Desalegn Hagirso

Desalegn Hagirso news company of
internal Ethiopian affairs

05/07/2025

ነገረ ኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን፤ “ዓሣ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል” ‼️

በሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ እና በወላታ ዲቻ መሐል ያለውን እስፖርታዊ ውድድር፤ እንደ ሀገርም ሆነ እንደ አፍርካ ለኳስ እድገት ያለው አስተዋጽኦ እጅግ ታላቅ መሆኑ ለህዝባችን ግልጽ ነው። ሆኖም ግን የእግር ኳስ ፌጄሬሽኑ፤ ስለ ኳስ እና የኳስ ህጉን ሳያውቅ የሚመራ፤ ከየትኛውም እስፖርታዊ እውቀት ነፃ መሆኑን (ፖለቲካዊ አሻጥር የተሸበበ) እንደሆነ በተፈጠረው ችግር መረዳት ተችሏል።

ከዚህም በላይ ችግሩን እጅግ ከባድ የሚያደርገው፤ ችግሩ ለሀገር ውስጥ ክሌቦች ላይ እና ደጋፊዎች ላይ ከሚያመጣ አውንታዊ ተጽኖ ባሻገር፤ እንደ ሀገር ያለንን የኳስ እድገት እውቀትና ብሎም ያስመዘገብነውንም ውጤት ጨምሮ የሚያሰርዝ፤ እንደ ሀገርም ትልቅ ችግር ላይ የሚጥለን ጉዳይ ሆኗል። ለምሳሌ ኢትዮጵያ ከጂቡቲ ጋር ላደረገችበት ጫወታ ከማድረግ በፊት ፌዴረሽኑ ከሲዳማ ቡና፣ ከሀዋሳ ከነማ እና ከመቻል ክለቦች በ 24 Feburary 2025 ላይ የቅጣት ውሳኔ ማስተላለፍ ይታወቃል።

ነገር ግን ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ 25 ማርች 2025 ባደረጉት ግጥሚያ ሀገራችንን ወክለው የተጫወቱት ተጫዋቾች መሐል፤ ቅጣት ተወስኖባቸው የነበሩ ተሰልፈዋል። ሌምሳሌ ከታገዱ ተጫዎቾች መስፍን ታፈሰ ከሲዳማ ቡና ክለብ የተሰለፈ ሲሆን፤ በረከት ደስታ ደግሞ ከመቻል FC ተሰልፎ፤ በአንድ ጫወታ ላይ (Hatrick ) ሦስት ጎል በማስገባት ኢትዮጵያ ጂቡቲን 6 ለ 1 እንድታሸንፍ ትልቅ ሚና ተጫውተዋል።

እንደ ሀገር በብሔራዊ ደረጃ ሆነ በክለብ ደረጃ የተቀጣን ወይንም ቅጣት ላይ ያለን ተጫዋች ማስለፈ ጥፋት ብቻ ሳይሆን፤ በFIFA ህግ ትልቅ ውሳኔ የሚያሰጥ ጉዳይ ነው። ይህ አድራጎት ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ከFIFA የሚያሳግዳትና ውጤቱንም የሚያሰርዝ ስለሆነ፤ ጉዳዩ ከውስጥ ጉዳይ ( ከሲዳማና ከዲቻ) አልፎ በሀገርንም የሚጎዳ ይሆናል ማለት ነው። ደረጃውን ወደ ታች ዝቅ ማስደረግ ብቻ ሳይሆን፤ ውጤቱን ሙሉ በሙሉ የሚያሰርዝ ይሆናል።

ስለዚህ ፌዴሬሽኑ ምን እያደረገ እንደሆነ ያልገባው ማንን ጠቅሞ ማንን እንደምጎዳ እንኳን ለይቶ የማያውቅ፤ ከኳስ ህግ ደንብና ሥርዓት ብቻ ሳይሆን ከእርሱ ጋርም የተጣላ ለመሆኑ ሥራቸው ምስክር ናቸው። ይህን መረጃን በግልጽ Google ላይ ያገኙታል። በሌላም ጥፋቱን ደግሞ በሲዳማ ውጤት ላይ ባስተላለፈው እብደት ተነስትተን ብቻ ሳይሆን፤ እስከዛሬ የሰራቸውን ስህተት መፈተሽ ይቻላል። ይህም የኢትዮጵያ ኳስ የጥፋት Foundation በሚል ስም እራሱ ፍርድ ቤት ሥራው የሚገትረው ይሆናል።

