ኢትዮ ሰላም ሚዲያ

ኢትዮ ሰላም ሚዲያ Competent and Comprehensive Media!
ተወዳዳሪና አቃፊ ሚዲያ
Miidiiyaa Hammataa fi Dorgomaa!

ስለ ሰላም ፤ ፖለቲካ ፤ ነጻነት፤ አንድነት፤ ጤና ፤ ስፖርት እና ምጣኔ ሀብት አገልግሎታችሁን በነጻ ለማስተዋወቅ እንኳን ወደ ድርጂታችን በደህና መጣችሁ፡፡
Tajaajila nageenyaa ,siyyaasaa, tokkummaa, bilisummaa , fayyaa ,spoortii fi diinagdee keessan bilisaan beeksifachuuf baga gara dhaabbilee keenyaa nagaan dhuftan
Well come toward our organization to freely promote and advertise about peace, unity, freedom, politics, healthy, sport and economic service

አመራሩ ሕዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል መዘጋጀት አለበት - አቶ ሙስጠፌ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2017 በየደረጃው ያለ አመራር ሕዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል ከመቼ...
16/06/2025

አመራሩ ሕዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል መዘጋጀት አለበት - አቶ ሙስጠፌ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2017 በየደረጃው ያለ አመራር ሕዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል ከመቼውም ጊዜ በላይ መዘጋጀት አለበት አሉ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሃመድ፡፡

በብልጽግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት እና በአፍሪካ አመራር ልቀት አካዳሚ ለክልሉ አመራሮች ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቅቋል።

አቶ ሙስጠፌ በዚህ ወቅት ÷ የለውጡን መልካም ጅምሮችና እየተመዘገቡ ያሉ ውጤቶችን የሚያስቀጥል ጠንካራ አመራር እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

አመራሩ ከምንም በላይ ሕዝብን በቅንነትና በታማኝነት ማገልገል እንዳለበት የተናገሩት ርዕሰ መስተዳድሩ ÷ ለዚህም በእውቀት የሚመራ ሙሉ ፍላጎትና ዝግጁነት ያለው አመራር ሊኖር ይገባል ብለዋል፡፡

በመሆኑም በየደረጃው ያለ አመራር ሕዝብን በላቀ ብቃትና ቁርጠኝነት ለማገልገል ከመቼውም ጊዜ በላይ መዘጋጀት አለበት ሲሉ አሳስበዋል።

በሁሉም ዘርፎች አሁን ላይ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ እየታገዙ፣ በእውቀት የሚመሩና በብቃትና ክህሎት የሚሰጡ በመሆኑ ከጊዜው ጋር እውቀትንና ብቃትን ማሳደግ ያስፈልጋል ነው ያሉት፡፡

በክልሉ በሁሉም መስኮች አስደናቂ የልማት ሥራዎችና ተጨባጭ ውጤቶች እየተመዘገቡ መሆኑን ጠቅሰው÷ የሕዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥና በትኩረት እንደሚሰራ ማስገንዘባቸውንም ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/ በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

ጀግናው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ-'--አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2017 በርካታ ጀግና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዓለም ላይ በሚያደርጓቸው ውድድሮችና በሚያመጧቸው ውጤቶች የሀገራቸውን ህዝብ በደስታ ...
13/06/2025

ጀግናው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ-'--አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2017 በርካታ ጀግና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዓለም ላይ በሚያደርጓቸው ውድድሮችና በሚያመጧቸው ውጤቶች የሀገራቸውን ህዝብ በደስታ ዕንባ አራጭተዋል፤ ስሜትን ከፍ ዝቅ የሚያደርጉ በርካታ አኩሪ ገድሎችንም ሰርተዋል፤ እየሰሩም ይገኛሉ።

ነገር ግን እርሱ ከሁሉም ልዩ ነው ትውልድ ከትውልድ የሚቀባበላቸው ዘመን ተሻጋሪ የጀግንነት እና የአሸናፊነት ታሪኮችን በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ጽፏል፤ የጀግንነቱን ግማሽ ያህል እንኳን ያልተዘመረለት ነው ቀነኒሳ በቀለ፡፡

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በዓለም መድረክ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ ካደረጉ ጀግና አትሌቶች መካከል በግንባር ቀደምነትም ይጠቀሳል፡፡

አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በመሮጫ ትራኩ ላይ ከተገኘ ኢትዮጵያ ወርቅ እንደምታገኝ ብዙዎች እርግጠኛ ሆነው ውድድሩን ይመለከታሉ፤ እሱም በተደጋጋሚ ውድድሮችን በበላይነት በማጠናቀቅ ኢትዮጵያውያንን የሚፈልጉትን የቀዳሚነት ስፍራ ባለማስነካት አኩርቷቸዋል።

