NBC Ethiopia

NBC Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from NBC Ethiopia, TV Network, Addis Ababa.
(1)

NBC Ethiopia is a television station broadcasting on Ethiosat 11105 H and DSTv Channel 477
የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን እዚህ ይገኛሉ👇
https://linktr.ee/NBCEthiopiaTV

የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ የአቋም መግለጫ ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሐሳብ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ....
03/02/2025

የብልፅግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ የአቋም መግለጫ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሐሳብ ከጥር 23 እስከ 25 ቀን 2017 ዓ.ም ለሦስት ተከታታይ ቀናት የብልፅግና ዐሻራ ደምቆ በሚታይባት፣ ከተመሠረተች መቶ ሃምሳ ዓመት በኋላ ዳግም እንደገና እየተሠራችና እየፈካች በምትገኘው፣ የፓርቲያችን የሐሳብና የምናብ ኃይል በተጨባጭ ተግባር በተገለጠባት፣ በመሪዎቿ ድንቅ ትጋት ዘመናዊ ካባ በተጎናጸፈችው ውቧ መዲናችን አዲስ አበባ፣ የነዋሪዎቿን ትብብርና ርብርብ እንዲሁም ብዝኃነታችንን ጌጥ አድርጎ የሚያሳይ፣ የመላ አፍሪካውያንና የዓለም ጥቁር ሕዝቦች የነጻነት ቀንዲል በሆነው የአድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ በመክተም ሲመክር የቆየው የፓርቲያችን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በድል መጠናቀቁን ስንገልጽ በታላቅ ደስታና ኩራት ነው።

ይህ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በአንድ በኩል መላው የፓርቲያችን አመራርና አባላት በሕልም ጉልበት እየተመሩ ዕዳን ወደ ምንዳ ለመቀየርና በሀገራችን እመርታዊ ዕድገት ለማረጋገጥ የሚያስችል የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ልቆ በታየበት፤ የዴሞክራሲ፣ የፍትሕና የሕግ አስከባሪ ተቋማት ነጻነትና ገለልተኝነት በተረጋገጠበት፤ የሀገር ሀብት አጠቃቀማችንን በማሻሻልና ምርትና ምርታማነትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ከ7 በመቶ በላይ በሆነ ፈጣን ዕድገትና ለውጥ ባሳየበት፤ በሰው ተኮርና ማኅበራዊ ካፒታል ግንባታ አቅጣጫችን ሰፋፊ የምገባ፣ የቤት እድሳትና ግንባታ እና የመሳሰሉ ሥራዎች የተሠሩበትና የማኅበረሰብ መረዳዳት ባህል ወደ መሆን እየተሸጋገረ ባለበት፣ ከመሽኮርመም ዲፕሎማሲ በመላቀቅ የሀገራችንን ሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅም የሚያስከብር ዲፕሎማሲያዊ ዐውድ በተፈጠረበት፣ በሌላ በኩል ደግሞ በእነዚህ ሁለንተናዊ ድሎች እየተደመምን ቀጣይ ሕልማችንን ከዳር ለማድረስና ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተልዕኮዎችን ለመፈጸም የሚያስችል ዐቅም ባጎለበትንበትና ቁርጠኝነታችን እያደገ በመጣበት ወቅት ላይ መሆኑ እጅግ ታሪካዊና ልዩ ያደርገዋል።

ይህን መደበኛ ጉባኤ ከማካሄዳችን አስቀድመን በሁሉም የሀገራችን አካባቢዎች ከታች ጀምሮ በየደረጃው በሚገኙ የፓርቲ አደረጃጀቶች በተካሄዱ የቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንሶች መላው አመራርና አባሎቻችን በፓርቲያችን ስኬቶች፣ ፈተናዎችና የመሻገሪያ ሐሳቦች ዙሪያ ጥልቅ ውይይትና ክርክር አካሂደናል። በዚህም የጉባኤያችንን ሂደትና ውጤት ዴሞክራሲያዊነት የሚያረጋግጡ፣ ሁሉም የአደረጃጀትና የፖለቲካ ሥራዎች በተሻለ ጥራትና ብቃት ተከናውነዋል። በተለይም በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት ለዘመኑ የተቀረጹ ተልዕኮዎችን ብቻ ሳይሆን በሀገራችን አንድንድ አካባቢዎች የተፈጠረው ግጭት ባስከተለብን ጉዳትና፣ ቀጣናዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፍዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ባሳደሩብን አሉታዊ ተጽዕኖ ምክንያት ያመለጡንን ዕድሎች በሚያካክስ መንገድ በሁሉም ዘርፎች እመርታ ለማምጣት በሚያስችሉ ዕሳቤዎች ዙሪያ የተሻለ መግባባት ፈጥረናል።

በመሆኑም እኛ የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ተሳታፊዎች ፓርቲያችን ባለፉት ሦስት ዓመታት በሁሉም ዘርፍ ያስመዘገባቸው ድሎች ወደ ላቀ ደረጃ እንዲሸጋገሩ የእኛን ዘመን የአመራር ትውልድ መፍትሔ የሚሹ ጉድለቶች ደግሞ በብቃት እንዲታረሙ በሙሉ ልብ በመተማመንና የላቀ ተስፋ በመሰነቅ የሚከተለውን ባለ 8 ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተናል።

1ኛ. የመጀመሪያው ጉባዔያችን ለጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ልዩ ትኩረት የሰጠው ጠንካራ ፓርቲ ለውጤታማ መንግሥትና ለጠንካራ ሀገር ግንባታ ያለዉን ፋይዳ ከግምት ውስጥ በማስገባት ነው። ስለሆነም በሁለተኛው ጉባኤያችን የዚህን ውሳኔ አፈጻጸም፣ ስኬቶችና ጉድለቶች በጥሞና ገምግመናል። ባለፉት ሦስት ዓመታት የጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ግባችንን ለማሳካት ታልመው የተፈጸሙ የፖለቲካና የአደረጃጀት ሥራዎች ፓርቲያችንን ከዕድሜው የቀደመ የውጤትና የዕድገት ምዕራፍ ውስጥ እንዲገኝ ማድረጋቸውን አይተናል። ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በትብብርና በፉክክር መካከል ሚዛን በመጠበቅ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ባህል ለመቀየር ያሳየነው ቁርጠኝነትም ለሌሎች ሀገራት ተሞክሮ እንደሚሆን አይተናል።

ይህም ሆኖ በቅድመ ጉባዔ ኮንፈረንሶቻችንና በጉባኤያችን አማካኝነት ባካሄድናቸው ተከታታይ ውይይቶች ጠንካራ፣ ጤነኛና ውጤታማ ፓርቲ የመገንባት አጀንዳ ቋሚ ትግል የሚጠይቅ መሆኑን ተገንዝበናል። በዚህ ምክንያት የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲያችንን በማጎልበት፣ የአደረጃጀቶቻችንን ሁለገብ የተጽዕኖ አድማስ በማስፋት፣ የአሠራር ሥርዓቶቻችንን የበለጠ በማዘመንና የኢንስፔክሽንና የሥነ ምግባር ኮሚሽናችንን በየደረጃው ማጠናከር፤ እንደሚገባ አምነናል፡፡ በዚህም ጉድለቶችና ብልሽቶችን የማረም ዐቅም ያለው፣ ሀገራዊ የመንግሥት ኢንሼቲቮችን በሐሳብ የሚመራና የሕዝብ ንቅናቄዎችን በብቃት የሚያስተባብር ጠንካራ ፓርቲ ለመፍጠር የጋራ አቋም ወስደናል።

በመሆኑም በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታትም የአመራራችንንና የአባላችንን ብቃትና ጥራት በሥልጠናና በተከታታይ ውይይቶች በማሳደግ በአስተሳሰብና በተግባር ብልጽግና የሆኑ፣ የተሰጣቸውን ተልዕኮ በውጤታማነት እየፈጸሙ የሕዝቡን ሕይወት የሚለውጡ፣ በሥራና በመኖሪያ አካባቢያቸው የጠንካራ ዲስፕሊንና የመልካም ሥነ ምግባር መገለጫ የሆኑ፣ የኢትዮጵያን ሕልም እውን የሚያደርጉ አመራሮችና አባላትን በማፍራት፣ በማብቃትና የለውጡ ሞተር እንዲሆኑ በማድረግ በላቀ ውጤት የሚገለጽ ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት የምንሠራ ይሆናል።

ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት እንዲቻል አባላትን ለማጥራት የሚያስችል ውጤታማ የምዘናና የግምገማ ሥርዓት እንዲዘረጋ፤የሥነ ምግባርና የሞራል ዝቅጠት ተጠቂ በሆኑ አመራሮችና አባላት ላይ የማረም ተግባር እንዲከናወን፤አዳዲስ አባላትን የመመልመል ሥራ በጥራትና በብቃት እንዲፈጸም እንደምናደርግ እናረጋግጣለን፡፡

ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት እንዲቻል ዘመኑን ማላመድ የሚያስችሉ የሐሳብና የታሪክ ውሕደት በመፍጠር፣ መዋቅራዊ ልህቀት በማረጋገጥ፣ የፖለቲካ ስክነትን እውን በማድረግና የውጤት ዘላቂነትን በቁርጠኝት ለመፈጸም ዳግም ቃል እንገባለን!!!

