራብ ዞን ጊዜያዊ ኃላፊ አቶ ቴዎድሮስ አረጋይ ለሮይተርስ እንደገለጹት የጥቂቶቹ ዝርዝራቸው ቢኖሯቸውም በመቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች መወሰዳቸው ገልጽዋል፡፡

የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል በበኩላቸው “ተፈናቃዮችን ለመሰብሰብ” ምንም ምክንያት እንደሌለ የተናገሩ ሲሆን የይገባኛል ጥያቄዎቹ ከህዳር ወር ጀምሮ ከፌደራል መንግስቱ ጋር እየተዋጋ ያለው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ፕሮፓጋንዳ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡

በቅርቡ የአዉሮፓ ህብረት የሰብአዊ መብት አስተባባሪ ባወጣዉ መረጃ በትግራይ እየተካሄደ ባለዉ ጦርነት እስካሁን በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ሞተዋል፤ 2 ሚልዮን ቤት ንብረታቸዉ ለቀዉ እንዲፈናቀሉ ተገደዋል፤ 91 በመቶ ወይም ወደ 6 ሚልዮን የሚጠጋዉ የክልሏ ህዝብ አስቸኳይ እርዳታ ይፈልጋል ብልዋል፡፡

አውሎ ሚድያ

መረጃ ከሁሉም 17-09-13 በእነ አቶ ስብሓት ነጋ ላይ ተገድጄ አልመሰክርም – ወ/ሮ ኬሪያ እብራሂም***********************************************በእነ አቶ ስብ...
25/05/2021

መረጃ ከሁሉም 17-09-13

በእነ አቶ ስብሓት ነጋ ላይ ተገድጄ አልመሰክርም – ወ/ሮ ኬሪያ እብራሂም
***********************************************
በእነ አቶ ስብአት ነጋ ላይ ተገድጄ አልመሰክርም ሲሉ የቀድሞ የፌደሬሽን ምክርቤት አፈ ጉባኤ ወ/ሮ ኬሪያ እብራሂም ለፍርድቤት ቃላቸዉን ሰጡ፡፡

ለመመስከር እራሳቸውን አስመዝግበው የነበሩት ወ/ሮ ኬሪያ እብራሂም በዛሬው ቀጠሮ አልመሰክርም አሉ፡፡

ዛሬ በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ በነበረው ቀጠሮ በእነ አቶ ስብሓት ነጋን ጨምሮ 42 ተጠርጣሪዎች ላይ የዓቃቢህግ የቅድመ ምርመራ ምስክር ለመስማት የተቀጠረ ሲሆን በቀዳሚነት በምስክርነት የቀረቡት ወ/ሮ ኬሪያ ልታሰር እንጂ በነሱ ላይ አልመሰክርም ማታቸው ተደምጠዋል።

ወ/ሮ ኬሪያ ዛሬ በዋለዉ ችሎት እንዲመሰክሩ ቢቀርቡም ለፍርድቤቱ መመስከር ካለብኝ የምመሰክረዉ ይህ መንግስት በትግራይና በኢትዮጵያ እናቶች ፤ ህጻናትና ህዝብ ላይ የሚያደርገዉን ጭፍጨፋ ከሆነ ብቻ ነዉ፡፡

ወ/ሮ ኬርያ አክሎም እኔ መመስከር ካለብኝ የምመሰክረዉ መንግስት በህዝብና ሀገር ላይ እየፈጸመ ያለዉን ክህደት እና ወንጀል ከሆነ ብቻ ነዉ፤ ፍርዱ ቤቱ እንዲያቅልኝ የምፈልገዉ ብቻየን እስካሁን በአንድ ክፍል ታስሬ ብመሰከርም ወደ ቃሊቲ እስርቤት እንወስድሻለን፤ ፍትህ ታገኛለሽ በማለትና በማስፈራራት፤ ቪድዮ በመቅረጽ መብቴ ተጥሶ ነዉ ያለሁት ብልዋል፡፡

አሁንም ቢሆን ይላሉ ወ/ሮ ኬርያ ብቻየን በአንድ ክፍል ብታሰርም በእነ አቶ ስብሓት ነጋ መዝገብ ላይ ተገድጄ ልመሰክር አልችልም ሲሉ ለፍርድቤቱ አቋማቸዉን መግለጻቸዉ ለአዉሎ ሚድያ የደረሰዉ መረጃ ያሳያል፡፡

