ሰላም ሚዲያ /ሰሚ/

ሰላም ሚዲያ /ሰሚ/ Competent and Comprehensive Media!
ተወዳዳሪና አቃፊ ሚዲያ
Miidiiyaa Hammataa fi Dorgomaa!

ስለ ሰላም ፤ ፖለቲካ ፤ ነጻነት፤ አንድነት፤ ጤና ፤ ስፖርት እና ምጣኔ ሀብት አገልግሎታችሁን በነጻ ለማስተዋወቅ እንኳን ወደ ድርጂታችን በደህና መጣችሁ፡፡
Tajaajila nageenyaa ,siyyaasaa, tokkummaa, bilisummaa , fayyaa ,spoortii fi diinagdee keessan bilisaan beeksifachuuf baga gara dhaabbilee keenyaa nagaan dhuftan
Well come toward our organization to freely promote and advertise about peace, unity, freedom, politics, healthy, sport and economic service

በአፋር ክልል የመልሶ ማቋቋም ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ*******የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ አደጋዎች ጉዳት በደረሰባቸው...
22/10/2025

በአፋር ክልል የመልሶ ማቋቋም ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ
*******

የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ በተፈጥሮና ሰው ሠራሽ አደጋዎች ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች የተለያዩ የትምህርት፣ የጤና እና የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶችን አስመርቀዋል።

በክልሉ በሚገኙ ሲፍራ፣ አዳዓርና ኡዋ ወረዳዎች የተመረቁት ፕሮጀክቶች ፤ በኅብረተሰቡ ላይ የነበረውን ተደራራቢ ጫና ለማቃለል ያስችላሉ ተብሏል።

በአጠቃላይ አራት የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ አንድ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ አምስት የጤና ኬላዎች እና ሦስት የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች በዓለም ባንክና በጣሊያን መንግሥት ድጋፍ ተሠርተው ተመርቀዋል።

የአርብቶ አደሩን ማኅበረሰብ በአንድ አካባቢ የእንስሳት መኖ፣ የመጠጥ ውኃ እና ሌሎች አገልግሎቶችን እንዲያገን በሶላር የሚሰሩ የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች ወደሥራ መግባታቸውንም ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ ገልፀዋል።

በክልሉ መልሶ መቋቋም ፅ/ቤት አማካኝነት በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ላይ በርካታ መሠረተ ልማት ሥራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝም ተጠቁሟል።

በቀጣይ በሌሎች የክልሉ አካባቢዎች መሠል የትምህርት፣ የጤና እና የመጠጥ ውኃ ፕሮጀክቶች ተመርቀው ለኅብረተሰቡ አገልግሎት እንደሚሰጡ ተገልጿል።

በሁሴን መሀመድ

‎ለሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለፀ‎***************‎(አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12/ 2018 ዓ.ም) የሴቶች ኢኮኖሚ ማብቃት ብሔራዊ ስት...
22/10/2025

‎ለሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገለፀ
‎***************
‎(አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12/ 2018 ዓ.ም) የሴቶች ኢኮኖሚ ማብቃት ብሔራዊ ስትራቴጂ ዝግጅት ላይ የግብዓት ማሰባሰቢያ መድረክ እየተካሄደ ነው።

‎በመድረኩ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ሂክማ ኸይረዲን፥ መንግስት ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ሪፎርም ማካሄዱን ተከትሎ ለውጦች መመዝገባቸውንና በሂደቱም የሴቶች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እያደገ መምጣቱን ተናግረዋል።

‎በተካሄደ ሰፊ የንቅናቄ ስራ በህብረት ስራ ማህበራት የተደራጁ ሴቶች ከ27 ቢሊዮን ብር በላይ መቆጠብ መቻላቸውን ገልፀዋል።

‎የገጠር ሴቶች በተናጠልና በጋራ በመሆን ግብርናን ማዕከል ባደረጉና በሌሎችም መስኮች በመሰማራት የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛል ብለዋል።

‎ይሁንና አሁንም የብድር፣ የዋስትና፣ የመስሪያ ቦታ፣ የክህሎትና መሠል ችግሮች መኖራቸው ለሴቶች የኢኮኖሚ ተሳትፎና ተጠቃሚነት መረጋገጥ ማነቆ ስለመሆናቸው አንስተዋል።

