NBC Ethiopia

NBC Ethiopia Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from NBC Ethiopia, TV Network, Addis Ababa.
(7)

NBC Ethiopia is a television station broadcasting on Ethiosat 11105 H and DSTv Channel 477
የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን እዚህ ይገኛሉ👇
https://linktr.ee/NBCEthiopiaTV

31/05/2026

በቄለም ወለጋ የአርሶአደሮች የምርጫ ዝግጅት

የልማት ስራዎቻችንን እያከናወንን በድምጻችን የሀገሪቱን መፃኢ እድል ለመወሰን ግንቦት 24ን እየተጠባበቅን ነው አሉ በቄለም ወለጋ ዞን የላሎ ቂሌ አርሶአደሮች፡፡

ምርጫው ሰላማዊ በሆነ መልኩ እንዲከናወን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እንሰራለንም ብለዋል፡፡

የአሜሪካ እና ኪዩባ የጦር አዛዦች ውይይትNBC Ethiopia። ። ። ። ። ። ። ። ። ።የአሜሪካ እና ኪዩባ ወታደራዊ ባለስልጣናት ባልተለመደ መልኩ በአካል ተገናኝተው በደህንነት ዙሪያ መከ...
31/05/2026

የአሜሪካ እና ኪዩባ የጦር አዛዦች ውይይት

NBC Ethiopia
። ። ። ። ። ። ። ። ። ።
የአሜሪካ እና ኪዩባ ወታደራዊ ባለስልጣናት ባልተለመደ መልኩ በአካል ተገናኝተው በደህንነት ዙሪያ መከሩ።

በጓንታናሞ ቤይ የባህር ሀይል ጦር ሰፈር ነው የተገናኙት ።

የአሜሪካ ደቡባዊ ዕዝ (ሳውዝኮም) የጦር አዛዡ ጀነራል ፍራንሲስ ዶኖቫን እና የኪዩባው ሌተናንት ጀነራል ሮቤርቶ ሶቶሎንጎ ጋር መገናኘታቸውን አሳውቋል።

በደህንነት ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ውይይት ተደረጓልም ብሏል ዕዙ።

የኪዩባ አብዮታዊ ጦር ሀይል ሚኒስቴር የወታደራዊ ባለስልጣናቱ መገናኘት በጎ ውጤት ያመጣል ብሎታል።

ሁለቱም ወገኖች በዕዞቻቸው መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከርም ስምምነት ላይ ደርሰዋል።

ዋሽንግተን በሃቫና መንግስት ላይ ጫና እያሳደረች ባለችበት ሰዓት የተደረገ ውይይት ነው።

ፕሬዚዳንት ትራምፕ ኪዩባን በሀይል እጥረት እየፈተኗት ሳለ ወታደራዊ ውይይቱ ውሃ የማያነሳ ሊሆን እንደሚችልም ተንታኞች ስጋታቸውን ያስቀምጣሉ።

የአሜሪካ የደህንነት ሰዎች ወደ ኪዩባ መመላለሳቸውን ተከትሎም ከስምምነት ይልቅ ስለላ ላይ እያተኮሩ ነው በሚልም የሃቫና ሚዲያዎች ይዘግባሉ።

የአሜሪካ የጦር መርከቦች በካሪቢያን ቀጠና ወታደራዊ እንቅስቃሴ ውስጥ መሆናቸውም ለአገሪቱ የደህንነት ስጋት ሆኖባታል።

ጀነራል ዳኖቫንም በባህር ሀይል ደህንነት፣የሚፈጠሩ ችግሮችን እንዴት መከላከል እንደሚቻል፣የጦር ዓባላት ደህንነትን በተመለከተ እና ለዘመቻ ያለውን ዝግጁነት ከጦር ሰፈሩ ባለስልጣናት ጋር ተወያይተናል ብለዋል።

