ሰላም ሚዲያ /ሰሚ/

ሰላም ሚዲያ /ሰሚ/ Competent and Comprehensive Media!
ተወዳዳሪና አቃፊ ሚዲያ
Miidiiyaa Hammataa fi Dorgomaa!

ስለ ሰላም ፤ ፖለቲካ ፤ ነጻነት፤ አንድነት፤ ጤና ፤ ስፖርት እና ምጣኔ ሀብት አገልግሎታችሁን በነጻ ለማስተዋወቅ እንኳን ወደ ድርጂታችን በደህና መጣችሁ፡፡
Tajaajila nageenyaa ,siyyaasaa, tokkummaa, bilisummaa , fayyaa ,spoortii fi diinagdee keessan bilisaan beeksifachuuf baga gara dhaabbilee keenyaa nagaan dhuftan
Well come toward our organization to freely promote and advertise about peace, unity, freedom, politics, healthy, sport and economic service

የተመድን 80 ዓመታት ያስቆጠሩ እሴቶች ለማደስ ጊዜው አሁን ነው - አንቶኒዮ ጉቴሬዝየተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የሻንጋይ የትብብር ድርጅት ጉባዔ 2025 ላይ ለ...
30/08/2025

የተመድን 80 ዓመታት ያስቆጠሩ እሴቶች ለማደስ ጊዜው አሁን ነው - አንቶኒዮ ጉቴሬዝ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የሻንጋይ የትብብር ድርጅት ጉባዔ 2025 ላይ ለመሳተፍ ቻይና ተገኝተዋል።

አንቶኒዮ ጉቴሬዝም ከቻይናው ፕሬዚዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ዛሬ በቲያንጂን ከተማ ውይይት አድርገዋል።

በወቅቱም ተመድ በዓለም አቀፍ የአስተዳደር መዋቅሩ ላይ አስቸኳይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልገው ጉቴሬዝ ገልጸዋል።

በድርጅቱ ከ80 ዓመታት በፊት የተቀመጡ የመጀመሪያዎቹን እሴቶች ለማደስም ጊዜው አሁን ነው ሲሉ በአፅንኦት ተናግረዋል።

ሺ ጂንፒንግ በበኩላቸው፤ ቻይና ሁልጊዜም የተመድ አስተማማኝ አጋር ሆና እንደምትቀጥል ገልጸዋል።

ከድርጅቱ ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር እና ድርጅቱ በዓለም አቀፍ ደረጃ ያለውን ሚና ለመደገፍ ፕሬዚዳንቱ ቃል ገብተዋል።

በቢታኒያ ሲሳይ

የጤና ሚኒስቴር የ2018 አመታዊ እቅድ ቀርቦ ውይይት ተካሄደበት____________የጤና ሚኒስቴር የስራ ክፍሎች የ2018 እቅዶቻቸውን በማናበብ አዘጋጅተው ማቅረባቸውን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ...
30/08/2025

የጤና ሚኒስቴር የ2018 አመታዊ እቅድ ቀርቦ ውይይት ተካሄደበት
____________

የጤና ሚኒስቴር የስራ ክፍሎች የ2018 እቅዶቻቸውን በማናበብ አዘጋጅተው ማቅረባቸውን የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የገለጹ ሲሆን፤ የቀረበው እቅድ በአግባቡ ተፈጻሚ እንዲሆን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ዶ/ር መቅደስ የ2018 የጤና እቅድ ስኬት በጋራ ኃላፊነት ላይ የተመሰረተ መሆኑን ጠቁመው የጤና ስርዓቱን ለማጠናከርና ጥራት ያለው አገልግሎት አሰጣጥን ለማረጋገጥ ሁሉም የስራ ክፍሎች በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። እንዲሁም ከሚመለከታቸው ተቋማትና ባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ለተቀናጀ ትግበራም ግልፅ አቅጣጫዎች ሰጥተዋል።

በጤናዉ ዘርፍ የጤና አስተዳደር እና አገልግሎት ሪፎርም በእቅዳቸው አካትተው እንዲተገብሩ የዲጂታላይዜሽን ስራዎችን በማስፋት ወረቀት አልባ አሰራርን መተግበር እና እንደ ጽዱ ጤና ተቋም ያሉ ሃገራዊ ኢንሼቲቭ ፕሮጀክቶችን መተግበር እንደሚያስፈልግ በመድረኩ ተገልጿል።