‎ሚኒስቴሩ የሴቶች ፖሊሲ ክለሳ እና የስርዓተ ፆታ እኩልነትና ማብቃት ፖሊሲ ዝግጅትን እየተጠናቀቀ መሆኑንና ሌሎች ደጋፊ የአሰራር ማዕቀፎች እንዲቀረፁና በስራ ላይ እንዲውሉ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፥ ለሴቶች ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልፀዋል።

‎ዩኤን ውመን/UNWOMEN/ በሴቶች የኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ዙሪያ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላትን ያቀፈ ፎረም ከማቋቋም በተጨማሪ ለስትራቴጂው ዝግጅት ላበረከተው የላቀ አስተዋፅዖ ምስጋና አቅርበዋል።

‎ስትራቴጂው እንደሀገር የሴቶች የኢኮኖሚ ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት እና የላቀ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ውጤታማ እንዲሆን የበኩሉን አገዛ እንደሚያደርግ ያላቸውን እምነት ገልፀው ለተግባራዊነቱ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

‎የዩኤን ውመን ኢትዮጵያ ሀገራዊ ፕሮግራም ተወካይ ሚስተር ሻድራክ ዱሳቤ በበኩላቸው፥ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለሴቶች መብት መከበር፣ ለስርዓተ ፆታ እኩልነትና ሴቶችን ለማብቃት የተጓዘውን ርቀትና የተገኘውን ውጤት አድንቀዋል።

‎በቀጣይም ዩኤን ውመን ሴቶችን በኢኮኖሚ ለማብቃት የተጀመሩ ስራዎችን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በጋራ እንደሚሰራና ድጋፍም እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

   በኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ የዶካቱ ማህበረሰብ ባህላዊ አስተዳደራዊ የትውልድ ሽግግር ሥርዓት በልዩ ልዩ ባህላዊ ኩነቶች እየተከበረ ነው።የትውልድ ሽግግር የሆነው ባህላዊ ስርዓት/“ካራ...
21/10/2025

በኮንሶ ዞን ካራት ዙሪያ ወረዳ የዶካቱ ማህበረሰብ ባህላዊ አስተዳደራዊ የትውልድ ሽግግር ሥርዓት በልዩ ልዩ ባህላዊ ኩነቶች እየተከበረ ነው።

የትውልድ ሽግግር የሆነው ባህላዊ ስርዓት/“ካራ” በስርዓቱ አስፈፃሚ አባቶች፣ በአስረካቢ እና ተረካቢ ትውልዶች/ኸሊታዎች እየተከበረ ይገኛል።

“ካራ” የትውልድ ባህላዊ የስልጣን ርክክብ ሥርዓት ሲሆን፤ የሠላም ነጋሪት የሚጎሰምበት፣ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ የተኮራረፉ ይቅርታ የሚጠያየቁበት፣ የተራራቁ ወገኖች የሚገናኙበት አሰባሳቢና በ18 ዓመት ሁለት ጊዜ የሚከበር ባህላዊ ኩነት ነው።

ስርዓቱን ለማስፈፀም በርካታ ጥብቅ ባህላዊ ስርዓቶች የሚከናወኑ ሲሆን፤ ወጣቶች/ ተረካቢ ኸሊታዎች/ “ክቶዋ” በሚባል የአብሮነት መሰባሰቢያ ቤት በመግባት ኃይል የማሰባሰብና የመመካከር ስርዓት ይፈፅማሉ።

የመንደሩ ወጣት ሴቶችና ያልተፈቀደላቸው አካላትም በመንደሩ/"ክቶዋ" በሚውሉበት ባለመገኘትና የትውልዱን ቀልብ ባለማሸፈት አጋርነታቸውን ይገልፃሉ።

የካራን ሥርዓት በቀደምትነት ያስረከቡ ታላላቅ አባቶች በበኩላቸው በመንደሩ መግቢያና መውጫ በር በመቀመጥ ያልተፈቀደላቸው አካላት ወደ መንደሩ እንዳይገቡ በመከላከል ወይንም ሲፈቀድላቸው በባህላዊ ስርዓት/በማንፃት እንዲገቡ ያደርጋሉ፤ ከመንደሩ/"ክቶዋ" የገቡ እንዳይወጡ ይጠብቃሉ።

