የሹፌሮች አንደበት

የሹፌሮች አንደበት
እባብ 🐍 እና ጊንጡ 🦂 በሞላበት ዓለም..🌍
ከሰው የበረታ በፍፁም መርዝ ☠️ የለም‼️

(2)

ደጉ ዘመን ናፈቀኝ..🙄😥🙄
25/10/2025

ደጉ ዘመን ናፈቀኝ..🙄😥🙄

ጤና ይስጥልኝ በሰሜን ሸዋ ዞን መርሐቤቴ ወረዳ ቁምአምባ ቀበሌ ወንጭት ድልድይ አካባቢ በ14/02/2018  ዓም  የሁለት መኪና እረዳትና ሹፌሮች ታግተው ተወስደዋል።እዛ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ ...
25/10/2025

ጤና ይስጥልኝ በሰሜን ሸዋ ዞን መርሐቤቴ ወረዳ ቁምአምባ ቀበሌ ወንጭት ድልድይ አካባቢ በ14/02/2018 ዓም የሁለት መኪና እረዳትና ሹፌሮች ታግተው ተወስደዋል።

እዛ አካባቢ የሚንቀሳቀሱ አሽከርካሪዎች ጥንቃቄ ቢያደርጉ ጥሩ ነው ሲሉ መልዕክት አድርሰውናል።

➤እናፋልጋቸውይህ ኪን ካፕ ቶዮታ መኪና  በቀን 14/02/2018 አዳስ አበባ ላይ ጋርመንት ሰፈራ አካባቢ በተለምዶ ናሆም አደባባይ ከሚባለው አካባቢ ባለው ንግድ ባንክ ፊትለፊት ከቆመበት ተሰ...
25/10/2025

➤እናፋልጋቸው

ይህ ኪን ካፕ ቶዮታ መኪና በቀን 14/02/2018 አዳስ አበባ ላይ ጋርመንት ሰፈራ አካባቢ በተለምዶ ናሆም አደባባይ ከሚባለው አካባቢ ባለው ንግድ ባንክ ፊትለፊት ከቆመበት ተሰርቋል።

መኪናውን አፋልጋችሁ ላገኛችሁ ወይም ለጠቆማችሁን ወሮታው እንከፍላለንና አፋልጉን ብለዋል።
ጥቆማ ያላችሁ በስልክ ቁጥር ፣
0911425724
0912241898 አግኙን ይላሉ!!!

የሹፌሮች አንደበት °¶15/2/2018

ተመስገን ነው ማለት..🤲ንብረት ተተኪ ነው✍️ተሽከርካሪው 150 ሜትር ርዝማኔ ያለው ገደል ገብቶ አርሶ አደር ግቢ ውስጥ ቢያርፍም ከቀላል ጉዳት ውጪ ያጋጠመ ከባድ ጉዳትና ሞት የለም።በትግራይ...
25/10/2025

ተመስገን ነው ማለት..🤲
ንብረት ተተኪ ነው✍️

ተሽከርካሪው 150 ሜትር ርዝማኔ ያለው ገደል ገብቶ አርሶ አደር ግቢ ውስጥ ቢያርፍም ከቀላል ጉዳት ውጪ ያጋጠመ ከባድ ጉዳትና ሞት የለም።

በትግራይ ክልል የሚገኘው የጥንታዊው አቡነ አረጋዊ ገዳም ዝክር በየዓመቱ የአገር ውስጥና ከውጭ የሚመጡ ምእመናን በተገኙነት ጥቅምት 14 ነው የሚከበረው።

ታዲያ " ቶዮታ ሪቮልዩሽን " በሚባለው ተሽከርካሪ ባለቤቱ እራሱን ጨምሮ 5 ሰዎች ጭኖ ዓመታዊው የአቡነ አረጋዊ ገዳም ለመሳለም በመጓዝ ላይ እያለ ተሽከርካሪው መንገድ ስቶ ተንሸራቶ ገደል ይገባል።

ተሽከርካሪው የገባበት ገደል ርዝማኔው 150 ሜትር ነው ብለዋል የአይን እማኞች።

ተሽከርካሪው መንገድ ስቶ ወደ ገደል ከተወረወረ በኃላ በፎቶው እንደሚታየው ወደ አንድ አርሶ አደር ቤት ግቢ ገብቶ ተዘቅዝቆ አርፏል።

