Desalegn Hagirso

Desalegn Hagirso news company of
internal Ethiopian affairs

04/09/2025
04/09/2025

: አቶ ጌታቸው ረዳ የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር በመሆን ተሹመዋል።

ላለፉት አራት አመታት ስያገለግል የነበሩ ዶ/ር ለገሰ ቱሉን አምባሳደር በማድረግ ከኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚንስተርነት ያነሱት ጠቅላይ ሚ/ር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በምትካቸው አቶ ጌታቸው ረዳን ተክተዋል፡፡

አቶ ጌታቸው ረዳ ኢህአዴግ/ህወሓትን ወክለው በብቃት ያገለገሉትን የቀድሞው መ/ቤታቸውን አድሱ ስምረት የተሰኘ ተቃዋሚ ፓርቲ መስርተው ድጋሚ ተመልሰዋል። ቀድሞ ትግራይ ግዜያዊ አስተዳደር በመሆን ያገለግሉ በነበሩበት ወቅት ከህወሓት አመራሮች ጋር በአንጃነት ሰጣእገባ ዉስጥ ገብቶ እንደነበር ይታወሳል።

የሰሜኑ ሀገራችን ክፍል የተከሰተዉ አዉዳሚ የብልጽግና እና የህወሓት (የትግራዩ) ጦርነት በህወሓት ወገን በቃለ አቀባይነት ተሰልፈው የፕሮፓጋንዳና ኮሙኒኬሽን ስራን በበላይነትና በውጤታማነት በመምራት ጉልህ ሚና ነበራቸው።

Via፦ ማለዳ ሚዲያ

ሉዋ ሚዲያ

03/09/2025

#መረጃ: የስዳማ ቡና ዩኒየን የክልሉ ባለስልጣናት ልጆች ከሀገር ዉጪ ማስተማሪያ ወጪ ከመሸፈን ጨምሮ ለተለያዩ ለዝርፍያ መጋለጡ ተነገረ፤

ይህንኑ የባለስልጣና የጥቅማጥቅም ዋሻ የሆነ ዩኒየኑ በዉስጡ የተሰሩ ብልሹ ስራዎች ኖርማላይዝ ለማድረግ የሥራ አመራር ኮሚተ አባል ያልሆኑትና ከዩኒየኑ ሥራ ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የሌላቸዉ የክልሉ ምክር ቤት አፌ ጉባኤ ወ/ሮ ፋንታዬ ከበደ የዩኒየኑን አመታዊ አፈጻጸም ሪፓርት ለመገምገም አድስአበባ መግባታቸዉ ምንጮች ይጠቁማሉ፡፡

ዩኒዬኑ ባለቤት አልባ ሆኖ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እንዳሻቸዉ እየዘረፈ የሚገኘዉ የሲዳማ ቡና ዩኒየን ፀጋዬ አነዎ ኃላፍነቱ የተወሰነ የግል ካምፓኒ ይመስል ተብሏል። ዩኒየኑ የክልሉ ባለስልጣናት ልጆች ከሀገር ዉጪ ትምህር ማስተማሪያ ወጪ ከመሸፈን ጨምሮ የተለያዩ የፍጆታ ወጪዎች እንደምሸፍን የተነገረ ስሆን፤ ለአብነት ከዝህ ቀደም ያለቦርዱ ዉሳኔ የአብረሃም ማርሻሎ ልጅ የሆነውን ቢኒያም አብረሃም በቱርክ ሀገር የጉዞ ትኬት ጨምሮ ሙሉ ወጪ በመሸፈን እያስተማረ እንደምገኝ ጠቅሶ፤ ዘንድሮ ደግሞ ሁለት የአቶ ደስታ ለዳሞ ልጆች ከትላንትና በስቲያ አሜሪካን ሲያቲል የገቡትን ሄር ደስታና ፌቬን ደስታ ከዓመት በፊት አሜርካ የገባችዋን ብሌን ደስታ አሜሪካ የምገኘዉ አንጋፋ ዩኒቨርስቲ ሙሉ ወጪ በሚሊዮኖች ሸፍኖ የላከ መሆኑን ተገልጿል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የክልሉ ህብረት ሥራ አጀንሲ ኃላፍ አቶ ሽመልስ ሀጥሦ በክልሉ የምገኙ የህብረት ሥራ ማህበራትን በመዝረፍ ከወረዳ ህብረት ሥራ መዋቅር ጋር አጣብቅኝ ዉስጥ የገባና በክልሉ ፕረዝዳንት የተቋሙን ተልዕኮ በወል አታውቅም ተብሎ ክልል ዐቀፍ መድረክ ላይ በፕረዝዳንቱ ነቀፈታ የቀረበበት ስሆን፤ በኤጀንዉ የቡና ማህበራትን እየዘረፈ ለመቀጠል ፕረዝዳንቱን በሎብስቶች መክበቡ ሳይበጅ አይቀርም በሚል ለአፈጉባኤዋ የአድስ አበባ ፕሮግራም እንዳመቻቸ ታውቋል።

ሉዋ ሚዲያ

03/09/2025
02/09/2025

#መረጃ: የሀዋሳ አየር ማረፊያ አለም አቀፍ በረራ ለማስተናገድ ከተመረጡ የሀገር ውስጥ አየር ማረፋያዎች ውስጥ ሳይካተት መቅረቱን ተነገረ፤

