AGMAS MEDIA

AGMAS MEDIA Art, Information & Entertainment

ቻይና የምድርን ሽክርክሪት በማዘግየት ቀኑን አስረዘመች። (ናሳ) የሳይንስ ሊቃውንት ስሌት እንደሚያሳየው እጅግ በጣም ብዙ ውሃ የፕላኔቷን የጅምላ ስርጭት በመቀየር የኢነርሺያ ጊዜዋን ጨምሯል።...
04/05/2025

ቻይና የምድርን ሽክርክሪት በማዘግየት ቀኑን አስረዘመች። (ናሳ)

የሳይንስ ሊቃውንት ስሌት እንደሚያሳየው እጅግ በጣም ብዙ ውሃ የፕላኔቷን የጅምላ ስርጭት በመቀየር የኢነርሺያ ጊዜዋን ጨምሯል።

በዚህም ምክንያት ቀኑ በ0.06 ማይክሮ ሰከንድ የረዘመ ሲሆን የምድር ዘንግ በ2 ሴንቲ ሜትር አካባቢ ተቀይሯል።

******
አግማስ ሚዲያን ይቀላቀሉ።

"China alters flow of time with Three Gorges Dam | RBC-Ukraine"

Read more

 #ሰበር ዜናፖፕ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።**********  (አግማስ ሚዲያ) የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡...
21/04/2025

#ሰበር ዜና
ፖፕ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።
**********
(አግማስ ሚዲያ)
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡

ሊቀ ጳጳሱ ባደረባቸው ከፍተኛ የሳንባ ሕመም የሕክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ቆይተው በዛሬው ዕለት በመኖሪያ ቤታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን ቫቲካን አስታውቃለች፡፡

"Pope Francis, groundbreaking Jesuit pontiff, dies aged 88 | Pope Francis | The Guardian" https://www.theguardian.com/world/2025/apr/21/pope-francis-dies
ምንጭ፦ ዘጋርድያን

#በንጉሤ የኔአባት

Death of 267th head of Catholic church triggers period of global mourning and Vatican conclave of cardinals to elect successor

 #ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው እና ሮቦትን በግማሽ ማራቶን አወዳደረች።(አግማስ ሚዲያ)በቤጂንግ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር ላይ 21 ሮቦቶች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሳትፈዋ...
19/04/2025

#ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው እና ሮቦትን በግማሽ ማራቶን አወዳደረች።

(አግማስ ሚዲያ)

በቤጂንግ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር ላይ 21 ሮቦቶች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሳትፈዋል።

ቲያንግ አልትራ የተሰኘው ሮቦት በ2 ሰዓት ከ40 ደቂቃ በማጠናቀቅ የውድድሩ አሸናፊ ሆኗል።

ሮቦቱን የሰራው የቤጂንግ ፈጠራ ማዕከል ሀላፊ ታንግ ጂያንግ ሮቦቶቹ ሰዎችን አይተው በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲሮጡ የሚያስችል እግር እንደተሰራላቸው ገልፀዋል።

አሸናፊው ሮቦት ውድድሩን እስኪያጠናቅቅ ድረስ ሶስት ጊዜ ባትሪ ተቀይሮለታል።

"ይህ ብዙ ባያኩራራኝም እስከ አሁን ግን በምዕራቡ ዓለም ያልተጀመረ ቴክኖሎጂ ነው" ብለዋል ሀላፊው።

ከሮቦቶቹ ጋር ከተወዳደሩ ወንድ ተወዳዳሪዎች መካከል አሸናፊው ውድድሩን አንድ ሰዓት ከ2 ደቂቃ ውስጥ ማጠናቀቁን ሲኤንኤን ዘግቧል።
https://amp.cnn.com/cnn/2025/04/19/asia/china-first-humanoid-robot-half-marathon-intl-hnk

#ንጉሤ የኔአባት አማረ
መልካም በዓል!