የሲዳማ ቡና ክለብ ሆነ ይህ ጉዳይ እንደ ሀገር ያገባኛል የሚል ሰው፤ ዋንጫው ከሲዳማ ቡና ከመንጠቅ ይልቅ፤ ይህ እብሪተኛ አላዋቂ ቡድን፤ በፌዴሬሽን ስም የኳስን ፍቅር የህዝሀ ስሜት የሀገርን ክብር ከሚገሉት ላይ ስልጣናቸውን ቀምቶ፤ የህዝብን የሀገርን የኳስንም ስሜት ለህዝባችን እንድተው ጥሪ እያደረግን፤ የሲዳማ ቡና ክለብ መረጃውን በመጠቀም ደጋፊውን እና መላው የኳስ አፍቃሪያን ክብር እንድጠብቅ በአግባቡ በመረጃና በማስረጃ እንድሟገት እናስገነዝባለን።

በሌላ በኩል የሲዳማ ቡናም ሆነ የወላይታ ዲቻ ደጋፊዎች፤ በህግና በሀገራዊና እንዲሁም ዓለም አቀፋዊ መርህ፤ ስሜቱን በኳስና ልብስ ብቻ በማድረግ፤ የሁሉቱን ወንድማማች ህዝቦችን ሰላም ለማጠልሸት፤ አንዳንድ ችግር ነጋዴዎችን በጋራ እንድንታገል ጥሪያችንን እናቀርባለን።

የህግ በላይነትን፣ ደንብና ሥርዓትን እንኳ ለህዝቡ እንድተውልን ድምፃችንን ከፍ አድርገን እናሰማለን።

ሉዋ ሚዲያ
July 05/2025

28/06/2025

በመጠኑ እንሁን የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሺነር ተስፋዬ ዴብሶ፤

ኮሚሺነሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸዉ ባስተላለፉት መልዕት የሲዳማ ህዝብ ራስን በራስ ለማስተዳደር የተከፈለውን የህይወት መስዋዕትነት ዋጋ እና የተገኘውን ነፃነት እንደዋዛ አንመልከት ካሉ በኃላ፤ የራሳችን መንግስት እራሳችን ከማዋረድ እንጠንቀቅ ብሏል።

ኮሚሺነር ተስፋዬ አክሎም የምንኖረዉ ከማህበረሰባችን ጋር ነዉ፣ ወጣቶችም የህዝባችን ክብር ዝቅ የሚያደርግ ድርጊት ከመፈጸም እንጠንቀቅ፣ ባለማወቅ የሚያጠፋትን አድቡ ብለን እንመክረዉ እንጂ ከነጥፋታቸዉ አንደግፈቸዉ ስል ምክረ ሀሳብ ለግሷል።

በትናንትና ወዲያ እለት የተከሰተውን ህዝብ በተሰበሰበበት ስፍራ ጦር መሳሪያ የተኮሰዉን ግለሰብ ጋር የተገናኘ ጉዳይ አስመልክቶ የታገልነዉ ለነጻነት እና ለእድገት ባለን ፍላጎት እንጅ፣ ያገኘነውን መንግስት አላግባብ ለመጠቀም አይደለም፣ መታገል የዜግነት ግዴታችን ነዉ፣ ለነጌያችን እና ለመጪው ትዉልድ ስምረት ነዉ፤ ነገር ግን በህግ ጥላ ስር መተዳደር ለህዝባችን ያለዉ ጠቀሜታ የላቀ ነዉ።