ለሥርዓቱ ጥንካሬና ክብር ሲባል ማንም የአባቶችን ትዕዛዝና ተግሳጽ አይጥስም፤ አይደፍርምም።

የስርዓቱን ሙሉ መረጃ በቪዲዮ የምናጋራችሁ ይሆናል።
ጥቅምት 11/2018ዓ.ም

አቶ አህመድ ሽዴ ከዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ግጭቶች መፍቻ ማዕከል ዋና ፀሐፊ ጋር ተወያዩአዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2018  የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ከዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት...
21/10/2025

አቶ አህመድ ሽዴ ከዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ግጭቶች መፍቻ ማዕከል ዋና ፀሐፊ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 11፣ 2018 የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ ከዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ግጭቶች መፍቻ ማዕከል ዋና ፀሐፊ ማርቲና ፖላሴክ ጋር ኢትዮጵያ የማዕከሉ አባል በምትሆንባቸው ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡

አቶ አህመድ ሽዴ በዚህ ወቅት÷ መንግስት ለባለሃብቶች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ግጭቶች መፍቻ ማዕከልን (ICSID) ከተቀላቀለች ሀገሪቱን ከዓለም አቀፍ የኢንቨስትመንት ማህበረሰብ ጋር ለማዋሃድ እንዲሁም የባለሃብቶችን አመኔታ ለማሳደግ ሚናው ከፍተኛ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የኢትዮጵያ የማዕከሉ አባል መሆን የንግዱን ዘርፍ ለማሳለጥ፣ የግሉን ዘርፍ ለማጠናከር እና የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረውም ጠቁመዋል፡፡

የማዕከሉ ዋና ፀሐፊ ማርቲና ፖላሴክ በበኩላቸው÷ ኢትዮጵያ ማዕከሉን ለመቀላቀል ያላትን ፍላጎት በማድነቅ በአባልነት ሂደቱ የቴክኒክ ድጋፍ እና መመሪያ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡

ኢትዮጵያ ያሳየችው ፍላጎትም በኢንቨስትመንት ዘርፍ የሚፈጠሩ አለመግባባቶችን ለመፍታት እና ለዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎች ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ መሆኑን አስገንዝበዋል፡፡

ሁለቱ ወገኖች ኢትዮጵያ የማዕከሉ አባል ለመሆን በምታደርገው ጥረት ተቀራርቦ ለመስራት እና በአዲስ አበባ የቴክኒክ አውደ ጥናት እንዲዘጋጅ ከስምምነት ደርሰዋል፡፡

የእምነት አባት የሆኑት አባታችን ሙፍቲ ሃጂ ኡመር ኢድሪስ በማረፋቸዉ የተሰማንን ሀዘን እየገለጽኩ ይኝህ አባታችን በነፈሳቸዉ ምድር ላይ በተመላለሱበት ወክት አበርክተዉልን የለፉትን በረከት ፤...
21/10/2025

የእምነት አባት የሆኑት አባታችን ሙፍቲ ሃጂ ኡመር ኢድሪስ በማረፋቸዉ የተሰማንን ሀዘን እየገለጽኩ ይኝህ አባታችን በነፈሳቸዉ ምድር ላይ በተመላለሱበት ወክት አበርክተዉልን የለፉትን በረከት ፤ሙስሊማዊ ስነምግባርና አስተምረዉ በአሁኑ ወክት አመራር ላይ ያሉ አባቶቻችን ወጉንና ህጉን አስጠብቀዉ እንዲያጸኑት ሊቦና እንዲሰጥልን፤ ጸጋቸዉን እንዲያበዛልን እንዲሁም የአባታችን ነፍስ ጄነት ለቤተሰቦቻቸዉና ለመላ ሙስሊም መህበረሰብ ጽናቱን እንዲሰጥልን መልካም ምኞታችን ነው፡፡

ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ለአዲስ ገቢ  ተማሪዎች ያስተላለፋት መልዕክትጥቅምት 11፣ 2018  ጅማ ዩኒቨርሲቲ*********************ውድ ተማሪዎቻችን !የምዕራቧ ፈርጥ በሆነችው በታሪካዊቷ...
21/10/2025