በመድረኩ የዘርፎች እቅድ ይዘት፣ አላማ፣ ስትራቴጂክ እርምጃዎች እና ዋና ዋና ተግባራት እቅድ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል፡፡ መድረኩ መስሪያ ቤቱን ለለቀቁ የቀድሞ አመራሮች እውቅና በመስጠት ተጠናቋል፡፡

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia

“በጎ ፈቃደኞች ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን በማጽናት ባከናወናችሁ ታላቅ ተግባር የሀገር ባለውለታ ናችሁ፡፡”                          የተከበሩ ዶ/ር አምባሳደር የሺመብራት ...
30/08/2025

“በጎ ፈቃደኞች ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን በማጽናት ባከናወናችሁ ታላቅ ተግባር የሀገር ባለውለታ ናችሁ፡፡”

የተከበሩ ዶ/ር አምባሳደር የሺመብራት መርሻ

ነሐሴ 24/2017 ዓ.ም (የሰላም ሚኒስቴር)፣ ብሔራዊ በጎ ፈቃድ የማኅበረሰብ አገልግሎት በሀገሪቱ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን እያጠናከረ መሆኑ ተገለፀ

የብሔራዊ በጎ ፈቃድ ማኅበረሰብ አገልግሎት ከተጀመረበት አንስቶ ለወጣቱ የጋራ ታሪኮችን እና የጋራ ማንነትን የሚያውቅበትን ዕድል በመፍጠር አብሮነት እያጠናከረ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አመራር የተከበሩ ዶ/ር አምባሳደር የሺመብራት መርሻ የብሔራዊ የበጎ ፈቃድ ማኅበረሰብ አገልግሎት ሀገር አቀፍ የልምድ ልውውጥ መድረክ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ገልፀዋል፡፡

የተከበሩ ዶ/ር አምባሳደር የሺመብራት የብሔራዊ በጎ ፈቃድ ማኅበረሰብ አገልግሎት ፖሊሲ ተቀርፆለት በራሱ መዋቅር የሚመራ ተቋም ሆኖ እንዲቋቋም በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ምክረ ሃሳብ መቅረቡን ጠቁመዋል።

ፕሮግራሙ ወጣቶችን ለቀጣይ ሀገራዊ ኃላፊነት የሚያዘጋጅና የበጎ ፈቃድ ተግባር ማኅበረሰባዊ መሠረት እንዲኖረው የሚያደርግ ውጤታማ ጅምር መሆኑን የገለጹት ደግሞ በሰላም ሚኒስቴር የሚኒስትር አማካሪ የሆኑት ክቡር አምባሳደር እሼቱ ደሴ ናቸው፡፡

“በማኅበረሰብ ውስጥ ሥር የሰደደና ማኅበረሰቡን ባለቤት ያደረገ የበጎ ፈቃድ ሥራ ማከናወን ከጊዜያዊነት ባሻገር ዘላቂነት ይኖረዋል” ያሉት አምባሳደር አሸቱ በፕሮግራሙ ወጣቶችን በስፋት ማሳተፍ ለሰላም፣ ለሀገራዊ አንድነትና ብሔራዊ መግባባት ቁልፍ ሚና እንደሚኖረው ገልፀዋል፡፡

በሲዳማ ክልል በግብርና ቴክኖሎጂ ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነውአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2017  የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂን በመጠቀም የአ...
30/08/2025

በሲዳማ ክልል በግብርና ቴክኖሎጂ ምርታማነትን ለማሳደግ እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2017 የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ በክልሉ የግብርና ቴክኖሎጂን በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ አሉ፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በክልሉ በተለያዩ ወረዳዎች በመኸር አርሻ እየተከናወነ ያለውን የሰብል ልማት ተዘዋውረው በመመልከት አርሶ አደሮችን አበረታተዋል።

በዚህ ወቅትም በክልሉ በ2017/18 የመኸር እርሻ በዋና ዋና ሰብሎች 3 ነጥብ 5 ሚሊየን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ እየተሰራ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

በመኸር እርሻው የግብርና ቴክኖሎጂን በአግባቡ በመጠቀም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት፡፡

