Desalegn Hagirso

Desalegn Hagirso news company of
internal Ethiopian affairs

14/03/2026

Sidaama federaaliste paarte ayirrado sidaamu dagara hawalle fichee cambalaallate ayyaanira keerunni iillishi'ne yitanno sokko saayissino.

Sidaamu daga ha'nura budese seeda yannanni kaayisse babbaxitino kadote gashshootubba bude ciiggishate adhitanni keeshsh*tino qaafo gufissukkini akkimale waaga baatte techo ilamara iillishshino. Konne bulduudda bude techo yannara tini ilama gobbatennino sa'e kalqete deerrinni afansha afire dhagete donira maarekkamanno gede loossinoti sidaamu dagaha sigiiga budu tareessonna s***a gede ugginannikki bareda daga ikkase leellishshanno.

Sidaama federaaliste paarteno sidaamu daga bulduudda bude polisenna pirograamese biso assatenni, bude yannite egenno ledo waaxxe bowirsate kaajjillunni loossanni nooota egensiissanno.

Jeefoteno SFP Sidaamu daga baalanta hawalle diru soorro fichee-canbalaallate ayyaannira keerunni iillishinoke yitanni, haaru diru soorro ayaani keerunniha, altennihanna baxillunniha ikkanno gede kaajjado halchose xawissanno.

AAYIIDDE CANBALAALLA !!!

06/10/2025

Beloved Brothers and Sisters, It is with deep sorrow that we share th… Assefa Debeko needs your support for Support for Dr. Darara Borodge's Funeral Costs

04/09/2025
04/09/2025

: አቶ ጌታቸው ረዳ የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር በመሆን ተሹመዋል።

ላለፉት አራት አመታት ስያገለግል የነበሩ ዶ/ር ለገሰ ቱሉን አምባሳደር በማድረግ ከኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚንስተርነት ያነሱት ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በምትካቸው አቶ ጌታቸው ረዳን ተክተዋል፡፡

አቶ ጌታቸው ረዳ ኢህአዴግ/ህወሓትን ወክለው በብቃት ያገለገሉትን የቀድሞው መ/ቤታቸውን አድሱ ስምረት የተሰኘ ተቃዋሚ ፓርቲ መስርተው ድጋሚ ተመልሰዋል። ቀድሞ ትግራይ ግዜያዊ አስተዳደር በመሆን ያገለግሉ በነበሩበት ወቅት ከህወሓት አመራሮች ጋር በአንጃነት ሰጣእገባ ዉስጥ ገብቶ እንደነበር ይታወሳል።

የሰሜኑ ሀገራችን ክፍል የተከሰተዉ አዉዳሚ የብልጽግና እና የህወሓት (የትግራዩ) ጦርነት በህወሓት ወገን በቃለ አቀባይነት ተሰልፈው የፕሮፓጋንዳና ኮሙኒኬሽን ስራን በበላይነትና በውጤታማነት በመምራት ጉልህ ሚና ነበራቸው።

Via፦ ማለዳ ሚዲያ

ሉዋ ሚዲያ

03/09/2025

#መረጃ: የስዳማ ቡና ዩኒየን የክልሉ ባለስልጣናት ልጆች ከሀገር ዉጪ ማስተማሪያ ወጪ ከመሸፈን ጨምሮ ለተለያዩ ለዝርፍያ መጋለጡ ተነገረ፤

ይህንኑ የባለስልጣና የጥቅማጥቅም ዋሻ የሆነ ዩኒየኑ በዉስጡ የተሰሩ ብልሹ ስራዎች ኖርማላይዝ ለማድረግ የሥራ አመራር ኮሚተ አባል ያልሆኑትና ከዩኒየኑ ሥራ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የሌላቸዉ የክልሉ ምክር ቤት አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ የዩኒየኑን አመታዊ አፈጻጸም ሪፓርት ለመገምገም አድስአበባ መግባታቸዉ ምንጮች ይጠቁማሉ፡፡