ጓንታናሞ ቤይ በኪዩባ ደቡብ ምስራቅ ባህር ዳርቻ የሚገኝ ሲሆን በ1903 ነው አሜሪካ የያዘችው።

አሜሪካ በሊዝ ስምምነት ስም አካባቢውን ብትይዝም ኪዩባ ህገ ወጥ ነው በሚል ትከሳለች።
ዋሽንግተን ሃቫና ላይ ጥቃት ለማድረስ ጦር ሰፈሩን ልትጠቀምበት እንደምችልም ተነግሯል።

ዘገባው የአር ቲ ነው።

በ-ቢኒያም ካሴ

🔴 ዝግጁ ‼️ኢትዮጵያ ትመርጣለች 🗳️ 7ተኛው ሐገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ 1 ቀን ብቻ ቀርቶታል።የተመዘገቡበትን የምርጫ ካርድ በመያዝ ➡️ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት ➡️ ድምፅዎን ይስጡ ➡️ዴ...
31/05/2026

🔴 ዝግጁ ‼️

ኢትዮጵያ ትመርጣለች 🗳️

7ተኛው ሐገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሊካሄድ 1 ቀን ብቻ ቀርቶታል።

የተመዘገቡበትን የምርጫ ካርድ በመያዝ ➡️ በምርጫ ጣቢያ በመገኘት ➡️ ድምፅዎን ይስጡ ➡️ዴሞክራሲያዊ መብቶን ይጠቀሙ።

NBC Ethiopia
። ። ። ።


#ምርጫ2018
#ኢትዮጵያትመርጣለች

📌 ትራምፕ አፈገፈጉ ፤ኢራን ዛተች! 📌 የሩሲያ ጦር ግስጋሴNBC Ethiopia  NBC ዓለም-አቀፍ 👉 https://youtu.be/1eMO8iJe6BQ። ። ። ማስፈንጠሪያውን (ሊንኩን) በመጫን...
30/05/2026

📌 ትራምፕ አፈገፈጉ ፤ኢራን ዛተች!

📌 የሩሲያ ጦር ግስጋሴ

NBC Ethiopia NBC ዓለም-አቀፍ

👉 https://youtu.be/1eMO8iJe6BQ

። ። ።

ማስፈንጠሪያውን (ሊንኩን) በመጫን NBC ኢትዮጵያን ይጎብኙ ይወዳጁ
https://linktr.ee/NBCEthiopiaTV


National Media SC is here to support, the success of our country's transformational journey; to develop a civic-democratic political culture; which will be f...

🔴 በጎንደር ከተማ የምርጫ ቁሳቁስ ሥርጭት እየተካሄደ ነው  #ምርጫ2018
30/05/2026

🔴 በጎንደር ከተማ የምርጫ ቁሳቁስ ሥርጭት እየተካሄደ ነው

#ምርጫ2018

ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ለሁለተኛ ጊዜ አነሳ      NBC Ethiopia። ። ። ። ። ። ። ። ።በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂ አርሰናልን በመለያ ምት  አ...
30/05/2026

ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫን ለሁለተኛ ጊዜ አነሳ


NBC Ethiopia
። ። ። ። ። ። ። ። ።
በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የፍጻሜ ጨዋታ ፒኤስጂ አርሰናልን በመለያ ምት አሸንፏል።

ማምሻውን በሀንጋሪ ቡዳፔስት በሚገኘው ፑሽካሽ አሬና ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ካይ ሃቫርትዝ በስድስተኛው ደቂቃ ባስቆጠረው ጎል አርሰናል መሪ ሆኗል።

የፒኤስጂው አምበል ማርኪኒዮስ ስህተት
ለሃቫርትዝ ግብ መቆጠር ምክንያት ሆኗል።

ከእረፍት መልስ ኡስማን ዴምቤሌ በ65ኛው ደቂቃ በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ ላይ ባሳረፈው ጎል ፒኤስጂ አቻ መሆን ችሏል።