ከአስፈሪ ገደል ተወርውሮ በሚታየው መልኩ ያረፈው ተሽከርካሪ በአርሶ አደር ቅጥር ግቢ ከነበሩት ሰዎችና እንስሳት ላይ አንድ ቀላል ጉዳት ከማድረሱ ውጪ የተከሰተ ከባድ ጉዳትና ሞት የለም።

አሽከርካሪዎች ለማሽከርከር በሚያዳግቱና ተዳፋት በሆኑ መንገዶች ላይ ሲያሽከረክሩ እርጋታና ማስተዋል ሊለያቸው አይገባም።

©ቲክቫህ ኢትዮጵያ

የሹፌሮች አንደበት °15/2/2018

እጅግ አሳዛኝ ዜና 😥😥😥በ 12/2/2018 ወለንጪቲ ለትምህርት ወደ ሀረማያ ዩንቨርስቲ ሲጓዙ በነበሩ  የጤና ባለሙያዎች ላይ  በደረሰ የትራፊክ አደጋ ብዛት ያላቸው የጤና ባለሙያወች ህይወት ...
23/10/2025

እጅግ አሳዛኝ ዜና 😥😥😥

በ 12/2/2018 ወለንጪቲ ለትምህርት ወደ ሀረማያ ዩንቨርስቲ ሲጓዙ በነበሩ የጤና ባለሙያዎች ላይ በደረሰ የትራፊክ አደጋ

ብዛት ያላቸው የጤና ባለሙያወች ህይወት ተቀጥፏል። 😢

በቀን 12/02/2018 ዓ.ም  ከደባርቅ- ጎንደር  ባለዉ  የመንገድ ክፍል ዳባት ከተማ ሳይደርስ የተፈጠረ  አደጋ ነዉ።የሰዉ ጉዳት አልደረሰም ሲሉ መልዕክት አድርሰውናል።ጥንቃቄ ‼️
22/10/2025

በቀን 12/02/2018 ዓ.ም ከደባርቅ- ጎንደር ባለዉ የመንገድ ክፍል ዳባት ከተማ ሳይደርስ የተፈጠረ አደጋ ነዉ።

የሰዉ ጉዳት አልደረሰም ሲሉ መልዕክት አድርሰውናል።

ጥንቃቄ ‼️

22/10/2025

ገርጂ የተፈጠረው‼️
ትናንት ጥቅምት 11/2018 ዓ.ም ገርጂ ወደ ዩኒቲ ዩኒቨርቲ መታጠፊያ መብራት ላይ አንዲት ሴት ዲዛየር መኪና እያሽከረከረች መጥታ ትቆማለች። ሁለት ወታደራዊ ዩኒፎርም የለበሱ ሰዎች ሴትዮዋን ከመኪናዋ ጎትተው ከአስፓልት ከጣሉዋት በኋላ መኪናዋን ቀምተው ለማምለጥ ይሞክራሉ። በዚህ ጊዜ ትራፈክ ፖሊሱ ያይና ሳይረን እያስጮኸ ይከተላቸዋል። የተደናገሩት ሌቦች ለማምለጥ በተቃራኒ አቅጣጫ ሲነዱ ከአንዲት ቪትዝ መኪና ጋር ይጋጫሉ። በዚህ ጊዜ ትራፊክ ፖሊሱ ይደርስና ግብግብ ይገጥማል።በአካባቢው ሰው ትብብር በቁጥጥር ስር ውለዋል። የተጎዳችው ባለ መኪናም ወደ ሆስፒታል ተወስዳለች። ሰዎቹ በትክክል የህግ አስከባሪ አልነበሩም።
ሴትዮዋ ለአደጋ የተጋለጠችው የመኪናዋን በር ሳትዘጋ በማሽከርከሩዋ ስለሆነ ስታሽከረክሩ በራችሁ መቆለፉን አረጋግጡ።

