የሹፌሮች አንደበት

የሹፌሮች አንደበት 🛰️ t.me/Voice_of_Drivers2017

አቤት አጨካከን...😥🙄😥==========================በትናንትናው ዕለት በ25/12/2017 ዓም ከጅቡቲ ነዳጂ ጭነው ሲጓዙ የነበሩ ተሽከርካሪዎች በአማራ ክልል በደቡብ ጎንደር እና...
01/09/2025

አቤት አጨካከን...😥🙄😥
==========================

በትናንትናው ዕለት በ25/12/2017 ዓም ከጅቡቲ ነዳጂ ጭነው
ሲጓዙ የነበሩ ተሽከርካሪዎች በአማራ ክልል በደቡብ ጎንደር እና በሰሜን ወሎ ከደብረ ዘቢጥ ጋይንት ባለው የመንገድ ክፍል እገታ ዝርፊያን በመፍራት በእጀባ እየሄዱ ባሉበት መኪኖቹ በጥይት ኮምፒተራቸው ሴንሰር በመመታቱ ቁመው ነበር በቆሙበት እንዱ በቀን እንዱ ከመሸ በድምሩ 2 ነዳጂ የጫኑ መኪኖች መቃጠላቸውን መልዕክት ደርሶናል።

2ቱ ተሽከርካሪዎች ጨጨሆ ተብሎ በሚጠራው የመቄት እና የላይጋይንት ወረዳዎች በሆነ ቦታ ላይ መቃጠላቸውን አድርሰውናል። 3ኛ መኪና ነዳጁ እየፈሰሰ እንዳለም ነግረውናል።

በእጀባ የሚደረግ ጉዞ እንዲህ ንብረን ከውድመት ሹፌሮችን ከሞት ካላስጣለ መንገዱን ባለመጠቀም በአዲስ አበባ ዙሮ መምጣት ምርጫ ሊያደርግ ይገባል ከጅቡቲ የምትመጡ ሹፌሮች ባለንብረቶች።

ካሁን በፊት በዚህ የመንገድ ክፍል ጋይንት ወጣ ብሎ ቦቴዎች በጥይት ተመተው ነዳጅ መደፋቱ ይታወቃል።

የደረሰው የንብረት ውድመት 40,000,000 (አርባ ሚሊየን )ብር የሚገመት ሲሆን ይህ የግለሰቦች ሀብት ለህዝብ ግልጋሎት የመጣ ነዳጂ ነው።

ፍትህ ለአሽከርካሪዎች 😥🙇‍♀️😥

❤❤❤ኧረ የሰው ያለህ❤❤❤በሞተሩ ሙቀት ውስጡ እየነደደበፊቱ እንደውሃ ላብ እየወረደስንቱን ዳገት ታግሎ ነፍስ እንዳላዳነላጣው ለገረጣው መጋቢ እንዳልሆነባበላው ወገኑ ለምን ተረሸነ?የምትፈልገው...
01/09/2025

❤❤❤ኧረ የሰው ያለህ❤❤❤
በሞተሩ ሙቀት ውስጡ እየነደደ
በፊቱ እንደውሃ ላብ እየወረደ
ስንቱን ዳገት ታግሎ ነፍስ እንዳላዳነ
ላጣው ለገረጣው መጋቢ እንዳልሆነ
ባበላው ወገኑ ለምን ተረሸነ?
የምትፈልገውን ጭኖ ላቀረበ
ለችግርህ ደርሶ አንተን ባጠገበ
ከረሀብ ላዳነህ አንተን ለመገበ
በበረሀ ነዶ አሮ ለከሰለ
ባንተው በወንድሙ ለምን ተገደለ?
ኧረ የሰው ያለህ ሰው ካለ ፈልጉ
ከህሊናው ታርቆ የሚኖር በወጉ
ድንገት ለሹፌሮች ዋስ የሚሆን ካለ
እኛን በመገቡ ባይሞቱ ምን አለ?
©ይፍቅር ጥግ✍️
ከፌስቡክ ገፃችን ውድ ቤተሰባችን የተገጠመ✍️
ምስጋናችን ባለህበት ይድረስህ🗣

01/09/2025

ፍትሕ ከመኪና መሪ ውጭ ምንም ለማያውቀው ሹፌር ፣ፍትሕ..🗣
(😥)🙄(😥)

01/09/2025

ውድ ሹፌሮች እንዲሁም በአራቱም የሀገሪቱ አቅጣጫወች የምትገኙ ሕዝቦች የበዓላት ሰሞን እንደመሆኑ መጠን አስከፊውን የትራፊክ አደጋ ለመከላከል ልዩ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው መሆኑን ለመጠቆም እንወዳለን።

የሹፌሮች አንደበት| 26/12/2017 ዓ.ም

01/09/2025

Big shout out to my newest top fans! Mulatu DE, Omer Borana, Getahun Amare, Abdul Malike Mudesir Abdu, Delesa Legesse, Ytayali Birhan, Mesele Abu, Megdad Afkadr, እስጢፋ አካል እስጢፉ, Mohammed Hussen, Sadame Husen, Dareskedar Baye, Bibi Kongo Ayele Bine, Amanuel Tilahun Daba, ሸይቾ ስርሞሎ, Habtamu Baysa, Dani Tesfay, Bilaal Kaabboo, Adem Ahmed, Tesfaye Wassie Alem, ፊያሜታዬ ሁሉነገሪ, ቼኮላታ ቼኮላታ, Endirs Sied, Endeis Abdu, Nebret Walelign, Sisay Mekurya, Senayit Taye, Suleman Dilbi, ዘናጩ ወሎየ ፍርዱ ከላይ, አህመድ አሊ አሊ, አዲስ አዲስ, Eyu Tda, Tedi Mengestu, Mequanint Kibretu, Waan Ofii Zaker, ሙራድ መሀመድ, Leul Sewagegn Berihun, Ashagre Befikadu, Gashaw Msk, Yoni Neon, እንዳለ ዳንኤል, Aschalew Zerihun, Samuel Tfte, Kubte Mam, Jamal A Ahmed, Kedir Adem, Birhanu Worku, Gech Belete, Ras Biruk, Elias Tashome