ዩኒዬኑ ባለቤት አልባ ሆኖ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እንዳሻቸዉ እየዘረፈ የሚገኘዉ የሲዳማ ቡና ዩኒየን ፀጋዬ አነዎ ኃላፍነቱ የተወሰነ የግል ካምፓኒ ይመስል ተብሏል። ዩኒየኑ የክልሉ ባለስልጣናት ልጆች ከሀገር ዉጪ ትምህር ማስተማሪያ ወጪ ከመሸፈን ጨምሮ የተለያዩ የፍጆታ ወጪዎች እንደምሸፍን የተነገረ ስሆን፤ ለአብነት ከዝህ ቀደም ያለቦርዱ ዉሳኔ የአብረሃም ማርሻሎ ልጅ የሆነውን ቢኒያም አብረሃም በቱርክ ሀገር የጉዞ ትኬት ጨምሮ ሙሉ ወጪ በመሸፈን እያስተማረ እንደምገኝ ጠቅሶ፤ ዘንድሮ ደግሞ ሁለት የአቶ ደስታ ለዳሞ ልጆች ከትላንትና በስቲያ አሜሪካን ሲያቲል የገቡትን ሄር ደስታና ፌቬን ደስታ ከዓመት በፊት አሜርካ የገባችዋን ብሌን ደስታ አሜሪካ የምገኘዉ አንጋፋ ዩኒቨርስቲ ሙሉ ወጪ በሚሊዮኖች ሸፍኖ የላከ መሆኑን ተገልጿል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የክልሉ ህብረት ሥራ አጀንሲ ኃላፍ አቶ ሽመልስ ሀጥሦ በክልሉ የምገኙ የህብረት ሥራ ማህበራትን በመዝረፍ ከወረዳ ህብረት ሥራ መዋቅር ጋር አጣብቅኝ ዉስጥ የገባና በክልሉ ፕረዝዳንት የተቋሙን ተልዕኮ በወል አታውቅም ተብሎ ክልል ዐቀፍ መድረክ ላይ በፕረዝዳንቱ ነቀፈታ የቀረበበት ስሆን፤ በኤጀንዉ የቡና ማህበራትን እየዘረፈ ለመቀጠል ፕረዝዳንቱን በሎብስቶች መክበቡ ሳይበጅ አይቀርም በሚል ለአፈጉባኤዋ የአድስ አበባ ፕሮግራም እንዳመቻቸ ታውቋል።

ሉዋ ሚዲያ

03/09/2025
02/09/2025

#መረጃ: የሀዋሳ አየር ማረፊያ አለም አቀፍ በረራ ለማስተናገድ ከተመረጡ የሀገር ውስጥ አየር ማረፋያዎች ውስጥ ሳይካተት መቅረቱን ተነገረ፤

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ከቦሌ አለም ዐቀፍ አየር ማረፊያ በተጨማሪ፤ የክልል አየር ማረፊያዎች ቀጥታ አለም ዐቀፍ በረራዎችን የሚያተስናግዱበትን አሰራር ይፋ አድርጓል።

የአየር ትራንስፖርትና አለም አቀፍ ጉዳዮች አማካሪ አቶ እንደሻው ይገዙ የኢትዮጵያ የአየር ግንኙነትን ያልተማከለ ማድረግ፣ የጉዞ ጫናን ማቃለል እና ቱሪዝምን ለማሳደግ የምትከተለው ስትራቴጂ አካል ነው ሲሉ የዕቅዱን ዓላማ ተናግረዋል።

ከዚህ ለንግድ፣ ለካርጎ ጭነት እንዲሁም አለም አቀፍ ኢንቨስትመንትን ለክልሎች ለመሳብ የጎላ ፋይዳ አለው በተባለው ቀጥታ በረራ ሀዋሳን ጨምሮ የደቡቡ የሀገሪቱ ክፍል አየር ማረፊየዎች ሳይመረጡ ቀርተዋል።

