Amhara Voice

Amhara Voice ስንኖር ኢትዮጵያዊ ስንሞት ኢትዮጵያ ነን

♦ እናቶች እና አዛውንቶች በስብሰባ ላይ ተማጽኖ አቅርበዋል ፤ ሆኖም ግን ዶሮ ማነቂያ ሰፈር ሙሉ ለሙሉ ሊፈርስ ነው !በተለምዶ አጠራር ዶሮ ማነቂያ እየተባለ የሚጠራው እንደሚፈር በዛሬው ዕለ...
27/02/2024

♦ እናቶች እና አዛውንቶች በስብሰባ ላይ ተማጽኖ አቅርበዋል ፤ ሆኖም ግን ዶሮ ማነቂያ ሰፈር ሙሉ ለሙሉ ሊፈርስ ነው !

በተለምዶ አጠራር ዶሮ ማነቂያ እየተባለ የሚጠራው እንደሚፈር በዛሬው ዕለት የአካባቢው ነዋሪዎች በወረዳ 5 የሰብሰባ አዳራሽ ተጠርተው ፤ ዶሮ ማነቂያ አካባቢ ሙሉ በሙሉ በአስቸኳይ እንደሚፈርስ ለነዋሪዎቹ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል ።

የዶሮ ማነቂያ ሰፈር ነዋሪዎች ፤እናቶች እና አዛውንቶች በስብስ ላይ ተማጽኖ አቅርበዋል ፤ እባካችሁን በችኮላ የንግድ እና የመኖሪያ ቤታችን አታፍርሱብን ፣ እኛ ልማት አንጠላም ፣ በአካባቢው የዕለት ጉርሳችን በተለያየ ሥራ ተሰማርተን እየሰራን ኑራችንን እየገፋን ነው ያለነው። ግዜ ስጡን እንመካከር እትብታችን ከተቀበረበት ዝም ብላችሁ አታፈናቅሉን ፣ ድህነት ወንጀል አይደለም ፣ለከተማ ገፅታ ሲባል እኛን አድራሻ አታሳጡን ፤ እኛ ድሆችን በማዕከለ መልኩ ከተማውን ማስዋብ ትችላላችሁ ፤ እባካችሁን ሕይወታችን አተመሰቃቅሉ በማለት ነዋሪዎች ተማጽኖ አቅርበዋል።

ከቀናቶች በፊት ፤ ማህበራዊ ፍትህ አመጣለሁ የሚለው "ኢዜማ" የፓርቲውም ከፍተኛ የመንግስት ሹመኛ የሆኑት አቶ ግርማ ሰይፉ ፤ ለከተማ ገፅታ ሲባል ድሆች በፍቃደኝነት ለቀው ወደ ሌላ ይዛወሩ የሚል የአለቆቻቸውን ሐሣብ አስቀድሞ ማቅረባቸው የሚዘነጋ አይደለም ።

የአዲስ አበባ ተወላጅ እና ነዋሪ ወደየትም ሳይዘዋወሩ ፤ የአዲስ አበባን የከተማውን ገጽታ መገንባት አይቻልም ወይ ?! ድሃን ከአዲስ አበባ የማፅዳት ዘመቻ ማብቂያው የት ሰፈር ነው ?! ማነው ባለሳምንት ?!

ይድነቃቸው ከበደ

ለዘራፊው ተቋም ጥያቄ❗❓መነሻ!ኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ዳታ ባቋረጠባቸው አካባቢዎች (በአማራ ክልል ሙሉ በሙሉ)  ለሚገኙ ደንበኞቹ ዳታውን ከመዝጋቱ በፊት የገዙትን ፓኬጅ ገንዘባቸውን ተመላሽ ...
19/01/2024

ለዘራፊው ተቋም ጥያቄ❗❓

መነሻ!
ኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል ዳታ ባቋረጠባቸው አካባቢዎች (በአማራ ክልል ሙሉ በሙሉ) ለሚገኙ ደንበኞቹ ዳታውን ከመዝጋቱ በፊት የገዙትን ፓኬጅ ገንዘባቸውን ተመላሽ አድርጓል ወይ?
ደንበኞች በውላቸው መሰረት ገንዘብ ከፍለው ነገር ግን አቅራቢው ባለማቅረቡ ምክንያት አገልግሎትቱን ካልተጠቀሙ ገንዘባቸው ተመላሽ(refund ) መደረግ አለበት።
... ጥያቄው አያልቅም

ማሳሰቢያ !
Terms and conditions ጂኒ ጃንካ ... Force majeure ምንም እዚህ ጋር አይሰራም ።

በመቐለ ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ ኣሉላ ኣባ ነጋ አየር ማረፊያ በማረፍ ላይ የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላን በማረፍ ላይ በነበረበት ሰዓት በተፈጠረው የቴክኒክ ችግር አብራሪው አይሮፕላ...
18/01/2024

በመቐለ ከቀኑ 8 ሰዓት ላይ ኣሉላ ኣባ ነጋ አየር ማረፊያ በማረፍ ላይ የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላን በማረፍ ላይ በነበረበት ሰዓት በተፈጠረው የቴክኒክ ችግር አብራሪው አይሮፕላኑ ማስተካከል ያለበትን አስተካክሎ በሰላም እንድታርፍ አድርጓል።

የተጎዳ የለም

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amhara Voice posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share