ለኢትዮጵያ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ በርካታ ወርቅ ያመጣ ሲሆን፤ በግል ውድድሮች ካገኛቸው ድሎች በላይ ለሀገር ያሳካቸው ድሎች ይበልጣሉ፡፡

አትሌት ቀነኒሳ ለሀገሩ ኢትዮጵያ 24 የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል፤ የሰበሰባቸው የወርቅ ሜዳሊያዎች ብዛት ብዙ ሀገራት አንድ ላይ ተደምረው ማምጣት የማይችሉትን ነው፡፡

ከበቆጂ ተነስቶ የሚሊየኖች ተምሳሌት ሆኖ ከትራክ እስከ ሀገር አቋራጭ ከዚያም በማራቶን የደመቀው ቀነኒሳ፤ በስብዕናውም ይወደዳል።

በአትሌቲክሱ ዓለም ባሳካቸው ገድሎች ከዘመን ዘመን የሚወሳ፣ ኢትዮጵያ የምትኮራበት እና ትውልድ ሊማርበት የሚገባው ጀግና ነው፡፡

የአትሌት ሀይሌ ገብረስላሴን ፈለግ እንደተከተለ የሚነገርለት ቀነኒሳ በቀለ፤ የመጨረሻ ዙርን ልክ እንደ አጭር ርቀት የሚሮጥ፣ በአትሌትነት ዘመኑ በሰራቸው ታሪኮች ስሙን በወርቅ ቀለም ማስፈር የቻለ የኢትዮጵያ ውድ ልጅ ነው።

የኢትዮጵያ የምንግዜም ምርጡ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ዛሬ 43ኛ ዓመት የልደት በዓሉ ነው፡፡

በወንድማገኝ ፀጋዬ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/ በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የማስፈፀሚያ  ማንዋሎች ላይ ለአስፈፃሚ አካላት አቅም ግንባታ  ስልጠና እየተሠጠ ነው(አዳማ፣ ሰኔ 6/2017 ዓ.ም) በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የማ...
13/06/2025

በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የማስፈፀሚያ ማንዋሎች ላይ ለአስፈፃሚ አካላት አቅም ግንባታ ስልጠና እየተሠጠ ነው

(አዳማ፣ ሰኔ 6/2017 ዓ.ም) በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የማስፈፀሚያ ማንዋሎች ላይ የአስፈፃሚ አካላት አቅም ለማጎልበት ያለመ ስልጠና እየተሠጠ ነው።

በመድረኩ ላይ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማህበራዊ ጥበቃ ማስተባበሪያና መከታተያ መሪ ስራ አስፈፃሚ ተወካይ አቶ ቴዎድሮስ ሹመቴ እንደገለፁት በገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ለዜጎች የሚሰጡ የስነ-ልቦናና ማህበራዊ አገልግሎቶች የተጠቃሚዎች መብትና ሰብዓዊ ክብር የሚያስጠብቁ ሊሆኑ ይገባል።

ከክልል ጀምሮ በየደረጃው በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች የስነ-ልቦናና ማህበራዊ ድጋፍ ሲያደርጉ የትግበራ ስርዓቶችንና እውቀትን መሰረት ባደረገ መልኩ ሊሆን እንደሚገባ ጨምረው ገልፀዋል።

በተለያዩ ችግሮች ውስጥ ያሉ የህብረተሰብ ክፍሎች ምን ዓይነት የስነልቦናና ማህበራዊ ችግር ያጋጥማቸዋል? የአእምሮ ጭንቀቶች መንስኤያቸው ምንድናቸው? ለነዚህ ችግሮች የምክር አገልግሎት ለመስጠት መርሆዎቹ ምንድናቸው? በሚሉት ዋና ዋና ሀሳቦች ላይ ስልጠናው ያተኮረ በመሆኑ ለስራቸው ውጤታማነት የበኩሉን እገዛ ያደርጋል ብለዋል።

ለዚህም ሰልጣኞች በስልጠናው ያገኙትን ክህሎት በአግባቡ በስራ ላይ እንዲያውሉም አሳስበዋል።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለፕሮጀክቱ ስኬታማ ትግበራ አስፈላጊውን እገዛና ድጋፍ እንደሚያደርግም አስታውቀዋል።

******
ስለ ሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ከታች ያሉ ገፆቻችንን ይጎብኙ

For more information follow Ministry of Women and Social Affairs pages
*
ድረ ገጽ፦ https://www.mowsa.gov.et/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/EthiopiaMoWSA
ቴሌግራም፦ https://t.me/MowsaEthiopia
ዩትዩብ፦ ministry of women and social affairs