አሲዳማ መሬትን ለማከም የኖራ አቅርቦትና አጠቃቀም እንዲሻሻል ከቅድመ ዝግጅት ጀምሮ ትኩረት በመሰጠቱ አርሶ አደሩ ኖራን በአግባቡ እንዲጠቀም ማድረግ ተችሏል።

በተጨማሪም የአርሶ አደሩ የምርጥ ዘር እና የማዳበሪያ አጠቃቀም እየተሻሻለ እንዲመጣ መደረጉን ነው ያስረዱት፡፡

በሌላ በኩል የሰብል በሽታ መከላከልና አረም ቁጥጥር ሥራ በአግባቡ እንዲመራ በትኩረት እንደሚሰራ አመልክተዋል፡፡

የሰላምም ጀግና አለው! - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማሕበራዊ የትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ ከጦርነት በላይ ሰላም ዋጋ ያስከፍ...
29/08/2025

የሰላምም ጀግና አለው! - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በማሕበራዊ የትስስር ገፃቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፤ ከጦርነት በላይ ሰላም ዋጋ ያስከፍላል፤ ትዕግሥት ያስጨርሳል፤ ትከሻ ያጎብጣል፤ እልህን ያስውጣል፤ ደካማ ያስመስላል ብለዋል።

ለዚህ ነው የሰላም ጀግንነት ከጦርነት ጀግንነት የሚበልጠው ሲሉ አስፍረዋል።

ሰላማዊ አማራጭን የተከተሉ፣ ሐሳባቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ ለማቅረብ የፈቀዱ፣ የሠለጠነውን መንገድ ለመሞከር የቆረጡ ታጣቂዎች ሰሞኑን ወደ ተሐድሶ ማዕከላት እየገቡ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

ይህ የሰላም ጀግንነት በመሆኑ ከአድናቆት ጋር እናመሰግናቸዋለን ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በዚህ ውሳኔያቸው ሀገር ታተርፋለች፣ እናት ትጽናናለች፣ መሬትም ታርፋለች ብለዋል። በዚህ ውሳኔያቸው አዲስ የሰላም ጀግንነት ታሪክ እንደሚፅፉ አስረድተዋል።

የዘመናችን ትልቁ ጀግንነት የሰላም ጀግንነት ነውና ሌሎችም የእነርሱን አርአያ ተከትለው የሰላምን አማራጭ እንደሚመርጡ እናምናለን ሲሉ አስፍረዋል።

የሰላም ጀግንነትን ዐውቀው ለወሰኑ፣ ላስተባበሩ፣ መርቀው ለተቀበሉ፣ ለሰላም እና ለሕግ የበላይነት ሁሌም የማይናወጥ አቋሙን ላሳየው ሕዝባችን የከበረ ምስጋና አቀርባለሁ ብለዋል።

የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ የከሊፋ ኢንተርናሽናል አዋርድ ዋና ፀሐፊ አብዱልሃብ ዛይድን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ(አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) የ...
29/08/2025

የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ የከሊፋ ኢንተርናሽናል አዋርድ ዋና ፀሐፊ አብዱልሃብ ዛይድን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ

(አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር)

የመጀመሪያው የኢትዮጵያ አለም አቀፍ የቴምር ፌስቲቫል
ከነሐሴ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ቀናት በአፋር ክልል ሰመራ ከተማ በድምቀት መከበሩ ይታወቃል።

በፌስቲቫሉ የውጭ እና የሀገር ውስጥ ቴምር አምራቾች ምርታቸውን አቅርበው ለማስተዋወቅና ተሞክሮዎቻቸውን ለማካፈል ዕድል የፈጠራላቸው ሲሆን የቴምር ልማት ቴክኖሎጂዎችም ቀርበዋል፡፡

የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ እና የከሊፋ ኢንተርናሽናል አዋርድ ዋና ፀሐፊ አብዱልሃብ ዛይድ አፋር ላይ የተከበረው የቴምር ፌስቲቫል ለኢትዮጵያ
መልካም አጋጣሚ መሆኑ ተጠቅሷል።

የከሊፋ ኢንተርናሽናል አዋርድ ዋና ፀሐፊ አብዱልሃብ ዛይድ (ዶ/ር) በዓለም አቀፍ የቴምር ፌስቲቫል በጥሩ ሁኔታ መከበሩን ግብረ መልስ ሰጥተዋል።