የወቅቱ የባለንዶር አሸናፊ ዴምቤሌ ዘንድሮ በውድድሩ ላይ ያስቆጠራቸውን ጎሎች ብዛት ስምንት አድርሷል።

መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ በአቻ ውጤት በመጠናቀቁ ምክንያት 30 ደቂቃ ተጨምሯል።

በጭማሪ ሰዓት ግብ ባለመቆጠሩ ምክንያት ጨዋታው ወደ መለያ ምት አምርቷል።

ፒኤስጂ በመለያ ምት 4 ለ 3 በማሸነፍ ለተከታታይ የውድድር ዓመት የሻምፒዮንስ ሊጉን ዋንጫ አንስቷል። የአውሮፓ ክብሩን አስጠብቋል።

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የማንሳት ህልሙ አልተሳካም።

አርሰናል ከፕሪሚየር ሊጉ ድል በኋላ ድርብ ስኬት ማሳካት አልቻለም።

። ። ።

ማስፈንጠሪያውን (ሊንኩን) በመጫን NBC ኢትዮጵያን ይጎብኙ ይወዳጁ
https://linktr.ee/NBCEthiopiaTV





30/05/2026

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአሶሳ መገሌ የምርጫ ቁሳቁስ ስርጭት እየተከናወነ መሆኑ ተገለጸ


#ምርጫ2018

ቦርዱ የምርጫ ቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ ጥቆማ ማድረጊያና ምላሽ መስጫ ሥርዓት አቋቋመNBC Ethiopia ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች ከ7ኛው ጠቅላ...
30/05/2026

ቦርዱ የምርጫ ቅድመ ማስጠንቀቂያ፣ ጥቆማ ማድረጊያና ምላሽ መስጫ ሥርዓት አቋቋመ

NBC Ethiopia
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች ከ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጋር የተያያዙ ችግሮችንና ክስተቶችን ደኅንነቱ በተጠበቀና ፈጣን በሆነ መንገድ ጥቆማ የሚያደርጉበትን “ከምርጫ ጋር ተያይዘው የሚፈጠሩ ችግሮች ሪፖርት ማድረጊያ እና ምላሽ መስጫ ሥርዓት” ዘርግቷል።

ይህ ሥርዓት ምርጫ ቦርድ፤ የሚመለከታቸው ተቋማት እና ባለድርሻ አካላት መረጃዎችን አስቀድመው እንዲያገኙ፣ ፈጣን ምላሽ እንዲሰጡ እንዲሁም ሰላማዊና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ እንዲካሄድ ለማገዝ ታስቦ የተዘጋጀ ነው።

ምን ዓይነት ችግሮችን ጥቆማ ማድረግ ይችላሉ?

• በምርጫ ሂደቶች ላይ የሚፈጠሩ መስተጓጎሎች፣
• በድምፅ አሰጣጥ ወይም በቆጠራ ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮች፣
• በምርጫ ጣቢያዎች አቅራቢያ የሚከሰቱ የፀጥታ ችግሮች፣
• በመራጮች ላይ የሚደርስ ማስፈራራት ወይም ትንኮሳ፣
• በምርጫ ቁሳቁስ ላይ የሚደርስ ጉዳት፣
• ዐመፅ ወይም ዛቻዎች፣
• ውጥረት የሚፈጥሩ የሐሰት መረጃዎች፣
• እንዲሁም ምርጫውን ሊያስተጓጉል የሚችል ወይም ማንኛውም ሌላ አጠራጣሪ ድርጊት ጥቆማ ማድረግ ይችላሉ።

መቼ ጥቆማ መስጠትይኖርብዎታል?

• የምርጫ ሂደቶች ሲስተጓጎሉ ሲመለከቱ፣
• ከላይ የተጠቀሱትን ክስተቶች በቀጥታ ከተመለከቱ፣
• የዐመፅ ወይም የግጭት ሥጋት ካለ፣
• እንዲሁም አስቸኳይ ዕርምጃ የሚያስፈልጋቸው ማንኛውም ምርጫን የሚያውኩ ክስተቶች ከተመለከቱ።
• ችግሮችን አስቀድሞ ሪፖርት ማድረግ ሁኔታዎች እንዳይባባሱ ለመከላከልና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ይረዳል።

እንዴት ጥቆማ መስጠት ይችላሉ?

