Multi Ethnic Shoa

Multi Ethnic Shoa ሸዋ የትልቋ ኢትዮጲያ ማዕከልነቱን እንዳስጠበቀ ኅብረ ብሄራዊ ክልላዊ አስተዳደር ይዋቀራል፡፡

15/11/2025
የጦስኝ የጤና ጥቅም  ከፍተኛ የደም ግፊትን በእጅጉ ይቀንሳል፡- የተለያዩ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ጦስኝ ስብ የጋገሩ የደም ቧንቧዎች በማስፋት ደም ያለምን መጨናነቅ በቱቦዎቹ ውስጥ በቀላሉ እን...
11/11/2025

የጦስኝ የጤና ጥቅም

ከፍተኛ የደም ግፊትን በእጅጉ ይቀንሳል፡- የተለያዩ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ጦስኝ ስብ የጋገሩ የደም ቧንቧዎች በማስፋት ደም ያለምን መጨናነቅ በቱቦዎቹ ውስጥ በቀላሉ እንዲዘዋወር በማድረግ ከፍተኛ የደም ግፊት መቀነሱ ተረጋግጧል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የደም ቅባት መጠን ወይም ኮሌስትሮልንም መቀነሱ ተረጋግጧል፡፡

ሳልን ያስቆማል፡- ጦስኝን ቀቀል ውሃውን መጠጣት ሳልን ጨምሮ አጣዳፊ ብሮንካይተስ የተሰኘውን የመተንፈሻ አካል ሕመም ያስቆማል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በሳል ሳቢያ የሚቆስልን ጉሮሮ ፈውስ ይሰጣል፡፡

የተፈጥሮ የበሽታ የመከላከል አቅማችንን ያጎለብታል፡- ጦስኝ በሽታ ተከላካይ የሆኑትን ጠቃሚ ቫይታሚኖች እንደ ቫይታሚን ሲ፣ ኤ እና ዲ የመሳሰሉትን በመያዙ በማንኛውም ጊዜ ቅጠሉን ቀቅለን እንደ ሻይ ብንጠጣ በቀላሉ ጉንፋን ጨምሮ ሌሎች የመተንፈሻ አካላት በሽታዎችን መከላከል ይቻላል፡፡

ፀረ-ሻጋታ ነው፡- በቀላሉ ሊሻጋቱ የሚችሉ እንጀራን ጨምሮ ማናቸውም ነገሮች ላይ የጦስኝ ቅጠል ብናደርግበት ከመሻገት ይድናል፡፡

ጦስኝ ጸረ- ነፍሳት ነው፡- በቤት ውስጥና ከቤት ውጭ ነፍሳትና ተባዮች ካስቸገራችሁ የጦስኝ ቅጠል ቀቅላችሁ የሚያስቸግራችሁ ቦታ እርጩት፡፡ ውጤቱን በፍጥነት ያዩታል፡፡

ከመልካም ማዕዛው በተጨማሪ ፀረ-ፈንገስና ፀረ-ተህዋሲያን ባህሪ ስላለው በጥርስ ሳሙናና በገላ ሽቶዎች ውስጥ ሳይቀር በቅመምነቱ በዘመናዊ መልኩ ይገባል፡፡

ስሜታችንን (mood) ከፍ ለማድረግ ይረዳል፡- ጦስኝ በውስጡ የያዘው Carvacrol የተሰኘው ንጥረ ነገር የአእምሮችን ሕዋሳትን በማነቃቃት ጥሩ ስሜት እንዲሰማን ያደርጋል፡፡

ጥሩ የምግብ ምንጭ ነው፡- በፈረንሳይና በጣሊያን አገራት እና በአብዛኛው ሜዲትራኒያን አካባቢ እንዲሁም በኛ ሀገርም ጦስኝ የተለያዩ ስጎዎችን ለመስራት ያገለግላል፡፡

ለብጉር ማጥፊያነት ያገለግላል፡- ፀረ-ባክቴሪያ ንጥረነገር ስላለው ከብዙዎቹ ያለሐኪም ትዕዛዝ ከሚሸጡ ዘመናዊ የብጉር ማጥፊያ መድሃኒቶች የተሻለ ነው፡፡ እርጥቡን ጦስኝ ወቅጦ በብጉሩ ላይ ለተወሰነ ሰዓታት በማስቀመጥ መታጠብ ጥሩ ውጤት ያስገኛል።