በአደባባይ በመዉጣት ጦር መሳሪያ መተኮስ፣ በትግሉ ወቅት የፈጸምነው ገድል ጋር አይገናኝም፤ ከዛ ጋር አገናኝቶ መመልከት ተገቢ አይመስለኝም፤ የታገልነው በህግ ልንተዳደር ነዉ፣ የህዝባችን ኑሮ እንድሻሻል በማሰብ ነዉ ካሉ በኃላ። የራሱ ቤት ላይ እሳት የሚሎክስ ሰዉ አለወይ!? ብሎ አመክንዮ የለሽ ድጋፍ ያደረጉትን አካላትን ጠይቀዋል።

የኮሚሺነሩ ጽሁፍ ቀጥታ ይህንን ይመስላል 👇
Bikkunni ikkino!
Sidaamu daga wolaphote daafira lubbote baatooshshe baatte afidhino umise umose gaahshate kaayyo laqqete gede assine la'noonke. uminke gashshoote uminke shollinshoonke hee'neemmohu daga dagoomu ledooti aja dume daganke ayirinye kisannore assinoonke afimale gede ikkannohano mimmitonke ye'e yino ikkinnina irkinsoonke. sharrammoommohu wolaphotenna lophotee wolsineeti uminke gashshoote seerimale gede horoonsi'noonke dagate daafira sharrama qansichimmate qeechaati ga'a ilamara seekkaraati seerunni gala ayeerano aleenni horaammeette dagankeeti tuuta fulle qawwe tokkonsanni ikkito sharramaanchimmate ledo xaadinse la'a gara dilabbinoe sharrammoommohu seerunni gallammoraati daganke heeshsho woyyaabbaraati umisi minira giira qasannohu nooni?

Luwa Media

13/06/2025

: ርዕሰ መስተዳድሩ አቶ ደስታ ለዳሞ ሀገር ጥሎ ለመኮብለል ስሞክሩ በደህንነት አማካይነት ተይዞ ተመልሶ እንደነበሩ ያዉቃሉ?

ሙሉ መረጃዉ ከነ የተረጋገጠ ሰነድ እጃችን ገብቷል ነገ ጠብቁን...!😎

መረጃ መላኪያ Telegram bot link፡ https://t.me/luwamediabot

Facebook: Luwa Media

Website: luwamedia.com

Telegram: https://t.me/luwamedia1

YouTube: https://youtube.com/?si=1SJ4IVlT234ndTTP

Tiktok : https://www.tiktok.com/.media?_t=ZM-8vpcBJiXxkF&_r=1

Gmail: [email protected]

13/06/2025

ሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ህገወጥ እስር ማዘዣ ደርሶናል ስሉ ለሉዋ ሚዲያ ገለጹ፤

ሲዳማ ክልልዊ መንግስታዊ ስርዓት አልበኝነት እና ህግ ጥሰት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነዉ፤ በገቡት ቃል-ክዳን መሰረት ቀጥተኛ ፍትህ እና እዉነተኛ ዳኝነት ለህዝባቸዉ የሚሰጡ እና ለአገዛዙ አፈና እና ህገወጥ አካሄድ ያልተመቹ ዳኞች ላይ አላስፈላጊ ማስፈራሪያ እና ወከባ እየደረሰባቸው መሆኑን ሉዋ ሚዲያ ቀጥተኛ መረጃ አግኝቷል።

ክልሉን ሶስቱንም የመንግስት ማለትም ህግ አዉጪ፣ ህግ ተርጓሚ እና ህግ አስፈጻሚ አካላት ጠቅልሎ በእጁ የያዘዉ አቶ ደስታ ለዳሞ አገዛዝ፤ የክልሉ ፍትህ ቢሮ በኩል ዳኞችን ጨምሮ በህገወጥ አፈና ያሻዉን ማድረጉን ቀጥሏል።

ሙያቸዉን አክብሮ ህግን ማስከበርየ ህዝብን ፍትህ ማስፈን እንደ ወንጀል የሚቆጠርበት አቶ ደስታ ለዳሞ አገዛዝ የሚትመራ ሲዳማ ክልል ብቻ ይመስላል።

