Zemen Media- ዘመን ሚዲያ

Zemen Media- ዘመን ሚዲያ To Get fast and timely information follow us!

23/01/2025

#ከትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት የተገኘ መረጃ

ዛሬ ጥር 15 ቀን 2017 የትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አመራሮችን ወክለው በሰጡት መግለጫ ጊዜያዊ አስተዳደርን ለመበተን፣ ስርዓት አልበኝነትን ለማንገስ እና ሰራዊቱን ለመበተን ከተልዕኳቸው ውጪ ከህገወጥ ቡድን ጋር በመሆን በግልፅ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለዋል።

ይህ መግለጫ በጊዜያዊ አስተዳደሩ የማይታወቅ ሲሆን በማንኛውም መስፈርት ህጋዊም ሆነ ሞራላዊ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። ጊዜያዊ ካቢኔው የሰራዊት አዛዦችን ያልተለመደ ውሳኔ ለማየት አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል። ሁኔታውን ከተመለከትን በኋላ ለህዝባችን ሰፊ ማብራሪያ እንሰጣለን ብለዋል።

የሰራዊቱን ከፍተኛ አዛዦች በመወከል የወጣው የዚህ ህገ መንግስት ይዘት በግልፅ መፈንቅለ መንግስት በማወጅ የፕሪቶሪያን ስምምነት አደጋ ላይ ጥሏል። መላው ህዝባችንን አደጋ ላይ የጣለ ኃላፊነት የጎደለው ውሳኔም ነው ይህ ወዲያውኑ መቆም አለበት ብለዋል። ይህ ካልሆነ የህዝባችንና የጸጥታ ሃይላችን አንድነት አደጋ ላይ ይወድቃል።

ሁሉም የጸጥታ ሃይሎች ይህንን ህገወጥ ውሳኔ ውድቅ እንዲያደርጉ እና ከዚህ ውጪ የትኛውንም ትዕዛዝ ተግባራዊ እንዳያደርጉ እናሳስባለን ሲል ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው አስታውቋል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት
መቐለ

 🇪🇹የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ቦይንግ 777F እቃ ጫኝ አውሮፕላን መረከቡን ገልጿል።ይህ አውሮፕላን የካርጎ ጭነት አገልግሎት አድማስን ለማሳደግ የራሱ አስተዋፅዖ ከማበርከቱ በተጨማሪ እያ...
23/01/2025

🇪🇹
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ ቦይንግ 777F እቃ ጫኝ አውሮፕላን መረከቡን ገልጿል።

ይህ አውሮፕላን የካርጎ ጭነት አገልግሎት አድማስን ለማሳደግ የራሱ አስተዋፅዖ ከማበርከቱ በተጨማሪ እያደገ የመጣውን የካርጎ አገልግሎት ለማስተናገድ የራሱ አስተዋፅዖ ይኖረዋል ብሏል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የካርጎና ሎጂስቲክስ አገልግሎት እየሰጠ ያለውን የላቀ የአየር እቃ ጭነት አገልግሎት አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።

አሁን የገባው አዲስ የካርጎ አውሮፕላን አየር መንገዱ ማህበራዊ ሀላፊነቱን በመወጣት ረገድ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን የሚያግዙና የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ላይ ለተሰማሩ ተቋማት የሚለገሱ ቁሳቁሶችን ወደ ሀገር ውስጥ ይዞ መምጣቱ ተገልጿል።

Credit:

 ,000 _ሠራተኞች የስራ  #ቪዛ አቀረበች።እንግሊዝ በግብርና እና እንስሳት እርባታ ዘርፍ የገጠማትን የሠራተኛ እጥረት ለመቅረፍ ከጥር ጀምሮ የሠራተኛ ቪዛ ለማቅረብ ማታቀዱን አስታውቃለች።አ...
14/11/2024

,000 _ሠራተኞች የስራ #ቪዛ አቀረበች።

እንግሊዝ በግብርና እና እንስሳት እርባታ ዘርፍ የገጠማትን የሠራተኛ እጥረት ለመቅረፍ ከጥር ጀምሮ የሠራተኛ ቪዛ ለማቅረብ ማታቀዱን አስታውቃለች።

አዲሱ እቅድ የሀገሪቱን የምግብ ምርት አቅርቦት ለማሳደግ ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

ከ18 አመት በላይ የሆነ እና ጤንነቱ የተረጋገጠ ማንኛውም ሰው ህጋዊ ፈቃድ ባለው ቀጣሪ ተቋም በኩል ቪዛ ማግኘት እንደሚችልም ተመላክቷል።