ዶ/ር ጀማል አባፊጣ ለአዲስ ገቢ ተማሪዎች ያስተላለፋት መልዕክት
ጥቅምት 11፣ 2018
ጅማ ዩኒቨርሲቲ
*********************
ውድ ተማሪዎቻችን !
የምዕራቧ ፈርጥ በሆነችው በታሪካዊቷ ፣ በለምለሚቷና በውቢቷ ጅማ ከተማ የሚገኘው ወደ ጅማ ዩኒቨሪሲቲ እንኳን በሰላም መጣችሁ። አንጋፋውና በማኅበረሰብ ተኮር የትምህርት ፍልስፍናው በሃገራችን ፈር ቀዳጅ የሆነውን ዩኒቨርሲቲያችንን -ጅማ ዩኒቨርሲቲ- መርጣችሁ በመምጣታችሁ ደስ ብሎናል፣ እንኳን ደስ አላችሁ !

በሐገር አቀፍ ደረጃ የተሰጠውን የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት በማስመዝገብ ምርጫችሁን ጅማ ዩኒቨርሲቲ በማድረጋችሁ የተሰማኝን ደስታም በራሴና በመላው የዩኒቨርሲቲያችን ማኅበረሰብ ስም ለመግለፅ እወዳለሁ!

ውድ ተማሪዎቻችን!
በጅማ ዩኒቨርሲቲ በሚኖራችሁ ቆይታ ከልጅነታችሁ ጀምሮ የሰነቃችሁት ራዕይ ተሳክቶ ፣ ውጤታማ እንድትሆኑ ለማስቻል መላው የጅማ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ የሚጠበቅብንን ሁሉ ለማድረግ አስፈላጊውን ሁሉ ዝግጅት አድርገን እየጠበቅናችሁ እንገኛለን።

በቆይታችሁ በዩኒቨርሲቲያችን ብቸኛውና ልዩ በሆነው በማኅበረሰብ ተኮር የትምህርት ፕሮግራማችን በመሳተፍ በክፍል ውስጥ የምትማሩትን የንድፈ ሃሳብ ትምህርት ወደ ተግባር በመቀየር ተግባራዊ ልምድ የመቅሰም እድል ይኖራችኋል።

በዘንድሮው አመት በተለይ ልዩ የወላጅ ተማሪ ቃልኪዳን ፕሮግራም ያዘጋጀን ሲሆን ፣ በዚህ ፕሮግራምም በእንግዳ አክባሪነቱ በሰላሙና በፍቅሩ የሚታወቀውን የጅማ አባጅፋርን ህዝብ በቅርበት የማወቅ ብሎም እንደ ወላጅ አስፈላጊውን የስነልቦናና ማህበራዊ ድጋፍ የምታገኙበት እድል ይኖራችኋል። በዚህም ከትምህርት ባሻገር ለዘመናት የሚታወስ ትዝታን ትሸምታላችሁ !

ውድ ተማሪዎቻችን !
እናንተ ሁሌም ውዶቻችን ናችሁ ! ለዚህም የመምህራኖቻችን ፣ የሰራተኞቻችን የስራ ሃላፊዎቻችን ሁሉ ዋነኛ ትኩረት እናንተ ተማሪዎቻችንና የእናንተ ትምህርት ነው ፣ በመሆኑም የእናንተን ደህንነት፣ የእናንተን ምቾት፣ የእናንተን ውጤታማነት ለማረጋገጥ የምንቆጥበው ጉልበት፣የምንሳሳለት ሃብት አይኖርም ! ስኬታችሁ ስኬታችን ነው ከዚያ ሌላ የስኬት መለኪያ የለንም !

ውድ ተማሪዎቻችን !
በድጋሚ ጅማ ዩኒቨርሲቲ በመመደባችሁ እንኳን ደስ ያላችሁ እያልኩ ፣ ቆይታችሁ ያማረ ይሆን ዘንድ ጥልቅ ምኞቴን ልገልፅላችሁ እወዳለሁ።

በማህበረሰቡ ውስጥ ነን !

