AGMAS MEDIA

AGMAS MEDIA Art, Information & Entertainment

05/08/2025

በሬክተር 5.4 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ በኢራን መከሰቱ ተዘገበ።

ዛሬ ማለዳ ላይ የ5.4 መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ በደቡብ ምስራቅ ኢራን ተከሰተ፡፡

የአሜሪካ የጂኦሎጂካል ሰርቬይ እንደገለጸው የመሬት መንቀጥቀጡ የተከሰተው በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር በ08፡36 ሲሆን፤ ጥልቀቱ በግምት 56.7 ኪ.ሜ (35.2 ማይል) ነው።

እስካሁን የመሬት መንቀጥቀጡ ስላደረሰው ጉዳት ከሀገሪቱ ባለስልጣናት የተሰጠ ማብራሪያ የለም።

ኢራን በሴስሚክ እንቅስቃሴ ባለበት ክልል ውስጥ የምትገኝ ሲሆን፤ በቅርብ ዓመታት ውስጥ ብዙ አውዳሚ የመሬት መንቀጥቀጦችን ማስተናገዷ ይታወሳል።

በአገሪቱ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ውስጥ እጅግ አሳዛኙ የመሬት መንቀጥቀጥ የተከሰተው በ2013 ነበር፡፡

በወቅቱም የ6.7 መጠን ያለው የመሬት መንቀጥቀጥ የባም ከተማን በመምታት ቢያንስ የ34 ሺህ ሰዎችን ህይወት አጥፍቷል ሲል ያስታወሰዉ አናዶሉ ኤጀንሲ ነዉ።


3,000 ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ ማር በግብፅ የቀብር ስፍራዎች ተገኝቷል።✔️ማሩ አሁንም ጣፋጭነቱ የሚያስደምም ነው ተብሎለታል።✔️የንብ ማር ልዩ ባህሪያት በድጋሚ በአስደናቂ ሁኔታ ተረጋግጧል ...
03/08/2025

3,000 ዓመት ዕድሜ ያስቆጠረ ማር በግብፅ የቀብር ስፍራዎች ተገኝቷል።

✔️ማሩ አሁንም ጣፋጭነቱ የሚያስደምም ነው ተብሎለታል።

✔️የንብ ማር ልዩ ባህሪያት በድጋሚ በአስደናቂ ሁኔታ ተረጋግጧል የተባለ ሲሆን በግብፅ በሚገኙ ጥንታዊ የቀብር ስፍራዎች ውስጥ ለ3,000 ዓመታት ያህል የተቀመጠ ማር አሁንም ሳይበላሽ መገኘቱ የሳይንስ ሊቃውንትን አስገርሟል።

✔️የማር ረጅም ዕድሜ ምስጢር በኬሚካላዊ ቅንብሩ ውስጥ ይገኛል ተብሏል።

✔️ማር የውሃ መጠን በጣም ዝቅተኛ ሲሆን፣ ከፍተኛ የስኳር ይዘት ያለው እና አሲዳማ በመሆኑ ባክቴሪያዎች እና ረቂቅ ተህዋሲያን እንዲያድጉበት አይፈቅድም ተብሏል።

✔️ይህ ተፈጥሯዊ ሂደት ማሩን ለረጅም ጊዜ እንዲቆይ የሚያደርግ እንደ መከላከያ (preservative) ያገለግላል ተብሎለታል።

✔️ምንም እንኳን "ማር አይበላሽም" የሚለው አባባል የተለመደ ቢሆንም፣ የሳይንስ ሊቃውንት ይህን ያህል ረጅም ዕድሜ እንዲኖረው የረዳው በግብፅ የቀብር ስፍራዎች ውስጥ የነበረው ደረቅና ከውጭ ተጽእኖ የፀዳ አየር አስተዋጽኦ እንዳለው ይገልጻሉ። ይህ ሁኔታ የማሩን ጥራት ለመጠበቅ ወሳኝ ነበር ተብሎለታል።

✔️ይህ ግኝት የማርን ልዩ ተፈጥሮ ከማሳየቱም በላይ፣ የጥንት ግብፃውያን ለሕይወት አስፈላጊ የሆኑ ቁሳቁሶችን ለዘለቄታው ለማስቀመጥ የነበራቸውን ጥልቅ ግንዛቤ የሚያሳይ ነው ተብሏል።

✔️ይህ ጥንታዊ ማር ለምግብነት ሊውል ቢችልም፣ በታሪክና በሳይንስ ምርምር ረገድ ያለው ጠቀሜታ ከጣዕሙ በላይ የላቀ ነው ተብሏል።