More than 20 two-legged robots competed in the world’s first humanoid half-marathon in China on Saturday, and – though technologically impressive – they were far from outrunning their human masters over the long distance.

https://www.cafonline.com/caf-u-20-africa-cup-of-nations/news/final-draw-for-totalenergies-caf-under-20-africa-cup-of-na...
14/04/2025

https://www.cafonline.com/caf-u-20-africa-cup-of-nations/news/final-draw-for-totalenergies-caf-under-20-africa-cup-of-nations-egypt-2025-to-be-held-on-sundayv/

ከ20 አመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ።

#በግብጽ አዘጋጅነት በሚካሄደው ከ20 አመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ 13 ሀገራት የሚሳተፉበትም ይሆናል።

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) በግብፅ ካይሮ ባወጣው ድልድል ምድብ አንድ ላይ አዘጋጇ ግብጽ ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ዛምቢያ ፣ ሴራሊዮን እና ታንዛኒያ ተደልድለዋል።

ጠንካራ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ በሚጠበቀው ምድብ ሁለት ናይጄሪያ ፣ ቱኒዚያ ፣ ሞሮኮ እና ኬንያ ሲደለደሉ በምድብ ሶስት ደግሞ ሻምፒዮኗ ሴኔጋል ፣ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ ፣ መካከለኛው አፍሪካና እና ጋና ተገናኝተዋል።

ለ25ኛ ጊዜ የሚደረገው ውድድር ሚያዚያ 19 ቀን እንደሚጀመር ካፍ አሳውቋል።

The final draw for the TotalEnergies CAF Under-20 Africa Cup of Nations (AFCON), Egypt 2025 will be conducted on Sunday, 13 April at 17:00 local time (15:00 GMT). The tournament will be staged from 27 April to 18 May, 2025, with Sunday’s draw LIVE from the Egyptian Football Association headquarter...

04/04/2025

የትራምፕ የታሪፍ ጭማሪ ውሳኔ አሜሪካውያን ሸማቾችንም እንደሚጎዳ ተገለጸ።
(አግማስ ሚዲያ መጋቢት 26/2017 ዓ.ም)
ዶናልድ ትራምፕ፣ በውጭ ንግድ ላይ የጣሉት ቀረጥ የዓለም የንግድ ስርዓትን የሚያዛባ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ የትራምፕ የታሪፍ ውሳኔ አሜሪካውያን ሸማቾችን የሚጎዳ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል፡፡


ኢኮኖሚስቶች ለቢቢሲ፤ እንደገለጹት፤ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአሜሪካ ጋር በሚነግዱ የዓለም ሀገራት ላይ በሙሉ ከ10 በመቶ ጀምሮ የጣሉት ቀረጥ የዓለምን የንግድ ስርዓት የሚያዛባ ነው፡፡ የፕሬዚዳንቱን ውሳኔ ተከትሎ ቀረጥ የተጣለባቸው ሀገራትም፣ የራሳቸውን ኢኮኖሚ ለመከላከል በአሜሪካ ላይ ቀረጥ እንዲጥሉ ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡

የዓለም ሀገራት ለትራምፕ ውሳኔ የሚሰጡት ምላሽ መልሶ የሚጎዳው አሜሪካንን ነው ያሉት ባለሙያዎች፤ ይህ አይነቱ ሁኔታ የዓለምን የንግድ ሥርዓት እንደሚያዛባም አስታውቀዋል፡፡ የአሜሪካ ትልቁ አቅም ከሌሎች ጋር መነገድና ራሷን መቻሏ እንደነበር አንስተው፤ አሁን ላይ ግን እንደ ቻይና ያሉት ሀገራት ብሪክስን ይዘው በራሳቸው ገንዘብ ለመነገድ እየወሰኑ ይገኛሉ፡፡ ይህ ደግሞ የሚጎዳው አሜሪካንን ነው ሲሉ አብራርተዋል፡፡

አሜሪካ የአረቢካ ቡናን ጨምሮ አንዳንድ ምርቶችን የግድ ከውጭ ማስገባት እንደሚኖርባት በመጠቆምም፣ የቀረጥ ውሳኔው ደግሞ አሜሪካዊያን ሸማቾችን የሚጎዳ ነው ብለዋል፡፡

የትራምፕ ሀሳብ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የአሜሪካን ኢኮኖሚ እናሳድጋለን ከሚል አመክንዮ የመጣ ነው ያሉት የኢኮኖሚስት ባለሙያዎቹ፤ ይህ ግን አሁን ላይ ጭምር የአሜሪካንን “ስቶክ ማርኬት” እየጎዳው እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡

ምንጭ = ከ BBC & CBS News ድህረ ገጽ

#በንጉሤ #የኔአባት

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።(አግማስ ሚዲያ)ድምፃዊ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ፣ መሰንቆና ዋሽንት ተጫዋች፣ ክራርና በገና ደርዳሪ፣ የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መምህር ...
11/03/2025

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

(አግማስ ሚዲያ)

ድምፃዊ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ፣ መሰንቆና ዋሽንት ተጫዋች፣ ክራርና በገና ደርዳሪ፣ የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መምህር የሆኑት አለማየሁ ፋንታ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ከ1960 ዓ.ም ጀምሮ በያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ውስጥ ከማስተማርም በዘለለ ትምህርት ቤቱ ሲከፈት የባህል ሙዚቃ ትምህርትን ለተማሪዎች እንዲሆን አድርገው ካሪኩለም በማዘጋጀት ከፍተኛ ሚናን ተጫውተዋል።

ውልደትና እድገታቸው በአሁኑ የዋግምራ ዞን ሰቆጣ አካባቢ ሲሆን፣ በልጅነታቸው በድቁና ማዕረግ ቤተክርስቲያንን አገልግለዋል፡፡

ሙዚቃን የጀመሩት በሀገር ፍቅር ቴአትር ሲሆን ከ1950 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር ዓመታት ያህል በክፍሉ ሰርተዋል፡፡ የኢትዮጵያን የባህል ሙዚቃ በመወከል በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በአሜሪካና በእስያ በርካታ ሀገራትንም ተዟዙረዋል።

በእንግሊዝ፣ ስዊድን፣ ኖርዌይ፣ ጀርመን፣ ኦስትሪያና ሌሎችም በርካታ የአውሮፓ ሃገራት የባህል ሙዚቃ አምባሳደርነት ማዕረግን ያገኙ ሲሆን፣ ከዚህም በተጨማሪ በ1968 ዓ.ም ከዳካር የኔግሮ አርትስ ፌስቲቫል ሽልማት ከዩኔስኮ ለሙዚቃ ስራዎቻቸው እውቅና (Recognition by UNESCO
an Analogy of African music (UNESCO collection digital)) ከኮርያ ስፕሪንግ ፍሬንድ ሺፕ አርት ፌስቲቫል ዲፕሎማና የክብር ሜዳሊያና መሰል በርካታ ሽልማቶችንም አግኝተዋል::

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ስርዓተ ቀብራቸው በነገው ዕለት ፒያሳ በሚገኘው በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ በ9 ሰዓት እንደሚፈፀምም ታውቋል።

https://amp.cnn.com/cnn/2023/07/21/china/china-second-superdeep-borehole-intl-hnk ቻይና ከ10 ሺህ ሜትር በላይ ጥልቀት ያለው የጉድጓድ ቁፋሮ ...
25/02/2025

https://amp.cnn.com/cnn/2023/07/21/china/china-second-superdeep-borehole-intl-hnk
ቻይና ከ10 ሺህ ሜትር በላይ ጥልቀት ያለው የጉድጓድ ቁፋሮ አከናወነች።
*****

የቻይና ብሄራዊ ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን በቻይና ሰሜናዊ ምዕራብ በረሃ 10 ሺህ 910 ሜትር ጥልቀት ያለው እና በእስያ አህጉር የመጀመሪያ የሆነውን ጥልቅ ጉድጓድ ፕሮጀክት ቁፋሮ ማጠናቀቁን አስታውቋል።

ጉድጓዱ በአለም ላይ ሁለተኛው ጥልቅ ጉድጓድ ሲሆን እምቅ የነዳጅ እና የጋዝ ሀብቶችን በውስጡ መያዙ ተነግሯል፡፡

ፕሮጀክቱ ሳይንቲስቶች የምድርን ታሪክ፣ የጂኦሎጂካል ዝግመተ ለውጥ እና ጥንታዊ የአየር ንብረት ለውጦችን እንዲረዱ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል ተብሏል።

በዢንጂያንግ ዩጉር ራስ ገዝ ክልል በታሪም ተፋሰስ ውስጥ በታክሊማካን በረሃ እምብርት ውስጥ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት፤ “ሼንዲታኬ 1” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

እንደ ሲኤንፒሲ ዘገባ ከሆነ ቁፋሮው የተጀመረው እ.ኤ.አ ግንቦት 30 ቀን 2023 ሲሆን ቁፋሮውን ለማጠናቀቅ ከ580 ቀናት በላይ ፈጅቷል ተብሏል።