አሁን ስራ ላይ የዋለዉ የተሻሻለው የሲዳማ ክልል ዳኞች አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 4/2016 አንቀፅ 38 ላይ እንደተደነገገው በክልሉ በዬትኛው ደረጃ ላይ ያለ ፍርድ ቤት ዳኛ፤ ከባድ ወንጀል ስሰራ እጅ ከፍንጅ ካልተያዘ በስተቀር፤ ያለ ዳኞች አስተዳደር ጉባአኤ ፍቃድ ውጪ፣ ወይም ያለመከሰስ መብቱ (immunity) ካልተነሳ እንደማይያዝ ወይም እንደማይከሰ‍ስ በግልፅ ተደንግጓል።

ይህ በእዲህ ሳለ የሲዳማ ክልል የተጻፈውን ህግ የማይገዛው፣ በጉልበት እና በስርዓተ አልበኝነት የሚያምነዉ የክልሉ ፍትህ ቢሮ፤ አላስፈላጊ ጫና በዳኞች ላይ ለማሳደር እና ለሚፈጽሙት ኢህገመንግስታዊ ስራዎች ተባባሪ ለማድረግ በማሰብ፣ ለፖሊስ ኮምሽን ትዕዛዝ በማስተላለፍ ይህንን ህግ በመጣስ ዳኞች ላይ የዕስር ትዕዛዝ አውጥቷል።

መረጃ መላኪያ Telegram bot link፡ https://t.me/luwamediabot

Facebook: Luwa Media

Website: luwamedia.com

Telegram: https://t.me/luwamedia1

YouTube: https://youtube.com/?si=1SJ4IVlT234ndTTP

Tiktok : https://www.tiktok.com/.media?_t=ZM-8vpcBJiXxkF&_r=1

Gmail: [email protected]

07/06/2025

አዋጭ ኅብረት ሥራ ማህበር ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አባላት የማህበሩ አሰራር ዙሪያ ቅሬታቸዉን ለሉዋ ሚዲያ ገለጹ፤

አዋጭ ኅብረት ሥራ ማህበር ሀዋሳ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አባላት የማህበሩ አሰራር ዙሪያ ቅሬታቸዉን ለሉዋ ሚዲያ ገለጹ፤ አባላቱ የማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን ብናሟላም ማህበሩ ግዴታውን በደንቡ መሠረት እየፈጸመ አይደለም ብሏል።

አዋጭ ኀብረት ሥራ ማህበሩ የሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል የቁጠባ እና የብድር አገልግሎት፣ አነስተኛ የብድር መድህን አገልግሎት፣ የትምህርት ስልጠና እና የማማከር አገልግሎት። እንደሆነ የማህበሩ ማህበራዊ ድህረገጽ ያገኘው መረጃ ያመላክታል።

በተጨማሪም አባላቱ ያነሱት ቅሬታ ተከትሎ ሉዋ ሚዲያ ያደረገዉ ማጣራት ስራ በማህበሩ በደንብ መሠረት አንድ አባል ብድር ለማግኘት ለተከታታይ 6 ወራት በየወሩ ገንዘብ መቆጠብ እንዳለበት እና የብድር ጥያቄ ለማቅረብ ህብረት ስራ ማህበሩ ብቁ ናቸዉ ያሉዋቸውን አባላት ስም ዝርዝር በማዉጣት፤ ብድር መጠየቅ እንደሚችሉ ይገልጻል። ይሁን እንጂ ለተከታታይ 3 አመታት ቆጥቦ ምንም አይነት የብድር መፍትሔ ያላገኙ የማህበሩ አባላት እንዳሉ ተመልክተናል።