ጀማል አባፊጣ (ፒ ኤች ዲ)
ፕሬዘዳንት

ከጉባ ብስራቶች አንዱ - የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ****************ኢትዮጵያ የምትገነባው የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ሀገሪቱ ከማዳበሪያ አቅርቦት ጋር ተያይዞ ሊደርሱባት የሚችሉ ጫናዎችን...
17/10/2025

ከጉባ ብስራቶች አንዱ - የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ
****************

ኢትዮጵያ የምትገነባው የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ሀገሪቱ ከማዳበሪያ አቅርቦት ጋር ተያይዞ ሊደርሱባት የሚችሉ ጫናዎችን እንድትቋቋም አቅም የሚሰጣት ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ ገለጹ።

አቶ አዲሱ ከኢቢሲ ኤፍ.ኤም አዲስ 97.1 ጋር ባደርጉት ቆይታ፥ የተለያዩ ሀገራት ከምግብ ዋስትና ባሻገር ሉዓላዊነትን እና የላቀ ምርታማነትን ማረጋገጥ የቻሉት መሰል የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በመጠቀም እንደሆነ አንስተዋል።

ኢትዮጵያ የምትገነባው የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካም ግንባታው ሲጠናቀቅ በተመሳሳይ የሀገሪቱን የግብርና ምርት እና ምርታማነት እንደሚያልቀው ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።

የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ምክትል ኃላፊ በሪሳ ፈይሳ በበኩላቸው፥ የሕዝብ የረጅም ጊዜ ጥያቄ የነበረውን የማዳበሪያ አቅርቦት ለማሳደግ ቁርጠኛ እርምጃ መወሰዱ ምርታማነትን የሚያሳልጥ ስለመሆኑ ነው የተናገሩት።

የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካው እየጨመረ የመጣውን የአርሶ አደሩ የማዳበሪያ ፍላጎት የሚያረካ እና የምግብ ዋስትናን የሚያረጋገጥ ነው ያሉት ደግሞ የሲዳማ ክልል እርሻ እና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ መምህሩ ሞኬ ናቸው።

በሌላ በኩል የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታው ፕሮጀክት መጀመር አዲስ ተስፋ የፈጠረባቸው አርሶ አደሮች፥ ይህ ጅማሮ ለተሻለ ምርታማነት ተነሳሽነትን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።

አክለውም፥ የአፈር ማዳበሪያ ፋብሪካው በሕዳሴ ግድብ ላይ ያየነውን የመንግሥት ቁርጠኝነት እና የሕዝብ አንድነት ይበልጥ ያረጋገጠ ነው ብለዋል።

በሴራን ታደሰ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርት ሱዳን የበረራ አገልግሎት ዳግም ጀመረ  የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዛሬ ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ፖርት ሱዳን የሚያደርገውን በረራ ዳግም መ...
15/10/2025

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖርት ሱዳን የበረራ አገልግሎት ዳግም ጀመረ


የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከዛሬ ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ፖርት ሱዳን የሚያደርገውን በረራ ዳግም መጀመሩን አስታውቋል።

በቀን አንድ በረራ በማድረግ ዛሬ ዳግም የጀመረው አገልግሎት ከጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በቀን ወደ ሁለት በረራዎች የሚያድግ መሆኑን አየር መንገዱ ገልጿል።

በላሉ ኢታላ

ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ከሶሪያ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ ጋር በሞስኮ ተወያዩየሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና የሶሪያ አረብ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ በክሬምሊን ውይ...
15/10/2025

ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ከሶሪያ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ ጋር በሞስኮ ተወያዩ

የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን እና የሶሪያ አረብ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ በክሬምሊን ውይይት አድርገዋል።

ሁለቱ ወገኖች በውይይታቸው በሀገራቱ መጻዒ የሁለትዮሽ ግንኙነት እና በሶሪያ የሚገኙ የሩሲያ ጦር ሠፈሮች ጉዳይ ላይ ትኩረት አድርገው መምከራቸው ተገልጿል፡፡

ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን፤ በሁለቱ ሀገራት መካከል ለረዥም ዘመናት የቆየ ወዳጅነትና ግንኙነት እንዳለ አንስተው፤ በአልሻራ የሚመሩት ኃይሎች በሶሪያ ድል መቀዳጀታቸው ለሀገሪቱና ለህዝቡ ትልቅ ስኬት መሆኑን ገልፀዋል፡፡

ፕሬዝዳንት አህመድ አል ሻራ በበኩላቸው፤ አዲሱ የሶሪያ መንግሥት ከሩሲያ ጋር ያለውን ታሪካዊ ግንኙነት ማደስ እንደሚፈልግ ተናግረዋል፡፡

