Voice of Ethiopia-VOE

Voice of Ethiopia-VOE Voice of Ethiopia-VOE
የኢትዮጵያዊያን ድምጽ!!

ታዳጊው ኮከብ ላሚን ያማል ፈርሟልምትሀታዊ ብቃቱን ገና በታዳጊነቱ ያስመሰከረው ላሚን ያማል እሰከ ፈረንጆቹ 2031 በባርሳ ቤት ለመቆየት ፈርሟል። Voice of Ethiopia-VOE
27/05/2025

ታዳጊው ኮከብ ላሚን ያማል ፈርሟል

ምትሀታዊ ብቃቱን ገና በታዳጊነቱ ያስመሰከረው ላሚን ያማል እሰከ ፈረንጆቹ 2031 በባርሳ ቤት ለመቆየት ፈርሟል።

Voice of Ethiopia-VOE

በጀርመን ወፍም የመጠለያ መብት አላትበጀርመኗ ቲዩቢንገን ከተማ በሚገኝ የዩኒቨርሲቲ ክሊንክ ጣሪያ ላይ አንዲት ወፍ ጎጆዋን ቀልሳ መኖር ከጀመረች ከራርማለች። ይህች ወፍ እንደሌሎች ዝርያቸው ...
28/10/2024

በጀርመን ወፍም የመጠለያ መብት አላት

በጀርመኗ ቲዩቢንገን ከተማ በሚገኝ የዩኒቨርሲቲ ክሊንክ ጣሪያ ላይ አንዲት ወፍ ጎጆዋን ቀልሳ መኖር ከጀመረች ከራርማለች። ይህች ወፍ እንደሌሎች ዝርያቸው በመጥፋት አደጋ ላይ ከሚገኙ የወፍ ዓይነቶች አንዷ ናት። የዩኒቨርሲቲ ክሊኒኩ የሕንጻ ማስፋፋት ሥራ ለማከናወን በተሰናዳበት አጋጣሚ በጣሪያው ጎጆዋን ቀልሳ የምትኖረውን ወፍ ይደርሱባታል። ክሊኒኩም በማስፋፋት ፕሮጀክቱ መቀጠሉን ይገታል። 250 ሚሊየን ዩሮ የሚያወጣው ፕሮጀክትም ለዘጠኝ ዓመታት ባለበት ቆመ። በአካባቢው የሚገኘው ደን ጥበቃውም ቀጠለ፤ ወፏም ያለ ስጋት በጣሪያው ላይ ትኖር ጀመር። የወፎን ሁኔታ በቅርብ የሚከታተሉ ባለሙያዎች ታዲያ ድንገት ወፏ ትሰወርባቸዋለች።

ዘሯ ሊጠፋ ነው የተባለላት ወፍ አለመኖር ግን ወዲያው የታቀደውን የሕንጻ ማስፋፋት ፕሮጀክት መጀመር አላስቻለም። በጥንቃቄና በትዕግሥት ወፏ ወደ ቀለሰችው ጎጆዋ ትመለስ ይሆናል በሚል ተጠበቀች። ጉዳዩ የግዛቷ ፖለቲከኞችና ምክር ቤት መነጋገሪያ ሆነ። ድመት በልቷት ይሁን ወይም አካባቢውን ለቃ ባልታወቀ ምክንያት የወፏ ከጎርጎሪዮሳዊው 2022 ጀምሮ አለመታየት በደስታ የማስፋፋት ሥራውን ለመጀመር አላጣደፈም። ይልቁንም የለመደችው አካባቢ ነውና ተመልሳ ብትመጣ ጎጆዋ ከፈረሰ የት ትገባለች የሚል ክርክር አስነሳ።

የከተማዋ ከንቲባ ወፏ አሁን እኛ ሳናባርራት ቦታውን ስለለቀች ሥራው መቀጠል ይችላል ቢሉም የጀርመን የተፈጥሮ ጥበቃ ሕግ ባለሙያዎች ግን አንቀጽ እየጠቀሱ ሞገቱ። የአእዋፍ ጥናት ባለሙያዎችም በዚህ እየተሳተፉ ነው።

ይህች ወፍ ፈጣሪ አድሏት ጀርመን ሀገር በመኖሯ ጎጆዋ ሳይፈርስ የዩኒቨርሲቲ ክሊኒኩን የማስፋፊያ ፕሮጀክት አጓተተ። ግንባታውን ለማድረግ በአካባቢው ከሚገኘው ደን የተወሰነው ይወገዳል መባሉም ሌላ ሙግት አስነስቷል። በጀርመን ወፍም መብት አላት።

