Central Politics

Central Politics & Broadcasting Production!!!

ኢትዮጵያ የመጀመርያ ሜዳልያዋን አገኝች***********ዛሬ በተደረገው የሴቶች 10 ሺ ሜትር ፍጻሜ አትሌት  ጉዳፍ ጸጋይ 3ኛ ወጥታለች፡፡የቡዳፔስት ዓለም ሻምፒዮና የርቀቱ የወርቅ ሜዳልያ አ...
13/09/2025

ኢትዮጵያ የመጀመርያ ሜዳልያዋን አገኝች
***********
ዛሬ በተደረገው የሴቶች 10 ሺ ሜትር ፍጻሜ አትሌት ጉዳፍ ጸጋይ 3ኛ ወጥታለች፡፡

የቡዳፔስት ዓለም ሻምፒዮና የርቀቱ የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊ ጉዳፍ ጸጋዬ ለሀገሯ የነሀስ ሜዳልያ አስገኝታለች፡፡

የርቀቱ ዓለም ክብረ ወሰን ባለቤት ኬንያዊቷ ቢያትሪስ ችቤት ውድድሩን በአንደኝት አጠናቃለች፡፡

ወረዳ አቀፍ የያሆዴ በዓል   በድምቀት እየተከበረ ነው።*************ወረዳ አቀፍ የሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ ያሆዴ በዓል የዞን፣የወረዳ አመራር አካላት፣ የባህል ሽማግሌዎች ፣ የሐይማ...
13/09/2025

ወረዳ አቀፍ የያሆዴ በዓል በድምቀት እየተከበረ ነው።
*************
ወረዳ አቀፍ የሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ ያሆዴ በዓል የዞን፣የወረዳ አመራር አካላት፣ የባህል ሽማግሌዎች ፣ የሐይማኖት አባቶች እንድሁም የአጎራባች ወረዳዎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በግቤ ወረዳ ሶዳ ከተማ እየተከበረ ይገኛል።

ይህ የሀዲያ ብሔር ዘመን መለወጫ የሆነዉ ያሆዴ በዓል በዞኑ በሚገኙ ሁሉም ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች የሚከበር ሲሆን የማጠቃለያ ማርሃ ግብር በዞን ደረጃ በሆሳዕና ከተማ ሀዲይ ነፈራ የሚከበር ይሆናል ሲል የሀዲያ ቲዢ ዘግቧል።

 #የቆሴ ጉዳይ የሁሉም ሀዲያ የህልውና ጥያቄ ነው!✍️የሀዲያ ልጆች፣ ከሰፍሩ ገበሬዎች እስከ ሚሻና አመካ፣ ከጊቤ፣ ጎምቦራ እና ሶሮ፣ ከሌሞና አኒ ሌሞ፣ ከሻሾጎ እና ባደዋቾ፣ ከዳውሮ፣ ሶኮሩ...
13/09/2025

#የቆሴ ጉዳይ የሁሉም ሀዲያ የህልውና ጥያቄ ነው!

✍️የሀዲያ ልጆች፣ ከሰፍሩ ገበሬዎች እስከ ሚሻና አመካ፣ ከጊቤ፣ ጎምቦራ እና ሶሮ፣ ከሌሞና አኒ ሌሞ፣ ከሻሾጎ እና ባደዋቾ፣ ከዳውሮ፣ ሶኮሩና ያማ ተራሮች፣ እንዲሁም በውጭ ሀገር ለምትኖሩ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በሙሉ።

✍️በቆሴ ያለው ችግር የቆሴ ነዋሪዎች ብቻ ነው የሚለው ወሬ ከእውነት የራቀና የተሳሳተ ነው። የቆሴ ሀዲያ ስቃይ የሁላችንም የሀዲያ ቤተሰቦች ስቃይ ነው። የቆሴ ትግል ለህልውናችን፣ ለክብራችን እና ለኢኮኖሚ ነፃነታችን የሚደረግ ትግል ነው።