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ፤ በዛሬው ዕለት በሁለቱ መሪዎች መካከል የተደረገው ውይይት ለሩሲያ እና ሶሪያ ግንኙነት ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን መጥቀሳቸውን ስፑቲንክ ዘግቧል።

አንጋፋው የኬንያ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ አረፉየቀድሞ የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና አንጋፋው የኬንያ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ ለህክምና በሄዱበት በህንድ ዛሬ በልብ ድካም አ...
15/10/2025

አንጋፋው የኬንያ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ አረፉ

የቀድሞ የኬንያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና አንጋፋው የኬንያ ተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ራይላ ኦዲንጋ ለህክምና በሄዱበት በህንድ ዛሬ በልብ ድካም አረፉ። የ80 ዓመቱ ኦዲንጋ በህንድ ከእህታቸው ከልጃቸውና ከግል ሐኪማቸው ጋር በእግር እየሄዱ ድንገት ተዝለፍልፈው ከወደቁ በኋላ ወዲያውኑ አፋፍሰዋቸው በአቅራቢያው ወደሚገኝ ሆስፒታል ተወስደው ነበር። ሆኖም ሆስፒታል እንደደረሱ መሞታቸው መረጋገጡን የህንድ ፖሊስን ጠቅሶ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት AFP ዘግቧል።

በወቅቱ አንድ የህንድ ፀጥታ አስከባሪ መኮንንና አንድ የኬንያ የፀጥታ መኮንን አብረዋቸው እንደነበሩም ፖሊስ ተናግሯል።ኦዲንጋ መሞታቸውን AFP ስማቸው እንዲጠቀስ ካልፈለጉ ከአንድ የፖለቲካ ፓርቲያቸው አባልም አረጋግጧል። በጎርጎሮሳዊው ጥር 1945 ዓ.ም. የተወለዱት ኦዲንጋ የወጣትነት እድሚያቸውን በእስር ቤት ወይም በስደት በያኔው የኬንያ ፕሬዝዳንት ዳንኤል አራፕ ሞይ የስልጣን ዘመን ዴሞክራሲ እንዲሰፍን በመታገል ነው ያሳለፉት።

የሉቦ ጎሳ ተወካይ ሆነው በጎርጎሮሳዊው 1992 የፓርላማ አባል የሆኑት ኦዲንጋ በጎርጎሮሳዊው 1997፣ 2007፣2013፣ 2017 እና 2022 ለፕሬዝዳንትነት ተወዳድረው ሳይሳካላቸው ቀርቷል። የኦዲንጋ ሞት በተቃዋሚዎች አመራር ዘንድ ክፍተት መፍጠሩ እንደማይቀር ይገመታል፤ ተቃዋሚዎችን በማንቀሳቀስ እርሳቸውን የሚተካ ፖለቲከኛ መገኘቱም ግልጽ አይደለም።

ኦዲንጋ በኬንያ የተቃውሞ ታሪክ በተለይም ከትውልድ አካባቢያቸው ከምዕራብ ኬንያ በርካታ ቁጥር ያላቸውን ሰዎች ማሰባሰብ የቻሉና ትልቅ ኃይል ሆነው የዘለቁ ፖለቲከኛ ነበሩ።
የኬንያ ፖለቲከኞች በኦዲንጋ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን በመግለጽ ላይ ናቸው። ከውጭ ሀገራት መሪዎች የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በራይላ ኦዲንጋ ሞት የተሰማቸውን ሀዘን ከገለጹትት የመጀመሪያዎቹ መሪዎች መካከል አንዱ ናቸው ሲል AFP ዘግቧል።

የኩታ ገጠም እርሻ ምርታማነትን ከ30 በመቶ በላይ ማሳደግ አስችሏል - አቶ አዲሱ አረጋየኩታገጠም እርሻ ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ ሚናን እየተጫወተ መሆኑን የግብርና ሚኒስ...
11/10/2025

የኩታ ገጠም እርሻ ምርታማነትን ከ30 በመቶ በላይ ማሳደግ አስችሏል - አቶ አዲሱ አረጋ

የኩታገጠም እርሻ ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ ሚናን እየተጫወተ መሆኑን የግብርና ሚኒስትሩ አቶ አዲሱ አረጋ ገለጹ።

