01/03/2026
እስራኤል እና ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ ጥቃት ከጀመሩ በኋላ፤ ሦስት የአሜሪካ ወታደሮች መገደላቸውን እና አምስት በጽኑ መጎዳታቸውን ፔንታጎን አስታወቀ። አሜሪካ ትላንት ቅዳሜ በተጀመረው ጦርነት ወታደሮቿ መገደላቸውን እና መቁሰላቸውን ይፋ ስታደርግ የመጀመሪያው ነው።
ፔንታጎን ተብሎ የሚታወቀው የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ወታደሮቹ የተገደሉት እና የተጎዱት “በዘመቻ ኤፒክ ፉሪ” በመሳተፍ ላይ ሳሉ እንደሆነ ዛሬ እሁድ ገልጿል። ሌሎች በርካታ ወታደሮች አነስተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ያስታወቀው የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስቴር ከፍተኛ ውጊያ እንደቀጠለ መሆኑን ገልጿል።
ይሁንና የአሜሪካ ወታደሮች የተገደሉበትን እና የተጎዱበትን ሁኔታ በዝርዝር ከመግለጽ ተቆጥቧል። የኢራን አብዮታዊ ዘብ “ከፍተኛ” ጥቃት እንደሚፈጽም ያሳወቀ ሲሆን በሪያድ፣ ዱባይ፣ አቡ ዳቢ፣ ዶሐ፣ ማናማ እና እየሩሳሌም ፍንዳታዎች ተሰምተዋል።
የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ሀገራቸው ከእስራኤል ጋር በጥምረት በምታካሒደው ድብደባ 48 የኢራን አመራሮች መገደላቸውን አስታውቀዋል። “እያገኘን ያለውን ስኬት ማንም ማመን አይችልም” ሲሉ ትራምፕ ፎክስ የተባለው የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል።
https://www.reuters.com/world/us/trump-says-48-leaders-killed-strikes-iran-fox-news-interview-2026-03-01/
via
ዘጋቢ - #ንጉሤ የኔአባት