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ከቦሌ አለም ዐቀፍ አየር ማረፊያ በተጨማሪ፤ የክልል አየር ማረፊያዎች ቀጥታ አለም ዐቀፍ በረራዎችን የሚያተስናግዱበትን አሰራር ይፋ አድርጓል።

የአየር ትራንስፖርትና አለም አቀፍ ጉዳዮች አማካሪ አቶ እንደሻው ይገዙ የኢትዮጵያ የአየር ግንኙነትን ያልተማከለ ማድረግ፣ የጉዞ ጫናን ማቃለል እና ቱሪዝምን ለማሳደግ የምትከተለው ስትራቴጂ አካል ነው ሲሉ የዕቅዱን ዓላማ ተናግረዋል።

ከዚህ ለንግድ፣ ለካርጎ ጭነት እንዲሁም አለም አቀፍ ኢንቨስትመንትን ለክልሎች ለመሳብ የጎላ ፋይዳ አለው በተባለው ቀጥታ በረራ ሀዋሳን ጨምሮ የደቡቡ የሀገሪቱ ክፍል አየር ማረፊየዎች ሳይመረጡ ቀርተዋል።

ከዓለም አቀፍ ከተሞች ጋር ቀጥታ እንዲገናኙ የተመረጡት የባህርዳር፣ ድሬዳዋ እና የመቐሌ አየር ማረፊያዎች ስሆኑ። ሀዋሳ አየር ማረፊያ ለዚህ አገልግሎት ሳይመረጥ የመቅረቱ ምክንያት ፖለቲካዊ ጠልቃ-ገብነት ያዉ ነዉ እየተባለ ይገኛል። ነዋሪዎቹ እንደሚያምኑት ሀዋሳ የቱሪስት መዳረሻነት በግንባር ቀደምነት የሚነሳ አከባቢ ብሆንም ሲዳማ ክልል ምስረታ ጋር ተያይዞ አከባቢውን ከተጠቃምነት ለማግለል እና ከጨዋታ ዉጪ ለማድረግ በብልጽግና ፓርቲ የተያዘዉ ስዉር (Systemic) የበቀል እርምጃ አንዱ አካል መሆኑን የሲዳማ ክልል ነዋሪዎች እየተናገሩ ይገኛሉ።

ሉዋ ሚዲያ

02/09/2025

የስልጣን ጥማት ማርከሻ እና እድሜ መግዣነት ታስቦ የተገነቡ፤ ራዕይ የማጣት ማሳያ እና ትጉም አልባ ናቸዉ።

ትናንትና የብልጽግና ፓርቲ ቢሮዎች በሁሉም ወረዳዎች ተገንብቶ መጠናቀቁን እየተነገረ ይገኛል። ይህንኑ ስንመረምር የምናገኘዉ አንድ ምስጥር ይገለጥልናል። እሱም የስልጣን ጥማት ማርከሻ እና እድሜ መግዣነት ታስቦ የተገነቡ ራዕይ የማጣት ማሳያ መሆኑ።

ይህንን ስባል አንዳንድ የዋህ ማህበረሰባችን ክፍል ልማትን እንደምንቃወም አድርጎ ለማቅረብ እንደሚሞክር እንረዳለን፤ ዳሩ ግን እንዲህ ያለዉ ፋይዳቢስ ስራ ልማት እንደአይደል ለማሳየት ነገሩን በምክንያት እንመልከት። ግንባታዎች የተከናወኑት በሁሉም ወረዳዎች አስገዳጅ መዋጮ መሆኑ በሌላ በኩል ነገሩን በአሉታዊ እንዲነሳ ያደርገዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ይሁን ብለን መልካም ነዉ ብንል እንኳን ነገሩ አዎንታዊ የማይሆንበት አንድ ምክንያት ግን አለ።

እሱም ሲዳማ ክልል ነባር ወረዳዎች በስተቀር 1998 ዓ.ም የተመሠረቱ ወረዳዎችን ጨምሮ በቅርቡ 2011 ዓ.ም የተመሰረቱ አብዛኞቹ አንድ ወይም ሁለት በስተቀር ከሀያ የሚልቁ ሰክተር መስሪያቤት የራሳቸዉ ቢሮ የላቸዉም። ለዚህም በአመት ከፍተኛ ገንዘብ ለቢሮ ክራይ ያወጣሉ። ይህ ደግሞ የወረዳዎቹ ኢኮኖሚ ብሎም ህዝቡን በከፍተኛ ሁኔታ እየጎዳ ይገኛል።

በሌላ በኩል ፓርቲው ከዚህ ቀደም በወረዳ አስተዳደር ህንጻዎች ዉስጥ ሶስት ክፍል ዉስጥ የሚኖሩ ህዝባዊ አገልግሎት እምብዛም የሆነ፣ ከስሩ ሌላ ሰራተኞች የሌሉት፤ በአንጻሩ ምንም አይነት የቢሮ ክራይ የማይወጣባቸዉ መሆኑን ይታወቃል።

ከዚህ ባሻገር አሁን የብልጽግና ፓርቲ ቢሮ ገንብቶ እያስመረቁ ያሉት አንዳንድ ወረዳዎች ሙሉ በሙሉ አንድም የራሳቸውን ቢሮ ገንብቶ የማያውቁ የወረዳ አስተዳደር ቢሮ ጭምር የሌላቸ ናቸዉ። ለአብነት ሙሉ በሙሉ ወይም በአብዛኛው ቢሮ የለላቸዉ ወረዳዎች ስንፈልግ በትንሹ የሚከተሉትን እናገኛለን፦ ጭሮኔ፣ ቡራ፣ ዳኤላ፣ ሻፋሞ፣ ሆኮ፣ ቡርሳ፣ ቦና፣ ቦካሶ ወንሾ እና ወዘተ ናቸዉ።