አቶ አዲሱ ከፌደራል እና ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በጉራጌ ዞን፣ በአበሽጌ ወረዳ እና በቀቤና ልዩ ወረዳ በኩታ ገጠም እየለሙ ያሉ የበቆሎ እና የጤፍ ማሳዎችን ጎብኝተዋል።

ሚኒስትሩ በዚሁ ወቅት እንዳሉት የኩታገጠም እርሻ ምርት እና ምርታማነትን በማሳደግ ረገድ ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል።

በዘንድሮው የመኸር እርሻ ከ20 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች ተሸፍኗል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ከዚህ ውስጥ 12.3 ሚሊዮን የሚሆነው በኩታገጠም እርሻ የለማ መሆኑን ገልጸዋል።

አሁን ላይ በሀገሪቱ በስፋት እየተሠራበት የሚገኘው የኩታ ገጠም እርሻ ምርታማነትን ከ30 በመቶ በላይ ማሳደግ አስችሏል ብለዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ስሩር በበኩላቸው፥ በክልሉ በመኸር እርሻ ከለማው 564 ሺህ ሄክታር መሬት ከ54 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠበቅ ገልጸዋል።

በወንድወሰን አፈወርቅ

እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!ኩባንያችን በትናንትናው እለት በተካሄደው ዓመታዊ ታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና ሥነ-ሥርዓት ላይ በ2017 በጀት ዓመት 37.5 ቢሊዮን ብር በመክፈል ...
10/10/2025

እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!

ኩባንያችን በትናንትናው እለት በተካሄደው ዓመታዊ ታማኝ ግብር ከፋዮች የእውቅና ሥነ-ሥርዓት ላይ በ2017 በጀት ዓመት 37.5 ቢሊዮን ብር በመክፈል በአንደኛ ደረጃ የፕላቲኒየም ታማኝ ግብር ከፋይነት እንዲሁም ላለፉት ተከታታይ 5 ዓመታት ግብርን በግንባር ቀደምነት በመክፈል ልዩ ተሸላሚ መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው::

ይህም የላቀ አፈጻጸም ሊመዘገብ የቻለው ኩባንያችን በበጀት ዓመቱ የተለያዩ የቢዝነስ አማራጮችን በመተግበር በተለይም መጠነ ሰፊ የመሰረተ ልማት ማስፋፊያዎችን በማከናወን፣ የተለያዩ የዲጂታል ሶሉሽኖችና አገልግሎቶችን በማቅረብ እንዲሁም የአገልግሎት ተጠቃሚ ደንበኞቻችን መጨመር ጋር ተያይዞ ገቢያችንን ማሳደግ በመቻላችን ነው፡፡

ኩባንያችን ከኮኔክቲቪቲ ባሻገር የማህበረሰባችንን ሁሉን አቀፍ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ዲጂታል አገልግሎቶችን በስፋት በማቅረብ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ራዕይ ስኬት ግንባር ቀደም ሚናው ጎን ለጎን ባለፉት 7 ዓመታት ከ157.5 ቢሊዮን ብር በላይ ግብር በታማኝነት በመክፈል የምንጊዜም የሃገር አለኝታና ኩራትነቱን አረጋግጧል።

ክቡራን ደንበኞቻችን እና አጋሮቻችን፤ ለማህበረሰባችን ህይወት መሻሻል እና ኢኮኖሚ ተጠቃሚነት እንዲሁም ለሀገር ግንባታ የበኩላችንን እንድናበረክት አብሮነታችሁ ስላልተለየን ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን።

በቀጣይም የሶስት ዓመት ቀጣዩ አድማስ፡ ዲጂታልና ከዚያም ባሻገር 2028 ስትራቴጂያችን የኢትዮጵያን የዲጂታል ልዕልና ማጎናጸፍ እና ከዚያም ባሻገር ራዕያችንን ከማሳካት ጎን ለጎን ግብርን በታማኝነት በመክፈል ለዜጎች ተጠቃሚነትና ለሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት እንደምንተጋ በድጋሚ እናረጋግጣለን።

ስለተሰጠን እውቅና ከልብ እናመሰግናለን!

ግብር፣ ለሀገር ክብር!

Address

Addis Ababa
1000

Telephone

+251900482656

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሰላም ሚዲያ /ሰሚ/ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share