ብድር ጥያቄ ለማቅረብ ብቁ ሆነዉ በህብረት ስራ ማህበሩ ደንብ መሰረት መሰፈረት አሟልተው ፋይላቸው ብቁ የሆኑ አባላት ያስገቡትን ብድር ጥያቄ ሰነድ በአንድ ወር ዉስጥ ተፈትሾ መጠናቀቅ እንዳለበት የህብረተስራ ማህበሩ ደንብ ላይ ተደንግጓል፤ ይሁን እንጂ ቀጥታ አባላቱ ወደ የጠየቁት ብድር አይነት ህደት ለመግባት ያስገባንዉ የብድር ጥያቄ ሰነድ ሳይጣራ ለወራት ቆይቷል በማለት ቅሬታ አቅራብ ማህበርተኞች ገልጿል።

ማህበሩ አባላት አክሎም ዉስጥ አሰራር ግልጽ አይደለም፣ እኛ ሀዋሳ ቅርንጫፍ ቆጥበን ሁኔታዉን በቅርንጫፋ ለመከታተል ስንሄድ የእናንተ ጉዳይ አዲስአበባ ነዉ ያለዉ እንባላለን፤ አዲስ አበባ ህደን ስንጠይቅ ደግሞ ወደ ቅርንጫፉ ህዱ ይደወልላቸዋል ይባላል ግን አይደዉሉም ብሏል። ቀርበን ስጠይቅ የተለያዩ ምክንያቶች ይደረድራሉ፣ እያጣራን ነዉ፤ አጣርተን ስንጨርስ እንደዉልላቸዋለን ህዱ ይላሉ ከዛ ለተዓምር አይደዉሉም፤ ሌላ ግዜ ስንሄድ ተመሳሳይ መልስ ነዉ የሚሰጡን፤ እዝህ መካከል ለተጨማሪ ወጪዎች ተዳርገናል ይላሉ።

ቅሬታ አቅራቢ የማህበሩ አባላት በርካታ የግልጽነት ችግር እንዳለበት ገልጾ የቆጠብነዉ ገንዘብ ለማዉጣት ብንፈልግ እንኳ ያም አስቸጋሪ ነዉ። ከሶስት ወር በላይ መንከራተት ይጠብቅብናል ብሏል። ያም ሆኖ እንዉሰድ ብንል የገንዘብ የመግዛት አቅም ከግዜ ወደ ግዜ እያሽቆለቆለ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞ አዉጥቶ ለመዉሰድ ራሱ ክሳራ ነዉ። ለምሳሌ የዛሬ አመት አንድ ሚልዮን ብር ቆጥበን ከሆነ ያብር ዘንድር ከግማሽ በላይ የመግዛት አቅም ወርዷል በጣም ትልቅ ችግር ዉስጥ ወድቀናል ይላሉ።

ከዚህ ባለፈ በብዙ ልፋት መጨረሻ ወደግዥ ፕሮሰስ ስንገባ፤ የህብረተ ስራ ማህበሩ የተጓተተ እና ግልጽ ያልሆነ አሰራር በፈጣን አገልግሎት ዕጦት ምክንያት ሽያጪዎች ውል ይሰርዛሉ፣ ገንዘቡ በጊዜ ስለማይከፈል ለአዋጭ ደምበኞች አንሸጥም እንባላለን ብሏል።

በዚህ መሠረት እኛም ከህብረተስራ ማህበሩን ሃሳብ ለማካተት ያደረግነዉ ሙከራ አልተሳካም። በተደጋጋሚ ያደረግነዉ ባለመሳካቱ የተነሳ የማህበሩን ምላሽ አላካተትንም። ቀጣይ የተለየ መረጃ ስናገኝ የምንመለስ ይሆናል።

የማህበሩን መረጃ ለማግኘት ያደረግነዉ አሰሳ በድረገጻቸዉ ላይ ያገኘንዉ መረጃ የሚከተለዉ ነዉ። አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኃላፊነቱ የተወሰነ መሠረታዊ የኅብረት ሥራ ማኅበር ህብረተሰቡ ከሚያገኘው ገቢ ላይ የተወሰነ ገንዘብ በመቆጠብ ራሱን በራሱ እንዲረዳና የቁጠባ ባህል በማዳበር ፈጣን የሆነ የብድር አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ በአቶ ዘሪሁን ሸለመ ዋና መስራችነት 41 አባላትን በማሰባሰብ መጋቢት 13 ቀን 1999 ዓ.ም በአራዳ ክፍለ ከተማ አዋጅ 147/91 ተመሰረተ፡፡