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴት እና አካል ጉዳተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ፖለቲካዊ ተሣትፏቸና የሚደርሱባቸው ተግዳሮቶችን የተመለከተ ሥልጠና ሰጠየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ...
13/06/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴት እና አካል ጉዳተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ፖለቲካዊ ተሣትፏቸና የሚደርሱባቸው ተግዳሮቶችን የተመለከተ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴት እና አካል ጉዳተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ፖለቲካዊ ተሣትፏቸውና የሚደርሱባቸው ተግዳሮቶችን የተመለከተ ሥልጠና ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም. ሰጠ። ሴት እና አካል ጉዳተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ወደ ፖለቲካ ተሣትፎ ሲመጡና በአመራርነት ሲሠሩ፤ እንዲሁም በምርጫ ወቅት ጭምር የሚያጋጥሟቸውን ተግዳሮቶችና መወሰድ ስላለባቸው የመፍትሔ ዕርምጃዎችን የተመለከተ ግንዛቤ መፍጠር ዐላማው አድርጎ የተሰጠውን ሥልጠና በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግርቸውም ቦርዱ እንደ አዲስ ሲቋቋምና ዐዋጅ ሲረቅ በዋነኝነት ታሳቢ ካደረጋቸው ነገሮች ውስጥ ሕጉ የሴቶችና የአካል ጎዳተኞች ተሣትፎን የሚያበረታቱ ድንጋጌዎች እንዲካተቱበት ማድረጉን በዋነኝነት ጠቅሰው፤ ቦርዱ በዛ ሳይወሠን በጉዳዩ ላይ የተለያዩ ሥልጠናዎችን ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም አሁንም ብዙ መሥራት እንደሚጠይቅ ተናግረዋል።

ቦርዱ ባሻሻለውና እንዲፀድቅለት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በላከው ዐዋጅ ላይ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞች ተሣትፎን የበለጠ ለማበረታታት የሚያስችል የሕግ ድንጋጌዎችን እንዲካተቱ ማድረጉን የገለጹት ሰብሳቢዋ፤ በጉዳዩ ላይ የተሻለ መፍትሔ ማምጣት ከተፈለገ በስትራቴጂ የተደገፉ ሥራዎችን መሥራት እንደሚጠይቅም አብራርተዋል።

ቦርዱ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞችን ተሣትፎን ለማበረታታት በማሰብ የሚያደርገውን ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ ተከትሎ፤ እንደ ቅድመ ሁኔታ ፓርቲዎች የሚያቀርቧቸው የፓርቲው ሴቶች እና አካል ጉዳተኛ አባላት ቁጥር እንዲሁም አመራሮች ብዛት ላይ የተሳሳተ መረጃ በሚያቀርቡበት ጊዜ ገንዘቡ ተመላሽ እንዲሆን የሚያደርገውና በሕጉ አስገዳጅነት እስከ ማገድና መሠረዝ የሚደርስ ውሣኔዎችን የሚያሳልፍበት ዋነኛ ምክንያት ገንዘብ የማስመለስ ጉዳይ ሣይሆን፤ ፓርቲዎች ሴቶችን እና አካል ጉዳተኞችን በአባልነት እና በአመራር ለማምጣት የሚደረገውን ጥረት ትኩረት እንዲሰጡት ለማድረግ ታስቦ እንደሆነ አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።

በጉዳዮ ላይ ሳይንሳዊ መንገድ ተከትሎ የተሠሩ ጥናቶችን መሠረት አድርጎ ሁሉም በግል የሚያደርገውን ጥረት በጋራ በማምጣት፤ መማማርና ልምድ መለዋወጥ እንዲቻ፤ በዘርፉ ላይ ጥናት ያደረጉት ባለሞያ ለዶ/ር ፍሬሕይወት ስንታየሁ እና የቦርዱ ሥርዓተ ፆታ ዕኩልነትና ማኅበራዊ አካታችነት ሥራ ክፍል ኃላፊዋ ክብረወርቅ ንጉሤ እንዲሁም ከፍተኛ የሥርዓተ ፆታ ባለሞያዋ ዮርዳኖስ ተወልደ በሰጡት ሥልጠና ላይ፤ ሴቶችና አካል ጉዳተኞች ወደ ፖለቲካ ፓርቲ ተሣትፎና ወደ አመራርነት እንዳይመጡ የሚያደርጓቸው ተግዳሮቶች ምንድናቸው የሚለውን የመለየት ሥራና ምን መፍትሔ መወሰድ ይገባል በሚለው ላይ ተሣታፊዎቹ ግንዛቤ እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን፤ ይኽም ሲሆን ከራሳቸው ከሴቶቹና ከአካል ጉዳተኞቹ፣ ከፓርቲዎች፣ ከሲቪል ማኅበረሰብ ተቋማት፣ ከመንግሥት እና ከምርጫ ቦርድ ምን ይጠበቃል የሚለውም በስፋት ለውይይት ቀርቧል።