2ኛ. የተቋማት ግንባታ ስኬት ለውጤታማ ሀገረ መንግሥት ግንባታ በእጅጉ ወሳኝ ነው ብለን እኛ ብልፅግናዎች ከልብ እናምናለን። ከዚህ ጽኑ እምነት ተነሥተንም ዴሞክራሲን ተቋማዊና ሕዝባዊ ባህል በማድረግ የሀገረ መንግሥት ቅቡልነትን ለማረጋገጥ ወደ ተጨባጭ ሥራ ገብተናል። በመሆኑም የተጀመረውን የተቋማት ሪፎርም በየዘርፉና በየደረጃው አጠናክረን በማስቀጠልና ነጻ፣ ገለልተኛና ብቃት ያላቸውን ተቋማት በማባዛት የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሥራችንን በጠንካራ መሠረት ላይ ለማቆምና ጠንካራ የዴሞክራሲ ባህል ለመፍጠር አበክረን የምንሠራ ይሆናል።

ፓርቲያችን የሚመራዉ መንግሥት ባለፉት ሦስት ዓመታት ልዩ ልዩ ሀገራዊ የዴሞክራሲ ተቋሞችንና የሀገር ደኅንነትንና ሉዓላዊነትን የሚጠብቁ ተቋሞቻችንን ዐቅም፣ ብቃትና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ባህል ወደ ላቀ ደረጃ በማሸጋገር የሀገራችንን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት የማስጠበቅ አስደናቂ ውጤት ማስመዝገቡን ጉባኤያችን በስኬት ተመልክቷል። በመሆኑም ሁሌም እነዚህ ተቋሞቻችን አስተማማኝ የሀገር ጋሻና መከታ ሆነው እንዲገነቡና ነጻነታቸው ተጠብቆ እንዲቀጥል በሙሉ ልብ እንደግፋለን!!! ከዚህም ጋር ተያይዞ የሕዝባችን ፍትሕ የማግኘት መብት በተሟላ መልኩ እንዲረጋገጥ፣ የፍትሕ ሥርዓቱን የማዘመን፣ ብቁ ባለሞያዎችን የማፍራት፣ ፈጣንና አስተማማኝ አገልግሎት እንዲሰጥ የማስቻል፣ የዳኞች ነጻነትንና የዳኞች ተጠያቂነትን በሚዛን የማረጋገጥ ተግባራት እንዲከናወኑ ለማድረግ በቁርጠኝነት እንታገላለን፡፡

3ኛ. ሕልማችን ኢኮኖሚያዊ ሉዓላዊነትን እውን በማድረግ የሀገራችንን ብልጽግና ማረጋገጥ ነው። ረጅም በማይባል ጊዜ ውስጥ ጠንካራና ተወዳዳሪ ኢኮኖሚ የገነባች ሀገር ማየትን በእጅጉ እንሻለን። ሕልማችን ሁለንተናዊ ብልጽግና የተረጋገጠበትና አፍሪካዊት የብልጽግና ተምሳሌት ለመሆን የበቃች እና ዓለም አቀፋዊ የተጽዕኖ አድማሷ የሰፋ ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ነው። በጉባኤያችንም ሆነ በቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንሶቻችን ሕልማችን እውን ይሆን ዘንድ እያንዳንዳችን ለኢትዮጵያ ብልጽግና በላቀ ተነሣሽነትና ቁርጠኝነት መሥራት እንዳለብን ከልብ ተግባብተናል።
ለኢኮኖሚ ብልጽግና ግቦቻችን በጋራ በመቆም ኢኮኖሚያችን ነባር ዐቅሞችን የሚያጠናክር፣ ወደ አዳዲስ ዘርፎች የሚሸጋገርና ወደ መጪው ዘመን የፈጠራ ኢኮኖሚ የሚያስፈነጥር እንዲሆን በውጤታማነት ለመታገል ወስነናል። ዘላቂ የልማት ፋይናንስ ሥርዓት በመፍጠር፣ ሀገራችንን ከብድር ጫና የሚያላቅቅ ኢኮኖሚ ለመገንባት የሚያስችሉን አቅጣጫዎች አስቀምጠናል። ገቢ የመሰብሰብ ዐቅማችንን በማጎልበት የሕዝባችንን አዳጊ ፍላጎቶች ለመመለስ በቁርጠኝነት እንሰራለን። የአረንጓዴ ዐሻራ ፕሮግራማችን ወደ ቋሚ ሕዝባዊ ባህልነት እንዲሸጋገር የሕዝባችንን ተሳትፎ ከፊት ሆነን ለመምራት ጠንካራ አቋም ወስደናል።
በመሆኑም በሚቀጥሉት ሦስት ዓመታት የተቃና የኢኮኖሚ ማሕቀፍ በመገንባት ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ ቱሪዝም፣ ማዕድንና ዲጂታል ኢኮኖሚ ልማት ተደምሮ መዋቅራዊ የኢኮኖሚ ሽግግር በማምጣት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ ያስችል ዘንድ በመፍጠር፣ በመፍጠንና በማላቅ እንሠራለን !!!

4ኛ. ብልጽግና ማኅበረሰቡ ሁለንተናዊ ደኅንነቱና ክብሩ ተጠብቆለት ማኅበራዊ መስተጋብሩም ለሀገረ መንግሥት ግንባታ አስተዋጽዖ እንዲያበረክት ለማስቻል ሁለንተናዊ ብልጽግናን የሚያረጋግጥ አካታች ማኅበራዊ ልማት ዓላማን ይዞ በቁርጠኝነት እየሠራ ይገኛል። ይህንን ለማረጋገጥ ጥራት ያለው ትምህርት ለትውልድ ሁለንተናዊ ልህቀት ወሳኝ ግብአት መሆኑን ያምናል። በሽታን ቀድሞ መከላከልና አክሞ ማዳን ለጤናማና አምራች ትውልድ ግንባታ ያለዉን ፋይዳም በጥልቀት ይገነዘባል። በዚህ ምክንያት ባለፉት ጥቂት ዓመታት በፓርቲያችን ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አነሣሽነት “ትምህርት ለትውልድ” የሚል ፕሮግራም ተቀርጾ በ2016 እና በ2017 ዓ.ም ብቻ 39 ቢሊዮን ብር የሚገመት የሕዝብ ተሳትፎ ለትምህርት ዘርፍ ልማት አውሏል።

በፓርቲያችን የሚመራው መንግሥት አዲስ የትምህርት ፍኖተ ካርታ አዘጋጅቶ ወደ ሥራ ገብቷል። ይህንኑ ወደ ተጨባጭ ውጤት ለመቀየርም የትውልድ ዕሴት ግንባታ ሥራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል እና ትውልዱ መቻቻልን፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነትን፣ ወንድማማችነትን/እኅትማማችነትንና ዐርበኝነትን እየተማረ እንዲያድግ የሚያስችሉ ሥራዎችን ለመሥራት የሚረዳ ሀገራዊ የድርጊት መርሐ ግብር ቀርፀን የምንንቀሳቀስ ይሆናል።
በጤና ዘርፉም የጤና መድኅን ተጠቃሚዎችን የማበራከት፣ ሆስፒታሎችንና የጤና ጣቢያዎችን የማስፋፋት ሥራዎችን ጨምሮ አመርቂ የጥራትና የተደራሽነት የማሻሻያ ርምጃዎች መወሰዳቸውን ጉባኤያችን ተመልክቷል። በተጨማሪም ፓርቲያችን ሰው ተኮር ባህሪውን መሠረት በማድረግ የሕጻናትን እና የአረጋውያንን ሁለንተናዊ መብት እና ጥቅም የሚያስከብሩ፣ የአካል ጉዳተኞችን ሁለንተናዊ መብት፣ ክብርና ደኅንነት የሚያስጠብቁ፣ ዐቅመ ደካሞችን እና ለችግር ተጋላጭ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የሚደግፉ ሥራዎች በውጤታማነት መሠራታቸውን አረጋግጠናል። የወጣቶችና የሴቶች ክንፎቻችንንም ከመቼውም ጊዜ በላቀ ደረጃ በማጠናከር ወጣቶችና ሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነታቸው ከማረጋገጥ አኳያ ከፍተኛ መሻሻል መታየቱን አይተናል።
በመሆኑም እነዚህ የጀመርናቸው የማኅበራዊ ልማት ሥራዎቻችን የዕድገትና የፍትሐዊ ተጠቃሚነት ግቦቻችንን በሚያሳካና ማኅበራዊ ብልጽግናን በሚያረጋግጥ መልኩ በከፍተኛ ቁርጠኝነት አጠናክረን እናስቀጥላለን!!!