ከዓለም አቀፍ ከተሞች ጋር ቀጥታ እንዲገናኙ የተመረጡት የባህርዳር፣ ድሬዳዋ እና የመቐሌ አየር ማረፊያዎች ስሆኑ። ሀዋሳ አየር ማረፊያ ለዚህ አገልግሎት ሳይመረጥ የመቅረቱ ምክንያት ፖለቲካዊ ጠልቃ-ገብነት ያዉ ነዉ እየተባለ ይገኛል። ነዋሪዎቹ እንደሚያምኑት ሀዋሳ የቱሪስት መዳረሻነት በግንባር ቀደምነት የሚነሳ አከባቢ ብሆንም ሲዳማ ክልል ምስረታ ጋር ተያይዞ አከባቢውን ከተጠቃምነት ለማግለል እና ከጨዋታ ዉጪ ለማድረግ በብልጽግና ፓርቲ የተያዘዉ ስዉር (Systemic) የበቀል እርምጃ አንዱ አካል መሆኑን የሲዳማ ክልል ነዋሪዎች እየተናገሩ ይገኛሉ።

ሉዋ ሚዲያ

02/09/2025

የስልጣን ጥማት ማርከሻ እና እድሜ መግዣነት ታስቦ የተገነቡ፤ ራዕይ የማጣት ማሳያ እና ትጉም አልባ ናቸዉ።

ትናንትና የብልጽግና ፓርቲ ቢሮዎች በሁሉም ወረዳዎች ተገንብቶ መጠናቀቁን እየተነገረ ይገኛል። ይህንኑ ስንመረምር የምናገኘዉ አንድ ምስጥር ይገለጥልናል። እሱም የስልጣን ጥማት ማርከሻ እና እድሜ መግዣነት ታስቦ የተገነቡ ራዕይ የማጣት ማሳያ መሆኑ።

ይህንን ስባል አንዳንድ የዋህ ማህበረሰባችን ክፍል ልማትን እንደምንቃወም አድርጎ ለማቅረብ እንደሚሞክር እንረዳለን፤ ዳሩ ግን እንዲህ ያለዉ ፋይዳቢስ ስራ ልማት እንደአይደል ለማሳየት ነገሩን በምክንያት እንመልከት። ግንባታዎች የተከናወኑት በሁሉም ወረዳዎች አስገዳጅ መዋጮ መሆኑ በሌላ በኩል ነገሩን በአሉታዊ እንዲነሳ ያደርገዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ይሁን ብለን መልካም ነዉ ብንል እንኳን ነገሩ አዎንታዊ የማይሆንበት አንድ ምክንያት ግን አለ።

እሱም ሲዳማ ክልል ነባር ወረዳዎች በስተቀር 1998 ዓ.ም የተመሠረቱ ወረዳዎችን ጨምሮ በቅርቡ 2011 ዓ.ም የተመሰረቱ አብዛኞቹ አንድ ወይም ሁለት በስተቀር ከሀያ የሚልቁ ሰክተር መስሪያቤት የራሳቸዉ ቢሮ የላቸዉም። ለዚህም በአመት ከፍተኛ ገንዘብ ለቢሮ ክራይ ያወጣሉ። ይህ ደግሞ የወረዳዎቹ ኢኮኖሚ ብሎም ህዝቡን በከፍተኛ ሁኔታ እየጎዳ ይገኛል።

በሌላ በኩል ፓርቲው ከዚህ ቀደም በወረዳ አስተዳደር ህንጻዎች ዉስጥ ሶስት ክፍል ዉስጥ የሚኖሩ ህዝባዊ አገልግሎት እምብዛም የሆነ፣ ከስሩ ሌላ ሰራተኞች የሌሉት፤ በአንጻሩ ምንም አይነት የቢሮ ክራይ የማይወጣባቸዉ መሆኑን ይታወቃል።