✍️ቆሴ ለዘመናት የኢኮኖሚያዊ ህይወታችን ማዕከል ናት፤ ሁላችንንም የምታገናኝ የደም ሥር ናት። የጊቤ ሸለቆ ማዕከላዊ የገበያ ቦታ ናት። የሶሮና የጎምቦራ ከብት አርቢዎች ከብቶቻቸውን፣ በጎቻቸውንና ፍየሎቻቸውን የሚያመጡባት ቦታ ናት። የዳውሮና የሶኮሩ ገበሬዎች ሰብሎቻቸውን የሚያመጡባት ቦታ ናት። ከየአካባቢው የሚመጣው የህዝባችን ምርት የሚሰባሰብባት፣ ከአመካ የእንሰት ውጤቶች እስከ ጊቤ ለምለም ጫት የሚሸጡበትና ወደ አዲስ አበባ የሚላኩበት ወሳኝ ስፍራ ናት። በየሳምንቱ ሁለት ጊዜ በቆሴ ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ብሮች በየማኅበረሰባችን እንዲዘዋወሩ ታደርጋለች።

✍️አሁን ግን ህገወጥ ቡድኖች ወታደራዊ ኃይልን ተጠቅመው ገበያችንን አንቀው ይዘዋል። ምርታቸውን ለመሸጥ ከሚመጣው ህዝባችን ላይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ብሮችን በግፍ ይወስዳሉ። ይህን ግፍ መገመት ትችላላችሁ? እነሱ ግብር ብቻ እየሰበሰቡ አይደለም፤ የወደፊት ህይወታችንን እየዘረፉ ነው። ፀሀይ ስር ደክማችሁ፣ እንስሳቶቻችሁን አሳድጋችሁ፣ ሰብላችሁን አጭዳችሁ፣ የጉልበታችሁን ፍሬ በጠመንጃ እየተቀማችሁ ነው! ይህ ግብር ሳይሆን በህዝባችን ላይ የተከፈተ የኢኮኖሚ ዘረፋ ነው።

✍️አሁን ወደ በዓሎቻችን እየተቃረብን፣ ወደ አዲስ ተስፋና ጅማሬ በምንሸጋገርበት በዚህ የመስቀልና የዘመን መለወጫ ወቅት፣ ሌቦቹ የጭነት መኪኖች በታጠቁ ወታደሮች ተሞልተው ህዝባችንን ለመዝረፍ ይመጣሉ። ትክክለኛ የንግድ ልውውጥን ለመዝጋትና ህዝባችንን ወደ ድህነት ለመምራት ኃይልን እየተጠቀሙ ነው።

✍️ቆሴ ከታፈነች ሁላችንም እንታፈናለን። ከብት አርቢዎች ከብቶቻቸውን በተገቢው ዋጋ መሸጥ ካልቻሉ ቤተሰቦቻቸውን መመገብ አይችሉም። ገበሬዎች ምርቶቻቸውን ወደ ገበያ ማምጣት ካልቻሉ ልጆቻቸው ይራባሉ። በቆሴ የተሰረቀው ገንዘብ በጎምቦራ ቤቶችን ሊገነባ፣ በሚሻ ለትምህርት ሊከፍል ወይም በጊቤ የጤና አገልግሎት ሊሰጥ የሚገባው ገንዘብ ነው።

✍️የቆሴ ህዝብ ምርቶቻቸውን በነፃነት ለመሸጥ እየተፋለሙ ነው። ለኢኮኖሚያዊ ፍትህ ያለንን መብት እየተሟገቱ ነው። ለሁላችንም እየታገሉ ነው። የቀድሞ አባቶቻችንን ጀግንነት፣ ለትክክለኛ ነገር ሁልጊዜ የቆመ ህዝብ ብርታት እያሳዩን ነው። እነሱን ብቻቸውን ለትግል ልንተዋቸው አይገባም፤ ፈጽሞ!