ከእንዲህ ዓይነቱ ተከታታይ ጥረት በኋላ ጉድጓዱ 12 የመሬት ጂኦሎጂካል ንጣፎችን ዘልቆ ገብቶ በመጨረሻም ከ500 ሚሊዮን ዓመታት በላይ የቆዩ የድንጋይ ንብርብሮች ላይ መድረሱ ተገልጿል።

በጥልቁ ጉድጓድ ውስጥ ያሉት ድንጋዮች እና ማዕድናት የምድርን ዝግመተ ለውጥ ለማጥናት ያገለግላሉም ነው የተባለው፡፡

በሩሲያ ሰሜናዊ ምእራብ ክፍል ሙርማንስክ በተባለች ከተማ አቅራቢያ በፈረንጆቹ 1989 ቁፋሮው የተጠናቀቀው ኮላ ሰው ሰራሽ ጉድጓድ 12 ሺህ 262 ሜትር ጥልቀት ያለው ሲሆን፤ በዚህም በዓለም ላይ እጅግ ጥልቅ ጉድጓድ በሚል ቀዳሚ ደረጃን ይዟል፡፡

ዘገባው የሲ ኤን ኤን ነው።
አግማስ ሚዲያ

Chinese engineers on Thursday broke ground on a new super deep borehole that will burrow far into the Earth’s crust as the country steps up its search for natural resources hidden tens of thousands of feet underground.

22/02/2025

የኤርትራ መንግሥት ከ60 አመት በታች ያሉ ዜጎቹ ወደካምፕ እንዲገቡ አዘዘ

| የኤርትራ መንግሥት ያገቡና የልጆች እናት የሆኑ ሴቶችን ጨምሮ እድሜአቸው ከ60 አመት በታች የሆኑ ዜጎቹ እንዲዘመገቡና ወደ ካምፕ እንዲገቡ ትዕዛዝ አስተላለፈ።

ወታደራዊ ግዳጁ ከዚህ በፊት በውትድርና ላይ የነበሩ ዜጎችን የሚጨምር ሲሆን፤ ስልጠናውን የወሰዱ አካላትም በተጠባባቂነት እንዲቆዩ ይደረጋል ተብሏል።

በተጨማሪም ያገቡ እና ልጆች ያሏቸው ሴት ወታደሮች ወደ ቀድሞ ወታደራዊ ክፍላቸው እንዲመለሱ ታዝዘዋል።

በወታደራዊ ግዳጁ መመሪያ መሰረት ዕድሜያቸው ከ50 አመት በታች የሆኑ ግለሰቦች ከሀገር እንዳይወጡ የተከለከሉ ሲሆን፤ ይህም የግዳጅ ምልመላው ጥብቅ መሆኑን የሚያመላክት ነው ተብሏል።

የወታደራዊ ግዳጁን መመሪያ ተከትሎ የእንቅስቃሴ ገደቦች ተጥለዋል።

የክልል አስተዳደሮች ለወታደራዊ ግዳጅ የሚመለምሏቸውን ዜጎች የማሰባሰብ፣ የመመዝገብ እና የማሳወቅ ስራ መጀመራቸውንም ዘገባዎች አመላክተዋል።

ለወታደራዊ ግዳጅ ምልመላው ድንገተኛ እና ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ቅስቀሳ እየተደረገ ሲሆን፤ ይህም በኤርትራ ህዝብ ዘንድ ድንጋጤ ፈጥሯል።

የኤርትራ መንግሥት ለሌላ ዙር የትጥቅ ግጭት እየተዘጋጀ ነው የሚል ስጋትም እየጨመረ መምጣቱ ተጠቅሷል።

ቀደም ሲል ከወታደራዊ አገልግሎት በተለያየ ምክንያት የወጡትን ጨምሮ የሲቪል ዜጎችን በግዳጅ መልሶ ማሰባሰብ የመንግስትን የማያቋርጥ ወታደራዊ ፖሊሲ እና መሰረታዊ የሰብአዊ መብቶችን ችላ ባይነት እንደሚያሳይ በውጭ የሚገኙ የኤርትራ ሕዝብ ተቆርቋሪ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