ከዚህ ባሻገር አሁን የብልጽግና ፓርቲ ቢሮ ገንብቶ እያስመረቁ ያሉት አንዳንድ ወረዳዎች ሙሉ በሙሉ አንድም የራሳቸውን ቢሮ ገንብቶ የማያውቁ የወረዳ አስተዳደር ቢሮ ጭምር የሌላቸ ናቸዉ። ለአብነት ሙሉ በሙሉ ወይም በአብዛኛው ቢሮ የለላቸዉ ወረዳዎች ስንፈልግ በትንሹ የሚከተሉትን እናገኛለን፦ ጭሮኔ፣ ቡራ፣ ዳኤላ፣ ሻፋሞ፣ ሆኮ፣ ቡርሳ፣ ቦና፣ ቦካሶ ወንሾ እና ወዘተ ናቸዉ።

እነዚህ ወረዳዎች በከፍል ከዛሬ አስራ ዘጠኝ አመታት በፊት የተመሰረቱ፤ ሌሎቹ ደግሞ ከዛሬ ስምንት አመታት በፊት የተቆረቆሩ ወረዳዎች ሆኖ ቢሮ ሳይኖራቸዉ ክራይ እየከፈሉ እየኖሩ፤ ትናንት የተፈጠረውን ብልጽግና ቢሮ ለመገንባት ህዝብን አስተባብረን (አስገድዶ፣ አስሮ፣ ገርፎና አሰቃይቶ) ህንጻ አስገነባን ስባል ነገሩ ትርጉም የሚያጣዉ እዝህ ላይ ነዉ።

በሌላ በኩል እነዚህ ግንባታዎች ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ የሌላቸዉ ከመሆኑም ባለፈ፤ ይህ ሁሉ ለአንድ ፓርቲ ህንጻ በየወረዳው ገንብቶ መክፈት፤ በአንጻሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተከራይቶ እንኳ የሚከፍቱት ቢሮዎች መስበር፣ ፓይፔላ መስረቅ፣ አባላትን ማሰር፣ ማሳደድ፣ ባለበት አንድ ፓርቲ ብቻ ይህንን ያህል ማስፋፋት ዬትም አያደርስም። እነዚ ስራዎች ትርጉም የሚያጡበት ሌላኛው ምክንያት ይህ ነዉ።

ስጠቃለል በአራት ምክንያት እነዚህ የቢሮ ግንባታዎች ትርጉም የሚያጡበት ይሆናሉ፦

1, በህዝባ ትብብር የተገነቡ መሆናቸውን ብነገርም እዉነታዉ ግን ተቃራኒ ሆኖ እናገኛለን። ለመዋጮ ግለሰቦችን፣ ሰራተኞችን፣ አርሶአደሮችን፣ ማስገደድ፣ ማሰር፣ ማስፈራራት እና ማሰቃየት የታከለበት በመሆኑ፤

2, ቢሮዎች እየተገነቡ ያሉት ወረዳዎች ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡበት አንድም የራሳቸዉ ቢሮ የሌላቸው በመሆኑ፤

3, እነዚህ ግንባታዎች ኢኮኖሚያዊ እና ህዝባዊ አገልግሎት ፋይዳ የለላቸዉ ከመሆኑም ባሻገር በስዉር የክልሉ ባለስልጣናት የማዕከላዊ መንግሰስት ልብ ለመማረክ እና ለብልጽግና ታማን አገልጋዮች መሆናቸዉን ብቻ ያሳዩበት በመሆኑ፤

4, ሌሎች ተቃማዊ ፓርቲዎች አንድም ቢሮ በወረዳዎችም ሆነ ሀዋሳ ከተማ መክፈት እንዳይችሉ ተደርጎ የዲሞክራሲ መህዳር የተዘጋበት በመሆኑ፤ ትርጉም የሌላቸው እና ራዕይ የማጣት ማሳያ መሆኑን ያስገነዝባሉ።

ሉዋ ሚዲያ

31/08/2025

#መረጃባንዳዎች! በእርግጥ አቶ አለማየሁ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላቸዉ እና ገንዘብ በመቀበል በርከት ያሉ ወንጀል ስራ ተሰማርታችሁ እንደነበር አደባባይ ምስጥር ነበር።