✍️የጋራ እጣ ፈንታችን ከቆሴ እጣ ፈንታ ጋር የተያያዘ ነው። የቆሴ ሀዲያ ድል የእኛ ድል ነው። የእነሱ ነፃነት የእኛ ነፃነት ነው። ይህ ለእያንዳንዱ የሀዲያ ወንድና ሴት የቀረበ የተግባር ጥሪ ይሁን። በአንድነት ቁሙ! ድምጻችሁን፣ ተጽዕኖአችሁን እና ሀብታችሁን በቆሴ የሚገኙ ወገኖቻችንን ለመደገፍ ተጠቀሙ። ከመሪዎቻችሁ ጋር ተነጋገሩ፣ በማኅበረሰባችሁ ውስጥ ግንዛቤ ፍጠሩ፣ እናም ከጋራ አላማችን ጀርባ ተሰባሰቡ።

✍️የሀዲያ አንድነት መንፈስ ምን ማለት እንደሆነ ለአለም እናሳይ። ለፍትህ እንታገል! ለክብራችን እንታገል! የኢኮኖሚ ልባችን የሆነው ቆሴ ለትውልዶች ጠንካራና ነፃ ሆኖ እንዲመታ እናረጋግጥ።
አንድ ላይ ሆነን ማንም ሊያቆመን አይችልም!

 #አፋልጉኝልጄን የት ህጄ ልፈልገው2015👉2016👉2017👉2018የቁም ስቃይ😭😭😭😭ከልጄ ጋር ከተለያየን 3ተኛ አመታችን መጣልጄ ከጠፋ ጀምሮ ያሳለፍኳቸውን የመስከረምና የሰኔ ወርሃቶችን ባሰብ...
12/09/2025

#አፋልጉኝ
ልጄን የት ህጄ ልፈልገው
2015👉2016👉2017👉2018
የቁም ስቃይ😭😭😭😭
ከልጄ ጋር ከተለያየን 3ተኛ አመታችን መጣ
ልጄ ከጠፋ ጀምሮ ያሳለፍኳቸውን የመስከረምና የሰኔ ወርሃቶችን ባሰብኩ ቁጥር ሁሌም ልቤ ይደማል 💔💔💔💔💔💔💔
ይሀው አሁንም መስከረም ወር መጣ የማሂሬ ጓደኞች ቦርሳቸውን እና ምሳ እቃቸውን ይዘው ወደ ት/ት ቤታቸው የሚመላለሱበት ግዜ ደረሰ
(ቁርዓኗን)(قرعن) እንደያዘች አቧራዋን ለብሳ መግቢያ መውጫዬ ላይ እሰከዛሬም ማሂሬን እየጠበቀች ነው
ወላጆች ሁሉ በልጅ እንዳይፈትናችሁ የዘውትር ምኞቴ ነው 🤲🤲🤲🤲🤲
የኔ ልጅስ የት ይሁን ያለው?
በህይወት አለ ይሁን ?
ድምፁስ ለምን ጠፋ?
ተርቦ ይሁን❓ ታርዞ ይሁን❓ ወይስ በህይወት የለም❓ የዘውትር ጭንቀቴ ነው
Seid Mohammed Godere
0911334363
0913915460

በህብረት ችለናል 🇪🇹የታላቁን ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ምክንያት በማድረግ  በመስቀል አደባባይ አሁን የብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እየተካሄደ ነው።የአዲስ አበባ  ነዋሪዎችም በዚሁ በመስቀል...
12/09/2025

በህብረት ችለናል 🇪🇹

የታላቁን ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ምክንያት በማድረግ በመስቀል አደባባይ አሁን የብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እየተካሄደ ነው።

የአዲስ አበባ ነዋሪዎችም በዚሁ በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ባለው የብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እየተሳተፉ ነው።
Central Politicscsስከረም 02/17ዓ.ም

🌼🌷🌻2018 ዓመትን መላው የኢትዮጵያ ህዝቦች እንኳን አደረሳችሁ!!!🌻️🌾እንቁጣጣሽ🌾🌻መልካም አዲስ አመት 2018 ዓ.ም🌼🌻️🌺አመትን🌄 የሚያቀዳጅ ፈጣሪ አዲሱን አመት የሰላም🕊 የመተባበር 👥 ...
11/09/2025

🌼🌷🌻2018 ዓመትን መላው የኢትዮጵያ ህዝቦች እንኳን አደረሳችሁ!!!
🌻️🌾እንቁጣጣሽ🌾🌻
መልካም አዲስ አመት 2018 ዓ.ም🌼🌻️🌺
አመትን🌄 የሚያቀዳጅ ፈጣሪ አዲሱን አመት የሰላም🕊 የመተባበር 👥 የስኬት 🏆፣የጤና እንዲሁም የደስታ ዘመን ያድርግልን 🌼🌾🌻️🌼 ✨ !!