 #የአጃ የጤና ጠቀሜታዎችአጃ በከፍተኛ ደረጃ በንጥረ ነገር የተሞላና ሀይል ሰጪ ሲሆን በተለያዩ ምግቦች ውስጥ ገብቶ መዘጋጀት ይችላልጥቅሞቹ :✧ የሆድ ድርቀትን ይከላከላል✧ ኮሌስትሮልን ለመ...
03/11/2025

#የአጃ የጤና ጠቀሜታዎች

አጃ በከፍተኛ ደረጃ በንጥረ ነገር የተሞላና ሀይል ሰጪ ሲሆን በተለያዩ ምግቦች ውስጥ ገብቶ መዘጋጀት ይችላል

ጥቅሞቹ :

✧ የሆድ ድርቀትን ይከላከላል

✧ ኮሌስትሮልን ለመቆጣጠር ይረዳል

✧ የደም ስኳር መጠንን ይቀንሳል

✧ በሰውነታችን ውስጥ ያለውን ቆሻሻና ቅባት ያስወግዳል

✧ የፎሊክ አሲድ፣ የታያሚን እና የናያሲን መገኛ በመሆኑ ለጤናማ የፅንስ እድገት ይረዳል

✧ ፎረፎርን ይከላከላል እንዲሁም ፀጉራችን እንዲያድግ ይረዳል

✧ መጥፎ ጠረንን ያስወግዳል (ለምሳሌ፦አንድ ሲኒ አጃ ማቀዝቀዢያ ማሽን ውስጥ ከተቀመጠ መጥፎ ጠረኖችን መጦ እንዲወገድ ይረዳል)

✧ የደረቀ የሰውነት ቆዳን ያለሰልሳል፣ ቆዳችን ወዛማ እንዲሆን በማድረግ ያሳምራል፣ የሚያሳክክ ቆዳን ያክማል

✧ ሰውነት ላይ የሚወጣ አለርጂን ይከላከላል እንዲሁም ያስታግሳል

✧ አጃ በፊታችን ላይ ስንቀባ የሞቱና የተጎዱ ህዋሶች እንዲወገዱ በማድረግ ፊታችን እንዲፈካ ያደርጋል

አጃን በቀላሉ በውሀ ወይም በወተት መመገብ ፣ እንዲሁም ጁስ ውስጥ በመቀላቀል መጠቀም እንችላለን ፣ በተጨማሪም አጃ ዳቦ እና ኩኪስ የመሳሰሉት ውስጥ ገብቶ አብሮ ሊጋገርም ይችላል።

እመጓ መንዝ ዑራኤል፦~~~~~~~~~~~ምድር በንፅዋን ደም ረክሳለችና ቅዱስ ዑራኤል በቀራኒዮ በብርሃን ፅዋ በቀዳው በክርስቶስ ደም ይቀድሳት ዘንድ ይህን ፅዑፍ ያነበበ ሁሉ share share...
31/10/2025