እነዚህ ወረዳዎች በከፍል ከዛሬ አስራ ዘጠኝ አመታት በፊት የተመሰረቱ፤ ሌሎቹ ደግሞ ከዛሬ ስምንት አመታት በፊት የተቆረቆሩ ወረዳዎች ሆኖ ቢሮ ሳይኖራቸዉ ክራይ እየከፈሉ እየኖሩ፤ ትናንት የተፈጠረውን ብልጽግና ቢሮ ለመገንባት ህዝብን አስተባብረን (አስገድዶ፣ አስሮ፣ ገርፎና አሰቃይቶ) ህንጻ አስገነባን ስባል ነገሩ ትርጉም የሚያጣዉ እዝህ ላይ ነዉ።

በሌላ በኩል እነዚህ ግንባታዎች ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ የሌላቸዉ ከመሆኑም ባለፈ፤ ይህ ሁሉ ለአንድ ፓርቲ ህንጻ በየወረዳው ገንብቶ መክፈት፤ በአንጻሩ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ተከራይቶ እንኳ የሚከፍቱት ቢሮዎች መስበር፣ ፓይፔላ መስረቅ፣ አባላትን ማሰር፣ ማሳደድ፣ ባለበት አንድ ፓርቲ ብቻ ይህንን ያህል ማስፋፋት ዬትም አያደርስም። እነዚ ስራዎች ትርጉም የሚያጡበት ሌላኛው ምክንያት ይህ ነዉ።

ስጠቃለል በአራት ምክንያት እነዚህ የቢሮ ግንባታዎች ትርጉም የሚያጡበት ይሆናሉ፦

1, በህዝባ ትብብር የተገነቡ መሆናቸውን ብነገርም እዉነታዉ ግን ተቃራኒ ሆኖ እናገኛለን። ለመዋጮ ግለሰቦችን፣ ሰራተኞችን፣ አርሶአደሮችን፣ ማስገደድ፣ ማሰር፣ ማስፈራራት እና ማሰቃየት የታከለበት በመሆኑ፤

2, ቢሮዎች እየተገነቡ ያሉት ወረዳዎች ለህዝብ አገልግሎት የሚሰጡበት አንድም የራሳቸዉ ቢሮ የሌላቸው በመሆኑ፤

3, እነዚህ ግንባታዎች ኢኮኖሚያዊ እና ህዝባዊ አገልግሎት ፋይዳ የለላቸዉ ከመሆኑም ባሻገር በስዉር የክልሉ ባለስልጣናት የማዕከላዊ መንግሰስት ልብ ለመማረክ እና ለብልጽግና ታማን አገልጋዮች መሆናቸዉን ብቻ ያሳዩበት በመሆኑ፤

4, ሌሎች ተቃማዊ ፓርቲዎች አንድም ቢሮ በወረዳዎችም ሆነ ሀዋሳ ከተማ መክፈት እንዳይችሉ ተደርጎ የዲሞክራሲ መህዳር የተዘጋበት በመሆኑ፤ ትርጉም የሌላቸው እና ራዕይ የማጣት ማሳያ መሆኑን ያስገነዝባሉ።

ሉዋ ሚዲያ

31/08/2025

#መረጃባንዳዎች! በእርግጥ አቶ አለማየሁ ጋር የጠበቀ ግንኙነት እንዳላቸዉ እና ገንዘብ በመቀበል በርከት ያሉ ወንጀል ስራ ተሰማርታችሁ እንደነበር አደባባይ ምስጥር ነበር።

በሳምንታት በፊት አንዳንድ ግለሰቦች ሰላማዊ ወጣቶችን ከቀድሞ ጸጥታ ቢሮ ሃላፊ ጋር በማበር ሀሰተኛ መረጃ እያቀበሉ ከማሳሰር እስከ ማሳደድ፣ ባለሀብቶችን የመረጃ ሰዎች ነን በማለት ማስፈራራት እና አንዳንድ ቢሮ ሃላፊዎች በማዋከብ አበል እንደሚሰበስቡ ዘግበን እንደነበር አይዘነጋም።

እነዚህ ግለሰቦች ይባስ ብሎ አሁን አቶ አለማየሁ መታሰሩን ተከትሎ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ግርግር በመፍጠር በወንጀል ተጠርጥረው የታሰረ ቀድሞ አለቃቸዉ እንዳይጠየቅ ተጽዕኖ ለመፍጠር እየሞከሩ መሆኑን እየታዘብን እንገኛለን።

በመሆኑም በእጃችን የገቡ የተለያዩ ሰነዶች ብኖሩም በመንገዳቸው እንዲመለሱ በምለዉ ሳናወጣ አቆይተናል። አሁን ግን ከመንገዳቸው መመለስ ስላልቻሉ ምን ስሰሩ እንደነበር አንድ በአንድ ለማጋለጥ እንገደዳለን።

ሉዋ ሚዲያ ያለተጨባጭ መረጃ አንድም ግለሰብ ጠቅሶ አይዘግብም።

ሉዋ ሚዲያ!