22/10/2025

ከአርባምንጭ-ኮንሶ መንገድ ለ2 ቀናት ዝግ ሆኗል ።

ከአርባ ምንጭ ኮንሶ ያለው የመንገድ ክፍል ኤልጎ ከተማ ላይ በተነሳ ግጭት ምክንያት መንገዱ መዘጋቱ ተገለፀ።

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከአርባ ምንጭ ኮንሶ ያለው የመንገድ ክፍል ኤልጎ ከተማ ላይ በተነሳ ግጭት ምክንያት መንገዱ ለ2ኛ ቀን እንደተዘጋ ይገኛል ስሉ ወደ አካባቢው የተጓዙ ያደረሱት መረጃ ያመለክታል።

መንገድ በመዘጋቱ ምክንያቱ ቱሪስቶችን ጨምሮ የሚበላሽ አትክልት የጫኑ ሌሎችም የህዝብ ትራንስፖርት ጉዞ ላይ የነበሩ የአካባቢው ነዋሪወች ችግር ላይ እንደወደቁ አትክልት ለብልሽት ቱሪስት ለስጋት መዳረጋቸውን መልዕክት አድርሰውናል።

የሹፌሮች አንደበት °12/2/2018

22/10/2025

ከአርባምንጭ ከተማ ወደ ኮንሶና ጂንካ የሚወስደው መንገድ ስለተዘጋ ሹፌሮች ወደዛ መስመር እንዳይሄዱ መልእክት አስተላልፉ።
ሸር

22/10/2025

-> እነዚህን የደጉ ዘመን የድሮ አውቶቡስ ተሽከርካሪዎች የተመለከተ ምስላቸውን ያጋራን..🗣

->ማሞ ካቻ ቀይ መደብ ወገቡ አረንጓዴ ፣
~>ንስር (አንዳርጌ) ሰማያዊ በነጭ ፣
~>መኮንን ነጋሽ ውሃ አረንጓዴ በአረንጓዴ ወገብ፣ ~>አጎናፍር ነጭ ማኪያቶ (cream white)
~>ቦጋለ ብሩ ሰማያዊ በነጭ፣
~>ሰሜናዊ ትራንስፖርት ሰማያዊ
~>ወሎ ፈረስ ቀይ

በ 11/2/2018 ከሀዋሳ ወደ ወላይታ ሶዶ እየተጓዘ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ  ኦቶና ጤና ካምፓስ ሲደርስ የመገልበጥ አደጋ ደርሶበታል።በአደጋው በመኪና ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች የ...
22/10/2025

በ 11/2/2018 ከሀዋሳ ወደ ወላይታ ሶዶ እየተጓዘ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ኦቶና ጤና ካምፓስ ሲደርስ የመገልበጥ አደጋ ደርሶበታል።

በአደጋው በመኪና ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች የአካል ጉዳት የደረሳባቸው ሲሆን የሕክምና እርዳታ እንዲደረግላቸው ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።

ቶሎ አገግማችሁ ወደ ቤተሰቦቻቸው እንድቀላቀሉ ምኞታችን ነው። አሽከርካሪዎች ከማሽከርከር በፊት የተሽከርካሪ ቴክኒክ ሁኔታ ማየትና መፈተሽ ይቀድማል። ከሁሉ በላይ በጥንቃቄ ረጋ ብሎ ማሽከርከር አስፈላጊ ነው የዕለቱ መልዕክታችን ነው።

የሹፌሮች አንደበት °12/2/2018

21/10/2025

በድሬዳዋ በባቡር አደጋ 14 ሰዎች ሞቱ!😥

በድሬዳዋ ደወሌ ባቡር ላይ በደረሰ አደጋ 14 ሰዎች ህይወት ማለፉ ተነገረ።

በድሬዳዋ ደወሌ ባቡር ላይ በደረሰ አደጋ 14 ሰዎች ሲሞቱ 29 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።

ከደወሌ መነሻውን አድርጎ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ባቡር ትላንት ሌሊት 8:00 አካባቢ በሶማሌ ክልል ሺኒሌ ወረዳ ላይ በደረሰበት አደጋ 14 ሰዎች ሲሞቱ 29 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን ከሽኒሌ ወረዳ አስተዳደር የደረሰን መረጃ ያመለክታል።
©ድሬ ቲቪ

የሹፌሮች አንደበት ° 10/2/2018

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሹፌሮች አንደበት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የሹፌሮች አንደበት:

Share