Menahria f.m 99.1

Menahria f.m 99.1 https://t.me/menaharia_fm

https://youtube.com/.1?si=dRLPxb2AKvsMaph-

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን!

#መናኸሪያሬዲዮ

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የደንበኞች ቁጥር 10 ሚሊዬን መድረሱን ገለጸሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዊም ቫንሄለፑት ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ...
01/07/2025

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የደንበኞች ቁጥር 10 ሚሊዬን መድረሱን ገለጸ

ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዊም ቫንሄለፑት ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ፤ተቋሙ ወደ ስራ በገባ በ4 አመታት ውስጥ 10 ሚሊዬን የሚጠጉ ደንበኞች ማፍራቱን ተናግረዋል፡፡

ይህ ቁጥርም ባለፉት 90 ቀናት የደንበኞች አጠቃቀም ላይ የተመሰረተ መረጃ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ተቋሙ ዲጂታል ኢትዮጰያን እውን ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የበኩሉን ሀላፊነት እየተወጣ መሆኑን በመግለጫው ላይ አንስተዋል፡፡

ተቋሙ ጠንካራ የቴሌኮም እና የዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎቶች መሰረተ ልማት ላይ ባለፉት 4 አመታት ከ300 ቢሊዬን ብር በላይ ወጪ ማድረጉን አመላክተዋል፡፡

አሁን ላይ የአራተኛው ትውልድ ኔትወርክ በግማሽ በላይ በሚሆን ደንበኞች ተጠቃሚ መሆናቸው የተገለጸ ሲሆን 150 በላይ ከተሞች ይህን የሚያሳልጡ መሰረተ ልማት ግንባታዎች መደረጋቸውን የገለፁት የሳፋሪኮም የውጭ ግንኙነት ሀላፊ ዶክተር አንዱለም አድማሴ ናቸው፡፡

ተቋሙ በየዕለቱ 31 ሺ ደንበኞችን እያገኘ መሆኑን በመግለፅ በተለይም አሁንም ድረስ የቴሌኮም አገልግሎት ተደራሽ ባልሆነባቸው አካባቢዎች ደንበኞችን ለማፍራት እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ዶክተር አንዷለም አክለውም በቀጣይ ሶስት አመታት ደንበኞችን ከ15 እስከ 17 ሚሊዬን ለማድረስ እንደሚሰራ ገልፀዋል፤፤

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ 900 ሰራተኞች ያሉት ሲሆን 20 ሺ የሚሆኑ ዜጎች ደግሞ በተዘዋዋሪ የስራ እድል እንዲያገኙ ማድረጉን ተመላክቷል፡፡

__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63

የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

ጀርመን በፊሊፒንስ በባህር ዳርቻ የንፋስ ኃይል ልማት 6.7 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት ልታደርግ ነውሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ጀርመን በፊሊፒንስ ውስጥ 3,260 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ...
01/07/2025

ጀርመን በፊሊፒንስ በባህር ዳርቻ የንፋስ ኃይል ልማት 6.7 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስት ልታደርግ ነው

ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)ጀርመን በፊሊፒንስ ውስጥ 3,260 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ባላቸው የባህር ዳርቻ የንፋስ ኃይል ፕሮጀክቶች ላይ 392 ቢሊዮን ፊሊፒንስ ፔሶ (6.7 ቢሊዮን ዶላር) ግዙፍ ኢንቨስትመንት ልታደርግ መሆኑን አስታውቃለች። ይህ ትልቅ ፕሮጀክት እንደ ኢሎኮስ ኖርቴ፣ ሚንዶሮ እና ሰሜናዊ ሳማር ባሉ ቁልፍ የባህር ዳርቻ አካባቢዎች እንደሚገነባ ተገልጿል።

ይህ ኢንቨስትመንት በጀርመኑ ግዙፍ ኩባንያ "wpd AG" የሚመራ ሲሆን፣ በደቡብ ምስራቅ እስያ ከሚደረጉት ትልልቅ የባህር ዳርቻ የንፋስ ኃይል ኢንቨስትመንቶች አንዱ ነው ተብሏል። የፊሊፒንስ መንግስት እስከ 2030 ድረስ 35% የሚሆነውን የኃይል ፍላጎቱን ከታዳሽ ኃይል ለማግኘት እና እስከ 2040 ደግሞ 50% ለማድረስ ላስቀመጠው ግብ ትልቅ መሻሻል እንደሆነ ተዘግቧል።

እነዚህ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ቤቶችን በኤሌክትሪክ የሚያቀርቡ ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ለአካባቢ ተስማሚ የሆኑ ሥራዎችን ይፈጥራሉ ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም፣ የፊሊፒንስ የቅሪተ አካል ነዳጆች ላይ ያለውን ጥገኝነት በመቀነስ፣ የኃይል ሉዓላዊነትን፣ ዘላቂነትን እና የኢኮኖሚ እድገትን ያመጣሉ ተብሎ እንደሚታመን እየተዘገበ ነው፡፡