አውሎ ሚዲያ

መረጃ ከሁሉም 16-09-13የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ኢትዮጵያና ሱዳን ከማሸማገል ገለል ማለቷ ተሰማ***********************************************ኢትዮጵያ እና ሱ...
24/05/2021

መረጃ ከሁሉም 16-09-13
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ኢትዮጵያና ሱዳን ከማሸማገል ገለል ማለቷ ተሰማ
***********************************************
ኢትዮጵያ እና ሱዳን በድንበር ጉዳይ ለገቡበት ውዝግብ የጋራ መፍትሄ ስታፈላልግ የቆየችው የተባበሩት አረብ ኤምሬት ውዝግቡን በራሳቸው ይፍቱት ማለቷ ተሰምቷል፡፡

ከዚሁ ጋር ተያይዞም የዉዝግቡ ምንጭ በሆነዉ የአል-ፋሽቃ አካባቢ የግብርና ፕሮጀክቶችን ልታለማ ነዉ በሚልም ስሟ ተደጋግሞ ተጠቅሶ ነበር፡፡

በአቡዳቢ የሚታተመዉን “አሻርክ” የተባለን ጋዜጣ ዋቢ አድርጎ ሱዳን ትሪቡን እንደዘገበዉ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ሁለቱ ሀገራት የገቡበትን ዉዝግብ በራሳቸዉ እንዲፈቱ ለሱዳን ቁርጡን ነግራታለች ብሏል፡፡

ችግሩንም በሰላማዊ መንገድ መፍታት ላይ እንዲያተኩሩ ነዉ ሀገሪቷ የገለጸችዉ፡፡

የሱዳን ባለስልጣናት ኢትዮጵያ በፈረንጆቹ 1902፣ 1903 እና 1972 የተፈረሙ ስምምነቶችን ለማደስ እንደፈለገች በማስመሰል ስሟን እየጠቀሱ ከፍ ሲልም እያጠለሹ መሆኑንም ዘገባዉ ጠቁሟል፡፡

የሱዳን የገንዘብ ሚንስትር ጅብሪል ኢብራሂም የገልፍ ሃገራት በአካባቢዉ የ 8 ቢሊዮን ዶላር ፕሮጀክቶችን ለማልማት መጠየቃቸዉን ተናግረዋል፡፡

ይሁንና የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የድንበር ጉዳያችሁን በራሳችሁ ጨርሱ ስትል ለሱዳን አሳዉቃለች ተብሏል ሲል ሱዳን ትሪቡን ዘግቧል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም

መረጃ ከሁሉም 16-09-13 ሰበር ሰሚ ችሎት እነ አቶ እስክንድር ነጋ በእጩነት እንዲመዘገቡ ወሰነ********************************************የባልደራስ ለእውነተኛ ...
24/05/2021

መረጃ ከሁሉም 16-09-13

ሰበር ሰሚ ችሎት እነ አቶ እስክንድር ነጋ በእጩነት እንዲመዘገቡ ወሰነ
********************************************
የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) አቶ እስክንድር ነጋን ጨምሮ አራት ከፍተኛ አመራሮች በመጪው ምርጫ በዕጩነት እንዲመዘገቡ፣ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ሰጠ።

ችሎቱ ዛሬ ግንቦት 16 ቀን 2013 ዓም ውሳኔ መስጠቱን የባልደራስ የሕግና የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ሔኖክ አክሊሉ ለሪፖርተር ገልጸዋል ።

እንደ ኃላፊው ገለጻ፣ እነ አቶ እስክንድር ከመከሳሳቸው ባለ ፈ በፍርድ ቤትም ሆነ በሕግ የተጣለባቸው ክልከላ ስለሌለለ ፓርቲው ደረጃውን ጠብቆ እስከ ሰበር ችሎት ባደረገው ክርክር ተከሳሾቹ በእጩነት መመዝገብ እንደሚችሉ መወሰኑን ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም እንዲመዘግብ ትዕዛዝ መሰጠቱን አክለዋል።
ሪፖርተር

መረጃ ከሁሉም 16-09-13ኢትዮጵያ የአሜሪካ ጣልቃገብነት “በፍጹም ተቀባይነት የለውም” አለች*******************************************የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴ...
24/05/2021