በፌስቲቫሉ የተለያዩ ቴምር አምራቾች ምርታቸውን አቅርበው ለማስተዋወቅና ተሞክሮዎቻቸውን ለማካፈል ትልቅ ዕድል ያገኙበት እንደነበር በውይይቱ ተገልጿል።

የግብርና ሚኒስትሩ እና የከሊፋ ኢንተርናሽናል አዋርድ ዋና ፀሐፊ በቀጣይ በቴምር ልማት በጋራ ለመስራት በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ፍሬያማ ውይይት አድርገዋል።

ዘጋቢ፦ ባህሩ ሰጠኝ
ፎቶግራፈር፦ ጌታቸው ምትኩ

‎ኢትዮጵያና ጆርዳን ያላቸውን የሁለትዩሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከርና በተለያዩ መስኮች በጋራ ለመስራት ፅኑ ፍላጎት እንዳላቸው ገለፁ‎*****************‎‎(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22/...
29/08/2025

‎ኢትዮጵያና ጆርዳን ያላቸውን የሁለትዩሽ ግንኙነት የበለጠ ለማጠናከርና በተለያዩ መስኮች በጋራ ለመስራት ፅኑ ፍላጎት እንዳላቸው ገለፁ
‎*****************

‎(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 22/ 2017 ዓ.ም) የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በኢትዮጵያ የጆርዳን አምባሳደር የሆኑትን ዶ/ር ኢማድ መሳልሜህ በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

‎የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ክብርት ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ በዚሁ ወቅት፥ ኢትዮጵያና ጆርዳን በባህልና በታሪክ እንዲሁም በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስኮች ጠንካራ ግንኙነት እንዳላቸው ገልፀዋል።

‎ሁለቱ ሀገራት የሴቶችና ወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት፣ የህፃናትን መብትና ደህንነት፣ የአረጋውያንና አካል ጉዳተኞችን ተካታችነትና ተደራሽነት ከማረጋገጥ አኳያ ያላቸውን ሰፊ ልምድና ተሞክሮ በመለዋወጥ ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር ይኖርባቸዋል ብለዋል።

‎በተጨማሪም በተለያዩ ምክንያቶች ለኢኮኖሚና ማህበራዊ ችግሮች ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመታደግ እየተከናወኑ ላሉ ተግባራት የጆርዳን ትብብርን ጠይቀዋል።

‎በየዘርፉ የተነደፉ ነባርና አዳዲስ ፕሮጀክቶች መኖራቸው ጠቁመው ለስኬታማነቱ ከጆርዳን ጋር ያለውን የሁለትዩሽ ግንኙነት ማጠናከርና በጋራ ለመስራት ፅኑ ፍላጎት እንዳላቸው ክብርት ሚኒስትሯ ገልፀዋል።

‎በኢትዮጵያ የጆርዳን አምባሳደር ዶ/ር ኢማድ መሳልሜህ በበኩላቸው፥ ሚኒስቴሩ ሴቶችን ከማብቃትና የውሳኔ ሰጪነት ሚና ከማሳደግ በተጨማሪ በሌሎችም ዘርፎች እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት አድንቀዋል።

‎በቀጣይም የቴክኒክ ኮሚቴ በማቋቋም የቀረበውን የፕሮጀክት ሃሳብ በአጭር ጊዜ ውስጥ በጋራ ለመተግበር የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ለመፈራረም የስራ ሃላፊዎቹ ተስማምተዋል።

የሶማሊያው መሪ ከተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች እና  ከሱዳን ጋር ውይይት አደረጉመንግስታዊው የሶማሊያ ብሄራዊ የዜና አገልግሎት (Sonna) እንደዘገበው የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ...
28/08/2025