እመጓ መንዝ ዑራኤል፦
~~~~~~~~~~~
ምድር በንፅዋን ደም ረክሳለችና ቅዱስ ዑራኤል በቀራኒዮ በብርሃን ፅዋ በቀዳው በክርስቶስ ደም ይቀድሳት ዘንድ ይህን ፅዑፍ ያነበበ ሁሉ share share ያድርግ ፦
•••
የጌታችን የመዳኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የደሙ ጠብታ ለመጀመሪያ ጊዜ ምድር ላይ ጠብ ያለው መንዝ ዑራኤል ነው ይህም በማይከለ ምድር በቀራኒዮ አደባባይ ስለ ሁላችን ደሙ ሲፈስ በብርሃን ፅዋ ደሙን የቀዳው ቅዱስ ዑራኤል ከቀራኒዮ መሬት አስቀድሞ ደሙን በዓለም ሲረጨው በኢትዮጰያ ምድር ቀድሞ ደሙ በመንዝ ምድር በእመጓ ዑራኤል አረፈ።
•••
መንዝ ማለት መንዛት መርጨት ሲሆን ስያሜው ከቅዱስ ዑራኤል ገቢረ ተአምራት ጋር የተያያዘ ስለሆነ ነው የእግዚአብሔር መላዕክት ምድርን በክርስቶስ ደም ያነፃው በኃላ የረጨበትን የብርሃን ፅዋ በእዚህ ስፍራ ቆጰሮስ በተባለው ስፍራ ተራራውን ሰንጥቆ ፅዋውን ሰውሮታል ።
•••
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በስደቷ ጊዜ በዚህ ቦታ መጥታ ያረፈች ሲሆን እስከዛሬ ድክሟት ያረፈችበት የዲንጋይ መቀመጫ ገሊላ ከሚባለው ተራራ ላይ ተቀምጦ ይገኛል።
•••
ጌታ በሕፃንነቱ ከእናቱ እቅፍ ወርዶ በጠጠር ዲንጋይ የተጫወተባት ቦታ ክፉ ሰው የማይሻገራት ጉድጓድ ቅን ሰው ግን የሚሻገራት ጉድጓድ ተኝተን እልም የምናይበትና ቅዱስ ጊዮርጊስ በፈረስ አምድ ወርዶ የረገጠበት ዘንዶውን የገደለበት የፈረሱ ኮቴ የሚገኝበት ድንቅ ስፍራም ነው።
•••
በነጭ ነብር የሚጠበቅ ፈዋሽ ፀበሉ በቅዱስ ዑራኤል የተቃኙ መነኩሴት ሲገኙ ከእሙአይ ጋር በስልክ የሚያወሩኝ ሲሆን እንድበረታ ታላቅ እናታዊ ምክር የሚሰጡኝ ታላቅ እናትም ይገኛሉ።
•••
የብዙ ስውራን አባቶች መገኛ የኢትዮጰያ የወርቅ ምድር የበረከት ከተማ አርያማዊቷ የመንዝ ዑራኤል በንፁሐን ደም የረከሰችውን ምድራችንን ዳግም ይቀድሳት ዘንድ አምላከ ቅዱስ ዑራኤል ይርዳን።
•••
ካህኑን ከደብሩ ፤ ታቦቱን ከመንበሩ፤ አገርን ከጥፋት ፤ ሕዝቡን ከርሀብ ከጦርነት፤ ይጠብቅልን ።

በያለንበት ቦታ በረከቱ ይድረስ!

ጨለሚት ኪዳነምህረት ገዳም

ሰበር ዜና‼️ጥምር ጦሩ በተጠና ኦፕሬሽን ድል ተቀናጀ=======================================በሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ አይሶፌ ቀበሌ መሽጎ የነበረው የፅን*ፈኛ ቡድን...
27/10/2025

ሰበር ዜና‼️
ጥምር ጦሩ በተጠና ኦፕሬሽን ድል ተቀናጀ
=======================================
በሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ አይሶፌ ቀበሌ መሽጎ የነበረው የፅን*ፈኛ ቡድን በጥምር ጦሩ እርምጃ እንደተወሰደበት የወረዳዉ ኮማንድ ፖስት ገለፀ።

ጥምር ጦሩ ጨለማና ብርዱ ሳይበግረዉ ለሊት 7:00 ሰዓት ላይ ጉዞዉን በመጀመር በካሄደዉ የተጠና ኦፕሬሽን ትጥቆችን ከመማረኩ በዘለለ ጠላትን መደምሰስ ችሏል።

ለሊቱን በተካሄደዉ ኦፕሬሽን የተገኘ ዉጤት :-

👉የተደመሰሰ ፅን*ፈኛ = 06
👉 ሰደፍ ክላሽ = 03