ሰሚት‼ይህ ዛሬ  ማለትም በ 25/12/2017 ጠዋት 2፡10 አካባቢ አዲስ አበባ ሰሚት ፊሊፐር ትምህርት ቤት አካባቢ የደረሰ የመኪና አደጋ ነው። በልምምድ ላይ የነበረ አሽከርካሪ ነው አደጋው...
01/09/2025

ሰሚት‼

ይህ ዛሬ ማለትም በ 25/12/2017 ጠዋት 2፡10 አካባቢ አዲስ አበባ ሰሚት ፊሊፐር ትምህርት ቤት አካባቢ የደረሰ የመኪና አደጋ ነው። በልምምድ ላይ የነበረ አሽከርካሪ ነው አደጋውን ያደረሰው። እስካሁን ባለው መረጃ መሠረት በሰው ህይወት ላይ የደረሰ አደጋ አለመኖሩ ተሰምቷል።
ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ‼️

አያት ጣፎ ገብርኤል  መግቢያ አካባቢ  ቅድሚያ ባለመስጠት በ 25/12/2017  11:00 ላይ
01/09/2025

አያት ጣፎ ገብርኤል መግቢያ አካባቢ ቅድሚያ ባለመስጠት በ 25/12/2017 11:00 ላይ

30/08/2025

ፍትሕ ለሹፌሮች ፣ፍትሕ..🗣
(😥)🙄(😥)

በትራፊክ አደጋ በ14 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደረሰ**********(አዲስአበባ ፡-ነሀሴ 24/2017 ዓ/ም ) በዛሬው ዕለት ከቀኑ 6፡48 ሰዓት አካባቢ በአሶሳ ዞን ኡራ ወረዳ አምባ...
30/08/2025

በትራፊክ አደጋ በ14 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደረሰ
**********
(አዲስአበባ ፡-ነሀሴ 24/2017 ዓ/ም ) በዛሬው ዕለት ከቀኑ 6፡48 ሰዓት አካባቢ በአሶሳ ዞን ኡራ ወረዳ አምባ 5 ቀበሌ በደረሰ የትራፊክ አደጋ በ1 ሰው ከባድ አደጋ ሲደርስ በ13 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት ደርሷል፡፡

አደጋው የደረሰው ሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3- 2127 ቤጉ የሆነ የህዝብ ማመላለሻ ባስ ከመንጌ ወረዳ ወደ አሶሳ ከተማ የሚጓዙ መንገደኞችን አሳፍሮ ሲጓዝ በነበረበት ወቅት ነው ።

በደረሰው አደጋ በ14 ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን ተጎጅዎቹም በአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛሉ።

አደጋው የደረሰው በፍጥነት ምክንያት ከመንገድ ወጥቶ መገልበጡን ዋና ሳጅን ሞሲሳ ጉደታ የገለፁ ሲሆን አሽከርካሪዎች የሚከሰት የትራፊክ አደጋን ለመከላከል ፍጥነትን መቀነስ እንደሚገባቸው አሳስበዋል ፡፡

አሳዛኝ ዜና‼️ዛሬ  ጠዋት ማለትም በ 24/12/2017 በአዲስ አበባ ከአስኮ አለፍ ብሎ ሳንሱሲ አንበሳ ባስ ፍሬን እምቢ ብሎት ለታክሲ የተሰለፉ ሰዎችን በመግጨቱ እስካሁን በደረሰን መረጃ መ...
30/08/2025

አሳዛኝ ዜና‼️
ዛሬ ጠዋት ማለትም በ 24/12/2017 በአዲስ አበባ ከአስኮ አለፍ ብሎ ሳንሱሲ አንበሳ ባስ ፍሬን እምቢ ብሎት ለታክሲ የተሰለፉ ሰዎችን በመግጨቱ እስካሁን በደረሰን መረጃ መሰረት 6 ሰዎች እዛው ህይወታቸው አልፏል፣በርካታ ሰዎች ቆስለዋል።
ሹፌሯ ሴት ስትሆን ከባድ አደጋ ደርሶባታል። መኪናው ከትናንት በስተያ bus station አካባቢ በተመሳሳይ እምቢ ብሎት እንደነበር የደረሰን መረጃ ያሳያል ።

➹ይሄ ተሽከርካሪ የቴክኒክ ችግር ሳይኖርበት እንዳልቀረ በተደጋጋሚ ከምናየው ዘግናኝ የትራፊክ አደጋ መመልከት እንችላለን ።
➹የዛሬ 5 አመት ከሽሮሜዳ ወደ እስቴድየም ሲሄድ እንዲሁ እስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን አካባቢ ካለው ወንዝ ወስዶ የጨመራቸው እና አሳዛኝ አደጋ መድረሱ የሚዘነጋ አይደለም 😥
➹ በሰፊው እንመለስበታለን ..✍️

➹Cc: Addis Ababa City Roads Authority /አዲስ አበባ ከተማ መንገዶችAddis Ababa City Roads Authority /አዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን

30/08/2025

ከአዲስ ዘመን፣ ጎንደር መንገድ፣ ከእንፍራዝ አዲስ ዘመን መሀል ትናንት በ23/12/2017 ዓም ብዛት ያላቸው መኪኖች በጥይት ተመተዋል 😥🙄😥

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when የሹፌሮች አንደበት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to የሹፌሮች አንደበት:

Share