አሣታፊ በነበረው ሥልጠና ላይ ፆታና ሥርጻተ-ፆታ እንዲሁም በፓርቲ ውስጥና ባጠቃላይ በፖለቲካዊ ምኅዳሩ ውስጥ እንዲሁም በምርጫ ወቅት የሚያጋጥሙ ፆታን መሠረት አድርገው የሚፈጸሙ ጥቃቶች የትኞቹ ናቸው የሚለውን በመለየት፤ መፍትሔዎቻቸውስ ምንድን ናቸው የሚለውም እንዲሁ በዝርዝር ታይቷል። ተሣታፊዎች በጠቀሱት ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ በቡድን እንዲወያዩበት የተደረገ ሲሆን፤ ሁሉም የውይይታቸው ግኝቶችን በቡድን ተወካዮቻቸው አማካኝነት እንዲያቀርቡት ተደርጓል።

የቦርዱ ሰብሳቢ በሥልጠናው መጨረሻም ባደረጉት ንግግርም፤ ቦርዱ ከሥልጠናው ቀደም ብሎ ሴቶች እና አካል ጉዳተኛ ፖለቲከኞች ያሉባቸውን ተግዳሮቶች አስመልክቶ ያስጠናው ጥናት ውጤት ለሥልጠናው መዘጋጀት እንደምክንያት ጠቅሰው፤ ውጤት መምጣት የሚችለው ተሣታፊዎቹ ከሥልጠናው ያገኙትን ዕውቀት በተዋረድ ለአባላቶቻቸውና በዙሪያቸው ላሉ የማኅበረሰብ ክፍሎች ማስተማር ሲችሉ መሆኑን አሳስበዋል።

ቦርዱን ጨምሮ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ትኩረት ሰጥተው መሥራት እንደሚጠበቅባቸው የገለጹት ሰብሳቢዋ፤ የዚኽ ሁሉ ጥረት ውጤት በ7ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ላይ እንደሚታይ ያላቸውን ዕምነት ገልጸዋል። በመጨረሻም ሥልጠናውን ለሰጡ ባለሞያዎችና ተሣታፊዎች እንዲሁም ላስተባበረው የቦርዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጉዳይ ሥራ ክፍል ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ከአውሮፕላን አደጋ የተረፈውን ብቸኛ ተሳፋሪ ጎበኙየሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ከትናንትናው የአውሮፕላን አደጋ በተዓምር የተረፈውን ብቸኛ ተሳፋሪ  በ...
13/06/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ከአውሮፕላን አደጋ የተረፈውን ብቸኛ ተሳፋሪ ጎበኙ

የሕንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ከትናንትናው የአውሮፕላን አደጋ በተዓምር የተረፈውን ብቸኛ ተሳፋሪ በዛሬው እለት ጎብኝተዋል፡፡

ከአደጋው የተረፈው የ40 ዓመቱ እንግሊዛዊ ቪሽዋሽ ኩመር ራምሽ በአህመዳባድ ከተማ በሚገኝ ሆስፒታል የሕክምና ክትትል እየተደረገለት ነው፡፡

ቪሽዋሽ ኩመር ራምሽ ከአደጋው እንዴት እንደተረፈ ምንም የሚያውቀው ነገር እንደሌለ መግለጹን ዘ ቴሌግራፍ ዘግቧል።

ጠቅላይ ሚንስትር ሞዲ በተፈጠረው አደጋ በእጅጉ ማዘናቸውን ገልጸው፤ በአደጋው ተጎጂ ለሆኑ ቤተሰቦች መፅፅናናትን ተመኝተዋል፡፡

ከሕንድ አህመዳባድ አውሮፕላን ማረፊያ 242 መንገደኞችን አሳፍሮ ወደ ለንደን ጉዞ ለማድረግ ከተነሳ በኋላ በሰከንዶች ውስጥ በተከሰከሰው የአውሮፕላን አደጋ ምክንያት እስካሁን ባለው መረጃ ከ240 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተረጋግጧል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ የታገዘ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓት መተግበሪያውን ለባለድርሻ አካላት አስተዋወቀየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ የታገዘ የምርጫ አስተዳደር ...
12/06/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ የታገዘ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓት መተግበሪያውን ለባለድርሻ አካላት አስተዋወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ የታገዘ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓት መተግበሪያውን ለፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች እንዲሁም ለሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አስተዋወቀ። ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም. የተካሄደውን የማስተዋወቂያ መርኅ-ግብር በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ማስፈጸሙ ተከትሎ የምርጫ ሥርዓቱን ለማዘመን ያግዛሉ ያላቸውን በርካታ ሥራዎች ሲሠራ መቆየቱን አስታውሰው፤ ከነዚኽም ውስጥ በባለድርሻ አካላት በተለያዩ ጊዜ አስተያየት ሲሰጥበት የነበረው ዘመናዊ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓትን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት መራጮችና ዕጩዎች በቴክኖሎጂ ታግዘው የሚመዘገቡበትን መተግበሪያ ማበልጸጉን ተናግረዋል።