በሚከተሉት መንገዶች ጥቆማ መስጠት ይችላሉ፦
• በነፃ የስልክ መስመር 6214 ላይ በመደወል
• አጭር የጽሑፍ መልዕክት ወደ 7555 በመላክ
ሪፖርት ሲያደርጉ የሚከተሉትን መረጃዎች ለማካተት ይሞክሩ፦
• ምን እንደተከሰተ
• የት እንደተከሰተ
• መቼ እንደተከሰተ
• ማን እንደተሣተፈበት (የሚታወቅ ከሆነ)

ማን ጥቆማ መስጠት ይችላል?

ማንኛውም ሰው ከምርጫ ጋር የተያያዙ ክስተቶችን ጥቆማ መስጠት ይችላል፤ ከእነዚህም መካከል፦
• ዜጎች፣
• የምርጫ ታዛቢዎች፣
• የፖለቲካ ፓርቲዎች፣
• የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች፣
• የሴቶችና የወጣቶች ማኅበራት፣
• ምርጫ አስፈጻሚዎች፣
• የቦርዱ ሠራተኞችና ኃላፊዎች ጥቆማ

ጥቆማ ከተሰጠ ካደረጉ በኋላ ምን ይከናወናል?

1. ጥቆማዎ እኛ ጋር ከደረሰ በኋላ ይመረመራል፣
2. የቀረበው መረጃ ትክክለኛነት ይረጋገጣል፣
3. እንደ አስፈላጊነቱ ምርጫ ቦርድ እና የሚመለከታቸው ተቋማት በቅንጅት ምላሽ ይሰጣሉ።
4. የተወሰደው ዕርምጃ ወይም የተሰጠው ምላሽ ለጥቆማ አቅራቢው ሊገለጽ ይችላል፣

የእርስዎ ጥቆማ መስጠት ለምን አስፈለገ?

የሚያቀርቡት ጥቆማ ለሚከተሉት ጉዳዮች ይረዳል፦
• የምርጫውን ግልጸኝነት ለማሻሻል፣
• ሰላማዊ እና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ እንዲካሄድ ለማገዝ፣
• መራጮችን እና የምርጫ አስፋጻሚዎችን ደኅንነት ለመጠበቅ፣
• ዐመፅ እና ግጭቶችን ለመከላከል፣
የምርጫውን ሂደት ሊያስተጓጉል የሚችል ማንኛውንም ችግር ካዩ ወይም ካጋጠመዎት እባክዎን ወዲያውኑ ጥቆማ ይስጡ!

እያንዳንዱ ጥቆማ ይበልጥ ደኅንነቱ የተጠበቀ የምርጫ ሂደት እንዲኖር አስተዋፅዖ ያበረክታል።
የመገናኛ መንገዶች
ነፃ የስልክ መስመር 6214
አጭር የጽሑፍ መልዕክት 7555
አድራሻ: የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ| አዲስ አበባ
ድረ-ገጽ www.nebe.org.et

ምርጫው በስኬት እንዲከናወን አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቅቋል – የአዲስ አበባ ፖሊስNBC Ethiopia ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።በምርጫና ድህረ ምርጫ ቀናት በሚከናወኑ የፀጥታ ማስከበ...
30/05/2026

ምርጫው በስኬት እንዲከናወን አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቅቋል – የአዲስ አበባ ፖሊስ

NBC Ethiopia
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

በምርጫና ድህረ ምርጫ ቀናት በሚከናወኑ የፀጥታ ማስከበር ተግባራት ምርጫው በስኬት እንዲከወን አስፈላጊው ዝግጅት ተጠናቅቋል አለ የአዲስ አበባ ፖሊስ፡፡

በአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ በቅድመ ምርጫ የተከናወኑ ተግባራትን ለመገምገም በተዘጋጀው መድረክ ላይ እንደተገለጸው÷ የምርጫና ድህረ ምርጫ ቀናት የጸጥታ ማስከበር ተግባራት በስኬት እንዲጠናቀቁ አስፈላጊው ዝግጅት ተደርጓል፡፡

የጸጥታ አካላት አስቀድመው የጋራ ዕቅድ በማውጣት ወደ ተግባር በመግባታቸው ቅድመ ምርጫውን በጥሩ ሁኔታ ማከናወን እንደተቻለ ተመላክቷል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ሌ/ጄነራል አስራት ደኔሮ÷ የምርጫን ደህንነት የማረጋገጥ ተግባር ልዩ ጥንቃቄን የሚሻ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ቀሪ ተግባራት ካሉ በአስቸኳይ ማጠናቀቅ እንደሚገባ አሳስበው÷ በምርጫው ላይ አሉታዊ ጫና ለማሳደር የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች እንዳሉ በመረዳት በምርጫ ዕለት እና ድህረ ምርጫም ሂደቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን ጠቅሰዋል፡፡

የከተማው ሠላምና ጸጥታ ቢሮ አስተዳደር ኃላፊ ሊዲያ ግርማ በበኩላቸው÷ የጸጥታ ሥራው ለሕብረተሰቡ ደህንነትን ያረጋገጠ እና ለፀረ ሠላም ኃይሎች ጫናን የሚያሳድር መሆን እንዳለበት አመልክተዋል፡፡

በተለይ ፀጉረ ልውጦችን ለመቆጣጠር በሸገር ከተማ ሥር ከሚገኙ ክፍለ ከተሞች ጋር ያለውን ትስስር ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ ነው ያስገነዘቡት፡፡

ምርጫው ያለ ምንም የፀጥታ እንከን እንዲከናወን ሕብረተሰቡ ማንኛውም ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በነጻ የስልክ መስመሮች 990፣ 991፣ 987፣ 816 እንዲሁም በ011-1-26-43-59፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን በመጠቀም ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠይቋል።

ፒኤስጂ 0 - 1 አርሰናል(የመጀመሪያው አጋማሽ)NBC Ethiopia። ። ። ። ። ። ። ። ።በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በአርሰናል አንድ ለ ባዶ መሪነት ለእረፍት ወጥተዋል።በፑሽ...
30/05/2026

ፒኤስጂ 0 - 1 አርሰናል

(የመጀመሪያው አጋማሽ)

NBC Ethiopia
። ። ። ። ። ። ። ። ።
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በአርሰናል አንድ ለ ባዶ መሪነት ለእረፍት ወጥተዋል።

በፑሽካሽ አሬና ስታዲየም እየተደረገ በሚገኘው ሀቨርትዝ በ6ኛው ደቂቃ አርሰናልን መሪ ያደረገች ግብ አስቆጥሯል።

ጀርመናዊው ተጨዋች በዘንድሮው የውድድር ዓመት በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ፣ በስድስት ጨዋታዎች ለአራተኛ ጊዜ ኳስን ከመረብ አሳርፏል።

ሀቨርትዝ ከሁለት የተለያዩ ክለቦች ጋር በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ፍጻሜ በማስቆጠር በታሪክ ሦስተኛው ተጫዋች ሆኗል።

ከ20 ዓመታት ጥበቃ በኋላ ለፍጻሜ የደረሰው አርሰናል በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የመድረኩን ክብር ለማንሳት የ45 ደቂቃዎች ዕድሜ ብቻ ቀርቶታል።

። ። ።

ማስፈንጠሪያውን (ሊንኩን) በመጫን NBC ኢትዮጵያን ይጎብኙ ይወዳጁ
https://linktr.ee/NBCEthiopiaTV





Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when NBC Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category