መረጃ ከሁሉም 16-09-13
ኢትዮጵያ የአሜሪካ ጣልቃገብነት “በፍጹም ተቀባይነት የለውም” አለች
*******************************************
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሜሪካ “በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ለመግባት በተደጋጋሚ የምታደርገው ሙከራ ተገቢ አይደለም፤ በፍጹም ተቀባይነት የለውም” ብሏል፡፡

የአሜሪካ መንግስት ቀደም ሲል ባወጣው መግለጫ ለትግራይ ክልል ግጭት ኃላፊነት አለባቸው ባላቸው የኢትዮጵያና የኤርትራ ባለስልጣናት እንዲሁም መደበኛ ባልሆኑ የአማራ ኃይሎች፣ የህወሓት አባላት ላይ የጉዞ እግድ ለመጣል መዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው ኢትዮጵያ የራሷን የውስጥ ጉዳይ እንዴት መምራት እንዳለባት ሊነገራት እንደማይገባ አመልክቷል፡፡ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ላላት ታሪካዊ ግንኙነት ትልቅ ቦታ እንደምትሰጥ ያመለከተው መግለጫው የጉዞ እገዳ መጣልና ሌሎች ተዛማጅ እርምጃች የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት በእጅጉ እንደሚጎዳ ገልጿል፡፡

ሚኒስቴሩ በመግለጫው የአሜሪካ መንግስት በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በአሸባሪነት ከተፈረጀው ህወሓት ጋር በእኩል ደረጃ ማየቱ እንዳሳዘነውና ይህም የአሜሪካን አስተዳደር የተሳሳተ አካሄድ ያሳያል ብሏል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ብሄራዊ ንግግር ለማድረግ እየሰራ መሆኑን የገለጸው መግለጫው “ነገርግን በሽብር ከተፈረጀ ድርጅት ጋር ቁጭ ብሎ ለመነጋጋር ሊገደድ አይችልም፤ህወሓት እንዲያንሰራራ ለማድረግ የሚደረግ ማንኛውም ሙከራ አፍራሽ ነው” ብሏል መግለጫው፡፡

ሚኒስቴሩ በዚህ ወሳኝ ወቅት የኢትዮጵያ መንግስት “በምርጫው ላይ ጥላ የሚያጠላ የተሳሳተ ውሳኔ አይጠብቅም” ብሏል

የአሜሪካን የቪዛ እገዳ ውሳኔ በተመለከተ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ይህ የቪዛ እገዳ ውሳኔ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን ኢኮኖሚያዊና የደህንነት ድጋፍ ለማቋረጥ ከዚህ በፊት ካወጣችው ውሳኔ በተጨማሪ መሆኑን ጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም የአሜሪካ ውሳኔ ፣ በኢትዮጵያ አዲስ የፖለቲካ ዘመን ያመጣል ተብሎ የሚጠበቀውን ብሔራዊ ምርጫ ለማካሄድ ሀገሪቱ እየተዘጋጀች ባለችበት ወቅት “የተሳሳተ መልዕክት ይኖረዋል” ብሏል ሚኒስቴሩ፡፡ 6 ኛው ብሔራዊ ምርጫ ፣ አዲስ መንግሥት ስልጣን ከያዘ በኋላ “ሁሉን አቀፍ ውይይት ለማድረግ የሚያስችለውን መንገድ ይከፍታል” ሲልም ነው የጠቆመው፡፡ ስለሆነም በዚህ ወሳኝ ወቅት ላይ የኢትዮጵያ መንግስት ድጋፎችን እና መረዳቶችን እንጂ “በምርጫው ላይ ያለአግባብ ጥላ የሚያጠላ የተሳሳተ ውሳኔአይጠብቅም” ሲል ገልጿል፡፡

መግለጫው በውስጥ ጉዳያችን ጣልቃ ገብ የሆኑና ያለንን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ዝቅ ያደረጉ ውሳኔዎች የማይቆሙ ከሆነ ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጋር ያላትን ከሁለትዮሽ የተሻገረ አንድምታ ያለውን ግንኙነት በድጋሚ ለማጤን ትገደዳለችም ነው ያለው፡፡

በውሳኔው ተስፋ ሳይቆርጥ ችግሮችን ለመፍታትና ሃገሪቱን ወደ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግና ጎዳና ለመምራት ሳይታክት እንደሚሰራም ነው ያስታወቀው፡፡

አል-ዐይን

24/05/2021

ለተፈጠረው መቋረጥ ይቅርታ !!