የሶማሊያው መሪ ከተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች እና ከሱዳን ጋር ውይይት አደረጉ
መንግስታዊው የሶማሊያ ብሄራዊ የዜና አገልግሎት (Sonna) እንደዘገበው የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ውይይት ያደረጉት ትናንት ሞቃዲሾ ውስጥ ከሱዳን ወታደራዊ መረጃ ሃላፊ እና ከተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ሚኒስትር የልዑካን ቡድን ነው።
እንደዘገባው የኤምሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሻክቦት ቢን ናህያን አል ናህያን «የወንድማማችነት ግንኙነቶችን እና ጥልቅ ትብብርን ለማጠናከር » ከሶማሊያው መሪ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት ማድረጋቸውን ገልፀዋል። ሁለቱ ሀገራት በጸጥታ እና ኢኮኖሚያዊ ግንኙነት ላይ አተኩረው ተወያይተዋልም ተብሏል።
የሁለቱ ሀገራት ውይይት የተካሄደው የሶማሊያው ፕሬዚዳንት፤ የሱዳኑን የስለላ ሀላፊ አህመድ ኢብራሂም አሊ ሙፋዳልን ተቀብለው ካነጋገሩ በኋላ ነው።በውይይቱ የሶማሊያ የስለላ ድርጅት ዳይሬክተር ማሃድ ሳላድ የተገኙበት ነበር።
በካርቱም የሚገኘው የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እና የሱዳን ወታደራዊ መንግስት ግንኙነት አሁንም ሻካራ ነው።ካፒታል ኦንላይን የተባለው የግል መገናኛ ዘዴ እንደዘገበው የሶማሊያው መሪ ከሱዳኑ የስለላ ኃላፊ ጋር የሚያደርጉት ግንኙነት የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች ልዑካንን እንዳሳሰበ ጠቁሟል።

በጌዴኦ ዞን በመሬት ናዳ የ9 ሰዎች ሕይወት አለፈአዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2017 -- በጌዴኦ ዞን ራጴ ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡አደጋው ትናንት ምሽት 5 ሰ...
28/08/2025

በጌዴኦ ዞን በመሬት ናዳ የ9 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2017 -- በጌዴኦ ዞን ራጴ ወረዳ በደረሰ የመሬት ናዳ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው ትናንት ምሽት 5 ሰዓት አከባቢ መከሰቱን የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ብሩ ማርቆስ ለፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ተናግረዋል፡፡

በተከሰተው አደጋም እስካሁን የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ማለፉን ነው የገለጹት፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በራጴ ወረዳ በደረሰው የመሬት ናዳ ሕይወታቸውን ላጡ ዜጎች የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸው ለተጎጂ ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

የክረምቱ ዝናብ መጠንከር ጋር ተያይዞ ለአደጋ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ተመሳሳይ አደጋ እንዳይከሰት አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስበዋል፡፡

በተመሳሳይ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልደ (ዶ/ር) እና ሌሎች የሥራ ሃላፊዎች ዛሬ በራጴ ወረዳ ተገኝተው የተጎጂ ቤተሰቦችን አጽናንተዋል።

ዋና አስተዳዳሪው በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ በተከሰተው አደጋ ለተፈናቀሉ እና ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች አስፈላጊው ድጋፍ ይደረጋል፡፡

በማስተዋል አሰፋ

ኩታ-ገጠም የአስተራረስ ዘዴ ፋይዳው የላቀ በመሆኑ አርሶአደሩ በፍቃዱ እየተገበረው ይገኛል(ጋምቤላ፣ ነሀሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) በጋምቤላ ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ...
28/08/2025

ኩታ-ገጠም የአስተራረስ ዘዴ ፋይዳው የላቀ በመሆኑ አርሶአደሩ በፍቃዱ እየተገበረው ይገኛል

(ጋምቤላ፣ ነሀሴ 22 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር)

በጋምቤላ ክልል የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት ቢሮ ም/ኃላፊ ኡጁሉ ሉዋል አርሶአደሮችን የኩታ-ገጠም የአስተራረስ ዘዴ (ክላስተር) ላይ ግንዛቤ በማስጨበጥ በተለይም በቆሎ፣ ሩዝ እና ማሽላ የሰብል አይነቶች በኩታ ገጠም እንዲለማ እየተደረገ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
ምክትል የቢሮ ኃላፊው አያይዘውም የኩታ ገጠም የአስተራረስ ዘዴ ለክትትልና ድጋፍ አመቺ በመሆኑ በዚህም የአርሶአደሩ ተጠቃሚነት የጎላ ነው ብለዋል፡፡