31/08/2025

የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕረዝዳን አቶ አደም ፋራሀ እና ከፍተኛ አመራሮች የሚጎበኙት በዓይን የምታዩ የረባ የልማት ሥራዎች በክልሉ አልተሰሩም ተባለ፡፡

በባለፈው የጠቅላይ ሚኒስተሩ ሀዋሳ ከተማ ጉብኝት በቪየትናም ባለሀብቶች፤ በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሶላር ኃይል የሚያመርተውን ባለሀብት ሥራ ከማስጀመር ባለፈ፤ በከተማዋ ጠብ የሚል የልማት ሥራዎች አለመኖራቸውን በመመልከት፤ ከተማዋ በለሎች ክልሎች ካሉ የዞን ከተሞች በታች መሆኗ፤ ቀደምት የነበራትን ዝናና ግንባር ቀደምትነት አለመኖሩና ከዝህ ቀደም በነበሩ ካንቲባዎች የተጀመሩ ፕሮጀክቶች ቆሞ በመቅረታቸው፤ ጠቅላይ ሚኒስተሩ በአመራሩ ድርጊት ደስተኛ ሳይሆኑ ተመልሰዋል ተብሏል፡፡

በክልሉ የህዝቡን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በሚደርገው ጥረት ምንም አስተዋጽኦ የሌላቸው፤ የተገልጋይ እርካታን የማይጨምሩ፤ በየወረዳው 13 ግለሰቦች ለብሮነት የምገለገሉ አባላት ሆነ ደጋፍዎች ሳይወያዩበትና ሳይወስኑ በግዳጅ ከመንግሥት ሰራተኞች ህጻናት ጉሮሮ ተነጥቆ ደመወዛቸውን የተቆረበት፤ አርሶ አደሮች በአከባቢ ሚሊሻ ተገደው የመሬት ይዞታ ግብር ጋር በነፍስ ወከፍ 1500 ብር በአስገዳጅነት እንድያዋጡ የተገደዱበትና ዘጎች ገንዘባቸው ያለአግባብ እንዳይቆረጥ ለሰበአዊ መብቶች ኮሚሽን፣ ለህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋምና ለአከባቢ ፍርድ ቤቶች አበቱታ አቅርበው ምላሽ ያጡበትን ፕሮጀክት፤ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕረዝዳን በማስመረቅ፤ የክልሉ ባለስልጣናት ፋይዳቢስ አክራሞት ተቃውሞ እና የህዝባዊ ቅቡልነት እጦት ለመሸፋፈን ለማዕከላዊ መንግሥት “ህዝቡ ከጎናችን ነው፣ በህዝብ ተሳትፎ የተገነቡ ፕሮጀክቶች ናቸው” በማለት የደስታ ለዳሞ አስተዳደር ተጨማሪ የሲዳማ ህዝብ የመከራ ጊዜ ለማራዘም ደፍ ቀና እያሉ አንደሆነ ታውቋል፡፡

በለላ በኩል የጽ/ቤቶች ምርቃ ጎን ለጎን ለሎች የልማት ሥራዎችን ለማስጎበኘት በግብርና ቢሮ ኃላፊ የሚመራ ኮሚተ አዋቅሮ ሊየታ ለማድረግ የተንቀሳቀሰው የደስታ ለዳሞ አስተዳደር፤ በአራቱም ዞኖች በክላስተር የለማ በዓይን የምታይ እርሻ አለመኖሩን ከኮሚተዉ የመርዶ ሪፓርት ቀርቦለት ተደናግጦ ከፍተኛ አመራሩን ከዝህ ቀደም እንደሚያደርገው በሽልማት እና በገንዘብ ለመደለልና ከፍተኛ አመራሩም በክልሉ በዉዳሴ እና “የቤተሰብ ብልጽግና ተረጋግጧል አመራሩና ህዝቡ ተቀናጅቶ እየሰሩ ናቸው” የምለውን ሀሰተኛ ምስክርነት ለማግኘት ለፈደራሉ አመራር ጎቦ ለማቀበል እንድያግዛቸው ቀድሞ የአቶ አደም ፋራሀ ጓደኛ የነበሩትን አቶ ጌታሁን ታደለ ሱማለ ላንድ የቁም ከብቶችን የምነግድ ነዎርነታቸውን ቶጎ ጫለ ያደረጉትን ለዝህ ተልዕኮ ወደ ሀዋሳ መጥራታቸው ታውቋል

ይህ በእንዲህ እንዳለ በቀድሞ ደቡብ ኢትዮጵያ ዴሞክራያስዊ ንቅናቀ (ደኢህደን) ማዕካላዊ ኮሚቴ
ጽ/ቤት ሆኖ እንዲያገለግል በ2008 ዓ.ም በዘነኛ ድርጅታዊ ጉባዔ በ260 ሚሊየን ብር ግንባታው ተጠናቆ ላለፋት ዘጠኝ ዓመት አገልግሎት ስሰጥ የቆየውን ቀለም ቀብቶ ዳግም ርባንን ለማስቆረጥ እንደተዘጋጁ ባለፈዉ መዘገባችን አይዘነጋም።

ሉዋ ሚዲያ!