ኅብረት ሥራ ማኅበሩ ባሳየው ከፍተኛ እድገት የሥራ ክልሉን በማስፋት በፌደራል ኅብረት ሥራ ኤጀንሲ ምዝገባ ቁጥር አገ/ቁ/ብ/005/09 ተመዝግቦ ፈቃድ ያለው፣ በፌደራል ህብረት ሥራ ኤጀንሲ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ብቃት ማረጋገጫ መመሪያ ቁጥር 018/2007 መሠረት ተመዝኖ 91.09 ከመቶ በማግኘት በከፍተኛ ደረጃ የብቃት ማረጋገጫ እና የዕውቅና ምስክር ወረቀት ሰኔ 7 ቀን 2013 ዓ.ም. የተሰጠው ኅ/ሥ/ማኅበር ነው፡፡

በተጨማሪም አዋጭ የገንዘብ ቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ማኅበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የዓለም አቀፍ ኅብረት ሥራ ኅብረት (International Cooperative Alliance) አባልና የአፍሪካ የቁጠባና ብድር ኅብረት ሥራ ኮንፌደሬሽን (African Confederation Saving & Credit Cooperative Association) ተባባሪ አባል የሆነ ማኅበረሰብ አቀፍ የኅብረት ሥራ ማኅበር ነው፡፡

04/06/2025
27/05/2025
26/05/2025

የሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ ሙስና እና በርከት ያለ ወንጀል ተፈጽሟል፤ የድርጊቱ ተባባሪዎች የክልሉ ፊት አመራሮች ወንጀለኞችን በመሸሸግ ላይ ይገኛሉ።

በዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ የሚመራዉ የክልሉ ጤና ቢሮ ያለጨረታ በርካታ ግዥዎችን በማከናወን ይታወቃል። በተጨማሪም ቢሮዉን የደስታ ለዳሞ ቅርብ ሰዎች እንደፈለጉ የሚዘወሩት ተቋም ነዉ። የዚህ ማሳያ የቢሮው ግዥና ፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ቃምሶ ናቸዉ። አቶ ተስፋዬ ቃምሶ ከደስታ ለዳሞ ጋር ቅርብ ስጋ ዘመዳሞች ናቸዉ፤ በፕሬዚዳንቱ ድጋፍ በማን አለብኝነት እንደፈለገ ይዘርፋል፣ በዘረፋ የተገኘዉን ይከፋፈላል። በተጨማሪም አቶ ተስፋዬ ቃምሶ የቀድሞው ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ የአቶ አዲሱ ቃምሶ ታላቅ ወንድም ሲሆን ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ የጤና ቢሮ ዉስጥ በርከት ያለ ሙስና ወንጀል አቀናባሪ እና ዋና አቀባይ ሆኖ በማገልገል ቆይቷል።

የተለያዩ ካፒታል እና መደበኛ ግዥዎችን የቡዱኑን ጥቅም በማስላት፣ ለክልሉ ቁንጮ አመራሮች በርከት ያለ ጥቅም አስገኝቶላቸዋል። ቀድሞ ሰሜናዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ አዲሱ ቃምሶ የዘረፈውን አና ያጭበረበረውን ገንዘብ ወደ አቶ ተስፋዬ ቃምሶ ካዞረ በኋላ በክልሉ ፕረዝዳንት አመቻችነት ከሀገር መውጣቱን በቀደሙ ዘገባችን ያገኙታል። እያከናወነ የነበረው ዘረፋም አቶ ተስፋዬ በሚሊዮኖች የሚገመት የናጠጠ ባለሀብት በመሆን የራሱን ኪስ ማሳበጥ ችሏል።

