
05/07/2025
ነገረ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን፤ “ዓሣ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል” ‼️
በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ እና በወላታ ዲቻ መሐል ያለውን እስፖርታዊ ውድድር፤ እንደ ሀገርም ሆነ እንደ አፍርካ ለኳስ እድገት ያለው አስተዋጽኦ እጅግ ታላቅ መሆኑ ለህዝባችን ግልጽ ነው። ሆኖም ግን የእግር ኳስ ፌጄሬሽኑ፤ ስለ ኳስ እና የኳስ ህጉን ሳያውቅ የሚመራ፤ ከየትኛውም እስፖርታዊ እውቀት ነፃ መሆኑን (ፖለቲካዊ አሻጥር የተሸበበ) እንደሆነ በተፈጠረው ችግር መረዳት ተችሏል።
ከዚህም በላይ ችግሩን እጅግ ከባድ የሚያደርገው፤ ችግሩ ለሀገር ውስጥ ክሌቦች ላይ እና ደጋፊዎች ላይ ከሚያመጣ አውንታዊ ተጽኖ ባሻገር፤ እንደ ሀገር ያለንን የኳስ እድገት እውቀትና ብሎም ያስመዘገብነውንም ውጤት ጨምሮ የሚያሰርዝ፤ እንደ ሀገርም ትልቅ ችግር ላይ የሚጥለን ጉዳይ ሆኗል። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ከጂቡቲ ጋር ላደረገችበት ጫወታ ከማድረግ በፊት ፌዴረሽኑ ከሲዳማ ቡና፣ ከሀዋሳ ከነማ እና ከመቻል ክለቦች በ 24 Feburary 2025 ላይ የቅጣት ውሳኔ ማስተላለፍ ይታወቃል።
ነገር ግን ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ 25 ማርች 2025 ባደረጉት ግጥሚያ ሀገራችንን ወክለው የተጫወቱት ተጫዋቾች መሐል፤ ቅጣት ተወስኖባቸው የነበሩ ተሰልፈዋል። ሌምሳሌ ከታገዱ ተጫዎቾች መስፍን ታፈሰ ከሲዳማ ቡና ክለብ የተሰለፈ ሲሆን፤ በረከት ደስታ ደግሞ ከመቻል FC ተሰልፎ፤ በአንድ ጫወታ ላይ (Hatrick ) ሦስት ጎል በማስገባት ኢትዮጵያ ጂቡቲን 6 ለ 1 እንድታሸንፍ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።
እንደ ሀገር በብሔራዊ ደረጃ ሆነ በክለብ ደረጃ የተቀጣን ወይንም ቅጣት ላይ ያለን ተጫዋች ማስለፈ ጥፋት ብቻ ሳይሆን፤ በFIFA ህግ ትልቅ ውሳኔ የሚያሰጥ ጉዳይ ነው። ይህ አድራጎት ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ከFIFA የሚያሳግዳትና ውጤቱንም የሚያሰርዝ ስለሆነ፤ ጉዳዩ ከውስጥ ጉዳይ ( ከሲዳማና ከዲቻ) አልፎ በሀገርንም የሚጎዳ ይሆናል ማለት ነው። ደረጃውን ወደ ታች ዝቅ ማስደረግ ብቻ ሳይሆን፤ ውጤቱን ሙሉ በሙሉ የሚያሰርዝ ይሆናል።
ስለዚህ ፌዴሬሽኑ ምን እያደረገ እንደሆነ ያልገባው ማንን ጠቅሞ ማንን እንደምጎዳ እንኳን ለይቶ የማያውቅ፤ ከኳስ ህግ ደንብና ሥርዓት ብቻ ሳይሆን ከእርሱ ጋርም የተጣላ ለመሆኑ ሥራቸው ምስክር ናቸው። ይህን መረጃን በግልጽ Google ላይ ያገኙታል። በሌላም ጥፋቱን ደግሞ በሲዳማ ውጤት ላይ ባስተላለፈው እብደት ተነስትተን ብቻ ሳይሆን፤ እስከዛሬ የሰራቸውን ስህተት መፈተሽ ይቻላል። ይህም የኢትዮጵያ ኳስ የጥፋት Foundation በሚል ስም እራሱ ፍርድ ቤት ሥራው የሚገትረው ይሆናል።
የሲዳማ ቡና ክለብ ሆነ ይህ ጉዳይ እንደ ሀገር ያገባኛል የሚል ሰው፤ ዋንጫው ከሲዳማ ቡና ከመንጠቅ ይልቅ፤ ይህ እብሪተኛ አላዋቂ ቡድን፤ በፌዴሬሽን ስም የኳስን ፍቅር የህዝሀ ስሜት የሀገርን ክብር ከሚገሉት ላይ ስልጣናቸውን ቀምቶ፤ የህዝብን የሀገርን የኳስንም ስሜት ለህዝባችን እንድተው ጥሪ እያደረግን፤ የሲዳማ ቡና ክለብ መረጃውን በመጠቀም ደጋፊውን እና መላው የኳስ አፍቃሪያን ክብር እንድጠብቅ በአግባቡ በመረጃና በማስረጃ እንድሟገት እናስገነዝባለን።
በሌላ በኩል የሲዳማ ቡናም ሆነ የወላይታ ዲቻ ደጋፊዎች፤ በህግና በሀገራዊና እንዲሁም ዓለም አቀፋዊ መርህ፤ ስሜቱን በኳስና ልብስ ብቻ በማድረግ፤ የሁሉቱን ወንድማማች ህዝቦችን ሰላም ለማጠልሸት፤ አንዳንድ ችግር ነጋዴዎችን በጋራ እንድንታገል ጥሪያችንን እናቀርባለን።
የህግ በላይነትን፣ ደንብና ሥርዓትን እንኳ ለህዝቡ እንድተውልን ድምፃችንን ከፍ አድርገን እናሰማለን።
ሉዋ ሚዲያ
July 05/2025