ይህ የጀርመን ኢንቨስትመንት የፊሊፒንስን የኃይል ዘርፍ የሚያሻሽል ብቻ ሳይሆን፣ የዜጎችን የኑሮ ጥራት በማሻሻል፣ ለአካባቢ ተስማሚ የሆነ የወደፊት ጊዜን በመገንባት እና ኢኮኖሚያዊ ብልፅግናን በማምጣት የፊሊፒንስን ዕለት ተዕለት ኑሮ በከፍተኛ ሁኔታ ሊለውጠው ይችላል ተብሎለታል።
__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

ኢንሳ ድሮንን በመጠቀም ለትራንስፖርት ምቹ ባለሆኑ ቦታዎች ላይ ክትባቶችን እና ለግብርና የሚወሉ ኬሚካሎችን እያጓጓዘ መሆኑን ገለጸሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢንፎርሜሽን መረብ ደ...
01/07/2025

ኢንሳ ድሮንን በመጠቀም ለትራንስፖርት ምቹ ባለሆኑ ቦታዎች ላይ ክትባቶችን እና ለግብርና የሚወሉ ኬሚካሎችን እያጓጓዘ መሆኑን ገለጸ

ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ኢንሳ ለትራንስፖርት ምቹ ባለሆኑና በፍጥነት መድረስ የሚገባቸውን እንደ ክትባትና ለግብርና ስራ ጥቅም ላይ የሚዉሉ ኬሚካሎችን በድሮን በመታገዝ እያጓጓዘ መሆኑን ለመናኸሪያ ሬዲዮ አስታውቋል፡፡

ባለፉት ጊዜያት በሲዳማ እና በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን ለክትባት አገልግሎት የሚውሉ መድኃኒቶችን በድሮን በመታገዝ ማድረሱን የተናገሩት በኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የፕሮጀክት ሃላፊ አቶ ካሳ ጠና ናቸው፡፡

አሁን ላይ ለኬሚካል ርጭት የሚውሉ ከ50 እስከ 100 ሊትር የሚይዙ ድሮኖች በአስተዳደሩ እንዳሉና በተመሳሳይ መድኃኒትን ለማጓጓዝ አገልግሎት ላይ የሚውሉ እስከ 105 ኪሎ ሜትር ድረስ የሚጓዝ ድሮን መኖሩን በማመላከት በቅርቡም አገልግሎት መስጠታቸውን ተናግረዋል፡፡

በተለይ ሀገሪቷ ያላት የቆዳ ስፋት ከፍተኛ በመሆኑ ይህን አካሎ ተደራሽነት ያለው አገልግሎት ለመስጠትና እንዲሁም ከተቋማት ጋር በቅንጅት ለመስራት ምን ታስቧል ያልናቸው ኃላፊው በቀጣይ በስፋት ለመስራትና ከተቋማት ጋር የመቀናጀት እቅድ እንዳላቸዉም ጠቁመዋል፡፡

ምንም እንኳ በስፋት ስራውን ለመስራት አሁን ላይ ያሉ ድሮኖች በቂ ናቸው ባይባልም ፤ በቀጣይ ሀገሪቷ የድሮን ምርትን በሀገር ውስጥ ማምረት በመጀመሯ ለዚህ ዓላማ የሚውሉ ድሮኖች በስፋት ለማሰማራት መታቀዱንም አክለዋል፡፡

በተለይ አሁን ላይ ወቅቱ የክረምት ወቅት እንደመሆኑ መጠን በስፋት ለመስራት ድሮኖችን ለመጠቀም መታቀዱ ተመላክቷል፡፡
__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

በትግራይ ከሚካሄደዉ የምክክር ሂደት በፊት ልዩ ዉይይት ከወጣቶች ጋር እንደሚኖር ተጠቆመሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል የሚካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የምክክር ሂደ...
01/07/2025

በትግራይ ከሚካሄደዉ የምክክር ሂደት በፊት ልዩ ዉይይት ከወጣቶች ጋር እንደሚኖር ተጠቆመ

ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) በትግራይ ክልል የሚካሄደው የአጀንዳ ማሰባሰብ እና የምክክር ሂደት ከመጀመሩ አስቀድሞ ከክልሉ ወጣቶች ጋር ልዩ የውይይት መድረኮች እንደሚኖሩ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለመናኸሪያ ሬዲዮ አስታወቋል፡፡

የትግራይ ክልል ለሁለት ዓመታት በጦርነት ውስጥ በማለፉ እና አሁንም ከስብራትቱ ሙሉ በሙሉ ባለማገገሙ የክልሉ በርካታ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለተካዊ ጉዳዮች፣ በምክክር ሂደቱ በልዩነት የሚታይ መሆኑን ያነሱት የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሸን ቃል አቀባይ አቶ ጥበቡ ታደሰ፣ በምክክር ሂደቱ በተለይ የክልሉ ወጣቶች ልዩ ትኩረት እንደሚያስፈልጋቸው ተናግረዋል፡፡