#በንጉሤ የኔአባት

"3000 year old honey found in Egypt"

3000 year old honey found in ancient Egypt in Tutankhomon's tomb struck the imagination of archaeologists and turned out to be edible

03/08/2025
ቻይና የምድርን ሽክርክሪት በማዘግየት ቀኑን አስረዘመች። (ናሳ) የሳይንስ ሊቃውንት ስሌት እንደሚያሳየው እጅግ በጣም ብዙ ውሃ የፕላኔቷን የጅምላ ስርጭት በመቀየር የኢነርሺያ ጊዜዋን ጨምሯል።...
04/05/2025

ቻይና የምድርን ሽክርክሪት በማዘግየት ቀኑን አስረዘመች። (ናሳ)

የሳይንስ ሊቃውንት ስሌት እንደሚያሳየው እጅግ በጣም ብዙ ውሃ የፕላኔቷን የጅምላ ስርጭት በመቀየር የኢነርሺያ ጊዜዋን ጨምሯል።

በዚህም ምክንያት ቀኑ በ0.06 ማይክሮ ሰከንድ የረዘመ ሲሆን የምድር ዘንግ በ2 ሴንቲ ሜትር አካባቢ ተቀይሯል።

******
አግማስ ሚዲያን ይቀላቀሉ።

"China alters flow of time with Three Gorges Dam | RBC-Ukraine"

Read more

 #ሰበር ዜናፖፕ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።**********  (አግማስ ሚዲያ) የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡...
21/04/2025

#ሰበር ዜና
ፖፕ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።
**********
(አግማስ ሚዲያ)
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡

ሊቀ ጳጳሱ ባደረባቸው ከፍተኛ የሳንባ ሕመም የሕክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ቆይተው በዛሬው ዕለት በመኖሪያ ቤታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን ቫቲካን አስታውቃለች፡፡

"Pope Francis, groundbreaking Jesuit pontiff, dies aged 88 | Pope Francis | The Guardian" https://www.theguardian.com/world/2025/apr/21/pope-francis-dies
ምንጭ፦ ዘጋርድያን

#በንጉሤ የኔአባት

Death of 267th head of Catholic church triggers period of global mourning and Vatican conclave of cardinals to elect successor

 #ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው እና ሮቦትን በግማሽ ማራቶን አወዳደረች።(አግማስ ሚዲያ)በቤጂንግ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር ላይ 21 ሮቦቶች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሳትፈዋ...
19/04/2025

#ቻይና ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው እና ሮቦትን በግማሽ ማራቶን አወዳደረች።

(አግማስ ሚዲያ)

በቤጂንግ በተካሄደው የግማሽ ማራቶን የሩጫ ውድድር ላይ 21 ሮቦቶች እና በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተሳትፈዋል።

ቲያንግ አልትራ የተሰኘው ሮቦት በ2 ሰዓት ከ40 ደቂቃ በማጠናቀቅ የውድድሩ አሸናፊ ሆኗል።

ሮቦቱን የሰራው የቤጂንግ ፈጠራ ማዕከል ሀላፊ ታንግ ጂያንግ ሮቦቶቹ ሰዎችን አይተው በተመሳሳይ ሁኔታ እንዲሮጡ የሚያስችል እግር እንደተሰራላቸው ገልፀዋል።

አሸናፊው ሮቦት ውድድሩን እስኪያጠናቅቅ ድረስ ሶስት ጊዜ ባትሪ ተቀይሮለታል።

"ይህ ብዙ ባያኩራራኝም እስከ አሁን ግን በምዕራቡ ዓለም ያልተጀመረ ቴክኖሎጂ ነው" ብለዋል ሀላፊው።

ከሮቦቶቹ ጋር ከተወዳደሩ ወንድ ተወዳዳሪዎች መካከል አሸናፊው ውድድሩን አንድ ሰዓት ከ2 ደቂቃ ውስጥ ማጠናቀቁን ሲኤንኤን ዘግቧል።
https://amp.cnn.com/cnn/2025/04/19/asia/china-first-humanoid-robot-half-marathon-intl-hnk

#ንጉሤ የኔአባት አማረ
መልካም በዓል!