የሆነ ሆኖ በረዥም አመታት በድብቅ ስፈጽሙ የቆዩትን ዘረፋ በታርክ አጋጣሚ የሰሞኑ ሌብነት ስራ በፀራራ ፀሐይ የፈጸሙትን ወንጀል በጥቆማ ጸረ ሙስና መያዝ ችሏል። ይህንን ለመሸፋፈን ፕረዚዳንቱን ጨምሮ ፍትህ ቢሮ ድረስ ከተጠያቂነት ለማስመለጥ እየሞከሩ ይገኛሉ።

የወንጀል አፈጻጸም እንደምከተለዉ ይቀርባል፤ በገጠርቱ ቤተሰብ ደረጃ የሽንት ቤት ሥራዎችን በገበያ መር ንጽሕና ለማስጠበቅ ለማገዝ UNICEF 50 ሚሊዮን ብር ለጤና ቢሮ ልኮ ነበር። በONE WASH በኩል የሚደገፉ ወረዳዎችን ተንተርሶ የመጣው ይህ ገንዘብ፤ የቢሮው ዋና ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ፣ የፕሮግራሙ ባለቤት አቶ በላይነህ በቀለ፣ አቶ ተስፋዬ ቃሚሶ እና ሶስት ስማቸዉ ለግዘዉ ያልጠቀሱ የቢሮው ግዥና ንብረት ክፍል ባለሙያዎች በመመሳጠር በህገወጥ መንገድ የመጣዉን ገንዘብ ወደ ራሳቸዉ ኪስ አስገብቷል።

ገንዘቡ የመጣው በህጋዊ መንገድ ሳቶፓን፣ ሲምንቶ፣ ብረት፣ አሸዋና ጠጠር እየገዙ በማህበራት በኩል ከላይ የተገለጹት እንዲቀርቡ የታለመ ቢሆንም ካለ ጨረታ ለሳቶፓን 11 ሚሊዮን፣ ለሲምንቶ 5 ሚሊዮን፣ ለብረታብረት 2.1 ሚሊዮን ለአሸዋና ለጠጠር 1.7 ሚሊዮን ወጪ ተደርጎ መበላቱን የመረጃ ምንጮቻችን አረጋግጠዋል።

ቢሮው ባለፈው መስከረም ወር ጨረታ አወጣሁ ቢሎ ከአንድ ማህበር ጋር ተመካክሮ በወቅቱ አንድ ኩንታል ዋጋ 1,400 ብር ሆኖ እያለ እነሱ ግን አንድ ኩንታል ሲሚንቶ በ2,400 ብር ሂሳብ የመጣ በማስመሰል ከእያንዳንዱ በኩንታል 1,000 ብር ለራሳቸው ጥቅም አውሎታል።

ለአንድ ሌላኛው ማህበር ቀጥታ 1,000 ገደማ ኩንታል ተጨማሪ ሲምንቶ በአቶ ተስፋዬ ትዕዛዝ እና ውል ቢያስገባላቸውም የዋጋው መነቃቱ ተከትሎ ክፍያ ባለመክፈላቸው ምክንያት ማህበሩ ፍርድ ቤት ክስ መስርቶ ጉዳዩ በዳኞች እጅ ይገኛል። ከዚህም የቢሮ አመራሮች እያንዳንዳቸው የድርሻቸውን ተከፋፍሏልም ተብሏል። ተጨማሪም ሳቶፓንንና ብረቶችን ብቸኛ አቅራቢ ነው ተብሎ በአቶ በላይነህ በቀለ አመቻችነት ግዥ ከተፈጸመ በኋላ ከ5 ሚሊዮን ብር ገደማ ለቢሮዋ ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ እና ክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተከፋፍሏልም ተብሏል።