ሀገሪቷ በ2025 #ለ45,000 ሠራተኞች የስራ #ቪዛ እንዳቀረበች ተነግሯል።

ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን ወደ ዱባይ በረራ አደረገ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን ሁለተኛ በረራውን ወደ ዱባይ አድርጓል፡፡ዱ...
09/11/2024

ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን ወደ ዱባይ በረራ አደረገ

በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ ኤ350-1000 አውሮፕላን ሁለተኛ በረራውን ወደ ዱባይ አድርጓል፡፡

ዱባይ በአፍሪካ የመጀመሪያ ለሆነው ኤ350-1000 አውሮፕላን ደማቅ አቀባበል እንዳደረገችም የኢትዮጵያ አየር መንገድ መረጃ አመልክቷል።

ኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላን የመጀመሪያ በረራውን ወደ ናይጀሪያ ሌጎስ ማድረጉ ይታወሳል።

(ኤፍ ቢ ሲ)

  ብር እድለኛው የልብስ ስፌት ባለሙያአቶ አሰፋ ተዘራ ይባላሉ የሻኪሶ ነዋሪ ሲሆኑ በከተማው በልብስ ስፌት ስራ በመሰማራት በሚያገኛት ገቢ ቤተሰቦቻቸውን ያስተዳድራሉ ፡፡ ስራው አጥጋቢ ገቢ ...
06/11/2024

ብር እድለኛው የልብስ ስፌት ባለሙያ

አቶ አሰፋ ተዘራ ይባላሉ የሻኪሶ ነዋሪ ሲሆኑ በከተማው በልብስ ስፌት ስራ በመሰማራት በሚያገኛት ገቢ ቤተሰቦቻቸውን ያስተዳድራሉ ፡፡ ስራው አጥጋቢ ገቢ ባይኖረውም እግዚአብሔር ይመስገን ሳላማርር ባለኝ ነገር ደስተኛ ነበርኩ ነገር ግን ህይወቴን ለመለወጥ የማላደርገው ሙከራ አልነበረም ከሙከራዎቼ አንዱ ሎተሪን መቁረጥ ሲሆን ማን ያውቃል አንድቀን ይወጣ ይሆናል በሚል ተስፋ ትላልቅ ዕጣዎች ሲኖሩ ሙሉውን ቲኬት መቁረጥ አዘወትር ነበር በማለት አቶ አሰፋ ይናገራሉ፡፡

ታድያ እንደተለመደው ጳጉሜን 5 ቀን 2016 የሚጣውን የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ሙሉውን ቲኬት ይቆርጡና መውጫውን ቀን ይጠባበቃሉ ፡፡ ሎተሪው ከወጣ በ12ኛው ቀን ከሻኪሶ ወደ አዶላ በሄዱበት ድንገት የሎተሪ አዟሪ ሲያዩ የቆረጡትን የእንቁጣጣሽ ለለተሪ ትዝ ሲላቸው አሳዩትና እንዴ ጋሼ 5 ሚሊየን ብር እኮ አለው ሲላቸው የተደበላለቀ ስሜታ ተሰማኝ ይላሉ ፡፡

እራሴን አረጋግቼ ወደ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ዋና መስሪያ ቤት በመሄድ እውነትም የ5 ሚሊየን ዕድለኛ መሆኔን አረጋገጥኩ በማለት በደስታ ግልጸዋል ፡፡ ሽልማታቸውም በሚሩበት ቦታ ድረስ በመሄድ በህዝብ ፊት ተረክበዋል ፡፡

ዶናልድ ትራምፕ 47ኛ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ‼️በአሜሪካ እጅግ ጠንካራ ፉክክር በታየበት 47ኛ የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዶናልድ ትራምፕ 279 ድምፅ በማግኘት አሸንፈዋል፡፡የቀድ...
06/11/2024

ዶናልድ ትራምፕ 47ኛ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ‼️

በአሜሪካ እጅግ ጠንካራ ፉክክር በታየበት 47ኛ የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዶናልድ ትራምፕ 279 ድምፅ በማግኘት አሸንፈዋል፡፡

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሪፐብሊካን ፓርቲን በመወከል ለ2ኛ ጊዜ አሜሪካንን ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ለመምራት የሚያስችላቸውን ድምፅ አግኝተዋል፡፡

የአሁኗ የአሜሪካ ምክትል ፕሬዚዳንት ካማላ ሃሪስ ዴሞክራት ፓርቲን በመወከል በታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ፕሬዚዳንት ለመሆን ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

በአውሮፓውያኑ 2024 በዓለም ከተካሄዱና ከሚካሄዱ ሀገራዊ ምርጫዎች መካከል የዓለምን ትኩረት የሳበ፣ ከአሜሪካ አልፎ በዓለም ፖለቲካ ትልቅ ትርጉም የሚኖረውን 47ኛውን የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዶናልድ ትራምፕ አሸንፈዋል፡፡