More than 20 two-legged robots competed in the world’s first humanoid half-marathon in China on Saturday, and – though technologically impressive – they were far from outrunning their human masters over the long distance.

https://www.cafonline.com/caf-u-20-africa-cup-of-nations/news/final-draw-for-totalenergies-caf-under-20-africa-cup-of-na...
14/04/2025

https://www.cafonline.com/caf-u-20-africa-cup-of-nations/news/final-draw-for-totalenergies-caf-under-20-africa-cup-of-nations-egypt-2025-to-be-held-on-sundayv/

ከ20 አመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ድልድል ይፋ ሆነ።

#በግብጽ አዘጋጅነት በሚካሄደው ከ20 አመት በታች የአፍሪካ ዋንጫ 13 ሀገራት የሚሳተፉበትም ይሆናል።

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌደሬሽን (ካፍ) በግብፅ ካይሮ ባወጣው ድልድል ምድብ አንድ ላይ አዘጋጇ ግብጽ ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ዛምቢያ ፣ ሴራሊዮን እና ታንዛኒያ ተደልድለዋል።

ጠንካራ ፉክክር ይደረግበታል ተብሎ በሚጠበቀው ምድብ ሁለት ናይጄሪያ ፣ ቱኒዚያ ፣ ሞሮኮ እና ኬንያ ሲደለደሉ በምድብ ሶስት ደግሞ ሻምፒዮኗ ሴኔጋል ፣ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ሪፐብሊክ ፣ መካከለኛው አፍሪካና እና ጋና ተገናኝተዋል።

ለ25ኛ ጊዜ የሚደረገው ውድድር ሚያዚያ 19 ቀን እንደሚጀመር ካፍ አሳውቋል።

The final draw for the TotalEnergies CAF Under-20 Africa Cup of Nations (AFCON), Egypt 2025 will be conducted on Sunday, 13 April at 17:00 local time (15:00 GMT). The tournament will be staged from 27 April to 18 May, 2025, with Sunday’s draw LIVE from the Egyptian Football Association headquarter...

04/04/2025

የትራምፕ የታሪፍ ጭማሪ ውሳኔ አሜሪካውያን ሸማቾችንም እንደሚጎዳ ተገለጸ።
(አግማስ ሚዲያ መጋቢት 26/2017 ዓ.ም)
ዶናልድ ትራምፕ፣ በውጭ ንግድ ላይ የጣሉት ቀረጥ የዓለም የንግድ ስርዓትን የሚያዛባ መሆኑን የምጣኔ ሀብት ባለሙያዎች እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ የትራምፕ የታሪፍ ውሳኔ አሜሪካውያን ሸማቾችን የሚጎዳ መሆኑንም አክለው ገልጸዋል፡፡


ኢኮኖሚስቶች ለቢቢሲ፤ እንደገለጹት፤ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከአሜሪካ ጋር በሚነግዱ የዓለም ሀገራት ላይ በሙሉ ከ10 በመቶ ጀምሮ የጣሉት ቀረጥ የዓለምን የንግድ ስርዓት የሚያዛባ ነው፡፡ የፕሬዚዳንቱን ውሳኔ ተከትሎ ቀረጥ የተጣለባቸው ሀገራትም፣ የራሳቸውን ኢኮኖሚ ለመከላከል በአሜሪካ ላይ ቀረጥ እንዲጥሉ ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡

የዓለም ሀገራት ለትራምፕ ውሳኔ የሚሰጡት ምላሽ መልሶ የሚጎዳው አሜሪካንን ነው ያሉት ባለሙያዎች፤ ይህ አይነቱ ሁኔታ የዓለምን የንግድ ሥርዓት እንደሚያዛባም አስታውቀዋል፡፡ የአሜሪካ ትልቁ አቅም ከሌሎች ጋር መነገድና ራሷን መቻሏ እንደነበር አንስተው፤ አሁን ላይ ግን እንደ ቻይና ያሉት ሀገራት ብሪክስን ይዘው በራሳቸው ገንዘብ ለመነገድ እየወሰኑ ይገኛሉ፡፡ ይህ ደግሞ የሚጎዳው አሜሪካንን ነው ሲሉ አብራርተዋል፡፡

አሜሪካ የአረቢካ ቡናን ጨምሮ አንዳንድ ምርቶችን የግድ ከውጭ ማስገባት እንደሚኖርባት በመጠቆምም፣ የቀረጥ ውሳኔው ደግሞ አሜሪካዊያን ሸማቾችን የሚጎዳ ነው ብለዋል፡፡

የትራምፕ ሀሳብ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በማምረት የአሜሪካን ኢኮኖሚ እናሳድጋለን ከሚል አመክንዮ የመጣ ነው ያሉት የኢኮኖሚስት ባለሙያዎቹ፤ ይህ ግን አሁን ላይ ጭምር የአሜሪካንን “ስቶክ ማርኬት” እየጎዳው እንደሚገኝ አመላክተዋል፡፡