በሳምንታት በፊት አንዳንድ ግለሰቦች ሰላማዊ ወጣቶችን ከቀድሞ ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ ጋር በማበር ሀሰተኛ መረጃ እያቀበሉ ከማሳሰር እስከ ማሳደድ፣ ባለሀብቶችን የመረጃ ሰዎች ነን በማለት ማስፈራራት እና አንዳንድ ቢሮ ሃላፊዎች በማዋከብ አበል እንደሚሰበስቡ ዘግበን እንደነበር አይዘነጋም።

እነዚህ ግለሰቦች ይባስ ብሎ አሁን አቶ አለማየሁ መታሰሩን ተከትሎ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ግርግር በመፍጠር በወንጀል ተጠርጥረው የታሰረ ቀድሞ አለቃቸዉ እንዳይጠየቅ ተጽዕኖ ለመፍጠር እየሞከሩ መሆኑን እየታዘብን እንገኛለን።

በመሆኑም በእጃችን የገቡ የተለያዩ ሰነዶች ብኖሩም በመንገዳቸው እንዲመለሱ በምለዉ ሳናወጣ አቆይተናል። አሁን ግን ከመንገዳቸው መመለስ ስላልቻሉ ምን ስሰሩ እንደነበር አንድ በአንድ ለማጋለጥ እንገደዳለን።

ሉዋ ሚዲያ ያለተጨባጭ መረጃ አንድም ግለሰብ ጠቅሶ አይዘግብም።

ሉዋ ሚዲያ!

31/08/2025

የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕረዝዳን አቶ አደም ፋራሀ እና ከፍተኛ አመራሮች የሚጎበኙት በዓይን የምታዩ የረባ የልማት ሥራዎች በክልሉ አልተሰሩም ተባለ፡፡

በባለፈው የጠቅላይ ሚኒስተሩ ሀዋሳ ከተማ ጉብኝት በቪየትናም ባለሀብቶች፤ በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሶላር ኃይል የሚያመርተውን ባለሀብት ሥራ ከማስጀመር ባለፈ፤ በከተማዋ ጠብ የሚል የልማት ሥራዎች አለመኖራቸውን በመመልከት፤ ከተማዋ በለሎች ክልሎች ካሉ የዞን ከተሞች በታች መሆኗ፤ ቀደምት የነበራትን ዝናና ግንባር ቀደምትነት አለመኖሩና ከዝህ ቀደም በነበሩ ካንቲባዎች የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ቆሞ በመቅረታቸው፤ ጠቅላይ ሚኒስተሩ በአመራሩ ድርጊት ደስተኛ ሳይሆኑ ተመልሰዋል ተብሏል፡፡

በክልሉ የህዝቡን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በሚደርገው ጥረት ምንም አስተዋጽኦ የሌላቸው፤ የተገልጋይ እርካታን የማይጨምሩ፤ በየወረዳው 13 ግለሰቦች ለብሮነት የምገለገሉ አባላት ሆነ ደጋፍዎች ሳይወያዩበትና ሳይወስኑ በግዳጅ ከመንግሥት ሰራተኞች ህጻናት ጉሮሮ ተነጥቆ ደመወዛቸውን የተቆረበት፤ አርሶ አደሮች በአከባቢ ሚሊሻ ተገደው የመሬት ይዞታ ግብር ጋር በነፍስ ወከፍ 1500 ብር በአስገዳጅነት እንድያዋጡ የተገደዱበትና ዘጎች ገንዘባቸው ያለአግባብ እንዳይቆረጥ ለሰበአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ ለህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋምና ለአከባቢ ፍርድ ቤቶች አበቱታ አቅርበው ምላሽ ያጡበትን ፕሮጀክት፤ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕረዝዳን በማስመረቅ፤ የክልሉ ባለስልጣናት ፋይዳቢስ አክራሞት ተቃውሞ እና የህዝባዊ ቅቡልነት እጦት ለመሸፋፈን ለማዕከላዊ መንግሥት “ህዝቡ ከጎናችን ነው፣ በህዝብ ተሳትፎ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ናቸው” በማለት የደስታ ለዳሞ አስተዳደር ተጨማሪ የሲዳማ ህዝብ የመከራ ጊዜ ለማራዘም ደፍ ቀና እያሉ አንደሆነ ታውቋል፡፡