5ኛ. ኅብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲጠናከርና የሀገረ መንግሥት ግንባታችን እንዲሳካ ነጣጣይ ትርክቶች ተሸንፈው አስተሣሣሪ ትርክት የበላይነት ማግኘት እንዳለበት እኛ ብልጽግናዎች እናምናለን፡፡ በመሆኑም ብሔራዊነት ገዥ ትርክት ሆኖ በልሂቃን እና በሕዝቡ ዘንድ እንዲሠርጽና ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን እንዲጠናከር እንሠራለን፡፡ ይህንንም የበለጠ ለማሳካት በማኅበረሰባችን መካከል መግባባትን የሚፈጥሩ ልዩ ልዩ ሕዝባዊ ውይይቶች በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎችና በሁሉም አማራጭ መንገዶች እንዲከናወኑ እናደርጋለን፡፡ በተለያዩ ማኅበረሰቦች መካከል የሕዝብ ለሕዝብ ውይይቶችን በማድረግ የብሔራዊነት ገዥ ትርክት እንዲሠርጽና በሕዝቦች መካከል ትሥሥርና ኅብረ ብሔራዊ አንድነት እንዲፈጠር እንሠራለን፡፡
የሚዲያ ነጻነትና ሐሳብን በነጻ የመግለጽ መብት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ አፍራሽ ተልዕኮ ይዘው ሚዲያውን ለግጭት፣ ለብጥብጥና ለወንጀል በሚጠቀሙት አካላት ላይ ሕግ የማስከበር ሥራ እንዲሠራ፤ አበክረን እንታገላለን፡፡ የብልጽግና አመራሮችና አባላት መላውን ሕዝብ በማሳተፍ፣ ማኅበራዊ ሚዲያውን ለገዥ ትርክት ግንባታ፣ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ለዕውቀት ሽግግር እና የኢትዮጵያን እውነት ለመግለጥ እንደምንጠቀምበት ቃል እንገባለን፡፡

6ኛ. ብልጽግና የሀገራችን ሲቪል ሰርቪስ የዕድሜውን ያህል ተቋማዊ ልህቀት ማረጋገጥ አልቻለም ብሎ ያምናል። በመሆኑም አሁን ላይ የጅምላ ሀገራዊ የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርም እያደረገ አይደለም። ከዚያ ይልቅ በየደረጃው እየተተገበረ ውጤታማነቱ የተረጋገጠ፤ በዘመናዊ የቴክኖሎጂ ዐቅም መሪነት የተሣሠረ፤ ከሌብነት እና ከብልሹ አሠራር የተላቀቀ፤ ሲቪል ሰርቪስ መገንባት እንዳለበት ፓርቲያችን ያምናል። ለዚህም ተቋማዊ ባህሪን መሠረት ያደረገ፣ ገቢር ነበብ ሪፎርምን ለማሳካት በቁርጠኝነት እና በከፍተኛ ትኩረት እየሠራ ይገኛል።
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የተጀመረው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር በተለያየ መልክና ደረጃ የሚገለጹ ብልሹ አሠራሮች ሕዝባችንን ለእንግልትና ለእሮሮ እያጋለጡ መሆናቸውን ጉባኤያችን በዝርዝር ገምግሟል። በመሆኑም ዜጎች የሚተማመኑበት የፍትሕ ስርዓት ለመገንባት የተጀመረውን የፍትሕ ሥርዓት ሪፎርም ወደ ተጨባጭ ውጤት ለማሻገር ወስኗል። የሲቪል ሰርቪስ ሪፎርሙን በፍጥነት በመተግበርም የመንግሥትን የማስፈጸምና የአገልግሎት ዐቅም ለማሻሻል ጠንካራ ዐቋም ወስዷል።
ሌብነትንና ብልሹ አሠራርን ለመቆጣጠር በፓርቲያችን መሪነት በየደረጃውና በየዘርፉ ጠንካራ ትግል ከማካሄድ በተጨማሪ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ውጤታማ የአሠራር ሥርዓት እንዲዘረጋ አቅጣጫ አስቀምጧል። ስለሆነም ውጤታማ የሆነ ገቢር ነበብ ሪፎርም ለማካሄድ እና በተለይም የሕዝብ ቅሬታ ምንጭ የሆኑ አገልግሎት ሰጪ ዘርፎች ላይ በልዩ ጥናት የአገልግሎት ማስተካከያ ዘርፎች ለማድረግና የሕዝቡን ርካታ ለማሳደግ ፓርቲያችን የወሰደውን ጠንካራ አቋም ለማስፈጸም ሌት ተቀን ለመሥራት ቃል እንነባለን!!!

7ኛ. ጉባኤያችን ባለፉት ዓመታት ፓርቲያችን በተከተለው ሀገራዊ ክብርን የሚያጎናጽፍና ሀገራዊ አንድነትን የሚያጠናክር የዲፕሎማሲና የውጭ ግንኙነት አቅጣጫ ብሔራዊ ጥቅማችንና ክብራችንን ከፍ ያደርጉ ሥራዎች መፈጸማቸውን በድል ተመልክቶታል። ኢትዮጵያን የብሪክስ አባል ለማድረግ የተካሄደው እልህ አስጨራሽ ትግልና የተገኘው ውጤት የፓርቲያችንና የመሪያችንን ዘመን የዋጀ ብቃት ህያው ማሳያ ነው።

የዘመናት የትውልድ ጥያቄ የነበረውን ዘላቂ የባሕር በር አጀንዳ በዓለም ዐደባባይ ተገቢ ትኩረት እንዲሰጠው ከማድረግ በተጨማሪ ጥያቄዉ ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔ እንዲያገኝ እየተደረገ ያለውን ጥረትም በከፍተኛ አድናቆት ተመልክተነዋል። ፓርቲያችን የቀረፃቸው የዜጐች ክብር የውጪ ግንኙነት መርሕ በውጭ ሀገራት የሚኖሩ ዜጎቻችንን ደኅንነትና ክብር በማስጠበቅ ረገድ ያስገኘውን ጥቅምም በሚገባ ገምግመናል። ዲፕሎማሲያችን ከመሽኮርመም እየወጣ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና ፍላጎት መርሕንና እውነትን መሠረት ባደረገ ይገባኛል ባይነት መጠየቅና ማስፈጸም የሚያስችሉ ተጨማሪ አቅጣጫዎችን መርምረን ትክክለኛውን መንገድ ቀይሰናል።

በመሆኑም እነዚህ አቅጣጫዎች በብቃት እንዲፈጸሙና ዘላቂ የባሕር በር የማግኘት ፍላጎታችን ሰላማዊና ዲፕሎማሲያዊ ምላሽ እስኪያገኝ በሙሉ ዐቅማችን በተገኘው የዓለም መድረክ ሁሉ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ቆርጠን መነሣታችንን እናረጋግጣለን!!!

8ኛ. ፓርቲያችን ዘላቂና አዎንታዊ ሰላም የሀገራችን የህልውና መሠረትና የሁለንታናዊ ብልጽግናችን ዓይነተኛ ዋስትና መሆኑን በጥልቀት ይረዳል። በመሆኑም ብልጽግና ፓርቲ በዚህ ጉባኤው የተጀመረው አካታች ሀገራዊ ምክክር በስኬት ተጠናቆ የኢትዮጵያን የዘመናት የፖለቲካ ስንክሳር እንዲዘጋ፣ በልዩነትና በግጭቶች አያያዛችን ላይ ዘላቂ የመፍትሔ መንገዶች እንዲቀይስና ከተቻለም በጋራ ራእያችን ላይ እንዲያግባባን ሂደቱን በሙሉ ልብ ለመደገፍ ወስኗል። ለተጀመረው የሽግግር ፍትሕ ፕሮግራም ተግባራዊነትና ስኬታማነት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣትም ይሰራል። አዎንታዊ ዘላቂ ሰላማችንን እያስተጓጐሉ ከሚገኙ የታጠቁ ኃይሎች ጋር የሚደረገው ውይይትና ድርድር ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ተጨማሪ አቅጣጫዎች አስቀምጧል።

ግጭትን ለማስቀረትና መረጋጋትን ለመፍጠር ሁሉም አመራርና አባል በትኩረት ሊሠራ እንደሚባ ተስማምተናል። ስለሆነም ለጉባዔያችን ውሳኔዎችና አቅጣጫዎች ተግባራዊነት ተግተን በመሥራት የሀገራችንን ሰላም ለማረጋገጥና ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን አጠናክረን ለማስቀጠል ሁላችንም በአንድነትና በጽናት እንቆማለን!!!
በመቀጠልም እኛ የብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ ጉባኤ ተሳታፊዎች ከዚህ የጋራ መሥዋዕትነታችንና ድላችን ዘለዓለማዊ ዓርማ ከሆነው የዐድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ለመላ ኢትዮጵያውያንና ለሁሉም ባለድርሻ አካላት የምናስተላልፈው መልዕክትና አደራ አለን።
የተከበራችሁ መላው የኢትዮጵያ ሕዝቦች!