30/08/2025

#መረጃ: በሲዳማ ክልል የጡረታ መዋጮ የተሰበሰበውን ገንዘብ ለማህበራዊ ዋስትና ገቢ መደረግ የሚገባውን ዘጠኝ መቶ ሚልዮን ብር መዘረፉ ተሰማ፤

በሲዳማ ክልል ለማህበራዊ ዋስትና የመንግሥት ሠራተኞች ከደመወዛቸው የተቀነሰ እና የመንግሥት ድርሻ የጡረታ መዋጮ የተሰበሰበውን በወቅቱ መከፈል የነበረበት ዘጠኝ መቶ ሚልዮን ብር በክልሉ መንግስት አማካኝነት ላልተገባ መንገድ መባከኑ ተነገረ።

ከወረት በፊት የክልሉ መንግሥት የጥሬ ገንዘብ እጥረት አጋጥሞኛል በማለት በሰኔ ወር 2017 ዓ.ም በክልሉ ካቢኔ አስወስኖ ከ2018 ባጀት ብድር ለመቀበል ለገንዘብ ሚኒስተር ጥያቄ ማቅረቡን ዘግበን እንደነበር አይዘነጋም። ገንዘብ ሚኒስተሩ ይህንን የብድር ጥያቄ ተከትሎ አቶ አህመድ ሽዴ ብድሩ እንድፈቀድላቸው ወደ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደብዳቤ የተላኩ ቢሆንም፤ በጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ባለመስማማት ምክንያት እንዲታገድ መደረጉ ተሰምቷል፡፡

የመረጃ ምንጫችን አንደገለጹት በሲዳማ ክልል በክልሉ መንግስት ደረጃ የተንሰራፋው ሌብነት እና ሙስና የመንግሥትን በጀት በጠራራ ፀሀይ እንድመዘበር አድርጓል የተባለ ስሆን፤ የ2017 በጀት አመት የተፈቀደውን በጀት ከታለመለት ዓላማ ውጪ በማዋል፤ ምንም ዓይነት የልማት ሥራዎች ሳይሠራ፤ በሙስና እና አላስፈላጊ ድግስ በማዘጋጀት እንድሁም፤ በሽልማት መልክ ያልተገባ ጥቅም በማሰባሰብ በጀቱን አባክኖ በመጨረስ፤ ገንዘብ ሚንስተር የጠየቀው ብድር ስከለክል፤ ከደሞዝተኛ የተቆረጠ ጡረታ ለማህበራዊ ዋስትና ገቢ መሆን የነበረበትን ዘጠኝ መቶ ሚሊየን ብር ከዓላማው ዉጭ ለግል ጥቅማቸው ብቻ ማዋላቸውን ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያስረዳል። ከመረጃ ምንጫችን መረዳት እንደተቻለው፤ በክልሉ መንግስት ከፍተኛ አመራራሮች ይህንን አስነዋሪ ተግባር በመደረጉ የተነሳ ለረዥም ጊዜ ሀገራቸውን አገልግለው በጡረታ የተገለሉና ቤተሰቦቻቸው በሞት ያጡ ወገኖች ለከፍተኛ ችግር መደረጋቸውን ታውቋል፡፡

ይህ በእንድህ እንዳለ ከፈደራል መንግሥት ግምጃቤት ብድር የተከለከለው የክልሉ መንግስት፤ ከሲዳማ ባንክ እና ከሲዳማ ቡና ዩኒየን 2.5 ቢልዮን ብር ብድር መውሰዱ የተረጋገጠ ስሆን፤ የብድሩ ዓላማ ሁለተኛ ዙር ኮርደር ልማት ማጠናቀቂያ የምል ሰበብ ቢሆንም፤ እስከአሁን ኮርደር ልማትን ለምሰራው ኮንትራክተር የክልሉ መንግስት አምስት መቶ ሚሊየን ብር ብቻ በመከፈሉ ሥራው በሚፈለገው ጥራትና ፍጥነት እየተከናወነ አለመሆኑን እስከ ቦታው ሄዶ ከጎበኙ የዓይን እማኞች ለሉዋ ሚዲያ አስረድተዋል።

ኮንትራክተሩ ለክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ቀሪዉን የክፍያ እንዲፈጸም ጥያቀ አቅርቦ፤ ከፋይናንስ ቢሮ የጥሬ ገንዘብ እጥረት አለን በማለት ባለመከፈሉና ሥራውም ስላልተጠናቀቀ በባለፈው የጠቅላይ ሚኒስተሩ ጉብኝት ወቅት የክልሉ አመራር በዓይን የሚታይ የልማት ሥራዎች ለማስጎብኘት መቸገራቸውን ለማወቅ ተችሏል።

በአጠቃላይ የአቶ ደስታ ለዳሞ አስተዳደር በሌብነት ተጨማልቆ የክልሉን ህዝብ ለሁለገብ ችግር በመዳረጉ የመንግሥት ፋይናንስ ብቃት የለላቸውና በሌባ አመራሮች እንዲመራ በማድረግ ክልሉን የከፋ ችግር እንዲዳረግ በማድረጉ እና ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንስ ያለአግባብ የተወሰደ ገንዘብ በፍርድ ቤት አስወስኖ ዘጠኝ መቶ ሚሊየን የባንክ ሂሳብ አሳግዶ በመውሰዱ የክልሉ ቢሮዎች ዞኖች እና ወረዳዎች የጥሬ ገንዘብ እጥረት አለን በሚል ምክንያት ምንም ዓይነት ሥራ ሳይሰሩ ሁለት ወር ማሳለፋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሉዋ ሚዲያ