ውብሸት ሰንደቁ

አሜሪካ ያወጣችውን ወጭ ዩክሬን ከማዕድኗ እንድትከፍላት የድርድር ጥያቄ አቀረበችከ400 እስከ 500 ቢሊዮን ዶላር ከዩክሬን እንፈልጋለን:- ፕሬዝዳንት ትራምፕ*********************...
22/02/2025

አሜሪካ ያወጣችውን ወጭ ዩክሬን ከማዕድኗ እንድትከፍላት የድርድር ጥያቄ አቀረበች

ከ400 እስከ 500 ቢሊዮን ዶላር ከዩክሬን እንፈልጋለን:- ፕሬዝዳንት ትራምፕ
***********************

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ላወጣነው ወጭ ዩክሬን ከውድ ማዕድኗ እድታካፍለን ማለታቸውን ተከትሉ የትኩረት አቅጣጫ ሆኗል::

አሁን ደግሞ የዋይት ሀውስ የብሄራዊ ደኅንነት አማካሪ ባለስልጣን የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪን ከአሜሪካ ጋር በማዕድን ውል ዙሪያ ወደ ድርድር እንዲመለሱ ጠይቀዋል ሲል አልጀዚራ ዘግቧል።

አማካሪው ማይክ ዋልትስ በጋዜጣዊ መግለጫቸው ላይ " ወደ ጠረጴዛው በመመለስ መመካከር ያስፈልገናል ወደ ጠረጴዛው አለመምጣት እኛ ያቀረብነውን ይህንን እድል ለመጠቀም ፈቃደኛ አለመሆን ነው" ሲሉም ተደምጠዋል::

አማካሪው "ለዩክሬናውያን በእውነት የማይታመን እና ታሪካዊ እድል አቅርበናል ይህ ዘላቂ የደኅንነት ዋስትና ነው" ሲሉም አክለዋል።

ይህን መሰሉን ጥያቄ ፕሬዝዳንት ዘለንስኪ ሉአላዊነትን አሳልፎ መስጠት ነው በማለት “ግዛታችንን መሸጥ አልችልም” ማለታቸው ይታወሳል::

ይህንንም ተከትሎ ታዲያ የአሜሪካው ተወካይ ኬሎግ ወደ ዩክሬን አቅንተው ከፕሬዝዳንቱ ጋር ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱም እንደ ደኅንነት እና ኢንቨስትመንት ባሉ ጉዳዮች ላይ ከአሜሪካ ጋር ሊደረጉ ስለሚችሉ ስምምነቶች ዝርዝር ውይይት እንዳደረጉ ዜለንስኪ ተናግረዋል።

ዜለንስኪ ከኬሎግ ጋር ካደረጉት ውይይት በኋላ ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር “የኢንቨስትመንት እና የደኅንነት ስምምነት” ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ታዲያ ይህ የአሜሪካ ቅፅበታዊ የአቋም ለውጥ የዩክሬን ደጋፊ የሆኑ የአውሮፓ ባለስልጣናትንም አስደንግጧል።

እናም ዩክሬን አጣብቂኝ ውስጥ ከሆነች ሩስያን የሚደግፍ ስምምነት ውስጥ ልትገባ ትችላለች የሚል ስጋትን ፈጥሮባቸዋል::

በሴራን ታደሰ

በሀማስ እና እስራኤል መካከል ያለውን ልዩነት ለማጥበብ የቀረበውን “የማቀራረብያ ሀሳብ” እስራኤል መቀበሏን ገለጸች።የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚንስትር ቤንያ...
20/08/2024

በሀማስ እና እስራኤል መካከል ያለውን ልዩነት ለማጥበብ የቀረበውን “የማቀራረብያ ሀሳብ” እስራኤል መቀበሏን ገለጸች።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚንስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ጋር መክረዋል።
"Blinken says Israel has agreed to US proposal to close remaining gaps on ceasefire deal and calls on Hamas to do the same | CNN"

US Secretary of State Antony Blinken said Monday that Israel has accepted a proposal to bridge gaps in ceasefire negotiations and the next step is for Hamas to accept ahead of further negotiations expected to take place later this week.

Tadesse Mesfin's artwork
29/02/2024

Tadesse Mesfin's artwork

Address

Asmara Road
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AGMAS MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AGMAS MEDIA:

Share