ምንጭ = ከ BBC & CBS News ድህረ ገጽ

#በንጉሤ #የኔአባት

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።(አግማስ ሚዲያ)ድምፃዊ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ፣ መሰንቆና ዋሽንት ተጫዋች፣ ክራርና በገና ደርዳሪ፣ የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መምህር ...
11/03/2025

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

(አግማስ ሚዲያ)

ድምፃዊ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ፣ መሰንቆና ዋሽንት ተጫዋች፣ ክራርና በገና ደርዳሪ፣ የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መምህር የሆኑት አለማየሁ ፋንታ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ከ1960 ዓ.ም ጀምሮ በያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት ውስጥ ከማስተማርም በዘለለ ትምህርት ቤቱ ሲከፈት የባህል ሙዚቃ ትምህርትን ለተማሪዎች እንዲሆን አድርገው ካሪኩለም በማዘጋጀት ከፍተኛ ሚናን ተጫውተዋል።

ውልደትና እድገታቸው በአሁኑ የዋግምራ ዞን ሰቆጣ አካባቢ ሲሆን፣ በልጅነታቸው በድቁና ማዕረግ ቤተክርስቲያንን አገልግለዋል፡፡

ሙዚቃን የጀመሩት በሀገር ፍቅር ቴአትር ሲሆን ከ1950 ዓ.ም ጀምሮ ለአስር ዓመታት ያህል በክፍሉ ሰርተዋል፡፡ የኢትዮጵያን የባህል ሙዚቃ በመወከል በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በአሜሪካና በእስያ በርካታ ሀገራትንም ተዟዙረዋል።

በእንግሊዝ፣ ስዊድን፣ ኖርዌይ፣ ጀርመን፣ ኦስትሪያና ሌሎችም በርካታ የአውሮፓ ሃገራት የባህል ሙዚቃ አምባሳደርነት ማዕረግን ያገኙ ሲሆን፣ ከዚህም በተጨማሪ በ1968 ዓ.ም ከዳካር የኔግሮ አርትስ ፌስቲቫል ሽልማት ከዩኔስኮ ለሙዚቃ ስራዎቻቸው እውቅና (Recognition by UNESCO
an Analogy of African music (UNESCO collection digital)) ከኮርያ ስፕሪንግ ፍሬንድ ሺፕ አርት ፌስቲቫል ዲፕሎማና የክብር ሜዳሊያና መሰል በርካታ ሽልማቶችንም አግኝተዋል::

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትናንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ስርዓተ ቀብራቸው በነገው ዕለት ፒያሳ በሚገኘው በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ በ9 ሰዓት እንደሚፈፀምም ታውቋል።

https://amp.cnn.com/cnn/2023/07/21/china/china-second-superdeep-borehole-intl-hnk ቻይና ከ10 ሺህ ሜትር በላይ ጥልቀት ያለው የጉድጓድ ቁፋሮ ...
25/02/2025

https://amp.cnn.com/cnn/2023/07/21/china/china-second-superdeep-borehole-intl-hnk
ቻይና ከ10 ሺህ ሜትር በላይ ጥልቀት ያለው የጉድጓድ ቁፋሮ አከናወነች።
*****

የቻይና ብሄራዊ ፔትሮሊየም ኮርፖሬሽን በቻይና ሰሜናዊ ምዕራብ በረሃ 10 ሺህ 910 ሜትር ጥልቀት ያለው እና በእስያ አህጉር የመጀመሪያ የሆነውን ጥልቅ ጉድጓድ ፕሮጀክት ቁፋሮ ማጠናቀቁን አስታውቋል።

ጉድጓዱ በአለም ላይ ሁለተኛው ጥልቅ ጉድጓድ ሲሆን እምቅ የነዳጅ እና የጋዝ ሀብቶችን በውስጡ መያዙ ተነግሯል፡፡

ፕሮጀክቱ ሳይንቲስቶች የምድርን ታሪክ፣ የጂኦሎጂካል ዝግመተ ለውጥ እና ጥንታዊ የአየር ንብረት ለውጦችን እንዲረዱ በማድረግ ረገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል ተብሏል።

በዢንጂያንግ ዩጉር ራስ ገዝ ክልል በታሪም ተፋሰስ ውስጥ በታክሊማካን በረሃ እምብርት ውስጥ የሚገኘው ይህ ፕሮጀክት፤ “ሼንዲታኬ 1” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