ምንጭ፦ ዶይቼ ቬለ አማርኛ

ትሁቱ የመብት ሰው Daniel Bekele ተሰናብተዋልየኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) ስለ በጎ ጥረትዎ በእጅጉ እናመሰግናለን፡፡ በእርስዎ የሥራ ዘመን ያየነው...
05/07/2024

ትሁቱ የመብት ሰው Daniel Bekele ተሰናብተዋል

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ዋና ኮሚሽነር ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) ስለ በጎ ጥረትዎ በእጅጉ እናመሰግናለን፡፡ በእርስዎ የሥራ ዘመን ያየነውን የተስፋ ጭላንጭል ሊያጨልም የሚችል ፈታኝ ጊዜ ከፊት ለፊት በተደቀነበት ወቅት መሰናበትዎ ያስቆጫል፡፡

የተሰቀለው ቀይ ባህር!ከኢትዮጵያ እጅ ወጥቶ 🌍 በግራ በቀኝ ያሰፈሰበት የቀይ ባህር ጉዳይ፣ ከሚታሰበው በላይ የተወሳሰበ ጂኦፖለቲካዊ ቅርጽ ይዟል።ከአረቡ እስከ ምዕራቡ ዓለም ዙሪያውን አሰፍሳ...
13/10/2023

የተሰቀለው ቀይ ባህር!

ከኢትዮጵያ እጅ ወጥቶ 🌍 በግራ በቀኝ ያሰፈሰበት የቀይ ባህር ጉዳይ፣ ከሚታሰበው በላይ የተወሳሰበ ጂኦፖለቲካዊ ቅርጽ ይዟል።

ከአረቡ እስከ ምዕራቡ ዓለም ዙሪያውን አሰፍሳፊ የበዛበት የያኔው የኢትዮጵያ የባህር በር፣ ዛሬ ላይ ታሪክ ተቀይሮ የቅርብ ሩቅ ሆኖ ተሰቅሏል።

የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አሕመድ በግድም በውድም አይነት አካሄድ ምን ይዞ እንደሚመጣ ስለ ቀይ ባህር ውስብስብ ፖለቲካ እያነበብን እንቆይ። 👇

The Red Sea is a vital economic artery and is likely to become more so in the coming decades. In geopolitical terms, it should increasingly be seen as worthy of unified policy attention on its own, perhaps more so than the traditional and broad “Middle East” focus of American and European policy...

01/06/2023

“መንግሥት አለ?”
አርሶ አደሩን አደባባይ ያስወጣው ጥያቄ

Source:- DW Amharic
Voice of Ethiopia-VOE

   ምክር ቤቱ ህወሓትን ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ሰረዘየኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ምክር ቤ...
22/03/2023



ምክር ቤቱ ህወሓትን ከሽብርተኛ ድርጅት ዝርዝር ሰረዘ

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ከሽብርተኛ ድርጅት እንዲሠረዝ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

ምክር ቤቱ ዛሬ ባሄደው ልዩ ስብሰባ ህወሓትን ከሽብርተኛ መዝገብ ለማንሳት በቀረበለት የውሳኔ ሀሳብ ላይ ከተወያየ በኋላ በአብላጫ ድምፅ ውሳኔውን አፅድቋል።

ለሰሜኑ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ ለመስጠት በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ጥቅምት 24 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስትና በህወሓት መካከል የሰላም ስምምነት መፈረሙ ይታወሳል።

የሀገሪቱን ሕገ መንግስታዊ ስርዓት ባከበረና የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ በተፈረመው የሰላም ስምምነት መሰረት በፌደራል መንግስት እና በህወሓት በኩል ስራዎች ሲከናወኑ ቆይተዋል።

የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል መሰረታዊ አገለግሎቶች እንዲጀመሩ እና የሰብዓዊ እርዳታ በተሳለጠ መልኩ እንዲቀርብ ማድረጉ የሚታወቅ ነው።

ህወሓትም ታጣቂዎቹን ወደ ካምፕ በመሰብሰብ ከባድ የጦር መሳሪያዎችን ለኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ማስረከቡም አይዘነጋም።

በዚህ የሰላም ስምምነት መሰረትም ነው ድርጅቱ ከሽብርተኝነት መዝገብ እንዲነሳ ምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳቡን ያፀደቀው።

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ...
21/03/2023

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

ሐምሌ 9 ቀን 2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አንብሮተ ዕድ የሾሙት ጳጳሳት 14 ኤጲስ ቆጶሳት መካከል አንዱ የሆኑት በቀድሞ ስማቸው አባ ኃይለማርያም መለሰ ዶ/ር በጵጵስና ስማቸው ብፁዕ አቡነ አረጋዊ፣ የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት እና የውጪ ግንኙነት መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና የጅቡቲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