መረጃ ከሁሉም 10-09-13 በአሜሪካ ያለጥፋታቸው ለ31 ዓመት ለታሰሩ ወንድማማቾች 84 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ተሰጣቸው***********************************************...
18/05/2021

መረጃ ከሁሉም 10-09-13

በአሜሪካ ያለጥፋታቸው ለ31 ዓመት ለታሰሩ ወንድማማቾች 84 ሚሊዮን ዶላር ካሳ ተሰጣቸው
***********************************************
አፍሪካ አሜሪካዊ የሆኑት ሁለቱ ወንድማማቾች ባልሰሩት ወንጀል ጥፋተኛ ናቸው በሚል ለ31 ዓመታት በእስር ላይ ቆይተዋል።

ወንድማማቾቹ ሄንሪ ሊ ማክኮልም እና ልዮን ብራውን ይባላሉ፤ መጠነኛ የአእምሮ ጤና ችግር እንዳለባቸውም ይነገራል።

ሁለቱ ወንድማማቾቾ በፈረንጆቹ 1983 ላይ ነበር የ11 ዓመት ሴት ልጅ አስገድዳችሁ ደፍራችኋል በሚል ለእስር የተዳረጉት።

ወንድማማቾቹ በወንጀሉ ተጠርጥረው ለእስር በተዳረጉበት ወቅት የ19 እና 15 ዓመት እድሜ ላይ የነበሩ ሲሆን፤ ባልሰሩት ወንጀል በግድ እንዲፈርሙ መደረጋቸውንም ይናገራሉ።

ሆኖም ግን በፈረንጆች በ2014 በዘረ መል (ዲ.ኤን.ኤ) የተገኘ የምርመራ ውጤት የሁለቱን ወንድማማቾች ጥፋተኝነት የሚቀይር ሆኗል።

በምርመራውም ልጅቷ በተደፈረችበት ወቅት ሁለቱ ወንድማማቾች አጠገቧ እንዳልነበሩ እና በስፍራው የነበረው ሌላ ሰው እንደነበረ መለየት ተችሏል።

ይህንን ተከትሎም ሄንሪ ሊ ማክኮልም እና ግማሽ ወንድሙ ልዮን ብራውን በጉዳያቸው ላይ ይግባኝ የጠየቁ ሲሆን፤ የሰብዓዊ መብታቸው መጣሱን በመግለጽም ክስ ይከፍታሉ።

በዚህም መሰረት ባሳለፈወነው አርብ የተሰየመው ችሎት ለሁለቱ ወንድማማቾች 84 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ካሳ እንዲከፈላቸው ወስኖላቸዋል።

ለሁለቱ ወንድማማቾች የተወሰነው ካሳም በሀገሪቱ ታሪክ ከፍተኛው ነው ተብሎለታል።

አል-ዐይን

መረጃ ከሁሉም 10-09-13 የባይቶና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ክብሮም በርኸ ወደ ቤታቸው መመለሳቸው ታውቋል። ዛሬ ጠዋት ፖሊስ መኖሪያ ቤታቸውን ከፈተሸ በኋላይፈለጋሉ ተብለው በማለ...
18/05/2021

መረጃ ከሁሉም 10-09-13

የባይቶና ፓርቲ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ክብሮም በርኸ ወደ ቤታቸው መመለሳቸው ታውቋል።

ዛሬ ጠዋት ፖሊስ መኖሪያ ቤታቸውን ከፈተሸ በኋላይፈለጋሉ ተብለው በማለት ወደ ቱሉ ዲምቱ ፖሊስ ጣቢያ ሄደው የነበረ ሲሆን ፤ አሁን ወደ ቤታቸው መመለሳቸውን አውሎ ሚዲያ አረጋግጧል።
አውሎ ሚድያ

መረጃ ከሁሉም 10-09-13የትግራይ ሁኔታ “እጅግ አስከፊ ነው” ሲሉ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሐኖም ተናገሩ**********************************************የዓለም ጤና ድር...
18/05/2021

መረጃ ከሁሉም 10-09-13
የትግራይ ሁኔታ “እጅግ አስከፊ ነው” ሲሉ ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሐኖም ተናገሩ
**********************************************
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሐኖም በትግራይ ያለው ሁኔታ እጅግ አስከፊ ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የዓለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተሩ ይህንን ያሉት በትላንትናው እለት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው፡፡

