Addis Zena

Addis Zena Addis Zena is Media and Advertising Company. Communication Consultation, Organize events and Master of Cermony. Follow and Like Our Page.

Contact Us for Any work enquiry !!

Where is this place ?
03/09/2024

Where is this place ?

 #ዜና የፐርፐዝ ብላክ ኢ ቲ ኤች ትሬዲንግ አክሲዮን ማኅበር ሥራ አስፈጻሚዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።ሥራ አስፈጻሚዎቹ ስልጣንን አለአግባብ በመገልገል እና ከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀሎች ተጠ...
30/08/2024

#ዜና
የፐርፐዝ ብላክ ኢ ቲ ኤች ትሬዲንግ አክሲዮን ማኅበር ሥራ አስፈጻሚዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ።

ሥራ አስፈጻሚዎቹ ስልጣንን አለአግባብ በመገልገል እና ከባድ አታላይነት የሙስና ወንጀሎች ተጠርጥረው ዛሬ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

በማኅበሩ ተጭበርብረናል ያሉ ባለአክሲዮኖች ለፖሊስ ባቀረቡት አቤቱታ መነሻነት ምርመራ ተጀምሮ የአክሲዮን ማኅበሩ ሥራ አስፈጻሚዎች ከላይ በተገለጹት ምክንያቶች በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ማኅበሩ መሀል ሜክሲኮ ላይ ገና በእጁ ባላስገባው መሬት እና ይዞታ ቤት ገንብቶ ባለ 3 መኝታ አፓርትመንት በ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚሸጥ መሆኑን በሚዲያ እና በራሪ ወረቀቶች በማስተዋወቅ ከሕዝቡ ገንዘብ ሲሰበስብ መቆየቱን በተለያየ መንገድ ከሕብረተሰቡ ሲቀርቡ የነበሩ ቅሬታዎች ያመላክታሉ ተብሏል።

በዚህ መነሻም ሥራ አስፈጻሚዎቹ በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ፍትሕ ሚኒስቴር ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ፍስሃ እሸቱ ከወራት በፊት ሀገር ጥለው አሜሪካ መግባታቸው ይታወቃል።
Addis Zena

 ኢንጅነርኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነው ተሾሙኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት ቀደም ሲል ከተማውን በም/ ከንቲባ ማእረግ ዋና ስ...
30/08/2024


ኢንጅነርኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነው ተሾሙ

ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በዛሬው እለት ቀደም ሲል ከተማውን በም/ ከንቲባ ማእረግ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነው ሲመሩ ከነበሩት ከወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን ጋር ርክክብ አድርገዋል።

ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ በም/ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ ሆነው እስከተሾሙበት ጊዜ ድረስ የኢፌዴሪ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ሆነው ሲያገለግሉ ነበር።

በተያያዘ ዜና በም/ ከንቲባ ማእረግ የአዲስ አበባ ከተማ ዋና ስራ አስኪያጅ የነበሩት ወ/ሮ ሂክማ ከይረዲን የኢፌዴሪ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ሰሞኑን ተሹመዋል።

(አ/አ ከተማ ሥራ አስኪያጅ ፅ/ቤት)

Addis Zena

 #ዜና ኢትዮጵያ በሶማሌላንድ  አምባሳደር ሾመችአዲስ የተሾሙት  አምባሳደር  ተሾመ ሹንዴ ሃሚቶ ሲሆኑ የሹመት ደብዳቤአቸዉን ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ማቅረባቸዉና ተቀ...
30/08/2024

#ዜና

ኢትዮጵያ በሶማሌላንድ አምባሳደር ሾመች

አዲስ የተሾሙት አምባሳደር ተሾመ ሹንዴ ሃሚቶ ሲሆኑ የሹመት ደብዳቤአቸዉን ለሶማሌላንድ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ማቅረባቸዉና ተቀባይነት ማግኘቱን የሶማሌላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና ዓለም አቀፍ ትብብር መስሪያ ቤት አስታውቋል።