በአሜሪካ ድምፅ መስጠት ከሚችሉ 240 ሚሊዮን ዜጎች መካከል 161 ሚሊዮን መራጮች ድምፅ ለመስጠት ካርድ ወስደዋል።

ከምርጫው በፊት በፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለማሸነፍ በአሪዞና፣ ጆርጂያ፣ ሚቻጋን፣ ኔቫዳ፣ ሰሜን ካሮላይና፣ ፔንሰልቫኒያ እና ዊስኮንሲን 7 ግዛቶች ሁለቱም ፓርቲዎች እኩል የመራጮች ድጋፍ ያላቸው በመሆኑና ከዚህ ቀደም ተፈራርቀው ስላሸነፉ አሁንም ቁልፍ ሚና እንዳላቸው ሲገለፅ ቆይቷል።

ይሁን እንጂ ዶናልድ ትራምፕ በ7ቱም ግዛቶች ተቀናቃኛቸውን ካማላ ሃሪስን በማሸነፍ ታሪካዊ ድል አስመዝግበዋል።

የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ በታሪኳ ትልቅ ኢኮኖሚ እንዲኖራት፣ ለአሜሪካ ሰራተኞች ፍትሃዊ የንግድ ሥርዓት ለመዘርጋት፣ በዓለም በኃይል አቅርቦት በሌሎች የተያዘውን የበላይነትን ለማስተካከል፣ የአሜሪካን ብሔራዊ ደህንነትና ድንበር ለማስጠበቅ፣ በአደንዛዥ እፅ እና ወንጀልን ለመቀነስ ቃል የገቡት ትራምፕ የአሜሪካውያንን ልብ አግኝተው ዳግም 47ኛ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ሆነው ተምርጠዋል፡፡

የትራምፕ ደጋፊዎች ፕሬዚዳንቱ ኢኮኖሚውን ለማሻሻል፣ በመመካከለኛው ምስራቅ ያለው ጦርነት እንዲቆም፣ በሩሲያና በዩክሬን መካከል ባለው ጦርነት ላለመሳተፍ የገቡትን ቃል እንያዲከብሩ መጠየቅ ጀምረዋል፡፡

 " አስደናቂ ድል ተቀዳጅቻለሁ " - ትራምፕዶናልድ ትራምፕ " አስደናቂ ድል ተቀዳጀሁ " አሉ።የሪፐብሊካኑ ዕጩ ትራምፕ ድላቸውን ለደጋፊዎቻቸው የተናገሩት በፍሎሪዳ በተካሄደ መድረክ ነው።ትራ...
06/11/2024

" አስደናቂ ድል ተቀዳጅቻለሁ " - ትራምፕ

ዶናልድ ትራምፕ " አስደናቂ ድል ተቀዳጀሁ " አሉ።

የሪፐብሊካኑ ዕጩ ትራምፕ ድላቸውን ለደጋፊዎቻቸው የተናገሩት በፍሎሪዳ በተካሄደ መድረክ ነው።

ትራምፕ ይህ የአሜሪካ ወርቃማ ዘመን እንደሚሆን ተናግረዋል።

" ይህ ለአሜሪካ ህዝብ ታላቅ ድል ነው፤ አሜሪካን እንደገና ታላቅ ለማድረግ ያስችለናል " ብለዋል።

በድንበሮች ያሉ ጉዳዮችን እልባት እንደሚሰጡ ቃል ገብተው ፓርቲያቸው እና እሳቸው ታሪክ የሰሩት በምክንያት እነደሆነ ተናግረዋል።

ትራምፕ ፥ " አሜሪካ ከዚህ በፊት ታይቶ የማያውቅ ስልጣን ሰጥታናለች " በማለት ፓርቲያቸው የህግ መወሰኛ ምክር ቤቱን የበላይነት ከዲሞክራቶች በመውሰድ መቆጣጠራቸውን እንዳሳወቁ ቢቢሲ ዘግቧል።

''  የቀጠለው ግጭት ያሳስበኛል''  -  #አሜሪካ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስር አቢይ አህመድ ጋር የስልክ ውይይት አካሂደዋል፡፡ብሊንከን ለሁለት አመታት...
05/11/2024

'' የቀጠለው ግጭት ያሳስበኛል'' - #አሜሪካ

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስር አቢይ አህመድ ጋር የስልክ ውይይት አካሂደዋል፡፡

ብሊንከን ለሁለት አመታት የዘለቀውን የሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያ የተኩስ አቁም ስምምነት (COHA) ሙሉ በሙሉ እንድተገበር ጠይቀዋል፡፡