በተደጋጋሚ ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት በኩል ለህወሓት እያገዙ ነው የሚል ትችት የሚቀርብባቸው ዶ/ር ቴዎድሮስ የትግራይ ህዝብ አሁን ያለበት ሁኔታ ለመግለፅ የምጠቀምበት ቃልም ካለ “እጅግ አስከፊ ነው በሚል ቃል ነው ልገልፀው የምችለው ብዋል፡፡

ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሐኖም ከኢትዮጵያ መንግስት ለህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህውሓት) ትደግፋለክ በሚል ለሚቀርብባቸው ክስ ለማንም የወታደራዊ ሃይል ምንም እንደ ማይደግፉ ሲገልጹ መቆየታቸው ቆይተዋል።

በትግራይ ብዙ ሰው በርሃብ እየሞቱ ነው ፤ 4.5 ሚሊዮን ህዝብ የሰብአዊ ድጋፍ ያስፈልገዋል ብለዋል። በተጨማሪም ዋና ዳይሬክተሩ 91 ፐርሰንት የሚሆነው ህዝብ በክልሉ ምግብ ያስፈልገዋል። ስደት መኖሩን ያነሩት ዶክተር ቴዎድሮስ ከ 60 ሺ በላይ ሰዎች ወደ ሱዳን ተሰደዋል ብለዋል።

የሴቶች መደፈርና ዘርን መሰረት ያረጉ የጅምላ ግድያዎች በትግራይ ህዝብ ላይ እየተፈፀመ ነው ብለዋል ዳይሬክተሩ፡፡

የትግራይ ህዝብ ካለበት ወቅታዊ ችግር አንፃር ስለ ኮሮና ቫይረስ መጨነቅ አቁሟል ያሉት ዶ/ር ቴዎድሮስ በክልሉ በኮሮና ከሚሞት ሰው በበለጠ አሁን ባለው ሁኔታ የሚሞተው ሰለሚበዛ ህዝቡ ስለኮሮና ደንታ የለውም ብለዋል።

ጨምረውም ዜጎች በክልሉ የህክምና አገልግሎትም በተገቢው ሁኔታ ማግኘት አይችሉም ብለዋል ዋና ዳይሬክተሩ፡፡
አውሎ ሚድያ

መረጃ ከሀሉም 10-09-13 የባይቶና ፓርቲ አመራር አቶ ክብሮም በርኸ ፖሊስ እንደ ወሰዳቸው ተሰማ**********************************************የባይቶና ትግራይ ፓ...
18/05/2021

መረጃ ከሀሉም 10-09-13

የባይቶና ፓርቲ አመራር አቶ ክብሮም በርኸ ፖሊስ እንደ ወሰዳቸው ተሰማ
**********************************************
የባይቶና ትግራይ ፓርቲ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ክብሮም በርኸ ዛሬ ጠዋት አንድ ሰዓት አካባቢ ከመኖሪያ ቤታቸው በፖሊስ መወሰዳቸው ተረጋግጧል።
አቶ ክብሮም መኖሪያ ቤት አምስት ፖሊሶች የጦር መሳሪያ ደብቀሃል በሚል ፍተሻ ያካሄዱ ሲሆን ከፍተሻ በኋላ አቶ ክብሮምን ትፈለጋለህ በማለት ወደ ቱሉ ዲምቱ ፖሊስ ጣቢያ እንደ ወሰዷቸው ታውቋል።
በአቶ ክብሮ በርኸ ቤት አምስት ፖሊሶች ፍተሻ አካሂደው ያገኙት ነገር የለም የተባለ ሲሆን ይህ ዜና እስከ ተጠናከረበት ሰዓት ድረስ አቶ ክብሮም በቱሉ ዲምቱ ፖሊስ ጣቢያ ውስጥ ናቸው።
የባይቶናትግራይ ከፍተኛ አመራር የሆኑቴ አቶ ክብሮም በሚያምኑበት የሰላማዊ ትግል ስልት ለትግራይ ህዝብ ጉዳት በተለያዩ ሚዲያዎች ሲያስረዱና ድምፃቸውን ሲያሰሙ የቆዩ ቢሆንም ዛሬ ወደ ፖሊስ ጣቢያ የተወሰዱት ለእስር ይሆን ወይንስ ለቃል ጥያቄ አልታወቀም።