በለላ በኩል የጽ/ቤቶች ምርቃ ጎን ለጎን ለሎች የልማት ሥራዎችን ለማስጎበኘት በግብርና ቢሮ ኃላፊ የሚመራ ኮሚተ አዋቅሮ ሊየታ ለማድረግ የተንቀሳቀሰው የደስታ ለዳሞ አስተዳደር፤ በአራቱም ዞኖች በክላስተር የለማ በዓይን የምታይ እርሻ አለመኖሩን ከኮሚተዉ የመርዶ ሪፓርት ቀርቦለት ተደናግጦ ከፍተኛ አመራሩን ከዝህ ቀደም እንደሚያደርገው በሽልማት እና በገንዘብ ለመደለልና ከፍተኛ አመራሩም በክልሉ በዉዳሴ እና “የቤተሰብ ብልጽግና ተረጋግጧል አመራሩና ህዝቡ ተቀናጅቶ እየሰሩ ናቸው” የምለውን ሀሰተኛ ምስክርነት ለማግኘት ለፈደራሉ አመራር ጎቦ ለማቀበል እንድያግዛቸው ቀድሞ የአቶ አደም ፋራሀ ጓደኛ የነበሩትን አቶ ጌታሁን ታደለ ሱማለ ላንድ የቁም ከብቶችን የምነግድ ነዎርነታቸውን ቶጎ ጫለ ያደረጉትን ለዝህ ተልዕኮ ወደ ሀዋሳ መጥራታቸው ታውቋል

ይህ በእንዲህ እንዳለ በቀድሞ ደቡብ ኢትዮጵያ ዴሞክራያስዊ ንቅናቀ (ደኢህደን) ማዕካላዊ ኮሚቴ
ጽ/ቤት ሆኖ እንዲያገለግል በ2008 ዓ.ም በዘነኛ ድርጅታዊ ጉባዔ በ260 ሚሊየን ብር ግንባታው ተጠናቆ ላለፋት ዘጠኝ ዓመት አገልግሎት ስሰጥ የቆየውን ቀለም ቀብቶ ዳግም ርባንን ለማስቆረጥ እንደተዘጋጁ ባለፈዉ መዘገባችን አይዘነጋም።

ሉዋ ሚዲያ!

30/08/2025

#መረጃ: በሲዳማ ክልል የጡረታ መዋጮ የተሰበሰበውን ገንዘብ ለማህበራዊ ዋስትና ገቢ መደረግ የሚገባውን ዘጠኝ መቶ ሚልዮን ብር መዘረፉ ተሰማ፤

በሲዳማ ክልል ለማህበራዊ ዋስትና የመንግሥት ሠራተኞች ከደመወዛቸው የተቀነሰ እና የመንግሥት ድርሻ የጡረታ መዋጮ የተሰበሰበውን በወቅቱ መከፈል የነበረበት ዘጠኝ መቶ ሚልዮን ብር በክልሉ መንግስት አማካኝነት ላልተገባ መንገድ መባከኑ ተነገረ።

ከወረት በፊት የክልሉ መንግሥት የጥሬ ገንዘብ እጥረት አጋጥሞኛል በማለት በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም በክልሉ ካቢኔ አስወስኖ ከ2018 ባጀት ብድር ለመቀበል ለገንዘብ ሚኒስተር ጥያቄ ማቅረቡን ዘግበን እንደነበር አይዘነጋም። ገንዘብ ሚኒስተሩ ይህንን የብድር ጥያቄ ተከትሎ አቶ አህመድ ሽዴ ብድሩ እንድፈቀድላቸው ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደብዳቤ የተላኩ ቢሆንም፤ በጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ባለመስማማት ምክንያት እንዲታገድ መደረጉ ተሰምቷል፡፡

