08/08/2026
ሳውዲ አረቢያ፣ ቱርክ እና ፓኪስታን አዲስ ወታደራዊ ስምምነት በማድረግ የጋራ ቡድን ፈጠሩ ❗️
የመካ የጋራ መከላከያ ስምምነት በሳውዲ አረቢያ፣ ቱርክ እና ፓኪስታን መካከል መፈረሙ በመካከለኛው ምስራቅ አዲስ ጂኦፖለቲካዊ ሚዛን እየፈጠረ ነው።
ትላንት በ3ቱ ሀገራት መካከል የተፈረመው ይህ ስምምነት “በአንዱ ላይ የተሰነዘረ ጥቃት በሁሉም ላይ እንደተሰነዘረ ይቆጠራል” የሚል መርህ ይዟል።
በእስራኤል እና በኢራን መካከል ካለው ከፍተኛ ውጥረት አንፃር፣ ስምምነቱ ቀጣናዊ ስጋቶችን ለመግታት ያለመ ነው።
ሆኖም ተንታኞች እንደሚሉት፣ በሶስቱ ሀገራት ውስጥ ያሉ የውስጥ ምጣኔ ሀብት እና የጸጥታ ቀውሶች የስምምነቱን ተግባራዊነት ሊገድቡት ይችላሉ።
ሳውዲ አረቢያ በፋይናንስ፣ ቱርክ በታጠቁ ድሮኖች፣ እና ፓኪስታን በኑክሌር አቅሟ ጥምረቱን ያጠናክራሉ።
ስምምነቱ አዲስ የጦርነት ቀጠና ከመፍጠር ይልቅ፣ እንደ ዲፕሎማሲያዊ መከላከያ ጋሻ ሆኖ ያገለግላል ተብሎ ይጠበቃል።
Addis Zena