29/08/2025

ሐዌላ ቱላ፣ ወታራ ራሳ፣ ያዬ፣ ወራንቻ 85 ኪ.ሜ አቋርጠው በርከት ያሉ ከተሞችን የሚያገናኝ አስፓልት መንገድ ግንባታ 2013 ዓ.ም ተጀምሮ፤ ለአመታት በመቋረጡ የአከባቢው ማህበረሰብ እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረሱ፤ ከህብረተሰቡ የተወጣጡ ሰዎች አማካይነት አቤቱታቸውን ለማዕከላዊ መንግስት አስገብተዋል። 👇👇
-----------------------------------
ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጽ/ቤት
ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት
ለሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት
ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር
ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር
ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
ለኢትዮጵያ የህዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም

ጉዳዩ:- ለህዝብ አደጋ የደቀነው የቱላ-ወተራራሳ-ያዬ-ወራንቻ መንገድን ይመለከታል

የመንገድ መሠረተ ልማት ለሀገር ሁለንተናዊ ልማት እና ለህዝብ የኢኮኖሚ እና ማህበራዊ ዕድገት መሠረት እንደሆነ ይታወቃል። የሲዳማ ክልል መንገድን ጨምሮ በርካታ የመሠረተ ልማት ጥያቄ ያለበት ከመሆኑም ባሻገር ከፍተኛ የህዝብ ሀብት የፈሰሰባቸው በጅምር የቆሙ እንዲሁም በመሠረተ ድንጋይ ደረጃ ብቻ የቀሩ ፕሮጀክቶች የሚገኙበት ሲሆን ከነዚህ ውስጥ የቱላ-ወተራራሳ-ያዬ-ወራንቻ መንገድ ይጠቀሳል፡፡

85 ኪ.ሜ. የሚሸፍነው የቱላ-ወተራራሳ-ያዬ-ወራንቻ መንገድ የካቲት 2 ቀን 2013 ዓ.ም. የትራንስፖርት ሚኒስትር የነበሩት ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፣ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ የትራንስፖርት ሚንስትር ዴኤታ የነበሩት አቶ ካሳሁን ጎፌ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ኢ/ር ሀብታሙ ተገኝ፣ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት እንዲሁም የሀገር ሸማግሌዎች እና የአካባቢው ማህበረሰብ በተገኘበት መሠረተ ድንጋይ ተቀምጦ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታው በይፋ መጀመሩ ይታወሳል፡፡

መንገዱ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ገቢ የሚያስገኙ ምርቶች መገኛ የሆኑ አከባቢዎችን በማስተሳሰር ምርቶቹን በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ እና ወደ አለም አቀፉ ገበያ ለማድረስ፣ ከኢንደስትሪ ዞኖች ለማገናኘት እንደሚያስችል፣ አከባቢው ያለውን ሰፋፊ የኢንቨስትመንት ዕድሎች እና እምቅ አቅም በመጠቀም ሰፊ የሥራ ዕድል ለመፍጠር እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን በማጠናከር ማህበራዊ ትስስሩን ለማጎልበት ያለውን ጉልህ ሚና በማገናዘብ የህዝቡን የዘመናት ጥያቄ ለመመለስ፣ በፌዴራል መንግስት 1.9 ቢሊዮን ብር ተመድቦ፣ በሶስት ዓመት ከስድስት ወራት ውስጥ ለማጠናቀቅ የካቲት 2 ቀን 2013 ዓ.ም. ነበር የተጀመረው፡፡

ይሁን እንጂ ብዙ እምነት የተጣለበት በሶስት ዓመት ከስድስት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃል የተባለው መንገድ ዛሬ ይህ አቤቱታ እስከቀረበበት ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም. በ4 ዓመት ውስጥ አጠቃላይ አፈጻጸሙ ከ10% በታች ይገኛል፡፡ የመንገዱ ግንባታ ከመጓተቱ ባሻገር ወደ መቆም ደረጃ እየደረሰ ሲሆን በዚህ የተነሳ ህዝቡ ለሁለንተናዊ ችግር ተዳርጓል።

የተወሰኑትን ለመጥቀስ ያክል፡-

1) ሲጠናቀቅ የትራንስፖርት ጊዜን ከ4፡30 ወደ 1፡30 ባልሞላ ጊዜ በማሳጠር የህዝቡን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በይበልጥ ያሳድጋል የተባለ የ85 ኪ.ሜ. መንገድ እርቀት ሁለት ቀን እየፈጀ፣ በተለይ በክረምት ወቅት ለቀናት መንገዱ እየተዘጋ ህዝቡ ለከፋ ጉዳት እየተዳረገ ይገኛል፡፡ በዚህም አስቸኳይ ህክምና የሚያስፈልጋቸው ታካሚዎችን የያዘ አምቡላንስ ጭምር መንገድ ላይ እሰከማደር ደርሷል፡፡

2) በቀደምት ዓመታት በየጊዜው በመንገዱ ላይ ጠጠር የማልበስ እና የጥገና ሥራ የሚከናወን ሲሆን ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ይህ ከነአካተው በመቆሙ ህዝቡ በእያንዳንዱ ኪሎሜትር እየወረደ በጭቃ የተያዘውን መኪና እየጎተተ ወደ ጉዳዩ ሳይደርስ መንገድ ላይ ውሎ እያደረ ለተለያዩ ችግሮች ጭምር እየተጋለጠ ይገኛል፡፡

3) የመንገድ ግንባታ መጀመሩን ተከትሎ በርካታ ኢንቨስተሮች በአከባቢው መዋዕለ ነዋያቸውን ለማፍሰስ ፍላጎት አሳይተው በተለያየ ዘርፍ ለመሳተፍ ያደረጉት ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ እና ጅምር ስራዎች የመንገዱ ግንባታ መጓተት እና እየተባባሰ የመጣውን የመንገዱን ብልሽት ተከትሎ እንዲያፈገፍጉ አስገድዷል፡፡ በዚህም የልማት ዕድል እንዲዘጋ እና ሊፈጠር የነበረው ብዙ የሥራ ዕድል እንዲመክን አድርጓል፡፡