አውሎ ሚዲያ

18/05/2021
መረጃ ከሁሉም 08-09-13የአውሮጳ ሕብረት በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ዕርዳታን ተደራሽነትን በማቀብ እንደ ጦር መሣሪያ መጠቀም ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ሕጎችን  የሚጥስ ተግባር ነው ሲል ኮነነ።...
16/05/2021

መረጃ ከሁሉም 08-09-13
የአውሮጳ ሕብረት በትግራይ ክልል የሰብዓዊ ዕርዳታን ተደራሽነትን በማቀብ እንደ ጦር መሣሪያ መጠቀም ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ሕጎችን የሚጥስ ተግባር ነው ሲል ኮነነ።
ተግባሩ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ሕይወት አደጋ ላይ እየጣለ ነው ብሏል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በበኩሉ በትግራይ አንዳንድ አካባቢዎች የሰብአዊ እርዳታ እንዳይደርስ የወታደራዊ ኃይሎች ዕቀባ እያደረጉ መሆኑን አረጋግጫለሁ ብሏል። የአውሮጳ ሕብረት በሁሉም የትግራይ አካባቢዎች የሰብአዊ እርዳታ ያለገደብ እንዲደርስ እና የኤርትራ ወታደሮች በፍጥነት ትግራይን ለቀው እንዲወጡ ሲጠይቅ እንደነበር የህብረቱ ከፍተኛ ተወካይ ጆሴፕ ቦሬል እና የቀውስ አስተዳደር ኮሚሽነር ያኔዝ ሌናርኪች ትናንት በጋራ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። «የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ለእርዳታ ተደራሽነቱም ሆነ የኤርትራ ወታደሮች ለቀው እንዲወጡ ቁርጠኛ መሆናቸውን» የጠቀሰው መግለጫው ፣ «ነገር ግን እውነታው መንገዶች በወታደራዊ ኃይሎች በመዘጋታቸው የሰብዓዊ ቀውሱ እጅግ የከፋ ደረጃ ላይ ወደደረሰባቸው ገጠራማ አካባቢዎች እርዳታ ለማድረስ አደናቃፊ ሆኗል »ብሏል። ሕብረቱ «በትግራይ ከሚገኙ 5.7 ሚሊዮን ሰዎች መካከል ቢያንስ 5.2 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ይፈልጋሉ »ብሏል።፡ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በበኩሉ ካለፉት ሁለት ሳምንታት ወዲህ ከአስቸኳይ መጠለያ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ከሚያስፈልጋቸው ሶስት ሚሊዮን ሰዎች መካከል 12 በመቶ ያህሉ ብቻ እንደደረሳቸው ገልጿል። በክልሉ ረሃብን ለማስወገድ አፋጣኝ እና የተሟላ ድጋፍ መደረግ አለበት ያለው የህብረቱ መግለጫ ፡፡ የሰብአዊ እርዳታ ተደራሽነትን የሚያስተጓጉሉ አካላት በህግ መጠየቅ እንዳለባቸው አሳስቧል።
DW Amharic

መረጃ ከሁሉም 08-09-13 በትግራይ ወታደሮች ሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተጓጎላቸውን አሜሪካ አወገዘች*********************************************በኢትዮጵያ ወታደሮች የሰ...
16/05/2021

መረጃ ከሁሉም 08-09-13

በትግራይ ወታደሮች ሰብዓዊ ዕርዳታ ማስተጓጎላቸውን አሜሪካ አወገዘች
*********************************************
በኢትዮጵያ ወታደሮች የሰብዓዊ ዕርዳታ ለአንዳንድ የትግራይ ክልል አካባቢዎች እንዳይደርስ ያደረጉባቸው የተረጋገጡ ማስተጓጎሎች እየጨመሩ መምጣታቸው እንደሚያሳስባት አሜሪካ አስታወቀች። የአውሮፓ ኅብረት ወታደራዊ ኃይሎች የሰብዓዊ ዕርዳታን ለማስተጓጎላቸው ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ማረጋገጫ መገኘቱን በመግለጽ ድርጊቱን ኮንኖ ነበር።

የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ምኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ትናንት ቅዳሜ ባወጡት መግለጫ “ይኸ ተቀባይነት የሌለው ባህሪ አፋጣኝ የሰብዓዊ ዕርዳታ የሚያስፈልጋቸው 5.2 ሚሊዮን ሰዎችን ለበለጠ አደጋ ያጋልጣል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