ይኽ ትግበራ የቴክኖሎጂ ኢንፍራስትራክቸር በተዘረጋባቸው አካባቢዎች በሙሉ ተግባራዊ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀው መተግበሪያ ሲሠራ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንደተደረገ የተናገሩት ሰብሳቢዋ፤ ለደኅንነት ሥጋት ሊኖረው የሚችለውን ተጋላጭነት ለማስቀረት ሲስተሙን ከውጭ ከመግዛት ይልቅ በራስ ዐቅም በባለሞያዎች በማበልጸግ የቴክኖሎጂ ሥርዓቱ ዋነኛ ባለቤትና ተቆጣጣሪ ምርጫ ቦርዱ እንዲሆን በሚያስችል አግባብ እንደተዘጋጀ አብራርተዋል።

በቴክኖሎጂ ስለሚታገዘው ሥርዓት ጠቀሜታ ሲያብራሩም፤ ምርጫ በመጣ ቁጥር መራጮችን እንደ’አዲስ የተለያየ ቁጥር በመስጠት የሚከናወን የአመዘጋገብ ልማድን በማስቀረት ቋሚ የመራጮች መታወቂያ ቁጥርና መዝገብ በማኖር፤ መራጮች እንደ አዲስ መታወቂያ ማውጣት ሳይጠበቅባቸው ቋሚ ቁጥራቸውን በማስገባት ብቻ የሚመዘገቡበት ሥርዓት በማበጀት፤ መራጮችን ለመመዝገብ የሚጠፋውን ገንዘብ፣ ጊዜና ጉልበት እንዲሁም ጥቅም ላይ የሚውሉ የምርጫ ቁሳቁስ ወጪዎችን መቀነስ እንደሚያስችል አብራርተዋል።

መተግበሪያው ከላይ ከተጠቀሱት ጠቀሜታዎች ባለፈ በአንድ ምርጫ ሁለቴና ከዛ በላይ ለመመዝገብና ለመምረጥ የሚደረግን ሕገ-ወጥ ተግባር በማስቀረት ዕጩዎች ፍትሐዊ በሆነ መልኩ ድምፅ እንዲያገኙ የሚያስችል ሲሆን፤ አኃዛዊ የሆኑትን ጨምሮ መረጃዎችን በቀላሉ ለማደራጀትም እንዲሁ ያግዛል።

በእጅ ስልክ አማካኝነት በራስ፤ እንዲሁም በቦርዱ ባለሞያዎች አጋዥነት በቴክኖሎጂ በመታገዝ የሚደረግ የመራጮች ምዝገባ ሥርዓት፣ በሌላ በኩል የግልና የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች ባሉበት ቦታ ወይም በጽ/ቤታቸው በመሆን በቴክኖሎጂ በመታገዝ የሚያከናውኑት የዕጩነት ምዝገባ ሥርዓት፤ እንዲሁም በድምፅ መስጫ ቀን መራጮች በምርጫ ጣቢያ በአካል በመገኘት በቴክኖሎጂ የታገዘ የመራጭነት ማመሳከሪያ በማድረግ የሚከናወን ድምፅ የመስጠት ሂደት ምን ሊመስል እንደሚችል በቅድም ተከተል ተሣታፊዎች እንዲያዩት የተደረገ ሲሆን፤ ይኽንንም ተከትሎ ተሣታፊዎቹ ባዩት ነገር እንደረኩና ለቦርዱም ትልቅ አድናቆት እንዳላቸው ገልጸው፤ በቴክኖሎጂ የታገዘው የመራጮችና የዕጩዎች የምዝገባ ሥርዓት ተግባራዊ በሚደረግበት ወቅት ሊከሰቱ የሚችሉ ተገማችና ተገማች ላልሆኑ ዕክሎች ቦርዱ ምን መፍትሔ አዘጋጅቷል ሲሉ በርካታ ጥያቄዎችን አንስተዋል። ለቀረቡት ጥያቄዎች የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ መልስ የሰጡ ሲሆን፤ ቴክኒካል ለሆኑት ሞያዊ ጥያቄዎች ደግሞ በቦርዱ ባለሞያ አማካኝነት መልስ ተሰጥቶባቸዋል።