4) ተሽከርካሪዎች በየጉዞው እየተበላሹ እና እየተገለበጡ በንብረት ላይ እየደረሰ ያለው ጉዳት ከፍ ያለ ሲሆን በሌላ በኩል ለመለዋወጫ ዕቃ የሚወጣው ገንዘብ የተሽከርካሪ ባለንብረቶችን ለከፋ ኪሳራ እየዳረገ በርካቶች ከስረው ከስራ ውጪ እንዲሆኑ እያደረገ ይገኛል።

5) በመንገዱ ብልሽት ማህበራዊ ህይወት የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ወደ መቋረጥ ደረጃ እየደረሰ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፤ ዘመድ-ከዘመድ፣ ቤተሰብ-ከቤተሰብ በሀዘን በደስታ መገናኘት አዳጋች እየሆነ መጥቷል።

6) አርሶ አደሩ ያፈራውን ምርት ወደ ገበያ በጊዜ ለማውጣት መንገዱ ስለማያስችለው በብርቱ ጥረት የተገኘ ምርት እየተበላሸ ሀብት እየባከነ እንዲሁም ነጋዴ የፍጆታ ዕቃዎችን በጊዜ ለተጠቃሚው ማድረስ አዳጋች እየሆነ መጥቷል፡፡

7) በተለያየ ዘርፍ በአካባቢው የሚደረጉ ምርምሮች፣ በተለያየ ምክንያት ከሌላ ቦታ ወደ አካባቢዎቹ መሄድ የሚፈልጉ መንግስታዊ ያልሆኑ የልማት ድርጅቶች፣ ቱሪስቶች፣ በክልሉ መንግስት የሚደረግ ድጋፍ እና ክትትል ጭምር የመንገዱ ሁኔታ አስቻይ ባለመሆኑ ወደ መቋረጥ ደረጃ እየደረሱ ይገኛሉ፡፡

📌በአጠቃላይ የቱላ-ወተራራሳ-ያዬ-ወራንቻ መንገድ መስመር ተጠቃሚ ህዝብ እየደረሰበት ያለው ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፈተና ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በመንገዱ ብልሽት አካባቢው በቱሪዝም፣ በግብርና፣ በማዕድን እና በተለያዩ ኢኮኖሚያዊ ሀብቶች የበለጸገ ቢሆንም ተጠቃሚ እንዳይሆን ከመገደቡም በላይ ህዝብ ከህዝብ እንዲቆራረጥ እና የማህበራዊ ቀውስ አደጋ እየደቀነ ይገኛል፡፡ ህዝቡ እየደረሰበት ያለውን መከራ በተለያዬ መንገድ ለሚመለከተው ሁሉ ያሳወቀ ቢሆንም ይህ አቤቱታ እስከቀረበበት ቀን ድረስ መፍትሄ ካለማግኘቱም ባሻገር ጉዳዩ ተገቢ ትኩረት አግኝቶ እንቅስቃሴ ሲደረግ አለመታየቱ የህዝቡን የመልማት እና ደህንነቱ በተጠበቀ አካባቢ የመኖር መብትን እየገደበ በመሆኑ በህዝቡ ዘንድ ከፍተኛ ቅሬታ ፈጥሯል፡፡

🎯በመሆኑም የቱላ-ወተራራሳ-ያዬ-ወራንቻ መንገድ ችግር አስቸኳይ መፍትሄ ካልተሰጠው፤ ከዚህ የከፋ ጉዳት እንደሚያስከትል ታውቆ፣ የመንገዱ ግንባታ በተባለው የጊዜ ሰሌዳ ያልተጠናቀቀበት ምክንያቶችን በመለየት፣ የመንገዱ ግንባታ እንዲጓተት ያደረጉ የግንባታ ተቋራጭና አማካሪ ድርጅቱን ጨምሮ ከክልል እስከ ፌደራል ያሉ አካላትን ተጠያቂ በማድረግ፣ የችግሩን አሳሳቢነት ከግምት በማስገባት ለመንገዱ ግንባታ በአስቸኳይ ተጨማሪ ማሽነሪዎችን በማሰማራት በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ እንዲደረግ፤ ከዚህ ጎን ለጎን ዓለምአቀፋዊ የግንባታ አሰራር መሠረት ደረጃውን የጠበቀ ተለዋጭ (Detour) መንገድ እንዲሰራ የህዝብ አደራ የተሰጠው አካል ሁሉ የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ መንግስት አስፈላጊውን የመፍትሄ እርምጃ እንዲወስድ እንጠይቃለን።

ከሠላምታ ጋር!
Via SBQ
ሉዋ ሚዲያ!

