Central Politics

Central Politics & Broadcasting Production!!!

መልካም ዜና ለኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በሙሉ‼️➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ኢትዮ ቴሌኮም ለ3 ቀናት የሚቆይ 1 ጂቢ ነፃ ኢንተርኔት አበረከተ።ኢትዮ ቴሌኮም ለደንበኞቹ የተለያዩ የምስጋና ስጦታዎችን አበረ...
24/07/2025

መልካም ዜና ለኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በሙሉ‼️
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
ኢትዮ ቴሌኮም ለ3 ቀናት የሚቆይ 1 ጂቢ ነፃ ኢንተርኔት አበረከተ።

ኢትዮ ቴሌኮም ለደንበኞቹ የተለያዩ የምስጋና ስጦታዎችን አበረከተ።

ኢትዮ ቴሌኮም በ2017 በጀት ዓመት ጥሩ አፈጻጸም በማስመዝገቡ ከዛሬ ሌሊት 6 ሰዓት ጀምሮ የምስጋና ስጦታዎችን ለደንበኞቹ አበርክቷል።

በዚህ መሰረትም ለ3 ቀናት የሚያገለግል 1 ጂቢ የኢንተርኔት፣ በየቀኑ የ5 ደቂቃ የድምጽ እና በየቀኑ 8 የአጭር የጽሑፍ መልዕክት ስጦታን ለደንበኞቹ አበርክቷል፡፡

እንዲሁም የ10 ደቂቃ ዓለም አቀፍ ጥሪ የምስጋና ስጦታን ለደንበኞቹ ማበርከቱ ነው የተመላከተው፡፡

ስጦታዎቹን ከዛሬ ሌሊት 6 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት 12 ሰዓት ድረስ መጠቀም እንደሚቻል ተጠቁሟል፡፡

ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸም 162 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ተከትሎ ነው ለደንበኞቹ የምስጋና ስጦታ ያበረከተው፡፡
Central Politics

በአሪ ዞን ደቡብ ኣሪ ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ  የ5 ሰዎች ህይወት አለፈበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል  ኣሪ ዞን በደቡብ ኣሪ ወረዳ በኮመር ቀበሌ ሞልሽር ልማት ቡድን  በቀን 13/11/2017 ዓ...
21/07/2025

በአሪ ዞን ደቡብ ኣሪ ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ የ5 ሰዎች ህይወት አለፈ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኣሪ ዞን በደቡብ ኣሪ ወረዳ በኮመር ቀበሌ ሞልሽር ልማት ቡድን በቀን 13/11/2017 ዓ.ም በትላንትው እለት በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ከምሽቱ 2:30 ላይ በደረሰው ናዳ የአምስት ሰዎች ህይወት ማለፍ ችሏል።

በተከሰተዉ ናዳ ምክንያት የአንድ ቤተሰብ ሙሉ የቤተሰብ አካል ህይወት ያለፈ ሲሆን ከህጻናትን ጨምሮ 3 ወንድ እንስ2 ሴት በአጠቃላይ የ5 ሰዎች ህይወት ማለፍ ችሏል።

ከዚህም በተጨማሪ 3 መኖርያ ቤቶች ከቤት እንስሳት ጋር በናዳው መስጠሙ ታውቋል ።
በቦታው የመንግስት አካላት፣ ቀይመስቀል እንዲሁም የአከባቢው ነዋሪዎች ደርሰው ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ።

ወቅቱ ክረምት በመሆኑ በሌሎች የክልሉ አከባቢዎችም ተመሳሳይ የሆነ አደጋ እንዳይከሰት የስጋት ቦታዎች ጋ ቅድመ ጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል ።

በአደጋው ህይወታቸውን ላጡ ቤተሰቦች መፅናናትን እንመኛል።

19/07/2025

ይሄ የሚያስዝን ልጅ ማሳደግ ለምትፈልጉ ኢትዮጵያውያን 🙏

ልብ የሚሰብር የ15 ቀን ህፃን ባባ ታሪክ እና የእናቱ መስዋዕትነት 😥

ይህ የትንሹ ባባ ልብ የሚነካ ታሪክ ነው። እናቱ ከወለደችው ገና የ15 ቀን ጨቅላ እያለች ህይወቷ አልፏል።

አባቱ በህይወት የሌለ በመሆኑ፣ ምስኪኗ አያቱ በታላቅ ችግር ውስጥ ሆነው የባባን ነፍስ ለማቆየት እየታገሉ ነው።

"ከእግዚአብሔር በታች እኔም በምችለው እያገዝኩት ነው" በማለት የባባን ሁኔታ በቅርበ የሚከታተለው በበጎ አድራጎት የሚታወቀው ነባ ተናግሯል።