ፓርቲያችሁ ብልፅግና በመጀመሪያ ጉባዔው ዋዜማ ላይ በተካሄደው ፍጹም ሰላማዊ፣ ነጻ፣ ፍትሐዊና ዴሞክራሲያዊ ሀገራዊና ክልላዊ ምርጫ የሌሊት ቁር፣ የቀን ሐሩር ሳይበግራችሁ፣ በአስደማሚ ጽናት፤ በእልህና በቁጭት ተሰልፋችሁ የጣላችሁበት ኃላፊነት አድልም አደራም እንደሆነ ከልብ ያምናል። ፓርቲያችን በምርጫ የጣላችሁበትን ኃላፊነትና የሰጣችሁትን እምነት የሚያከብረው ሁለንተናዊ ብልጽግናን ለማረጋገጥና የኢትዮጵያን ሕልም እውን ለማድረግ በሚረዱ ሥራዎች ላይ በመረባረብ፣ ድህነት፣ ተረጂነትና ውርደትን ድል በመንሣት፣ የዜጎችን ሕይወት በዘላቂነት በመቀየርና ጠንካራ ተቋማትንና ሥርዓትን በመገንባት እንደሆነ በአንክሮ ይገነዘባል።

በዚህ ረገድ ባሳለፍናቸው ጥቂት ዓመታት ዓለምን የሚያስደምም ዕድገትና መነቃቃት የፈጠርነውና ሀገራችንን በአፍሪካ 5ኛ፣ ከሰሐራ በታች ካሉ ሀገራት 3ኛ፣ ከምሥራቅ አፍሪካ ደግሞ 1ኛ ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላት ሀገር እንድትሆን ማድረግ የቻልነው ሀገር በቀል እና የብዝኃ ዘርፍ የኢኮኖሚ ልማት አቅጣጫ ተከትለን ነው። ቀድሞም ቢሆን በጀግንነት ሀገራዊ ክብራችንን ተጎናጽፈን ስናበቃ ዓለም በተመጽዋችነት የመዘገበን በራሳችን ስሕተት ነው።
ዛሬ ግን ፓርቲያችን ለልጆቻችን ምንዳን እንጂ ዕዳን አላወርስም በሚል አቋም ቆርጦ ተነሥቷል። ስለሆነም በራሳችን ጥረት በዐውደ ውጊያ ወደ ተጎናጸፍነው የክብር ማማ ተመልሰን መውጣት አለብን። ድህነት ያመጣብንን ሀገራዊ ውርደት መስበርና ዳግም ገናና መሆን የምንችለው በእልህ፣ በቁጭትና በአዲስ ብሔራዊ የዐርበኝነት ስሜት የራሳችንን ታሪክ ለመሥራት ከታገልንና ለድል ከበቃን ብቻ ነው። በጥቅሉ ኢትዮጵያ እንድታንሠራራ የማድረግ ትልቁ ሸክም የሚወድቀው በእኛ ኢትዮጵያውያን ትከሻ ላይ ነው። ታዲያ ይህ ራእይ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝቦች ይሁንታ፣ ሙሉ ትብብርና ጠንካራ ተሳትፎ ውጪ ለስኬት ሊበቃ አይችልም።

ፓርቲያችን ባለፉት ዓመታት የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና ለማረጋገጥ የወሰደውን ተልዕኮ ለማሳካት የሚመራበትን የመደመር ዕሳቤ መሠረት በማድረግ ያዘጋጃቸው እና የውስጠ ፓርቲ ዐቅሙን ለማጎልበት የተጠቀመባቸውን ያደጉና አሻጋሪ ሐሳቦቹን ከፓርቲ አጥር እያወጣ የሕዝቡን ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት ማዕከል ባደረገ መልኩ ለሕዝቡ እንዲደርስ ከፍተኛ ጥረት ያደርገው ለዚህ ነው። ከጉባኤ እስከ ጉባኤ ያስመዘገብናቸው ሁሉም ድሎች የተገኙትም ሕዝቡ በፓርቲያችን ላይ ባሳደረው እምነት፣ በሰጠው ድጋፍና ባደረገው ተሳትፎ ልክ ነው። እስከ ቀጣዩ ጉባኤው ድረስም ሕዝቡን በሁሉም ሀገራዊና ከባቢያዊ አጀንዳዎች ዙሪያ በንቃትና በስፋት ለማሳተፍ በልዩ ትኩረት እንደሚሠራ ሲያረጋግጥላችሁ በላቀ ኩራትና ቁርጠኝነት ነው።
እኛ ብልጽግናዎችና መላው ኢትዮጵያውያን የጀመርነው ለውጥ የሀገራችንን የቆዩ ውስብስብ ችግሮች ከመሠረቱ የሚፈታና ስብራቶችን የሚጠግን ነው። በመሆኑም በለውጡ ሂደት እዚም እዚያም ያጋጠሙ ችግሮችና ጉዳቶች እያመመንም ቢሆን ለውጥ የሚያልፍበትን ተፈጥሯዊ ባሕሪ በመረዳትና መጭውን ብሩህ ዘመን በመሻት ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን። ይህን የትግል ጉዞ የሚፈትኑ አንድም ከነባሩ የፖለቲካ ባህል የሚመነጬ ፈተናዎች፣ ሁለትም አዲሱ ዘመን በራሱ የሚፈጥራቸው አዳዲስ ፈተናዎች መኖራቸውን ተገንዘበንና ፈተናን ወደ ዕድል የመቀየር ልምዳችንን ተጠቀምን ሁል ጊዜም ወደ ፊት እንራመዳለን።

የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ብልጽግና እውን ለማድረግ የጀመርነው ትግል ግቡን ይመታ ዘንድም ትናንትን፣ ዛሬንና ነገን አስተሣሥረን በመመልከት፣ የወል ትርክታችንን በመገንባትና ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ጠብቀን በፍጹም የዐርበኝነት መንፈስና ወኔ እንዘልቃለን። በሂደቱም ጠንካራ ፓርቲና መንግሥት በመገንባት የወል ሕልማችን ዳር እንዲደርስ የድርሻችንን በማበርከት የሀገራችንን ቅቡልነትና ከፍታ ከግብ እናደርሳለን። ይህን የተቀደሰ ዓላማችንን በመደገፍ ከፓርቲያችንና ከመንግሥታችን ጎን ለቆማችሁት በሙሉ ያለንን ልባዊ አክብሮት እየገለጽን በቀጣይም አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር ታደርጉልን ዘንድ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን። እኛም ክቡር ቃላችንን ወደ ባህል በማሸጋገር ኢትዮጵያን ማጽናት ብቻ ሳይሆን ወደ ብልጽግና ማማ ማድረሳችን አይቀሬ መሆኑ እሙን ነው!!!
በቀጣዩ ጉባኤያችን ስንገናኝ ከተሰጠን በላይ ሠርተን፤ ከሚጠበቅብን በላይ ፈጽመን፤ ኢትዮጵያን ይበልጥ ወደ ሁለንተናዊ ብልጽግና አሸጋግረን እንደሚሆን እምነታችን ጽኑ ነው፡፡ ከጉባኤያችን ያየነው ተስፋ ይሄንኑ በጽኑ ያረጋገጠ ነው፡፡

ጥር 25 ቀን 2017 ዓ.ም

አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ
እናመሰግናለን!

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዕለቱ የምንዛሪ ዋጋ፡
03/02/2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የዕለቱ የምንዛሪ ዋጋ፡

የአሜሪካ ማስጠንቀቂያ ለፓናማአሜሪካ በፓናማ ቦይ የቻይናን ተጽዕኖ ከመቀነሰ እና  ከዋሽንግተን ከሚመጣባት አጸፋ   ፓናማ ትምረጥ አለች፡፡የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የፓናማ...
03/02/2025

የአሜሪካ ማስጠንቀቂያ ለፓናማ

አሜሪካ በፓናማ ቦይ የቻይናን ተጽዕኖ ከመቀነሰ እና ከዋሽንግተን ከሚመጣባት አጸፋ ፓናማ ትምረጥ አለች፡፡

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የፓናማውን ፕሬዚዳንት ሁሴ ራውል ሙሊኖን ቤይጂንግ በቦዩ ያላትን ተጽዕኖ ፈጣሪነት በማስቆም አስቸኳይ እርምጃ እንዲወስዱ አስጠንቅቀዋል፡፡

ፓናማ ቦይን ቻይና መቆጣጠር የለባትም የሚል ሀሳባቸውን ማርክ ሩቢዮ ከፓናውም ፕሬዚዳንት ጋር በአካል በተገናኙበት ሰዓት አስገንዝበዋል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን ከመጡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው የውጭ ጉዞ ያደረጉት፡፡