👉ታ /ባለ /አንድ ክላሽ = 01
👉ኤስኬስ = 01
👉የክላሽ መጋዘን =12
👉የደረት ትጥቅ =02
👉የወገብ ትጥቅ =02
👉የድሽቃ ሸንሸል ባለ60= 02
👉የድሽቃ ጥይት =101
👉የክላሽ ጥይት =439
👉ስልክ በተን . =02
👉ተች ስልክ =01 እነዚህን ንብረቶች ጥምር ጦሩ ከፅንፈኛዉ ቡድን የማረከ መሆኑን የወረዳዉ ኮማንድ ፖስት ገልፆል።

ደብረሲና ራማ ቅድስት ኪዳነ ምህረት አንድነት ገዳም ራማ ማለት ከሰባቱ ሰማያት አንዱ ሲሆን ይህ ተራራማ ሃገር የነ ቅዱስ ገብረኤል  ከተማ ነው ። ደብረሲና ራማ ኪዳነ ምህረት ከመድረሳችን በ...
27/10/2025

ደብረሲና ራማ ቅድስት ኪዳነ ምህረት አንድነት ገዳም

ራማ ማለት ከሰባቱ ሰማያት አንዱ ሲሆን ይህ ተራራማ ሃገር የነ ቅዱስ ገብረኤል ከተማ ነው ። ደብረሲና ራማ ኪዳነ ምህረት ከመድረሳችን በፊትም በአጤ ዮሃንስ ዘመነ መንግስት የቅዱስ ገብራኤል ቤተክርስቲያን ተተከለ።

ስሙንም በዙፋኑ ስም ራማ አሉት ። እንግዲህ መዳንን ለወደደ የደብረሲና ራማ ኪዳነ ምህረት መገኛ በወሎ ክፍለ ሃገር በራያ ቆቦ አውራጃ በምስራቅ በኩል ወደ ዞብል ተራራ 25 ኪሜ በመኪና ከተጓዙ በኋላ ለበረታ 2 ሳአት ለደከመ 3 ስአት ይደረሳል።

በ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከውጭ ሃገር ከመጡ ዘጠኙ ቅዱሳት (nine saint) መካከል አባ ጉባ እና አባ ገሪማ የተባሉት ታላላቅ አባቶች እንደገደሙት ገድላቸው ይናገራል።

በ8ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ዮዲት ጉዲት አድባራት እና ገዳማትን ስታጠፋ ገዳሙን አጥፍታው ነበር ። በፈጣሪ ፍቃድ እና በአባቶች ብርታት ገዳሙ ቢያገግምም በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን አህመድ ግራኚ የተረፈውን አውድሞታል።

በ አጤ ሲሲኒዮስ (ጎንደር) ዘመነመንግስት በካቶሊካውያን መስፋፋት ምክኒያት ፍቅርተ ክርስቶስ የምትባል ከጎንደር ፈልሳ መጥታ ይህንን ቦታ በ እግዚያብሔር ፍቅድ እንዳቀናችው እና 12 ዓመታትንም እንደኖረችበት ገድሏ ይናገራል።

ከዛ ጊዜ ጀምሮ የሷ ደቀመዛሙርቶች ዛሬም በዋሻዎቹ ተሰውረው እንደሚኖሩ ገድሏ ይናገራል።

ከዛም በኋላ በብዙ ፈተናዎች የመፍረስ አደጋ ቢጋረጥበትም በአጤ ዮሃንስ ዘመነ መንግስት ራሳቸው ንጉሱ ወደቀደመው ክብሩ እንዲመለስ አድርገዋል። የካቲት 16 እና ነሃሴ 16 የደብረሲና ራማ ኪዳነ ምህረት እንድነት ገዳም ባዓል በድምቀት ይከበራል።

አመት እስከ አመት ያለ ህማማት እና ብዓለ ሃምሳ ውጭ ስዓታት የሚቆምበት ቦታ መንፈስን ያድሳል ነብስን
ያለመልማል።

 ‼️ በሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ አይሶፌ ቀበሌ መሽጎ የነበረው የፅን*ፈኛ ቡድን ከሌሊቱ 7 ሰአት በተሰራ ኦፕሬሽን በጥምር ጦሩ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረስ የተቻለ ሲሆን 6 ፅን #ፈኛ የተደመ ...
27/10/2025

‼️