ስምምነቱ ተግባራዊ እንዲሆን ኢትዮጵያ እያደረገች ያለውን ጥረት እንደሚፈግፉ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ በኢትዮጵያ የሚስተዋሉ የውስጥ ግጭቶችን በዘላቂነት ለመፍታት ፖለቲካዊ ውይይት ማካሄድ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡

ሀገራቸው አሜሪካ በአማራ ክልል የቀጠለው ግጭት እንደሚያሳስባት በስልክ በተደረገው ውይይት ማንሳታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማት ሚለር ተናግረዋል፡፡

ብሊንከን እና አቢይ በአፍሪካ ቀንድ ስላለው ቀጠናዊ ውጥረትም ተመካክረዋል ተብሏል፡፡

05/11/2024

#ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ሰጠች

በአለም አዲስ አገር ለሆነችው የተሰጠው ብድር በሁለቱ አገራት መካከል አገናኝ ለሚሆን መንገድ ግንባታ የሚውል ነው።

የአራት አመት እፎይታ ኖሮት በ10 አመታት ተከፍሎ የሚጠናቀቀው ብድር ከ738 ሚሊየን ዶላር በላይ ነው።

በደቡብ ሱዳን ድንበር ውስጥ የሚገነባው 220 ኪሜ መንገድ በኢትዮጵያ ተቋራጮች እና አማካሪዎች እንዲከናወን በሁለቱ አገራት ከስምምነት መደረሱ ተገልጿል።

የብድር አመላለሱም በካሽ እና በድፍድፍ ነዳጅ እንደሚሆን ነው የተጠቀሰው ሲል ካፒታል ነው ያስነበበው።

''ኢራን ኃይለኛ ጥቃት ለማድረስ እቅድ ይዛለች'' - ሪፖርት ቴህራን፣ ''ውስብስብ እና አዲስ''  ያለችውን ጥቃት ለማድረስ በዝግጅት ላይ መሆኗን ለተለያዩ አረብ ሀገራት በዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖ...
04/11/2024

''ኢራን ኃይለኛ ጥቃት ለማድረስ እቅድ ይዛለች'' - ሪፖርት

ቴህራን፣ ''ውስብስብ እና አዲስ'' ያለችውን ጥቃት ለማድረስ በዝግጅት ላይ መሆኗን ለተለያዩ አረብ ሀገራት በዲፕሎማቲክ ሚሲዮኖቿ በኩል ገልጻለች ሲል ዌል ስትሪት ጆርናል ያወጣው ሪፖርት ያሳያል፡፡

ኢራን በእስራዔል ላይ 'አደርሰዋለሁ' ላለችው ጥቃት ካሁን በፊት ያልተጠቀመቻቸውን ከባባድ የጦር መሳሪያዎች በጥቅም ላይ እንደምታውልም ሪፖርቱ ያስረዳል።

ሪፖርቱ፣ "ኢራን ኃይለኛ ጥቃት ለማድረስ እቅድ ይዛለች" ይላል።

የኢራኑ ጠቅላይ መሪ አያቶላህ ካሚኒ፣ ሀገራቸው በእስራዔልና በአሜሪካ ላይ ጠንካራ ምላሽ እንደምትሰጥ ተናግረው ነበር፡፡

አሜሪካ በበኩሏ፣ እስራዔል የአጸፋ እርምጃ ከወሰደች በኋላ ኢራን ምላሽ እንዳትሰጥ ስታሳስብ ቆይታለች፡፡

  የጥሪ ማስታወቂያ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች   የምዝገባ  ጊዜ ኀዳር 09-10/2017 ዓ.ም መሆኑን ይገልጻል፡፡ የምዝገባ ...
04/11/2024



የጥሪ ማስታወቂያ


የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም በመደበኛ የዲግሪ ፕሮግራም አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ኀዳር 09-10/2017 ዓ.ም መሆኑን ይገልጻል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
• የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዋናው ግቢ
• የማህበራዊ ሳይንስ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት

ማሳሰቢያ፤
ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲመጡ የሚከተሉትን ይዘው መምጣት ይጠበቅባችኋል፡፡
• የ12ኛ ክፍል ፈተና ማጠቃለያ ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
• ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው
• አራት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
• አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና ትራስ ጨርቅ፣
• የስፖርት ትጥቅ

ማሳሰቢያ:-

ከተጠቀሰው ቀን በፊትም ሆነ በኃላ የሚመጣ ተማሪ የማናስተናግድ መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን፡፡

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ጽ/ቤት

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zemen Media- ዘመን ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share