የፓናማው ፕሬዚዳንት ሙሊኖ ከቻይና ጋር ያለውን ግንኙነት እንደሚያጤኑትም አሳውቀዋል፡፡

ያም ሆኖ ግን በዓለም ላይ ሁለተኛውን ግዙፍ የውሃ መስመር ፓናማ ለድርድር እንደማታቀርበው ይፋ አድርገዋል ፕሬዚዳንቱ፡፡

በሆንግ ኮንግ መቀመጫውን ያደረገ ኩባንያ በሁለት ወደቦች ስራ ላይ ነው ፡ለዛውም በፓናማ ቦይ መግቢያ ላይ የሚል ቅሬታ አሜሪካ አለባት፡፡

ይህ ደግሞ የአሜሪካንና የፓናማን ስምምነት የሚጥስ ነው የሚል መልዕክት የውጭ ጉዳዩ ሚኒስትሩ ከትራምፕ ተቀብለው ለፓናማ አድርሰዋል።

ማርኮ ሩቢዮ ፓናማ ምን ዓይነት እርምጃ መውሰድ እንዳለባት እና የአሜሪካ አጸፋ ምን ሊሆን እንደሚችል በግልጽ ያሉት ነገር የለም፡፡

ዘገባው የአልጀዚራ ነው

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ ዶክተር አንዱዓለም ዳኘ ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየሠራ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምና ...
03/02/2025

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ ዶክተር አንዱዓለም ዳኘ ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየሠራ መሆኑን አስታውቋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽት እና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊቲ ሃኪም፣ ተመራማሪ፣ መምህር እና በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር የነበሩት ዶክተር አንዱዓለም ዳኘ ባልታወቁ ኃይሎች መገደላቸው ተገልጿል፡፡

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር ዋለልኝ ቢምረው ጥር 24/2017 ዓ.ም ምሽት 1፡30 ሰዓት ገደማ ዶክተር አንዱዓለም ዳኘ ሥራ ቆይተው ጥበብ ግዮን ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው እየሄዱ ባለበት ወቅት በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ እስካሁን በውል ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል፡፡

ሁለት ተሽከርካሪዎች ተከታትለው እየሄዱ ባለበት ወቅት አንደኛው ተሽከርካሪ ሲያመልጥ ዶክተር አንዱዓለም በነበሩበት ተሽከርካሪ ላይ በተደጋጋሚ ጥይት በመተኮስ የግድያ ወንጀል መፈጸሙን ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ ድርጊቱ እንደተፈጸመ በደረሰው ጥቆማ መሠረት ወደ ቦታ በመሄድ የማጣራት ሥራ እየሠራ መሆኑን ነው የተናገሩት፡፡ በሥፍራው የተገኙ የቴክኒክ ማስረጃዎችን የማንሳት እና ሌሎች ሥራዎች መሠራቱን ገልጸዋል፡፡

ዶክተር አንዱዓለም እያሽከረከሩ በነበረበት ወቅት በተተኮሰ ጥይት መገዳላቸውንም አንስተዋል፡፡ ፖሊስ አጥፊዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ጥረት እያደረገ መሆኑንም አስታውቋል፡፡

በዶክተር አንዱዓለም ላይ በደረሰው የግድያ ወንጀል የጸጥታ ተቋሙ አዝኗል ነው ያሉት፡፡ ለሀገር እና ለሕዝብ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያደርጉትን ዶክተር ማጣት ጉዳቱ ከፍተኛ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሞት የአንድ ሰው ብቻ አይደለም ያሉት ኀላፊው ሞቱ ሀገርን እና ሕዝብን የሚጎዳ ነው ብለዋል፡፡

ፖሊስ ግድያውን የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል በሚያደርገው ጥረት ማኅበረሰቡ ተባባሪ እንዲሆንም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ዘገባው የአሚኮ ነው።

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሃሳብ ሲካሄድ የቆየው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ ባለስምንት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡ጉባዔው ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) በፕሬዚዳ...
03/02/2025

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ሃሳብ ሲካሄድ የቆየው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባዔ ባለስምንት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡

ጉባዔው ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) በፕሬዚዳንትነት እንዲሁም አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና አቶ አደም ፋራህን በምክትል ፕሬዚዳንትነት እንዲያገለግሉ በድጋሚ መርጧል፡፡

እንዲሁም ጉባዔው ባለስምንት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል፡፡

በቀጣይ ዓመታት ለዘመኑ የተቀረጹ ተልዕኮዎች ብቻ ሳይሆን በሀገር ውስጥ ግጭቶች እና ዓለም አቀፋዊ ተለዋዋጭ ሁኔታዎች ሳቢያ ያመለጡ ዕድሎችን በሚያካክስ መልኩ ማከናወን የሚያስችሉ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ መግባባት ላይ መድረሳቸውን የጉባኤው ተሳታፊዎች ባወጡት የአቋም መግለጫ አስታውቀዋል።

የጉባኤው ተሳታፊዎች ባወጡት የአቋም መግለጫ፣ ባለፉት 3 ዓመታት የጠንካራ ፓርቲ ግንባታ ግብ ለማሳካት የተፈጸሙ ስራዎች ፓርቲውን ከእድሜው የቀደመ የውጤትና የዕድገት ምዕራፍ ውስጥ እንዲገኝ ማድረጉንም ገልጸዋል።

ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በትብብር እና በፉክክር መካከል ሚዛን በመጠበቅ የኢትዮጵያን የፓለቲካ ባህል ለመቀየር የታየው ቁርጠኝነት ለሌሎች ሀገራት ተሞክሮ መሆን የቻለ መሆኑም ተመላክቷል።

ጠንካራ፣ ጤነኛና ውጤታማ ፓርቲ የመገንባት አጀንዳ ቋሚ ትግል የሚጠይቅ በመሆኑ የውስጥ ፓርቲ ዴሞክራሲን በማጎልበትና የአሰራር ስርዓትን በማዘመን እንዲሁም የኢንስፔክሽን እና የስነምግባር ኮሚሽንን በማጠናከር ጉድለቶችና ብልሽቶችን የማረም አቅም ያለው ጠንካራ ፓርቲ ለመገንባት ተወስኗል።

የተጀመረውን የተቋማት ሪፎርም ስራን አጠናክሮ ለማስቀጠል እና ገለልተኛና ብቃት ያላቸው ተቋማትን በማብዛት ሀገረመንግስት ግንባታን ጠንካራ መሰረት ላይ ለመጣል እንደሚሰራም በአቋም መግለጫው ተነስቷል።

"የካናዳን ግዙ "ትሩዶየካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ አሜሪካ በአገራቸው ላይ ታሪፍ መጣሏን ተከትሎ ማሳሰቢያ ሰጡ፡፡ተጠቃሚዎች የካናዳን ምርት ቅድሚያ ሰተው እንዲሸምቱ ያስገነዘቡበት...
03/02/2025

"የካናዳን ግዙ "ትሩዶ

የካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ አሜሪካ በአገራቸው ላይ ታሪፍ መጣሏን ተከትሎ ማሳሰቢያ ሰጡ፡፡

ተጠቃሚዎች የካናዳን ምርት ቅድሚያ ሰተው እንዲሸምቱ ያስገነዘቡበት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የትራምፕ ውሳኔ ለዓለም ስጋት ነው ብለዋል።

በካናዳ የተመረቱ ምርቶችን ቦታ ሰቶ ለመምረጥ ጊዜው አሁን ነው በሚል ሀሳባቸውን አጠናክረዋል፡፡

የትም ሆነን የካናዳን እንምረጥ የሚሉት ጀስቲን ትሩዶ ብሄራዊ አንድነት እናጠናክር የሚል ጥሪም አቅርበዋል፡፡

75 በመቶ የሚሆነው የካናዳ የወጪ ምርት ቀጥታ ወደ አሜሪካ ደንበኞች ነበር ሚላከው፡፡

ከአምስት እስከ ስድስት ወር ባለው ጊዜ ታሪፉ ካልተንሳ ጫናው የዋዛ አይሆንም፡፡
ቢቢሲ እንደዘገበው፡

ተጠባቂ የነበረው የአርሰናልና ማንችስተር ሲቲ የድህረ ጨዋታ ዳሰሳበእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተጠባቂው የአርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ  ጨዋታ በአርሰናል 5-1 አሸና...
02/02/2025

ተጠባቂ የነበረው የአርሰናልና ማንችስተር ሲቲ የድህረ ጨዋታ ዳሰሳ

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የ24ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ተጠባቂው የአርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ ጨዋታ በአርሰናል 5-1 አሸናፊነት ተጠናቀቀ።

በኳስ ቁጥጥር መጠነኛ ብልጫ ተወስዶበት ላመሸው ባለሜዳው ቡድን አምበሉ ማርቲን ኦዲጋርድ በመጀመሪያ አጋማሽ ቶማስ ፓርቴ፣ማይለስ ሌዊስ- ስኪል፣ካይ ሃቨርትዝ እንዲሁም ኢታን ንዋኔሪ ደግሞ በሁለተኛው አጋማሽ አስቆጥረዋል።