የሌማት ትሩፋት እና የአረንጓዴ አሻራ ኢንሼቲቮች በክልሉ በህዝብ ንቅናቄ እየተተገበሩ መሆኑንም አንስተው፤ በዚህም አበረታች ውጤት እየተመዘገበ እንደሆነ አስገንዝበዋል፡፡ በሌማት ትሩፋት ፕሮግራም ወጣቶች እየተደራጁ በዶሮ፣ በዓሳ፣ በንብ እና በወተት ሃብት ልማት አመርቂ ውጤት መገኘቱን አቶ ኡጁሉ ገልፀዋል፡፡

በዘንድሮ የመኸር እርሻ ምርትና ምርታማነትን ለማስደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ያነሱት ም/ቢሮ ኃላፊው ለአርሶአደሩ የግብርና ግብዓት በወቅቱ እንዲደርስ እየተደረገ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ዮሐንስ ደመቀ

የኢትዮጵያ ልዑክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የተላከ መልዕክት ለደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት አደረሰ   አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2017 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ልዑክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ...
27/08/2025

የኢትዮጵያ ልዑክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የተላከ መልዕክት ለደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት አደረሰ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 21፣ 2017 የኢትዮጵያ ከፍተኛ ልዑክ ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተላከ መልዕክት ለደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ማያርዲት አድርሷል።

በገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሺዴ የተመራው ከፍተኛ ልዑክ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ ጉዳዮች ልዩ አማካሪ ግርማ ብሩ እና ሌሎች ከፍተኛ ኃላፊዎችን የያዘ ነው።

ልዑኩ መልዕክቱን ባደረሰበት ወቅት የደቡብ ሱዳን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

ትውልድ ቁጭቱን በተስፋ የገለጠበት ፕሮጀክትየውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ትውልዱ የዘመናት የልማት ቁጭቱን በራሱ አቅም ታላቁ የሕዳሴ ግድብን እውን በማድረግ መወጣ...
27/08/2025

ትውልድ ቁጭቱን በተስፋ የገለጠበት ፕሮጀክት

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ትውልዱ የዘመናት የልማት ቁጭቱን በራሱ አቅም ታላቁ የሕዳሴ ግድብን እውን በማድረግ መወጣት መቻሉን ገለፁ።

ኢትዮጵያ በዜጎቿ ርብርብ ያሳካችውን ግዙፍ የኃይል ማመንጫ ግድብ በቅርቡ በልዩ ድምቀት ለመመረቅ በዝግጅት ላይ መሆኗን ጠቅሰዋል።

የሕዳሴ ግድብ የሚያመነጨው ኤሌክትሪክ ሀገራዊና ቀጣናዊ የኃይል ተደራሽነትን ለማስፋት ትልቅ አቅም እንደሆነም ተናግረዋል።

ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በውሃ ሃብቶቿ ለመጠቀም በተለያዩ ጊዜያት ሙከራዎችን ስታደርግ እንደነበር አንስተው፤ ሕዳሴ ግድብ የቁጭት ፕሮጀክት ነው ብለዋል።

የአሁኑ ትውልድ ሕዳሴ ግድብን በብርቱ ክንዱ እውን በማድረግ የኢትዮጵያን የዘመናት ቁጭት ያሳካ ጀግና ትውልድ ነው ሲሉ ገልፀዋል።

ግዙፉ ፕሮጀክትም ለቀጣዩ ትውልድ ጭምር የይቻላል መንፈስን የሚያወርስ ደማቅ የልማት አሻራ እንደሆነ ነው የተናገሩት።

በሀገር ውስጥ እና በዓለም ዙሪያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በፕሮጀክቱ ግንባታ ሂደት ያለአንዳች ልዩነት በንቃት በመሳተፍ ደማቅ ታሪክ መፃፋቸውንም አውስተዋል።ቅ

ፕሮጀክቱ ለዘመናት የቆየውን ኢ-ፍትሐዊ የውሃ ሀብት አጠቃቀም የቀየረ መሆኑንም አንስተዋል።

ግድቡ ለታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በቂ ውሃ በመልቀቅ የጎርፍ አደጋን ማስቀረት እንዳስቻለም ገልፀዋል።

በግዙፉ ፕሮጀክት የግንባታ ሂደት እስከ ሕይወት መስዋዕትነት የከፈሉ ዜጎች ከትውልድ ትውልድ ሲዘከሩ ይኖራሉ ብለዋል።

Address

Addis Ababa
1000

Telephone

+251900482656

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሰላም ሚዲያ /ሰሚ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share