Central Politics

ወጥቶ ከመቅረት ይጠብቀን‼ፖሊስ መረጃውን አጋሩልኝ ብሏል።ከዚህ በታች በፎቶ ለይ የምትመለክቱት ግለሰብ በሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ ዞቤቻሜ የቀድሞ ማዘጋጃ ቤት አጠገብ ጷጉሜ 3/2017 ምሽት ህ...
10/09/2025

ወጥቶ ከመቅረት ይጠብቀን‼

ፖሊስ መረጃውን አጋሩልኝ ብሏል።

ከዚህ በታች በፎቶ ለይ የምትመለክቱት ግለሰብ በሀላባ ዞን ቁሊቶ ከተማ ዞቤቻሜ የቀድሞ ማዘጋጃ ቤት አጠገብ ጷጉሜ 3/2017 ምሽት ህይወቱ አልፏል።

በግለሰቡ ላይ ማንነቱን የሚገልጽ ነገር ስለሌለ በፎቶ ግራፍ አይቶ የሚያውቅ ካለ አስክሬኑ በሀላባ ቁሊቶ አጠቀላይ ሆስፒታል በአስክሬን መቆያ ክፍል ስለሚገኝ ለቤተሰቡ ማሳወቅ የሚችለው መሆኑን እንገልፃለን።

ምንጭ ፦ የሀላባ ዞን ፖሊስ መምሪያ

10/09/2025

የአሜሪካ ታዋቂ ትክቶኬር ዲለን ስለ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ትልቅ ትንታኔ ያዘለ ዜና ሰርቷል።

ዜናው የአለም አቀፍ ህዝብ ትኩረት እንድስብ አድርጓል። ስለኢትዮጵያ ፈጣሪ በሁሉም አቅጣጫ ግልጽ እያደረገ ነው።

ከዚህ ብኋላ ሚስት ልታመጡ የምትሄዱ ሽማግሎች"ልጁ ምን አለው!?" ሲባልግድብ አለው በሉ!!!😁😁😁
10/09/2025

ከዚህ ብኋላ ሚስት ልታመጡ የምትሄዱ ሽማግሎች
"ልጁ ምን አለው!?" ሲባል
ግድብ አለው በሉ!!!😁😁😁

 !!!
08/09/2025

!!!

የቀቤና ብሔረሰብ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል::

08/09/2025
ወቅታዊ መረጃ ❗️ዊልያም ሩቶ በህዳሴ ግድብ ምረቃ ይታደማሉ!!!🇪🇹💡🇰🇪የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊልያም ሳሞይ ሩቶ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ በዓል የክብር እንግዳ በመሆን በጉባ ተራሮች ...
08/09/2025

ወቅታዊ መረጃ ❗️

ዊልያም ሩቶ በህዳሴ ግድብ ምረቃ ይታደማሉ!!!
🇪🇹💡🇰🇪

የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊልያም ሳሞይ ሩቶ የታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምረቃ በዓል የክብር እንግዳ በመሆን በጉባ ተራሮች ሥር ይገማሸራሉ።

የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአፍሪካ እራስን መቻል ተምሳሌት ነው በሚል ንግግራቸው የሚታወቁት ዊልያም ሩቶ የግድቡን ሪባን ከሚቆርጡ የክብር እንግዶች ውስጥ በመጀመሪያው እረድፍ ይገኛሉ።

በጉባ ተራራ ስር የሚታደሙ የሌሎች መሪዎች ሥም ዝርዝር ይጠብቁ !

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Politics posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Central Politics:

Share

Category