ከመጨረሻ አምስት ግጥሚያዎች አራቱን በድል እንደመደምደሙ በጥሩ መነቃቃት ላይ ሆኖ ወደ ለንደን ለተጓዘው ማንችስተር ሲቲ አጥቂው አርሊንግ ብራውት ሀላንድ በ55ኛው ደቂቃ በግንባሩ ከመረብ አሳርፏል።

በጨዋታው በተለይም 3ኛዋ ጎል ከተቆጠረችበት በኋላ ከፍተኛ መፋዘዝ ውስጥ የገባው ማንችስተር ሲቲ አራት ኢላማቸውን የጠበቁ ሙከራዎችን ሲያደርግ አርሰናል በአንጻሩ ሰባት ሞክሮ አምስቱን ወደ ግብነት ቀይሯል።

አርሰናል የመጀመሪያውን ጎል በአምበሉ ማርቲን ኦዲጋርድ አማካኝነት ለማስቆጠር የ103 ሴኮንዶች ዕድሜ ብቻ ፈጅቶበታል።

ድሉን ተከትሎ አርሰናል በሊጉ ያለመረታት ጉዞውን ወደ 14 አሳድጓል።

በዘጠኙ ሲያሸንፍ በአምስቱ ነጥብ ተጋርቶ ተለያይቷል።

መድፉ በአርቴታ ስር ከዚህ ቀደም በዚህ ልክ ረዥም ያለመረታት ጉዞ ያደረገበት አሃዝ አልነበረውም።

ለመጨረሻ ጊዜ ከዚህ አሃዝ ተመሳሳይ 14 ያለመሽነፍ ጉዞ ያደረገው በ2018 በኡናይ ኤምሪ እየተመራ ነበር።

የሰሜን ለንደኑ ሀያል አንድ ተስተካካይ ጨዋታ እየቀረው ሊጉን በ56 ነጥብ ከሚመራው ሊቨርፑል ጋር ያለውን ልዩነት በስድስት አጥብቧል።

ማንችስተር ሲቲ በአንጻሩ ከመርሲሳይዱ ክለብ ጋር ልዩነቱ በ15 ሰፍቶበታል።

በ26ኛው ደቂቃ ዴክላን ራይስ ከኮቫችች ነጥቆ ለኦዲጋርድ ያሻገረለትን ኳስ ካይ ሃቨርትዝ ተቀብሎ ያልተጠቀመበት አጋጣሚ የሚያስቆጭ ነበር።

በሁለተኛው አጋማሽ የመጀመሪያ 10 ደቂቃዎች ፍጹም የበላይነት የነበረው ሲቲ በ55ኛ ደቂቃ በሀላንድ አማካኝነት ወደ አቻነት ቢመለስም አርሰናል በ105 ሴኮንዶች ልዩነት በቶማስ ፓርቴ ምላሽ ሰጥቷል።

በመጨረሻ ስድስት ጨዋታዎች ስድስት ጎሎችን ማስቆጠር የቻለው ኖርዌያዊው አጥቂ በማንችስተር ሲቲ ማልያ በሁሉም ውድድሮች 250ኛ ጎሉን ነው ዛሬ ያስቆጠረው።

ዴቪድ ራያ መረብ ላይ ማሳረፍ የቻለው ዘጠነኛ የኳስ ንክኪውን ሲሆን ጎሏ የማንችስተር ሲቲ የመጨረሻ ሙከራም ሆናለች።

በ18 ዓመት ከ129 ቀን ዕድሜው የመጀመሪያ የሊግ ጎሉን ያስቆጠረው ማይልስ ሌዊስ -ስኪሊ ለአርሰናል አራተኛው በዕድሜ ትንሹ አስቆጣሪ ተብሏል።

አራተኛዋን ጎል ያስቆጠረው ካይ ሃቨርትዝ በያዝነው የውድድር ዓመት በሊጉ 9ኛ በሁሉም ውድድሮች ደግሞ 15ኛ ጎሉ ሆኖ ተመዝግቦለታል።

አሃዙ በ2019 -20 ባየር ሌቨርኩሰን ቤት እያለ ካስቆጠረው 18 ጎል በኋላ ትልቁ አሃዝ ሆኖ ተመዝግቧል።

ተቀይሮ የገባው ኢታን ንዋኔሪ ከሳጥን ውጭ በአስገራሚ ብቃት የመታው ምት የጨዋታውን የማሳረጊያ ጎል አስገኝቷል።

ንዋኔሪ በሳምንቱ አጋማሽ ጅሮና ላይ ከዚህ በተቀራራቢ መንገድ ማስቆጠሩ ይታወሳል።

በ-ይበልጣል ሰውነት

ፕሬዝዳንት ታዬ ለብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ለብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ና ምክ...
02/02/2025

ፕሬዝዳንት ታዬ ለብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንቶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላለፉ

ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ለብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ና ምክትል ፕሬዝዳንቶች አቶ ተመስገን ጥሩነህ እና አቶ አደም ፋራህ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ታዬ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

አርሰናል ማንችስተር ሲቲን በሰፊ ጎል ልዩነት አሸነፈበ24ኛ ሳምንት ተጠባቂ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ  የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ተቀናቃኙን ማንችስተር ሲቲን 5ለ1 አሸንፏል።የአር...
02/02/2025

አርሰናል ማንችስተር ሲቲን በሰፊ ጎል ልዩነት አሸነፈ

በ24ኛ ሳምንት ተጠባቂ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ተቀናቃኙን ማንችስተር ሲቲን 5ለ1 አሸንፏል።

የአርሰናልን ጎሎች ማርቲን ኦዲጋርድ፣ ካይ ሀቨርትዝ፣ቶማስ ፓርቴ፣ልዊስ ስኬሊ እና ኢታን ኑዋኔሪ ሲያስቆጠሩ ለማንችስተር ሲቲ ኤርሊንግ ሀላንድ ብቸኛዋን ጎል ማሰቆጠር ችሏል

የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ እየተከናወነ ነውየብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ በግልፅ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀ...
02/02/2025

የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ እየተከናወነ ነው

የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ በግልፅ፣ አሳታፊና ዴሞክራሲያዊ መንገድ እየተከናወነ መሆኑን የፓርቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ገለጹ።

ብልፅግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን ከጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በማካሄድ ላይ ነው::

የጉባኤውን ሶስተኛ ቀን ውሎ በተመለከተ ለመገናኛ ብዙሃን ማብራሪያ የሰጡት የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዘርፍ ኃላፊ ቢቂላ ሁሪሳ (ዶ/ር) ከማለዳው ጀምሮ የአመራር ምርጫ ሲካሄድ መዋሉን ገልጸዋል።

በዚህም በጠዋቱ ክፍለ ጊዜ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)ን በከፍተኛ የድምፅ ብልጫ ለፓርቲው ፕሬዝዳንት መምረጡን ተናግረዋል።

አቶ አደም ፋራህና አቶ ተመስገን ጥሩነህ ደግሞ የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንቶች ሆነው በከፍተኛ ድምፅ መመረጣቸውን አንስተዋል።

ፕሬዝዳንቱና ምክትል ፕሬዝዳንቶቹ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ቃለ መሃላ መፈጸማቸውንም ነው ያነሱት።

ጉባኤው በከሰዓት ክፍለ ጊዜው የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ በማካሄድ ላይ ነው ብለዋል።

በአዲሱ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት ቀድሞ የማዕከላዊ ኮሚቴ የሚለው አወቃቀር አሁን የብልጽግና ምክር ቤት በሚል መተካቱን ተናግረዋል።

በአዲሱ መተዳደሪያ ደንብ መሰረት የብልፅግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ ቀርቶ የብልፅግና ፓርቲ ምክር ቤት አባላት ምርጫ እየተካሄደ ይገኛል ብለዋል።

በምርጫው በርካታ ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የተወከሉ ተሳታፊዎች ነጻ፣ ገለልተኛና ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እጩዎችን ጠቁመው ድምጻቸውን እየሰጡ እንደሚገኙም አንስተዋል።

ከጥቂት ሰዓታት በኋላ የምክር ቤት አባላት መርጫው ውጤት ለህዝብ ይፋ እንደሚሆን አንስተው፥ በመቀጠል የፓርቲው ኢንስፔክሽንና የስነምግባር ኮሚሽን እንዲሁም የስራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ምርጫ እንደሚከናወን አንስተዋል።

የድምፅ አሰጣጡ ለመጀመሪያ ጊዜ በቀጥታ በቴክኖሎጂ በተደገፈ መንገድ ድምጽን ለመስጠት በሚያስችል መልኩ እየተካሄደ ነው ብለዋል።

ጉባኤው የብልጽግና የሀሳብ ልዕልና የተገለጸበት እና የውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲ እየጎለበተ መምጣቱ የታየበት ነው ብለዋል።

እስከሚቀጥለው ጉባኤ የሚተገበሩ ውሳኔዎች እና አቅጣጫዎች ይፋ እንደሚደረጉም ገልጸዋል ዘገባው የኢዜአ ነው።

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላለፉየደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ...
02/02/2025

ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ለጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላለፉ

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ሆነው በመመረጣቸው የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ሦስተኛ ቀኑን የያዘው የብልጽግና ፓርቲ ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ዐቢይ አሕመድን (ዶ/ር) ከፍተኛ በሆነ ድምጽ የፓርቲው ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል።

ይህንን ተከትሎም የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል።

ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዲሞክራሲያዊ በሆነ ሂደት ተመርጠው የብልፅግና ፓርቲው ፕሬዚዳንት በመሆን ህዝቡን ዳግም ለማገልገል ዕድል ማግኘታቸውን በመጠቆም መልካም የስራ ዘመን እንዲሆንላቸውም ተመኝተዋል።

ኢትዮጵያ በሁለተኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውደድር ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀችኢትዮጵያ በሁለተኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርአንና አዛን ውደድር በወንዶች አዛን እና በሴቶች የቁ...
02/02/2025

ኢትዮጵያ በሁለተኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርአንና የአዛን ውደድር ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች

ኢትዮጵያ በሁለተኛው ዙር ዓለም አቀፍ የቁርአንና አዛን ውደድር በወንዶች አዛን እና በሴቶች የቁርአን ሂፍዝ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቀቀች።

ኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ያስተናገደችው የ2017 ዓለም አቀፍ የቁርአንና አዛን ውድድር ማጣሪያ ባለፉት ቀናት ዓለም አቀፍ የቁርአን ዳኞች በተገኙበት ሲካሔድ ቆይቷል።

በዛሬው ዕለት ደግሞ አሸናፊዎች የተለዩበት የማጠቃለያ ውድድር እና የሽልማት ስነ-ስርዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ተከናውኗል፡፡

በመርኃ ግብሩ ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋን ጨምሮ፣ ዓለም አቀፍ ዳኞች፣ ከሀገራት የመጡ ተወዳዳሪዎች፣ ዲፕሎማቶችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በፍጻሜው ኢትዮጵያ በሴቶች የቁርአን ሂፍዝ ዘርፍ በቀመሪያ ወልዩ ሙሀመድ አማካኝነት ሶስተኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች።

እንዲሁም በወንዶች አዛን ደግሞ በአደም ጅብሪል አማካኝነት ሶስተኛ ደረጃን ይዛ ጨርሳለች።

በውድድሩ በወንዶች በቁርአን ሂፍዝ ሊቢያ አንደኛ፤ በወንዶች አዛን ኢንዶኔዢያ አንደኛ፤ በቁርአን ሂፍዝ ሴቶች የመን አንደኛ እንዲሁም በወንዶች ቁርአን ቲላዋ (ድምጽ ማውጣት) ግብጽ የአንደኝነት ደረጃን ይዘው ጨርሰዋል።

ለአሸናፊዎቹ የተለያዩ ሽልማቶች ተበርክቶላቸዋል።

በሽልማት ስነ ስርዓቱ የተገኙት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ፤ ለፕሮግራሙ መሳካት አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ውድድሩ በስኬት የተካሄደው በሀገራችን ሰላም በመኖሩ ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ፥ ለዓለም ዘላቂ ሰላም ሁሉም ዘብ ሊቆም ይገባል ብለዋል።

በውድድሩ የተሳተፉ የውጭ ሀገራት ዜጎች የመስህብ ስፍራዎችን የጎበኙ ሲሆን ኢትዮጵያ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ ሃብቶች ባለቤት መሆኗን መመልከታቸውን ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የበላይ ጠባቂነትና በዘይድ ኢብን ሳቢት የቁርዓን ማኅበር አማካኝነት በተዘጋጀው ዓለም አቀፍ የቁርአንና አዛን ውድድር ላይ 60 ሀገራት ተሳትፈዋል ዘገባው የኢዜአ ነው።

የግድያ ወንጀል የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየሠራ መኾኑን  ፖሊስ አስታወቀ፡፡  ዶክተር አንዱዓለም ዳኘ ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየሠራ መኾኑ...
02/02/2025

የግድያ ወንጀል የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየሠራ መኾኑን ፖሊስ አስታወቀ፡፡

ዶክተር አንዱዓለም ዳኘ ላይ የግድያ ወንጀል የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል እየሠራ መኾኑን የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡

በባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ሕክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጠቅላላ ቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት እና የጉበት፣ የቆሽት እና የሃሞት መስመር ሰብ ስፔሻሊቲ ሃኪም፣ ተመራማሪ፣ መምህር እና በጥበበ ግዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የቀዶ ሕክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር የነበሩት ዶክተር አንዱዓለም ዳኘ ባልታወቁ ኃይሎች መገደላቸው ተገልጿል፡፡

የባሕር ዳር ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ ኀላፊ ኮማንደር ዋለልኝ ቢምረው ጥር 24/2017 ዓ.ም ምሽት 1፡30 ሰዓት ገደማ ዶክተር አንዱዓለም ዳኘ ሥራ ቆይተው ጥበብ ግዮን ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው እየሄዱ ባለበት ወቅት በተለምዶ ቆሼ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ እስካሁን በውል ባልታወቁ ሰዎች መገደላቸውን ተናግረዋል፡፡

ሁለት ተሽከርካሪዎች ተከታትለው እየሄዱ ባለበት ወቅት አንደኛው ተሽከርካሪ ሲያመልጥ ዶክተር አንዱዓለም በነበሩበት ተሽከርካሪ ላይ በተደጋጋሚ ጥይት በመተኮስ የግድያ ወንጀል መፈጸሙን ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ ድርጊቱ እንደተፈጸመ በደረሰው ጥቆማ መሠረት ወደ ቦታ በመሄድ የማጣራት ሥራ እየሠራ መኾኑን ነው የተናገሩት፡፡ በሥፍራው የተገኙ የቴክኒክ ማስረጃዎችን የማንሳት እና ሌሎች ሥራዎች መሠራቱን ገልጸዋል፡፡

ፖሊስ ድርጊቱን ማን ፈጸመው እንዴት ተፈጸመ የሚለውን ለመለየት ሥራ ላይ መኾኑን ነው ያመላከቱት፡፡ ዶክተር አንዱዓለም እያሽከረከሩ በነበረበት ወቅት በተተኮሰ ጥይት መገዳላቸውንም አንስተዋል፡፡ ፖሊስ አጥፊዎችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ጥረት እያደረገ መኾኑንም አስታውቋል፡፡

በዶክተር አንዱዓለም ላይ በደረሰው የግድያ ወንጀል የጸጥታ ተቋሙ አዝኗል ነው ያሉት፡፡ ለሀገር እና ለሕዝብ ትልቅ አስተዋጽኦ የሚያደርጉትን ዶክተር ማጣት ጉዳቱ ከፍተኛ መኾኑንም ገልጸዋል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሞት የአንድ ሰው ብቻ አይደለም ያሉት ኀላፊው ሞቱ ሀገርን እና ሕዝብን የሚጎዳ ነው ብለዋል፡፡

ማኅበረሰቡ ከጸጥታ ኀይሉ ጋር በትብብር በመሥራት በዚህ ግድያ ወንጀል የተሳተፈ አካል ለሕግ መቅረብ እና አስፈላጊው እርምት መወሰድ አለበት ነው ያሉት፡፡ ፖሊስ ድርጊቱ ከተፈጸመበት ጊዜ ጀምሮ ትልቅ ሥራ እየሠራ መኾኑንም ነው የገለጹት፡፡

በከተማዋ ከማኅበረሰቡ ጋር በተሠራው ሥራ የእገታ፣ የፍንዳታ እና ሌሎች ወንጀሎችን ማስቆም ተችሎ እንደነበር የተናገሩት ኀላፊው አሁን አሁን ደግሞ በከተማዋ ዳርቻ አካባቢ የእገታ ወንጀሎች መከሰት ጀምረዋል ነው ያሉት፡፡

ከአሁን ቀደም እንደተሠራው ሁሉ ከማኅበረሰቡ ጋር በጋራ በመሥራት ድርጊቱን ማስቆም ይገባል ብለዋል፡፡ በትብብር ማስቆም ካልተቻለ ይህ ዓይነት ድርጊት ከሁሉም ቤት በየተራ ይገባል ያሉት ኀላፊው ማኅበረሰቡ ከፖሊስ ጋር በመሥራት፣ መረጃዎችን በመሥጠት፣ ወንጀለኞችን በማጋለጥ እና ፊት ለፊት በመጋፈጥ ማገዝ አለበት ነው ያሉት፡፡ ያለ ኅብረተሰብ ተሳትፎ ወንጀልን መከላከል እንደማይቻልም አመላክተዋል፡፡

ማኅበረሰቡ ሌባን እና አጋችን እየያዘ እያመጣ መኾኑንም ተናግረዋል፡፡ ዶክተሩ ከጥበበ ግዮን ወደ ከተማ እየሄዱ ባለበት ወቅት ተገደሉ እየተባለ የሚነገረው ወሬ ሀሰተኛ መኾኑንም ተናግረዋል፡፡ ዶክተሩ የተገደሉት ሥራ ቆይተው ጥበበ ግዮን ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ሲያቀኑ በነበረበት ጊዜ ነው ብለዋል፡፡ ፖሊስ ግድያውን የፈጸሙ አካላትን በቁጥጥር ሥር ለማዋል በሚያደርገው ጥረት ማኅበረሰቡ ተባባሪ እንዲኾንም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ዘገባው የአሚኮ ነው