የአገሪቱ ፕሬዝደንት ሙሴ ቢሂ አብዲ ለአዲሱ አምባሳደር ደማቅ አቀባበል እንዳደረጉላቸው የተገለፅ ሲሆን አምባሳደሩ የሁለቱን አገራት ግንኙነት በማጠናከርና የወደፊት ቀጠናዊ ሰላምና ደህንነት ማስጠበቅ በሚያስችሉ የትብብር ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት ከፕሬዝዳንቱ ጋር መክረዋል ተብልዋል፡፡

በቅርቡ ኢትዮጵያ በተለያዩ ሃገር ከሾመቻቸው 24 አምባሳደሮች ውስጥ 14ቱ በልዩ እና ባለ ሙሉ ስልጣን አምባሳደርነት ቀሪዎቹ 10 ደግሞ በአምባሳደርነት ደረጃ መሆኑ ይታወሳል፡፡
EBS Addis Zena

 የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር  አንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል ።
29/08/2024


የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዝዳት ፕሮፌሰር አንድርያስ እሸቴ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ዛሬ ነሐኔ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል ።

    አንደኛው "የሚዲያ አዋርድ" የሽልማት ሥነሥርዓት ዛሬ ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ካዛንቺስ በሚገኘው በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ተከናውኗል።በዚህም መሰረት ፦~በምርጥ የቴሌቪ...
28/08/2024


አንደኛው "የሚዲያ አዋርድ" የሽልማት ሥነሥርዓት ዛሬ ነሐሴ 22 ቀን 2016 ዓ.ም አመሻሽ ላይ ካዛንቺስ በሚገኘው በኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ተከናውኗል።

በዚህም መሰረት ፦

~በምርጥ የቴሌቪዥን መዝናኛ ፕሮግራም ሴት አቅራቢ - አስካለ ተስፋዬ
~በምርጥ ዜና ዘጋቢ ዘርፍ - ግርማ ፍሰሃ
~በምርጥ የስፖርት ጋዜጠኛ - መንሱር አብዱልቀኒ
~በምርጥ ዶክመንተሪ አዘጋጅ - አክሊሉ ሲራጅ
~በምርጥ የሬድዮ ሴት ዜና አንባቢ - ለምለም ዮሐንስ
~በምርጥ የሬድዮ ወንድ ዜና አንባቢ - ሶዶ ለማ
~በምርጥ የቴሌቪዥን ሴት የዜና አንባቢ - የሸዋ ማስረሻ
~በምርጥ የቴሌቪዥን ወንድ የዜና አንባቢ - ሠለሞን ኃይለኢየሱስ
~በምርጥ የቴሌቪዥን መዝናኛ ፕሮግራም ወንድ አቅራቢ - ሀብተማርያም መንግስቴ
~በምርጥ የአምድ ፀሃፊ - አክሲያ ኢታሎ
~በምርጥ የምርመራ ዘገባ - ክብረት ካህሳይ
~በምርጥ ዲጄ - ዲጄ ኪንግስተን (ወዝወዝ አዲስ)
~ልዩ ተሸላሚ - የፎቶግራፍ ጋዜጠኛ ዳኜ አበራ
~በምርጥ የትምህርት ፕሮግራም - የእርቅ ማዕድ የሬድዮ ፕሮግራም
~በምርጥ የሬድዮ ፕሮግራም - ታዲያስ አዲስ
~በህዝብ ድምፅ ብቻ የተመረጠ የዓመቱ ምርጥ ጋዜጠኛ - አንዋር ጀማል
~የህይወት ዘመን ተሸላሚ - መዓዛ ብሩ
በመሆን ተሸልመዋል ።
Addis Zena

 በሦስተኛ ወገን የተሽከርካሪ አደጋ የመድን ፖሊሲ የሚሸፈነው የካሳ መጠን አዲስ የተሻሻለው ምን ይመስላል የሚለውን መረጃ ከታች በተያያዙ የሰንጠረዥ መሰጃዎች ይመልከቱ።Addis Zena    ...
28/08/2024