የውጭ ጉዳይ ምኒስትሩ "የኤርትራ እና የኢትዮጵያ መንግሥታት በትግራይ የሚገኙ ወታደሮቻቸው ይኸን የሚወገዝ ተግባር እንዲያቆሙ አስፈላጊ የሆኑ እርምጃዎችን ሁሉ እንዲወስዱ አሜሪካ ጥሪ ታቀርባለች" ብለዋል።

የአውሮፓ ኅብረት ከትናንት በስቲያ አርብ ባወጣው መግለጫ ወታደራዊ ኃይሎች የሰብዓዊ ዕርዳታን ለማስተጓጎላቸው ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ማረጋገጫ መገኘቱን በመግለጽ ድርጊቱን ኮንኖ ነበር።

"የወታደራዊ ኃይሎች ክልከላ የሰብዓዊ ቀውስ እጅግ የከፋ ደረጃ ላይ በደረሰባቸው ገጠራማ አካባቢዎች ዕርዳታ የማድረስ አቅምን በእጅጉ እያደናቀፈ ነው" ያለው የአውሮፓ ኅብረት በትንሹ 5.2 ሚሊዮን ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ ጠባቂ መሆናቸውን ገልጾ ነበር።

የአውሮፓ ኅብረት በዉጪ ግንኙነት ኃላፊው ጆሴፕ ቦሬል እና የቀውስ አስተዳደር ኮሚሽነሩ ያኔዝ ሌናርቺች በኩል፤ እንዲሁም አሜሪካ በውጭ ጉዳይ ምኒስትሯ አንቶኒ ብሊንከን አማካኝነት ባወጧቸው መግለጫዎች የኤርትራ ወታደሮች ከትግራይ ለቀው እንዲወጡ በድጋሚ ጠይቀዋል።

"የኤርትራ ወታደሮች በትግራይ አሁንም መገኘት የኢትዮጵያን መረጋጋት እና ብሔራዊ አንድነት ጥያቄ ላይ ይጥላል" ያሉት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ምኒስትር ይኸንኑ ተግባራዊ ለማድረግ ከዚህ ቀደም ሁለቱ አገሮች በተደጋጋሚ ቃል ገብተው የነበረ ቢሆንም “ለተግባራዊነቱ ምንም እንቅስቃሴ አላየንም” ሲሉ ወቅሰዋል።

ከስድስት ወራት በላይ ባስቆጠረው የትግራይ ግጭት እጃቸው ያለበት "ወገኖች ለሰላማዊ ሰዎች ደሕንነት ጥበቃ፣ ሁሉንም ግጭት በአፋጣኝ ለማቆም፣ ለተቸገሩ የሰብዓዊ ዕርዳታ ለማድረስ የሚፈቅዱትን ጨምሮ በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ሕግጋት ውስጥ የሚገኙ ግዴታዎቻቸውን እንዲወጡ" ጠይቀዋል። አንቶኒ ብሊንከን በውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ በኩል ባወጡት መግለጫ እንዳሉት የኢትዮጵያ መንግሥት በዚህ ረገድ ለግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ሙሉ እና ያልተገደበ እንቅስቃሴ አሁኑኑ በማመቻቸት ግንባር ቀደም ሚና መጫወት አለበት።

"በትግራይ የሚገኙ የታጠቁ ኃይሎች በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጾታዊ ጥቃት፣ ሌሎች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እና ጭካኔዎች ለመፈጸማቸው በርካታ ተዓማኒ መረጃ" መኖሩን የገለጹት ውጭ ጉዳይ ምኒስትሩ በተለይ በኤርትራ ወታደሮች እና በአማራ ክልል ኃይሎች ተፈጽመዋል ያሏቸውን “አስከፊ” ብለዋቸዋል።

የኢትዮጵያው ጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለተፈጸሙ ግፎች ኃላፊነት ያለባቸውን ተጠያቂ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት የአማራ ክልል ኃይሎችን ከትግራይ እንዲያስወጣ፤ የምዕራባዊ ትግራይ ቁጥጥር በትክክል አብርሃም በላይ ወደሚመሩት ጊዜያዊ አስተዳደር መመለሱን እንዲያረጋግጥ ጭምር ጠይቀዋል።

DW Amharic

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when መረጃ ከሁሉም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share