የመረጃ ምንጫችን አንደገለጹት በሲዳማ ክልል በክልሉ መንግስት ደረጃ የተንሰራፋው ሌብነት እና ሙስና የመንግሥትን በጀት በጠራራ ፀሀይ እንድመዘበር አድርጓል የተባለ ስሆን፤ የ2017 በጀት አመት የተፈቀደውን በጀት ከታለመለት ዓላማ ውጪ በማዋል፤ ምንም ዓይነት የልማት ሥራዎች ሳይሠራ፤ በሙስና እና አላስፈላጊ ድግስ በማዘጋጀት እንድሁም፤ በሽልማት መልክ ያልተገባ ጥቅም በማሰባሰብ በጀቱን አባክኖ በመጨረስ፤ ገንዘብ ሚንስተር የጠየቀው ብድር ስከለክል፤ ከደሞዝተኛ የተቆረጠ ጡረታ ለማህበራዊ ዋስትና ገቢ መሆን የነበረበትን ዘጠኝ መቶ ሚሊየን ብር ከዓላማው ዉጭ ለግል ጥቅማቸው ብቻ ማዋላቸውን ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያስረዳል። ከመረጃ ምንጫችን መረዳት እንደተቻለው፤ በክልሉ መንግስት ከፍተኛ አመራራሮች ይህንን አስነዋሪ ተግባር በመደረጉ የተነሳ ለረዥም ጊዜ ሀገራቸውን አገልግለው በጡረታ የተገለሉና ቤተሰቦቻቸው በሞት ያጡ ወገኖች ለከፍተኛ ችግር መደረጋቸውን ታውቋል፡፡

ይህ በእንድህ እንዳለ ከፈደራል መንግሥት ግምጃቤት ብድር የተከለከለው የክልሉ መንግስት፤ ከሲዳማ ባንክ እና ከሲዳማ ቡና ዩኒየን 2.5 ቢልዮን ብር ብድር መውሰዱ የተረጋገጠ ስሆን፤ የብድሩ ዓላማ ሁለተኛ ዙር ኮርደር ልማት ማጠናቀቂያ የምል ሰበብ ቢሆንም፤ እስከአሁን ኮርደር ልማትን ለምሰራው ኮንትራክተር የክልሉ መንግስት አምስት መቶ ሚሊየን ብር ብቻ በመከፈሉ ሥራው በሚፈለገው ጥራትና ፍጥነት እየተከናወነ አለመሆኑን እስከ ቦታው ሄዶ ከጎበኙ የዓይን እማኞች ለሉዋ ሚዲያ አስረድተዋል።

ኮንትራክተሩ ለክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ቀሪዉን የክፍያ እንዲፈጸም ጥያቀ አቅርቦ፤ ከፋይናንስ ቢሮ የጥሬ ገንዘብ እጥረት አለን በማለት ባለመከፈሉና ሥራውም ስላልተጠናቀቀ በባለፈው የጠቅላይ ሚኒስተሩ ጉብኝት ወቅት የክልሉ አመራር በዓይን የሚታይ የልማት ሥራዎች ለማስጎብኘት መቸገራቸውን ለማወቅ ተችሏል።

በአጠቃላይ የአቶ ደስታ ለዳሞ አስተዳደር በሌብነት ተጨማልቆ የክልሉን ህዝብ ለሁለገብ ችግር በመዳረጉ የመንግሥት ፋይናንስ ብቃት የለላቸውና በሌባ አመራሮች እንዲመራ በማድረግ ክልሉን የከፋ ችግር እንዲዳረግ በማድረጉ እና ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንስ ያለአግባብ የተወሰደ ገንዘብ በፍርድ ቤት አስወስኖ ዘጠኝ መቶ ሚሊየን የባንክ ሂሳብ አሳግዶ በመውሰዱ የክልሉ ቢሮዎች ዞኖች እና ወረዳዎች የጥሬ ገንዘብ እጥረት አለን በሚል ምክንያት ምንም ዓይነት ሥራ ሳይሰሩ ሁለት ወር ማሳለፋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሉዋ ሚዲያ

Address

Chercher
Addis Ababa
...

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Desalegn Hagirso posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share