በሦስተኛ ወገን የተሽከርካሪ አደጋ የመድን ፖሊሲ የሚሸፈነው የካሳ መጠን አዲስ የተሻሻለው ምን ይመስላል የሚለውን መረጃ ከታች በተያያዙ የሰንጠረዥ መሰጃዎች ይመልከቱ።
Addis Zena

 በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩት እነ ዮሀንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል) መዝገብ ላይ የተጠየቀው የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ተፈቀደ።********የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዛሬው እለት በዋለው ተረኛ...
27/08/2024



በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩት እነ ዮሀንስ ዳንኤል (ጆን ዳንኤል) መዝገብ ላይ የተጠየቀው የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ተፈቀደ።
********

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በዛሬው እለት በዋለው ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሀንስ ዳንኤል ላይ የጠየቀውን የ14 ቀን የግዜ ቀጠሮ ፈቅዷል።

ተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው በጠበቆቻቸው አማካኝነት ጠይቀዋል።

ፍርድ ቤቱ የፖሊስን የምርመራ ውጤት ለመጠባበቅ ለጳጉሜ 4 ቀን 2016ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ዮሀንስ ዳንኤል በርሄ፣ አማኑኤል መውጫ አብርሃ፣ ናትናኤል ወንድወሰን ሹሜ፣ ኤልያስ ድሪባ በዳኔ፣ ይዲድያ ነጻነት አበበ እና እሌኒ ክንፈ ተክለአብ ናቸው።

ከትላንት በስቲያ ፌዴራል ፖሊስ ነሀሴ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከአዲስ አበባ መቀሌ ለጉዞ በተዘጋጀ አውሮፕላን ውስጥ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ በፈጠሩ 6 ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ መጀመሩን ማስታወቁ ይታወሳል።
Addis Zena Ethiopian Airlines

 በሰሜን ጎንደር በመሬት መንሸራተት የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ! በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኖላ በተባለ ቦታ በመሬት መንሸራተት አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት ሲያል...
26/08/2024



በሰሜን ጎንደር በመሬት መንሸራተት የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ!

በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኖላ በተባለ ቦታ በመሬት መንሸራተት አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ስምንት ሰዎች ከባድ የአካል ጉዳት ደረሰባቸው፡፡

የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖች በደጃች ሜዳ ጤና ጣቢያ የሕክምና እርዳታ እያገኙ መሆኑን የወረዳው የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ተስፋዬ ወርቅነህ ተናግረዋል፡፡

በአደጋው ምክንያት 480 አባወራዎች እና 2 ሺህ 400 የቤተሰብ አባላት መፈናቀላቸውን በመጥቀስ በጊዜያዊ መጠለያዎች እንደሚገኙ ለአሚኮ ገልጸዋል፡፡ከ35 በላይ የቤት እንሰሳት መሞታቸውን እና ከ30 ሔክታር በላይ በሰብል የተሸፈነ መሬትም ከጥቅም ውጭ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

Addis Zena Amhara Communications Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን Gondar city communication

 #ዜና በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ ፖሊስ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቀ👉🏿ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተ...
26/08/2024

#ዜና
በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ ፖሊስ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ፍርድ ቤቱን ጠይቀ

👉🏿ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራ ቀኙን ሰፊ ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል።

የፌዴሬል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቡድን ተጠርጣሪዎቹ ላይ የአቪዬሽን አሰራር ሕግ ከመጣስ ባለፈ በሽብር ወንጀልም ምርመራ ስለጀመርኩ የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ይደረግ በማለት ተከራክሯል።

ዛሬ ፍርድ ቤት የቀረቡት ተጠርጣሪዎች ዮሐንስ ዳንኤል ፣ አማኑኤል መውጫ ፣ ናትናኤል ወንድወሰን ፣ ኤልያስ ድሪባ ፣ ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ተክለአብ ናቸው።

የፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ መዝገብ እንደሚያሳየው እነዚህ ተጠርጣሪዎች ተፈጥሮ በፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት አውሮፕላኑ መብረር አይችልም እየተባለ፣ አስገድዶ ለማስኬድ የፈጠሩት አምባጓሮ በወንጀል ሕጉ ተጠያቂ ያደርጋቸዋል ብሏል።

ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ ተግባር መጠቀም ሲገባቸው፣ የሀገር ኩራት እና የራሳቸው ንብረት የሆነውን አየር መንገድ ማንቋሸሻቸው አሳዛኝ ተግባር ስለመሆኑ የፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ መግለፁን ይታወሳል።

 #ዜናየሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃምዛ አብዲ ባሬ ኢትዮጵያ በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ ከሶማሌላንድ ጋር ከተፈራረመችው አወዛጋቢ የመግባቢያ ስምምነት እስካልወጣች ድረስ የኢትዮጵያ ጦር በመጪው...
24/08/2024

#ዜና
የሶማሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃምዛ አብዲ ባሬ ኢትዮጵያ በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ ከሶማሌላንድ ጋር ከተፈራረመችው አወዛጋቢ የመግባቢያ ስምምነት እስካልወጣች ድረስ የኢትዮጵያ ጦር በመጪው የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (AUSSOM) አካል እንደማይሆን ገለፁ::

ባሬ ሞቃዲሾ ውስጥ ከሶማሌላንድ ጋር ከተፈራረመችው የመግባቢያ ስምምነት ካልወጣች ወታደሮቿ በመጪው ኦፕሬሽን አካል አይሆኑም። የሚቆዩም ከሆነ በአፍሪካ ህብረት ስልጣን ስር አይሆኑም ሲሉ ተናግረዋል።

ባሳለፍነው ሀሙስ ሞቃዲሾ ከሚገኙት የከተማው ማዘጋጃ ቤት ታዳሚዎች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ባሬ እንዳሉት የሶማሊያ መንግስት ከሶማሌላንድ ጋር የተደረሰውን ስምምነት ተግባራዊ እንዳይሆን የሶማሊያ መነንግስት በብቃት መምራት ችሏል።

"የመግባቢያ ስምምነቱን በተመለከተ ኢትዮጵያ አሁን አሳሳቢ ደረጃ ላይ ትገኛለች፤እኛ አልተቀበልንም ብለን ወደ ኬንያ፣ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ፣ በመጨረሻም ወደ ቱርክ ወንድሞቻችን ዞረን አሳውቀናል። በግድ ተቀበሉ የሚሉን ከሆነ እራሳችንን ለመከላከል ዝግጁ ነን” ብለዋል።

 #ዜና ፒያሳ የሚገኘው የመብራት ሀይል ህንፃ የንግድ ቤት ኪራይ ጨረታ በካሬ 19ሺ ብር መቅረቡ ተሰማበአዲስ አበባ ፒያሳ የሚገኘው የመብራት ሀይል ህንፃ ለንግድ ቤቶች ኪራይ ጨረታ መቅረቡን ...
24/08/2024

#ዜና
ፒያሳ የሚገኘው የመብራት ሀይል ህንፃ የንግድ ቤት ኪራይ ጨረታ በካሬ 19ሺ ብር መቅረቡ ተሰማ

በአዲስ አበባ ፒያሳ የሚገኘው የመብራት ሀይል ህንፃ ለንግድ ቤቶች ኪራይ ጨረታ መቅረቡን ተከትሎ በካሬ 19ሺ ብር እየተጫረተ መሆኑን የወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ፡፡

ይህ የብር ተመን የቀረበው 40 ካሬ ላለዉ ምድር ላይ ለሚገኘው የንግድ ቤት ሲሆን አሸናፊው ቫት እና የጋራ ወለል ኪራይን ሳይጨምር በወር 760 ሺህ ብር ይከፍላልም ተብሏል ።

Address

Togo Avenue
Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Zena posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Zena:

Share