05/07/2025

ነገረ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን፤ “ዓሣ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል” ‼️

በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ እና በወላታ ዲቻ መሐል ያለውን እስፖርታዊ ውድድር፤ እንደ ሀገርም ሆነ እንደ አፍርካ ለኳስ እድገት ያለው አስተዋጽኦ እጅግ ታላቅ መሆኑ ለህዝባችን ግልጽ ነው። ሆኖም ግን የእግር ኳስ ፌጄሬሽኑ፤ ስለ ኳስ እና የኳስ ህጉን ሳያውቅ የሚመራ፤ ከየትኛውም እስፖርታዊ እውቀት ነፃ መሆኑን (ፖለቲካዊ አሻጥር የተሸበበ) እንደሆነ በተፈጠረው ችግር መረዳት ተችሏል።

ከዚህም በላይ ችግሩን እጅግ ከባድ የሚያደርገው፤ ችግሩ ለሀገር ውስጥ ክሌቦች ላይ እና ደጋፊዎች ላይ ከሚያመጣ አውንታዊ ተጽኖ ባሻገር፤ እንደ ሀገር ያለንን የኳስ እድገት እውቀትና ብሎም ያስመዘገብነውንም ውጤት ጨምሮ የሚያሰርዝ፤ እንደ ሀገርም ትልቅ ችግር ላይ የሚጥለን ጉዳይ ሆኗል። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ከጂቡቲ ጋር ላደረገችበት ጫወታ ከማድረግ በፊት ፌዴረሽኑ ከሲዳማ ቡና፣ ከሀዋሳ ከነማ እና ከመቻል ክለቦች በ 24 Feburary 2025 ላይ የቅጣት ውሳኔ ማስተላለፍ ይታወቃል።

ነገር ግን ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ 25 ማርች 2025 ባደረጉት ግጥሚያ ሀገራችንን ወክለው የተጫወቱት ተጫዋቾች መሐል፤ ቅጣት ተወስኖባቸው የነበሩ ተሰልፈዋል። ሌምሳሌ ከታገዱ ተጫዎቾች መስፍን ታፈሰ ከሲዳማ ቡና ክለብ የተሰለፈ ሲሆን፤ በረከት ደስታ ደግሞ ከመቻል FC ተሰልፎ፤ በአንድ ጫወታ ላይ (Hatrick ) ሦስት ጎል በማስገባት ኢትዮጵያ ጂቡቲን 6 ለ 1 እንድታሸንፍ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።

እንደ ሀገር በብሔራዊ ደረጃ ሆነ በክለብ ደረጃ የተቀጣን ወይንም ቅጣት ላይ ያለን ተጫዋች ማስለፈ ጥፋት ብቻ ሳይሆን፤ በFIFA ህግ ትልቅ ውሳኔ የሚያሰጥ ጉዳይ ነው። ይህ አድራጎት ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ከFIFA የሚያሳግዳትና ውጤቱንም የሚያሰርዝ ስለሆነ፤ ጉዳዩ ከውስጥ ጉዳይ ( ከሲዳማና ከዲቻ) አልፎ በሀገርንም የሚጎዳ ይሆናል ማለት ነው። ደረጃውን ወደ ታች ዝቅ ማስደረግ ብቻ ሳይሆን፤ ውጤቱን ሙሉ በሙሉ የሚያሰርዝ ይሆናል።

ስለዚህ ፌዴሬሽኑ ምን እያደረገ እንደሆነ ያልገባው ማንን ጠቅሞ ማንን እንደምጎዳ እንኳን ለይቶ የማያውቅ፤ ከኳስ ህግ ደንብና ሥርዓት ብቻ ሳይሆን ከእርሱ ጋርም የተጣላ ለመሆኑ ሥራቸው ምስክር ናቸው። ይህን መረጃን በግልጽ Google ላይ ያገኙታል። በሌላም ጥፋቱን ደግሞ በሲዳማ ውጤት ላይ ባስተላለፈው እብደት ተነስትተን ብቻ ሳይሆን፤ እስከዛሬ የሰራቸውን ስህተት መፈተሽ ይቻላል። ይህም የኢትዮጵያ ኳስ የጥፋት Foundation በሚል ስም እራሱ ፍርድ ቤት ሥራው የሚገትረው ይሆናል።

የሲዳማ ቡና ክለብ ሆነ ይህ ጉዳይ እንደ ሀገር ያገባኛል የሚል ሰው፤ ዋንጫው ከሲዳማ ቡና ከመንጠቅ ይልቅ፤ ይህ እብሪተኛ አላዋቂ ቡድን፤ በፌዴሬሽን ስም የኳስን ፍቅር የህዝሀ ስሜት የሀገርን ክብር ከሚገሉት ላይ ስልጣናቸውን ቀምቶ፤ የህዝብን የሀገርን የኳስንም ስሜት ለህዝባችን እንድተው ጥሪ እያደረግን፤ የሲዳማ ቡና ክለብ መረጃውን በመጠቀም ደጋፊውን እና መላው የኳስ አፍቃሪያን ክብር እንድጠብቅ በአግባቡ በመረጃና በማስረጃ እንድሟገት እናስገነዝባለን።

በሌላ በኩል የሲዳማ ቡናም ሆነ የወላይታ ዲቻ ደጋፊዎች፤ በህግና በሀገራዊና እንዲሁም ዓለም አቀፋዊ መርህ፤ ስሜቱን በኳስና ልብስ ብቻ በማድረግ፤ የሁሉቱን ወንድማማች ህዝቦችን ሰላም ለማጠልሸት፤ አንዳንድ ችግር ነጋዴዎችን በጋራ እንድንታገል ጥሪያችንን እናቀርባለን።

የህግ በላይነትን፣ ደንብና ሥርዓትን እንኳ ለህዝቡ እንድተውልን ድምፃችንን ከፍ አድርገን እናሰማለን።

ሉዋ ሚዲያ
July 05/2025

Address

Chercher
Addis Ababa
...

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Desalegn Hagirso posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share