እንደ ሲኤንፒሲ ዘገባ ከሆነ ቁፋሮው የተጀመረው እ.ኤ.አ ግንቦት 30 ቀን 2023 ሲሆን ቁፋሮውን ለማጠናቀቅ ከ580 ቀናት በላይ ፈጅቷል ተብሏል።

ከእንዲህ ዓይነቱ ተከታታይ ጥረት በኋላ ጉድጓዱ 12 የመሬት ጂኦሎጂካል ንጣፎችን ዘልቆ ገብቶ በመጨረሻም ከ500 ሚሊዮን ዓመታት በላይ የቆዩ የድንጋይ ንብርብሮች ላይ መድረሱ ተገልጿል።

በጥልቁ ጉድጓድ ውስጥ ያሉት ድንጋዮች እና ማዕድናት የምድርን ዝግመተ ለውጥ ለማጥናት ያገለግላሉም ነው የተባለው፡፡

በሩሲያ ሰሜናዊ ምእራብ ክፍል ሙርማንስክ በተባለች ከተማ አቅራቢያ በፈረንጆቹ 1989 ቁፋሮው የተጠናቀቀው ኮላ ሰው ሰራሽ ጉድጓድ 12 ሺህ 262 ሜትር ጥልቀት ያለው ሲሆን፤ በዚህም በዓለም ላይ እጅግ ጥልቅ ጉድጓድ በሚል ቀዳሚ ደረጃን ይዟል፡፡

ዘገባው የሲ ኤን ኤን ነው።
አግማስ ሚዲያ

Chinese engineers on Thursday broke ground on a new super deep borehole that will burrow far into the Earth’s crust as the country steps up its search for natural resources hidden tens of thousands of feet underground.

22/02/2025

የኤርትራ መንግሥት ከ60 አመት በታች ያሉ ዜጎቹ ወደካምፕ እንዲገቡ አዘዘ

| የኤርትራ መንግሥት ያገቡና የልጆች እናት የሆኑ ሴቶችን ጨምሮ እድሜአቸው ከ60 አመት በታች የሆኑ ዜጎቹ እንዲዘመገቡና ወደ ካምፕ እንዲገቡ ትዕዛዝ አስተላለፈ።

ወታደራዊ ግዳጁ ከዚህ በፊት በውትድርና ላይ የነበሩ ዜጎችን የሚጨምር ሲሆን፤ ስልጠናውን የወሰዱ አካላትም በተጠባባቂነት እንዲቆዩ ይደረጋል ተብሏል።

በተጨማሪም ያገቡ እና ልጆች ያሏቸው ሴት ወታደሮች ወደ ቀድሞ ወታደራዊ ክፍላቸው እንዲመለሱ ታዝዘዋል።

በወታደራዊ ግዳጁ መመሪያ መሰረት ዕድሜያቸው ከ50 አመት በታች የሆኑ ግለሰቦች ከሀገር እንዳይወጡ የተከለከሉ ሲሆን፤ ይህም የግዳጅ ምልመላው ጥብቅ መሆኑን የሚያመላክት ነው ተብሏል።

የወታደራዊ ግዳጁን መመሪያ ተከትሎ የእንቅስቃሴ ገደቦች ተጥለዋል።

የክልል አስተዳደሮች ለወታደራዊ ግዳጅ የሚመለምሏቸውን ዜጎች የማሰባሰብ፣ የመመዝገብ እና የማሳወቅ ስራ መጀመራቸውንም ዘገባዎች አመላክተዋል።

ለወታደራዊ ግዳጅ ምልመላው ድንገተኛ እና ከዚህ በፊት ታይቶ የማይታወቅ ቅስቀሳ እየተደረገ ሲሆን፤ ይህም በኤርትራ ህዝብ ዘንድ ድንጋጤ ፈጥሯል።

የኤርትራ መንግሥት ለሌላ ዙር የትጥቅ ግጭት እየተዘጋጀ ነው የሚል ስጋትም እየጨመረ መምጣቱ ተጠቅሷል።

ቀደም ሲል ከወታደራዊ አገልግሎት በተለያየ ምክንያት የወጡትን ጨምሮ የሲቪል ዜጎችን በግዳጅ መልሶ ማሰባሰብ የመንግስትን የማያቋርጥ ወታደራዊ ፖሊሲ እና መሰረታዊ የሰብአዊ መብቶችን ችላ ባይነት እንደሚያሳይ በውጭ የሚገኙ የኤርትራ ሕዝብ ተቆርቋሪ ሚዲያዎች ዘግበዋል።

ውብሸት ሰንደቁ

Address

Asmara Road
Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AGMAS MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AGMAS MEDIA:

Share