በተመሳሳይ ደግሞ ትንሹ ባባ በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ ከእናትና አባት ፍቅር የተነጠቀ በመሆኑ አስቸኳይ እርዳታ ያስፈልገዋል።

ባባን እንደ ገዛ ልጁ አድርጎ ህጋዊ ነገርን በማሟላት ማሳደግ የሚፈልግ ደግ ልብ ያለው ሰው ካለ፣

በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች
በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላል፦

* 0910893008
* 0916514072

ይህን መልዕክት በማጋራት ብዙ ሰዎች እንዲደርስ እና ትንሹ ባባ ሞቅ ያለ ቤተሰብ እንዲያገኝ የበኩላችንን እንወጣ።

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

19/07/2025

ፌስቡክ 10 ሚሊዮን አካውንቶችን ዘጋ‼️

ፌስቡክ ከተያዘው ዓመት ከጥር ወር 2025 ጀምሮ ከ 10 ሚሊዮን በላይ የፌስቡክ አካውንቶችን መሉ ለሙሉ መዝጋቱን አስታውቋል።

አካውንቶቹ እንዲዘጉ የተደረጉት ሁለት አመት እና ከዚያ በላይ active ስላልነበሩ መሆኑን ፎርብስ መፅሄት አስነብቧል።

19/07/2025
19/07/2025

የ40 ብር ቡና 😮 ☕️

Inbox ጉርሻዬ ይህ የ40 ብር ቡና

ቦሌ አራብሳ ነው መቁጠር ድብሮኛ ነው እንጂ
ቡናው በፍሬ ከ30 እስከ 35 ፍሬ ይሆናል

እንዴት እያችሁት ዋጋውን በልልኝ ?

Via ዩሐንስ የማርያም ከስፍራው

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

19/07/2025

ዛሬ አንድ እንግዳ እናስታውቃችኋለን ፦ አበገዳ ወንድሙ ጡምዳዶ ይባላሉ።
ተወልደው ያደጉት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት ሀዲያ ዞን ጊቤ ወረዳ ሀሞላ ኡታ ቀበሌ ነው
።በሀዲያ ዞን በብዙ ኃላፊነት ቦታዎች የፍት አመራር በመሆን አገልግሏል ።
በኃላፊነት ከገለገሉበት በታዎች ውስጥ በጥቅቱ፦

1ኛ በሀዲያ ዞን የጊቤ ወረዳ የገቢዎች ጽ/ቤት ኃላፊ በመሆን ያገለገሉ፦
2ኛ በሀዲያ ዞን የጊቤ ወረዳ ም/አሰተዳደር በመሆን ያገለገሉ ፦
3ኛ የጊቤ ዋና አሰተዳደር በመሆን ያገለገሉ ፦
4ኛ የሀዲያ ዞን ሠራተኛና ማህበራዊ መምሪያ ኃላፊ ያገለገሉ፦
5ኛ የሀዲያ ዞን ኅብረት ሥራ ኃላፊ በመሆን ያገለገሉ ፦
6ኛ በኢትዮጵያ ቃላ ሕይወት ቤተክርስቲያን ደቡብ ሸዋ ቀጠና
ምዕራብ ሀዲያ አጥቢያ ቃለሕይወት ቤተክርስቲያን ህብረት ጽ/ቤት ሆመቾ ዋና ሊ/መንበር ሆኖ ያገለገሉ ስሆን ፤

በአጠቃላይ አበገዳ ወንድሙ ጡምዳዶ በተሰጠበት ኃላፊነት ቦታዎች እና በተሠማሩበት ሙያ ሁሉ በመልካም ተግባራት የተመሰከረለት ፈረ እግዚአብሔር ያለ የመልካም ስብዕና ባለቤት ናቸው ።
በሀዲዮማ ሚዲያ ኔትወርክ ስም ለአበገዳ ወንድሙ ጡምዳዶ እና ለባለቤታቸው ወ/ሮ ደስታ ካሣ መልካሙ ሁሉ ተመኛን።

19/07/2025

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Central Politics posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Central Politics:

Share

Category