ክፍለ ጦሩ ከፅንፈኛው ያስለቀቃቸውን የህዝብ ተሸከርካሪዎች ለባለንብረቶች አሥረከበ። በሰሜን ጎጃም ዞን አማሪት ፣ ዳና ማርያምና ጎጃው  አካባቢ ፅንፈኛውን ሃይል በመደምሰስ ከህዝብ የዘረፋቸው...
02/02/2025

ክፍለ ጦሩ ከፅንፈኛው ያስለቀቃቸውን የህዝብ ተሸከርካሪዎች ለባለንብረቶች አሥረከበ።

በሰሜን ጎጃም ዞን አማሪት ፣ ዳና ማርያምና ጎጃው አካባቢ ፅንፈኛውን ሃይል በመደምሰስ ከህዝብ የዘረፋቸውን ተሸከርካሪዎችና ቀብሯቸው የነበረ ቁምቡላዎችን የምስራቅ ዕዝ ክፍለ ጦር አባላት ባደረጉት የተጠናከረ ስምሪት በቁጥጥር ስር ማዋል ተችሏል።

የክፍለ ጦሩ አዛዥ ኮሎኔል ግፋወሰን አበበ ፅንፈኛው ሃይል የክልሉን ሰላም በማደፍረስ የዘረፋ ዓላማውን ለማሳካት ቢጥርም የክፍለጦሩ ሠራዊት ባደረገው ብርቱ ክትትል ንብረቱን ማስመለስ ተችሏል ብለዋል።

በስምሪቱም 01 ሰሊጥ የጫነ ከባድ ተሸከርካሪ፣ 01 የቻይና የኮንሰትራክሽን አይሱዙ፣ 01 የመንግሰት ላንድ ክሮዘርና 01 ካዚኖ ገልባጭ ከፅንፈኛው ማሥመለስ መቻሉን ተናግረዋል።

አሁን የተገኘውን አንፃራዊ ሰላም የበለጠ ለማጠናከር ፅንፈኛውን የገባበት በመግባት አሳዶ በመምታት ተሸከርካሪዎቹን ለባለ ንብረቶቹ አስረከበናል ብለዋል።

አካባቢው የበለጠ ሰላሙ እንዲጠናከር የአካባቢው ማህበረሰብ፣ ወጣቱና የፀጥታ ሃይሉ ከሠራዊቱ ጎን በመሆን የበኩላቸውን ሚና ሊወጡ እንደሚገባ አሳሰበዋል።

ዘገባው፦ የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ነው

02/02/2025

የብልጽግና ፓርቲ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በዛሬው የከሰዓት በኋላ ውሎው የፓርቲውን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ምርጫ በማካሄድ ላይ ይገኛል።

ጉባኤው በጠዋቱ ክፍለ ጊዜው ዐቢይ አሕመድን(ዶ/ር) የፓርቲው ፕሬዚዳንት እንዲሁም አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና አቶ አደም ፋራህን የፓርቲው ምክትል ፕሬዚዳንቶች አድርጎ መምረጡ ይታወሳል።

"የሠላምን መንገድ መምረጥ ህዝብን ለመካስ ዕድል የሚሰጥ የሰለጠነ አስተሳሰብ ማሳያ  ነው" ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ።።።።።።።።።።።።።።የመረጣችሁት የሰላም መንገድ በብዙ የምታተርፉበ...
02/02/2025

"የሠላምን መንገድ መምረጥ ህዝብን ለመካስ ዕድል የሚሰጥ የሰለጠነ አስተሳሰብ ማሳያ ነው" ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ
።።።።።።።።።።።።።።
የመረጣችሁት የሰላም መንገድ በብዙ የምታተርፉበት ነው፤ የሠላምን መንገድ መምረጥና መከተል ደግሞ የሰለጠነ አስተሳሰብ ማሳያ ነው ሲሉ የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናገሩ።

በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የሠላም አማራጭን ተቀብለው በዳባት የተሃድሶ ማዕከል ስልጠናቸውን ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ንግግር ያደረጉት ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ሀገርና ህዝብን ለማዳን የመረጣችሁት የሰላም መንገድ በብዙ የምታተርፉበት እንዲሁም ህዝባችሁን የምትክሱበት ዕድልን የሚሰጣችሁ ነው ብለዋል ፡፡

ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊያን የሚያስፈልገው ሰላምና ልማት ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ፅንፈኛውና ዘፊው ቡድን የአማራ ክልል ህዝብን ሠላም በማሳጣት ለከፋ ችግር ዳርጎት ቆይቷል ነው ያሉት ፡፡

ፅንፈኛው ቡድን የኢትዮጵያን መልማትና ማደግ በማይፈልጉ ታሪካዊ ጠላቶቻችን እየታዘዙ በክልሉ የጤና አገልግሎት መስጫና የትምህርት ተቋማት ላይ ወድመትና ኪሳራን በማድረስ በክልሉ በትምህርት ገበታ መገኘት የሚገባቸው ህፃናት ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዳይገኙ እንዲሁም በፌደራልና በክልሉ መንግስት ሊሰሩ የታቀዱ ፕሮጀክቶች እንዳይሰሩ ማድረጉን ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ተናግረዋል።

የሠላምን አማራጭ ተከትለው እጃቸውን ለሚሰጡ ታጣቂዎች አሁንም ቢሆን በሩ ክፍት ነው ያሉት የሰሜን ምዕራብ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ብርሃኑ በቀለ ከዚህ ውጪ በሚደረግ እንቅስቃሴ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ጠንከር ያለ ነው ሲሉም አሳስበዋል።

ሰልጣኞቹ በበኩላቸው በተሳሳተ የፅንፈኛው ፕሮፖጋንዳ ተታለን ህዝባችንን በድለናል ለከፋ ችግርም ዳርገናል ስለሆነም የበደልነውን ህዝብ ይቅርታ እንጠይቃለን ሌሎች ወንድሞቻችንም እጃቸውን ሰጥተው ህዝባቸውን እንዲክሱ መልእክታችንን እናስተላልፋለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ዘገባው፦ የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት ነው።

የብልጽግና ፓርቲ አማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት!።።።።።።።።።።።።።።።።።።ሁለተኛውን ጉባዔ እያካሄደ የሚገኘው ፓርቲያችን ብልጽግና ዛ...
02/02/2025

የብልጽግና ፓርቲ አማራ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይርጋ ሲሳይ የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት!
።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ሁለተኛውን ጉባዔ እያካሄደ የሚገኘው ፓርቲያችን ብልጽግና ዛሬ ባከናወነው የፕሬዘዳንት እና ምክትል ፕሬዘዳንቶች ምርጫ ክቡር ዶክተር ዐቢይ አሕመድን በፕሬዘዳንትነት እንዲሁም ክቡር አቶ ተመስገን ጥሩነህን እና ክቡር አቶ አደም ፋራህን በምክትል ፕሬዘዳንትነት መርጧል።

ክቡራን የፓርቲያችን ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዘዳንቶች እነኳን ደስአላችሁ እያልኩ መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ ።

ከቃል እስከ ባሕል !

"የኢትዮጵያን የልዕልና ጉዞ እናሳካዋለን።ብልፅግና ፓርቲ የጠራ ሀሳቡንና ትክክለኛ ፖሊሲዎቹን በትጉህ አመራርና አባላቱ በመፈጸም በአስደማሚ ድሎች ጉዞውን ቀጥሏል።ፓርቲያችን ከእነዚህ ድሎች ማ...
02/02/2025

"የኢትዮጵያን የልዕልና ጉዞ እናሳካዋለን።
ብልፅግና ፓርቲ የጠራ ሀሳቡንና ትክክለኛ ፖሊሲዎቹን በትጉህ አመራርና አባላቱ በመፈጸም በአስደማሚ ድሎች ጉዞውን ቀጥሏል።

ፓርቲያችን ከእነዚህ ድሎች ማግስት ባካሄደው ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤ ሀገርና ህዝብን እንድናገለግል አደራ ተሰጥቶናል።

በዚሁ መሠረት እኛም የኢትዮጵያን የማንሰራራት ጉዞ እና የህዝባችንን መሻት ለማሳካት ቃላችንን በድጋሚ አድሰናል።

ሁለንተናዊ ክብርና ብልፅግናን የተቀዳጀች ኢትዮጵያን ለትውልዱ ለማስረከብ ለፈተናዎች ሸብረክ ሳንል ያለ እረፍት እንደምንሠራ ለመላው ህዝባችን ማረጋገጥ እፈልጋለሁ" ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Address

Addis Ababa

Opening Hours

09:00 - 17:00

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when NBC Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category