ለዝህም ምክንያት የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ከጤና ቢሮው ባለሙያዎች የተሰጠዉን ጥቆማ ከጸረ ሙስና ጋር የተጠናከረ ክትትል በማድረግ ለህዝቡ ከማድረስ ይልቅ ጉዳዩን በውስጥ አፍኖ ለማስቀረት እና የክልሉ አቃቤ ህግ ህገወጥ የህግ ሽፋን በመሰጠት ላይ ይገኛል። በዚህ ጉዳይ የቢሮው ገዥ ቡድን ውስጥ 3 የግዥ ባለሙያዎች የታሰሩ ሲሆን፤ ቢሮ ዋና ኃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻን ቀጥተኛ የክልሉ ባለስልጣናት ትዕዛዝ የጋራ ቅሌታቸውን እንዳይታወቅ ለመሸፋፈን ተብሎ በዋስ እንድትለቀቅ ተደርጓል። ምንም እንኳ ጉዳዩ እንድናከናውን በፍርማ ያረጋገጡ የቢሮዉ ሃላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ ብትሆንም፤ እስከ አሁን ጥፋተኛ ተደረገው የታሰሩት የግዥና ክፍያ ባለሙያው ቡድን ሲሆን ጉዳዩን ከእቅዱ ጀምሮ በትዕዛዝና በደብዳቤ ያጀበው የባለሥልጣኑ ጎራ አልተጠየቀም።

የክልሉ ጤና ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ሰላማዊት መንገሻ የምታወቁበት ጉዳይ መካከል፦ የመድኃኒት ህገወጥ ግዥና ኮንትሮባንድ። የተለያዩ ጤና ተቋማት ግንባታዎች በባለቤቷ በማሰራት። መንግሥታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የሚሰጥ የድጋፍ ገንዘብ ከታለመለት ዓላማ ውጪ በማዋል እና የጤና ባለሙያዎች ጥያቄዎችን በማናናቅና በማራከስ ትታወቃለች፤

የአቶ ደስታ ለዳሞ አመራር ከቀበሌ እስከ የክልሉ መጨረሻ እርከን ያለዉ ሀብት ዘረፋ ረዥም እጅ ሰደዉ የምዘርፉ ስብስብ መሆናቸውን በተደጋጋሚ መዘገባችን ይታወቃል።

Contact as: መረጃ መላኪያ Telegram bot link፡ https://t.me/luwamediabot

TikTok: https://www.tiktok.com/.media?_t=ZN-8vpDPL9UWms&_r=1

Facebook: https://www.facebook.com/share/16a32HKjCP/

Website: luwamedia.com

Telegram: https://t.me/luwamedia1

YouTube: https://youtube.com/?si=1SJ4IVlT234ndTTP

Gmail: [email protected]

ከሉዋ ሚዲያ ጋር ወደፊት!

24/05/2025

አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ መኖሪያ ቤት ከበባ ዉስጥ መሆኑን ተነገረ፤

ዛሬ ከሰዓት የተደረገዉ የክልሉ ስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የሲዳማ ክልል ሠላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ በመሆን በማገልገል ላይ የሚገኙት አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ ከስልጣኑ እንድታገድ ተወስኗል።

በአሁኑ ሰዓት በቤቱ ከፍተኛ መሳሪያ ክምቸት ይኖራል የሚል ጥርጣሬ ትዕዛዝ በመተላለፉ መኖሪያ ቤቱ በጥበቃ ኃይሎች ተከቦ እንደሚገኝ ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያሳያታል። ጸጥታ ሀይሎች የቤት ብርበራ ለማከናወን የፍርድ ቤት የፍተሻ ፈቃድ አውጥተው ቅኝት ላይ መሆናቸው ተነግሯል። አቶ አለማየሁ በአሁኑ ሰዓት ወዳልታወቀ ስፍራ እንደተሰወረ የመረጃ ሚንጮቻችን ያመላክታል።

Contact as: መረጃ መላኪያ Telegram bot link፡ https://t.me/luwamediabot

TikTok: https://www.tiktok.com/.media?_t=ZN-8vpDPL9UWms&_r=1

Facebook: https://www.facebook.com/share/16a32HKjCP/

Website: luwamedia.com

Telegram: https://t.me/luwamedia1

YouTube: https://youtube.com/?si=1SJ4IVlT234ndTTP

Gmail: [email protected]

ከሉዋ ሚዲያ ጋር ወደፊት!

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Desalegn Hagirso posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share