ብፁዕነታቸው ለረጅም ጊዜ ከሀገር ውጪና በሀገር ውስጥ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ሊሻላቸው ሳይችል ቀርቶ ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል።

ምንጭ፦ ኢኦተቤ ቲቪ

ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ተገኝታለች ከቀናት በፊት በሞግዚቷ ተሰርቃ የተወሰደችው የ2 ዓመቷ ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ሱሉልታ ከተማ ላይ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡የ2 ዓመት ዕድሜ ያ...
21/03/2023

ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ተገኝታለች

ከቀናት በፊት በሞግዚቷ ተሰርቃ የተወሰደችው የ2 ዓመቷ ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ሱሉልታ ከተማ ላይ መገኘቷን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡

የ2 ዓመት ዕድሜ ያላት ህፃን ሶሊያና ዳንኤል ሳሪስ አዲስ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ሃሙስ መጋቢት 7 ቀን 2015 ዓ/ም ረፋድ ላይ ቤዛ በቀለ በተባለችው የቤት ሰራተኛቸው ተሰርቃ ስለመወሰዷ በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገፆች መረጃው ሲሰራጭ መቆየቱ ይታወሳል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ በህፃኗ ወላጆች የቀረበለትን አቤቱታ ተቀብሎ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመቀናጀትና ከአዲስ አበባ ውጪ ወደተለያዩ የሃገራችን ከተሞች እና አካባቢዎች በመሄድ ጭምር አስፈላጊ መረጃዎችን በፖሊሳዊ ጥበብ በማሰባሰብ ከፍተኛ ጥረትን የጠየቀ ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል፡፡

የክትትል ስራው ቀንና ሌሊት ደጅ ውሎ ማደርን የግድ የሚል እጅግ አድካሚ እንደነበር ያስታወሰው የአዲስ አበባ ፖሊስ በስተመጨረሻም ቤዛ በቀለ ዛሬ መጋቢት 12 ቀን 2015 ዓ/ም ሱሉልታ ከተማ "ኖኖ መና አቢቹ" ተብሎ በሚጠራው ቀበሌ በአንድ መኖሪያ ቤት ውስጥ ህፃን ሶሊያና ዳንኤልን ሸሽጋ በተቀመጠችበት በቁጥጥር ስር መዋሏን አስታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዋ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለች በኋላ እንደተናገረቸው 40 ሺህ ብር ይከፈልሻል ብለው ሰዎች ስላግባቧት ህፃኗን ሰርቃ ልትሰወር ችላለች፡፡ በወንጀሉ ላይ ተሳትፎ አላቸው የተባሉ ሌሎች ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ምርመራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል።

Voice of Ethiopia-VOE

 #ሰበር ዜና   አባቶች  በይቅርታ ተመልሰዋል
15/02/2023

#ሰበር ዜና
አባቶች በይቅርታ ተመልሰዋል

 የቤተክርስቲያን አባቶች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር እየመከሩ ነውየቤተክርስቲያን አባቶች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በቤተመንግሥት በመምከር ላይ ይገኛሉ።ብጹእ ወቅዱስ አ...
10/02/2023


የቤተክርስቲያን አባቶች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር እየመከሩ ነው

የቤተክርስቲያን አባቶች ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በቤተመንግሥት በመምከር ላይ ይገኛሉ።

ብጹእ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስን ጨምሮ ሊቀነ ጳጳሳት የተካተቱበት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ልዑክ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር እየተወያየ እንደሚገኝ ታውቋል፡፡ ውይይቱ በወቀታዊ የቤተክርስቲያን ችግር ላይ መፍትሔ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርትዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ትናንት የካቲት 2/2015 ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ መንግሥት ቤተ ክርስቲያኒቱ መግለጫውን ባወጣች 72 ሰዓታት ውስጥ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሃይማኖት፣ ቀኖና እና አስተዳደራዊ ሕግጋትን ባልጣሰ መልኩ ከመንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ ለመወያየት መንፈሳዊ በሯ ክፍት መሆኑን በመግለጽ ጥሪ ማስተላለፏ ይታወሳል።

Addis Ababa - Ethiopia From Above|| Drone film || sky views
25/01/2023

Addis Ababa - Ethiopia From Above|| Drone film || sky views

Address

4 Kilo
Addis Ababa

Telephone

+251949941535

Website

https://t.me/VOEEthiopia, https://t.me/VOEEthiopia, https://t.me/VOEEthiopia,

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Voice of Ethiopia-VOE posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Voice of Ethiopia-VOE:

Share