በሰሜን ሸዋ ዞን ሞጃና ወደራ አይሶፌ ቀበሌ መሽጎ የነበረው የፅን*ፈኛ ቡድን ከሌሊቱ 7 ሰአት በተሰራ ኦፕሬሽን በጥምር ጦሩ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረስ የተቻለ ሲሆን 6 ፅን #ፈኛ የተደመ #ሰሰ ፣ 3 ሰደፍ ክላሽ፣ 1 ታጣፊ ክላሽ ፣1 ኤስኬስ ፣ 12 የክላሽ መጋዘን ፣ 2 የደረት ትጥቅ ፣ 2የወገብ ትጥቅ፣ 2 የድሽቃ ሸንሸል ባለ60፣ 101 የድሽቃ ጥይት ፣ 439 የክላሽ ጥይት ገቢ ተደርጓል።

የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን በደብረ ብርሃን ተከበረ።ደብረ ብርሃን፤ ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ ም (ሰሸዞመኮ) "የማትደፈር ሀገር፤ የማይበገር ሠራዊት" በሚል መሪ ቃል 118ኛው የሀገር መ...
25/10/2025

የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን በደብረ ብርሃን ተከበረ።

ደብረ ብርሃን፤ ጥቅምት 15 ቀን 2018 ዓ ም (ሰሸዞመኮ) "የማትደፈር ሀገር፤ የማይበገር ሠራዊት" በሚል መሪ ቃል 118ኛው የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀን በደብረ ብርሃን ከተማ ተከበረ።

በበዓሉ ላይ የሀገር መከላከያ ሠራዊት የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ዋና አዛዥ ሌቴናል ጄነራል ሹማ አብዴታ፣ የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ፣ የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት፣ የሰሜን ሸዋ ዞን ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኤልያስ አበበን ጨምሮ የሀገር መከላከያ ሠራዊት መኮንኖችና አባላት፣ የአድማ ብተና፣ የፓሊስና ሚሊሻ አባላት፣መንግስት ሠራተኞች፣ የሀይማኖት አባቶችና የከተማ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።

ከሪፎርሙ በኋላ ሀገርን በመጠበቅ ሊናወጥ የማይችል ሀገር ወዳድ ሠራዊት ተገንብቷል ያሉትና በዓሉን በንግግር የከፈቱት የደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል አንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት፤ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ቀንን ስናከብር ዘላቂ ሠላማችንን ለማስከበር በትብብር በመቆም መሆን አለበት ብለዋል።

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ዋና አዛዥ ሌቴናል ጄነራል ሹማ አብዴታ "ብሄራዊ ጥቅሞቻችንን ለማስከበር ሁሌም ዝግጁ ነን" በሚል ርዕስ የመወያያ ሠነድ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።

በዓሉን ስናከብር በተለያዩ ዘመናት ለሀገር መከበር ዋጋ የከፈሉ ቀደምት አባላቶቻችንን በመዘከር ነው ያለው ሰነዱ፤ ሠራዊታችን ተልዕኮዎችን በቡድን የሚፈፅም የህዝብና የሀገር ምሽግ መሆኑን ተጨባጭ ክዋኔዎችን በመጥቀስ አስረድቷል።

የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን በመከላከል ውድ ዋጋ ከፍሎ ወገኖቻችንን የታደግና በመታደግ ላይ ያለ ሠራዊት እንዲሁም በተለያዩ የልማት ሥራዎች በመሳተፍ የልማት አርበኛነቱን በተግባር ያረጋገጠ ሠራዊት መሆኑንም አስምሮበታል።

ሠራዊታችን የድል ባለቤት እንዲሆን ያደረገው ህዝባዊነቱ ነው ያሉት የሰሜን ሸዋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መካሻ አለማየሁ፤ ራሱን ከዘመኑ ጋር በቴክኖሎጂ እያዋሃደ ሀገር የገጠማትን ፈተናዎች ዋጋ ከፍሎ እየፈታ በመሆኑ ሊመሰገን ይገባዋል ብለዋል፡፡

ሠራዊቱ እንደ ሠራዊት የውስጥና የውጭ ጠላቶችን አደብ ከማስገዛት ባለፈ ሀገራዊ የልማት ሥራዎችን በተለያዩ አግባቦች በመደገፍና የሰብዓዊነት ስራዎችንም በመስራት በአርዓያነት የሚጠቀስ ነውም ብለዋል፡፡

ሠራዊቱ ውድ ህይወቱን የሚከፍለው የህዝብንና የሀገርን ዘላቂ ተጠቃሚነት ተስፋ በማድረግ ነው ያሉት ሌቴናል ጄነራል ሹማ አብዴታ፤ አሁን ላይ ከቂምና በቀል ነፃ ወጥተን ሀገርን ሊያሻግር የሚችለውን ሀሳብ ዕውን ለማድረግ በትብብር መስራት ይገባናል፤ ሲሊ አጠናቀዋል፡፡

@መረጃዉ የሰሸዋ መ/ኮ ነዉ።

ብቃትሽ ልዩ ነው አሁን ሰሜን ሸዋ🔥✊
23/10/2025

ብቃትሽ ልዩ ነው አሁን ሰሜን ሸዋ🔥✊

የአቡነ መልከ ጼዲቅ ገዳምሚዳ ወረሞ ወረዳ የብዙ ታሪካዊ ቦታዎችና የታላላቅ ቅርስ ባለቤት ናት፡፡ ከዚህም መካከል የለብቃ ፍል ውሃ ፀበል፣ከዞኑ 3ኛው የቱሪስት መዳረሻ የዋሻ አብነ መልከ ጼዲ...
22/10/2025

የአቡነ መልከ ጼዲቅ ገዳም
ሚዳ ወረሞ ወረዳ የብዙ ታሪካዊ ቦታዎችና የታላላቅ ቅርስ ባለቤት ናት፡፡ ከዚህም መካከል የለብቃ ፍል ውሃ ፀበል፣ከዞኑ 3ኛው የቱሪስት መዳረሻ የዋሻ አብነ መልከ ጼዲቅ አንድነት ገዳም ፣ የጠሃ ሚካኤል ዋሻ ፣ የደንጎሬ የድንጋይ ላይ ቅጠል ፣ ላይ ወረሞ ጊዮርጊስ ፣ የደብረ ነጎድጓድ ቅድስት ስላሴ አንድነት ገዳም እና የካራ ምሽግ የጦር ካምፕ ይገኙበታል፡፡
ውድ የፌስ ቡክ ገፅ ታዳሚዎቻችን የክፍል አንድ ዝግጅታችን የአቡነ መልከ ጼዲቅ ገዳም ታሪክን ገፅታ ይዘን ስንቀርብ በሚቀጥለው ዝግጅታችን የፈዋሹ የለብቃ ፍል ውሃ ፅበል ታሪክን ገፅታ ይዘን እንደምንቀርብ ከወዲሁ ቀጠሮ እየያዝን በቀጣይ ክፍላችን ደግሞ ቀሪዎቹን ታሪካዊ ቦታዎች ይዘን እንደምንቀርብ ከወዲሁ ለመጠቆም እንወዳለን፡፡
መልካም ንባብ!!
በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንደተመሰረተ የሚነገርለት የአቡነ መልከ ጼዲቅ ገዳም በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በሚዳ ወረሞ ውረደ ይገኛል ፡፡
የወረዳው ዋና ከተማ መራኛ ስትሆን ከአዲስ አበባ በስተሰሜን 255ኪ/ሜትር ከአማራ ክልል ርዕሰ መዲና ባህርዳር 785ኪ/ሜትር እንዲሁም ከዞኑ ዋና ከተማ ደ/ብርሃን 191ኪ/ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል ፡፡ ወረዳዋ ብዙ ታርካዊና የቱሪስት መስህቦች የሚገኙባት ስትሆን ከነዚህ ውስጥ አንዱ የሆነው የአቡነ መልከ ጼዲቅ ገዳም ነው ፡፡ገዳሙ ከርእሰ ከተማዋ መራኛ 4ኪ/ሜትር ርቀት ላይ በሶርች አረዳዋዩ ቀበሌ ይገኛል ፡፡ ወደ ገዳሙ ለመድረስ 836 