ለጊዜው በከፊል ተግባራዊ ይደረጋል ተብሎ የታሰበው መተግበሪያን የደኅንነት ሥጋት አስመልክቶ ለቀረበው ጥያቄ የቦርዱ ባለሞያው መልስ ሲሰጡም፤ መተግበሪያው በርካታ የደኅንነት መፈተሻ ሥርዓቶችን ያለፈ እንደሆነና ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግበት ተናግረዋል።

መተግበሪያው ተግባራዊ በሚደረግባቸው አካባቢዎች ጎን ለጎን የቦርዱ ባለሞያዎች የማስተባበር ሥራ እንደሚሠሩና፤ ተግባራዊ በማይደረግባቸው አካባቢዎች ግን ቀደም ሲል በነበረው የማንዋል ሥርዓት ምርጫው እንደሚደረግ ዋና ሰብሳቢዋ ገልጸዋል። ቦርዱ መተግበሪያውን በሚያበለጽግበት ጊዜ ከፍተኛ ትኩረት ካደረገባቸው ጉዳዮች ውስጥ የደኅንነት ጉዳይና አካታችነት ዋነኞቹ እንደሆኑና፤ በቀጣይ መተግበሪያው በዐዋጅ ፀድቆ ለሕዝብ ይፋ በሚያደርግበት ጊዜም በማስተዋወቅያ መድረኩ ላይ የተሰጡ ግብዓቶችንና ዐዋጁ ላይ የተቀመጡትን ድንጋጌዎች ከግምት ውስጥ ባስገባ መልኩ የበለጠ ዳብሮ እንደሚሆን ሰብሳቢዋ በአጽንዖት ተናግረዋል።

የቻይና መንግስት ለኢትዮጵያ 321,000 ዶዝ የኮሌራ ክትባት ድጋፍ አደረገ  _____________የቻይና መንግስት ለኢትዮጵያ ያደረገዉ የ 321,000 ዶዝ የኮሌራ ክትባት ድጋፍ ርክክብ ተከ...
12/06/2025

የቻይና መንግስት ለኢትዮጵያ 321,000 ዶዝ የኮሌራ ክትባት ድጋፍ አደረገ
_____________

የቻይና መንግስት ለኢትዮጵያ ያደረገዉ የ 321,000 ዶዝ የኮሌራ ክትባት ድጋፍ ርክክብ ተከናወነ።

በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ለቻይና ህዝብና መንግስት ላደረጉት ድጋፍ ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ይህ ድጋፍ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጠንካራ አጋርነት ያሳያል ብለዋል። በቀጣይም ድጋፉ ተጠናክሮ እንድቀጥል የጠየቁት ሚኒስትሯ በጤናው ሴክተር በሁለቱ ሀገራት መካከል በትብብር እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ይበልጥ ተጠናክሮ እንደሚቀጥሉ ያላቸዉን እምነት ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼንግ ሃይ ሁለቱ ሀገራት በጤናው ዘርፍ ያላቸውን የቆየ ትብብር አስታውሰው፤ "ኢትዮጵያ እና ቻይና ሁልጊዜም ተቀራርበው ሲሰሩ መቆየታቸዉን ገልጸዋል። እነዚህ ክትባቶች ውጤታማ በሆነ መንገድ ጥቅም ላይ እንድዉሉ የጠየቁት አምባሳደሩ፤ ከኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር ጋር ቀጣይነት ያለው ትብብር ለማድረግ ቁርጠኛ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ መድሃኒት አቅርቦት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱላቃድር ገልገሎ በበኩላቸው ድጋፉ የኢትዮጵያን የህብረተሰብ ጤና ተግዳሮቶች ለመቅረፍ ያለውን ወሳኝ ሚና በመጥቀስ ድጋፉን ተቀብለዋል። ዳይሬክተሩ "ይህ ድጋፍ ራቅ ባሉ አካባቢዎች የሚገኙ ማህበረሰቦችን በእጅጉ ይጠቅማል፣ ኮሌራን ለመዋጋት የምናደርገውን ጥረት ያጠናክራል" ብለዋል።

ድጋፉ ኢትዮጵያ የበሽታዎችን ክትትልና ምላሽ አቅሟን ለማሳደግ እየሰራች ባለችበት ወሳኝ ወቅት ላይ የተደረገ መሆኑን የገለፁት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ሃይሉ፤ ክትባቶቹ የኮሌራ ወረርሽኞችን በመከላከል እና በመላ ሀገሪቱ የህብረተሰቡን ጤና ለመጠበቅ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወቱ ይጠበቃል ብለዋል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ የሰላም ሜዳሊያ ተሸለሙ  በአማራ ክልል ያጋጠመው የሰላም ችግር በውይይት እንዲፈታ ጥረት በማድረግ ክልሉን ወደ ሰላም ያመጡት የክልሉ ርዕሰ መ...
12/06/2025

የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ የሰላም ሜዳሊያ ተሸለሙ

በአማራ ክልል ያጋጠመው የሰላም ችግር በውይይት እንዲፈታ ጥረት በማድረግ ክልሉን ወደ ሰላም ያመጡት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ የሰላም ሜዳሊያ ተበርክቶላቸዋል።

ርዕሰ መስተዳድሩ ሽልማቱ የተበረከተላቸው በባሕር ዳር ከተማ በተካሄደው ኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሰላም ኮንፈረንስ ማጠናቀቂያ ላይ ነው።

የሰላም ኮንፈረንሱ በስኬት እንዲከናወን ያስቻሉ አካላትም በመርሐ-ግብሩ ማጠቃለያ ላይ እውቅና እና ምስጋና አግኝተዋል።

የሐረሪ ክልል ቀጣዩን 4ኛ ሀገር አቀፍ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የሰላም ኮንፈረንስ ለማዘጋጀት የሰላም ዋንጫ ተረክቧል።

በራሔል ፍሬው

በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላአዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በየብስም ሆነ በባሕር የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክ...
11/06/2025

በየትኛውም ሁኔታ የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል- ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በየብስም ሆነ በባሕር የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት ሠራዊት ተገንብቷል አሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ፡፡

በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የመከላከያ ሚኒስቴርን የ2017 በጀት ዓመት የ10 ወራት አቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ገምግሟል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷መከላከያ ሠራዊቱ የምስራቅ አፍሪካ ቀጣናን ሰላምና ደህንነት በዘላቂነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራነው።

ኢትዮጵያ የባሕር በር እንድታገኝ ከቀጣናው ሀገራት ጋር በትብብር ለመስራትና በጋራ ለመበልጸግ ያላሳለሰ ጥረት እያደረገች እንደምትገኝ አንስተዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት በየብስም ሆነ በባሕር የሚቃጡ ትንኮሳዎችን የሚመክት እንዲሁም የሀገሪቱን ሉዓላዊነት የሚያስከብር ሠራዊት መገንባቱን ነው ያስገነዘቡት፡፡

የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሐመድ (ኢ/ር) በበኩላቸው÷ የተቋሙን የማስፈጸም አቅም በማጎልበት ሀገርና ሕዝብን ከማንኛውም ጥቃት የመከላከል ሥራ በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

ተዓማኒነት ያለው ነጻና ገለልተኛ ወታደራዊ የፍትህ ዳኝነት እየተሰጠ መሆኑን ጠቁመው ÷ የሠራዊቱን አስተማማኝ የሎጂስቲክስ ክምችት ማሟላት መቻሉንም ተናግረዋል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/ በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴ (ዶ/ር) ጋር ተወያዩ(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) የግብ...
10/06/2025

የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴ (ዶ/ር) ጋር ተወያዩ

(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር)

የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴን በፅ/ቤታቸው ተቀብለው ኢትዮጵያ እና እስራኤል በግብርናው ዘርፍ በትብብር መስራትን አጠናክሮ ማስቀጠል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

የግብርና ሚንስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)ኢትዮጵያ እና እስራኤል የረጅም ዓመታት ታሪካዊ ግንኙነት እንዳላቸው ጠቅሰው የእስራኤል መንግስት በግብርናው ዘርፍ እያደረገ ያለውን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡

የግብርናና ገጠር ልማት ፖሊሲን በማሻሻል ዘርፉን ለማዘመን በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለፁት ሚንስትሩ የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን በሚደረገው ጥረት የእስራኤል መንግስት ድጋፍ አበርክቶው የላቀ ነው ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ የእስራኤል አምባሳደር አብርሃም ንጉሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው እስራኤል በኢትዮጵያ በግብርናው ዘርፍ እያበረከተች ያለውን አስተዋፅዖ አብራርተዋል፡፡

አምባሳደሩ አያይዘውም በቀጣይ የግብርና ማሽነሪዎች አቅርቦት፣ በስንዴ ልማት እና በአቅም ግንባታ ስራዎች ላይ በትብብር ለመስራት የእስራኤልን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል፡፡

ሚንስትሩ እና አምባሳደሩ በቀጣይ በሚሰሩ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገው መግባባት ላይ ደርሰዋል፡፡

ዘጋቢ፡- ዮሐንስ ደመቀ
ፎቶግራፍ፡- ማቲዎስ ተገኝ

#ከማምረትበላይ


----------------
ስለግብርና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፦
ድረ-ገጽ፦ www.moa.gov.et
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/MoAEthiopia
ዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/MoAEthiopianews
ቲዊተር፦ https://x.com/MoA_Ethiopia

የገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ቀጣይ አቅጣጫ የተቀናጀና ልማት ተኮር  ይሆናል-  ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር)  (አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ፣ ግብርና ሚኒስቴር)የገጠር ልማታዊ ሴ...
09/06/2025

የገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ቀጣይ አቅጣጫ የተቀናጀና ልማት ተኮር ይሆናል- ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር)

(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 2 ቀን 2017 ዓ.ም ፣ ግብርና ሚኒስቴር)

የገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የዘጠኝ ወር አፈጻጸም ግምገማ መድረክ የፌደራልና የክልል ኋላፊዎችና ባለሙያዎች እንዲሁም የአለም ባንክና ሌሎች የልማት አጋር ድርጅቶች በተገኙበት እየተካሄደ ነው፡፡

በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ (ዶ/ር) እ.ኤ.አ ከ2021 ጀምሮ በመተግበር ላይ ያለው የገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ምዕራፍ 5 ለመጠናቀቅ ጥቂት ግዜ እንደቀረው በመጥቀስ ፕሮግራሙ ተባብሮ ለመስራት ትልቅ መሰረት የተጣለበት፣ ትምህርት የተወሰደበትና ለቀጣይ ስራ ቅድመ ትንበያ ለማድረግ አሰፈላጊ መረጃ የተያዘበት መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ሚኒስትር ዴኤታው አያይዘውም ፕሮግራሙ በልማት አጋር ድርጅቶችና በፌደራል መንግስት በጀት ድጋፍ እየተተገበረ ያለ መሆኑን ተናግረው፣ የገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ቀጣይ አቅጣጫ የተቀናጀና ልማት ተኮር ይሆናል ብለዋል፡፡

የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው በበኩላቸው የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ያለውን ጥቂት ሀብት በአግባቡ እንዲጠቀሙ ከማድረግ አንጻር በልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ትልቅ ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡

የአለም ባንክ ዲቪዥን ዳይሬክተር ማሪያም ሳሊም በበኩላቸው የገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮግራም ተልዕኮ የተለየ፣ ወሳኝና ከ8 ሚሊዮን የሚበልጡ ዜጎችን ህይወት የማዳን እና ወደተሻለ ኑሮ ደረጃ በማሸጋገር ሀብት እንዲያፈሩ ማድረግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የግምገማ መድረኩ ለሶስት ቀናት ይቀጥላል፡ ፡

ዘጋቢ፡- ካሳሁን ማለቶ
ፎቶግራፈር፡- ማትዎስ ተገኝ

#ከማምረትበላይ


----------------
ስለግብርና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፦
ድረ-ገጽ፦ www.moa.gov.et
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/MoAEthiopia
ዩቲዩብ፦ https://www.youtube.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/MoAEthiopianews
ቲዊተር፦ https://x.com/MoA_Ethiopia

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስተዳደር ወደ ሥልጣን መምጣትን ተከትሎ በከፍተኛ ኃላፊነት መንግሥትን ከተቀላቀሉ ሰዎች መካከል አንዱ ናቸው፤ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መ...
09/06/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስተዳደር ወደ ሥልጣን መምጣትን ተከትሎ በከፍተኛ ኃላፊነት መንግሥትን ከተቀላቀሉ ሰዎች መካከል አንዱ ናቸው፤ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሐመድ።
አቶ መስጠፌ፤ ከሰሞኑ በኬንያ ተገኝተው የሶማሊ ማኅበረሰብ ተወካዮች፣ እንዲሁም ኬንያ ከሶማሊያ ጋር ከምትዋስንበት ጋሪሳ ካውንቲ ባለሥልጣናት ጋር ውይይት አድርገዋል።
አቶ ሙስጠፌ በኬንያ ቆይታቸው ከቢቢሲ ሶማሊኛ እና ቢቢሲ አማርኛ ጋር ቃለ መጠይቆችን አድርገዋል።
የቢቢሲ ጋዜጠኞች አቶ ሙስጠፌ በሚያስተዳድሩት የሶማሌ ክልል ውስጥ ያሉ ወቅታዊ ሁኔታዎችን፣ በክልሉ የሚፈጸሙ እስሮችን፣ የተቃዋሚውን የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባርን (ኦብነግ) የተመለከቱ ጥያቄዎችን አንስተውላቸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሆኑት አቶ ሙስጠፌ መሐመድ በቅርቡ በኬንያ ተገኝተው ከሶማሊ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር እንዲሁ....

Address

Addis Ababa
1000

Telephone

+251900482656

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ኢትዮ ሰላም ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share