ደረጃዎችን በእግር መጓዝ ቢያስፈልግም ቀሪውን መንገድ በመኪና መጓዝ በመቻሉ ተጎዦች /ጎብኛች/ ምንም አይነት እንግልትና ድካም ሳይደረስባቸው ዘና ብለው በመጓዝ ለመጎብኘትና ታሪካዊ ቦታውን ለማወቅ ያስችላል፡፡ ከገዳሙ አስደናቂ ታሪኮች ውስጥ አንዱና የመጀመሪያው እጅግ ለብዙ አመታት ቆይተው ከአፈር ውስጥ የወጡ የሰው አፅሞች ምንም አይነት የመበስበስ ባህሪ ሳይታይባቸው ወይም ስጋቸው ከመድረቅ ውጪ ከአጥንቱ ጋር ደርቆ ይገኛል፡፡ ይህ ለምን ሆነ ብለን በአካባቢው የሚገኙትን የእምነቱ ተከታዮች መነኮሳትና ቀሳውስት ስንጠይቅ እግዚአብሔር አምላክ ለፃድቁ አባት ለአቡነ መልከ ጼዲቅ የገባላቸው ቃልኪዳን መሆኑን ይጠቁማሉ፡፡ የተገባላቸውም ቃልኪዳን በገዳምህ የደረሰና አፈርህን የረገጠ እስከ 7 ትውልድህ እምርልሃለሁ እንደተባለና በገዳሙ ውስጥ የተቀበረ ትውልድህ ስጋው እንዳማይበሰብስ /እንደሚደርቅ /እንጂ ወደ አፈርነት እንደማይለወጥ እና ስጋውም እንደማይፈራርስ ቃል እንደተገባላቸው ገልፀዋል፡፡ ሌላውና አስደናቂው የእኝህ ፃድቅ አባት አፅም የተቀበረው በዚህ ገዳም አካባቢ መሆኑ ቦታውን የበለጠ ታሪካዊነቱ እንዲጎላ ከማድረጉም በተጨማሪ የገዳሙ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥና እድሜ ጠገብ የተለያዩ አይነት ዛፎች የበለጠ አማላይና ልብ ሰቃይ ያደርጉታል ፡፡በዚህ አካባቢ አንድ አርሶ አደር ሲንቀሳቀስ ለእርሻ ስራ አገልግሎት ወይም ለሞፈር የሚሆን የወይራ እንጨት በመምረጥ ቆርጦ ወደሚኖርበት አካባቢ ይዞ ይጎዛል፡፡ እቤቱም ከደረሰ በኋላ ከትከሻው ላይ ለማውረድ ሲሞክር እንጨቱ አልወርድ ይለዋል ፤ በመጨረሻም የአካባቢው ሰዎች ይሰበሰባሉ የቆረጠበትንም አካባቢ ይጠቁማል ፤ አርሶ አደሩም ለተሰበሰቡት የአካባቢው ሰዎች የቆረጠበትን ቦታ ሲነግራቸው ሰዎቹም ከቆረጠበት ቦታ መልሶ እንዲወስድ ይነገረዋል መልሶም በመውሰድ ከቆረጠበት ቦታ ላይ ሲያቆመው ዛፏ እንደ ነበረች ወይም ከመቆረጧ በፊት የነበረበችበትን አቋም ይዛ እንደቆመችና የተቆረጠችበት ወይም የተከረከረችበት እያስታወቀ እንደሚኖር የሚታይ ሃቅ ነው ፡፡ በተጨማሪ ይህ ድንቅ ስፍራ በጥቅምት 14 እና ግንቦት 4 በአመት ሁለት ጊዜ በደማቅ ሁኔታ ይከበራል። ይህንን እንግዳ ተቀባይ የሆነው የወረዳዊ ማህብረሰብ ታሪካዊ ቦታ በአካል መጥታችሁ በመጎብኘት የበረከቱ ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ እንጋብዛለን ፡፡

ከሚዳወረሞ ኮሙኒኬሽን

እነዚህ ደግሞ በመከታው ማሞ ትዕዛዝ ሸዋ ላይ ተደራጅተው የአማራን ህዝብ የሚዘርፉ ናቸው ‼️ መቼም ለአማራ ህዝብ ነፃነት እየታገልን ነው አትሉኝም 😂😂
16/10/2025

እነዚህ ደግሞ በመከታው ማሞ ትዕዛዝ ሸዋ ላይ ተደራጅተው የአማራን ህዝብ የሚዘርፉ ናቸው ‼️

መቼም ለአማራ ህዝብ ነፃነት እየታገልን ነው አትሉኝም 😂😂

Address

Addis Ababa
WWW.MULTIETHNICSHOA.COM

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Multi Ethnic Shoa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share