በዚህም መሰረት የምክክር ሂደቱ ከመጀመሩ በፊት ከወጣቶች ጋር የተለያዩ የውይይት መድረኮች እንደሚዘጋጁ የጠቆሙት ቃል አቀባዩ፣ በክልሉ የሚገኙ ሌሎች የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር እንደሚደረገው ሁሉ፣ ወጣቶችም የራሳቸውን አጀንዳዎች እንዲሰጡ አስቻይ ሁኔታዎች እንደሚመቻቹ አመላክተዋል።

የክልሉ ወጣቶች ለሁለት ዓመታት በዘለቀው ጦርነት ውስጥ በግንባር ቀደምትነት የተሳተፉና ከፍተኛ የኑሮ ፈተናዎችን ያሳለፉ በመሆናቸው፣ የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ወጣቶች በጦርነቱ ሳቢያ የደረሰባቸውን ስነ ልቦናዊ እና ማህበራዊ ተፅዕኖ ተገንዝቦ፣ በምክክሩ ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ እንደ ትልቅ ግብዓት እንደሚወስደዉም ነው ያመላከቱት፡፡

በጦርነቱ ምክንያት ወደ ተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች እና ወደ ጎረቤት ሀገራት የተሰደዱ በርካታ ወጣቶች እና የማህበረሰብ ክፍሎች መኖራቸውን የገለጹት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አመራር አቶ ጣዕመ አረዶም፣ በክልሉም ሆነ በጎረቤት ሀገራት በሚገኙ የተፈናቃይ መጠለያዎች፣ ለእያንዳንዱ መጠለያ ጣቢያ ተወካይ እንዳለው ይናገራሉ፡፡

በመሆኑም በመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ የክልሉ ወጣቶች እና ሌሎችም የማህበረሰብ ክፍሎች በተወካዮቻቸው አማካኝነት ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ አጀንዳ እንዲያቀርቡ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ምቹ ሁኔታዎችን እያመቻቸ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

ይህም በጦርነቱ ሳቢያ የተፈናቀሉ ዜጎች አጀንዳቸውን ለማካተት እና የሀገራዊ ምክክሩ ሂደት ሁሉን አቀፍ እንዲሆን ለማስቻል ያለመ ነው ብለዋል፡፡ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ተፈናቃዮች ያጋጠሟቸውን ችግሮች፣ ስጋቶቻቸውን እና ለቀጣይ የሰላም ግንባታ እና እርቅ ሂደቶች ያላቸውን ሀሳብ ለምክክር ኮሚሽኑ እንዲያቀርቡ ከፌዴራሉ መንግስት ጋር ሰፋፊ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም ነው ያመላከቱት፡፡

ወጣቶችን እንዲሁም ተፈናቃይ የማህበረሰብ ክፍሎችን በሀገራዊ ውይይት ውስጥ ማካተት ከጦርነቱ በኋላ ለሚኖረው የሰላም እና የመረጋጋት ግንባታ አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ ያስችላል ተብሎ እንሚጠበቅም ተመላክቷል፡፡
__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

አስቶን ቪላ ቅጣት ላለማስተናገድ ሲሉ የሴቶች ቡድናቸውን ለመሸጥ ተገደዋልሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የነጥብ ቅጣት ላለማስተናገድ የሴቶች ቡድኑን የሰዋው ይህ ክለብ መነጋገሪያ እየሆ...
01/07/2025

አስቶን ቪላ ቅጣት ላለማስተናገድ ሲሉ የሴቶች ቡድናቸውን ለመሸጥ ተገደዋል

ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ)የነጥብ ቅጣት ላለማስተናገድ የሴቶች ቡድኑን የሰዋው ይህ ክለብ መነጋገሪያ እየሆነ ይገኛል።

የፕሪሚየር ሊጉ ትርፋማነት እና ይዘት ክፍፍል ወይም የPSr ህግጋቶችን በመጣሱ ምክንያት ከፍተኛ ስጋት ውስጥ ወድቆ የነበረው ክለቡ ከስብስቡ ውስጥ 1 ቁልፍ ተጫዋች የመሸጥ ግዴታ ውስጥ ወድቆ እንደነበር አይዘነጋም።

ታዲያ አሁን ክለቡ ከዚ ህግ ጋር ተጣጥሞ ለመሄድ በማሰብ ማስገባት የነበረባቸውን ገንዘብ የቡድኑን የሴቶች ቡድን ለመሸጥ በመገደድ በሰአቱ ምንም ተጨማሪ ቅጣት ከማስተናገድ መትረፋቸው ተገልጿል።

ለdaily telegraph ጋዜጣ የሚፆፉት ማት ሎው እና ሳም ዎለስ ቪላዎች የሴቶች ቡድናቸውን በ55 ሚሊዮን ፓውንድ መሸጣቸውን አረጋግጠዋል። ያንን ተከትሎ የበርሚንጋሙ ቡድን ቪላ ልክ እንደ ኤቨርተን እና ኖቲንጋም ፎረስት ሁሉ ከሚተላለፍ የነጥብ ቅጣት መትረፍ ችለዋል።

አምናም ኒውካስል ዩናይትድ የፈረንጆቹ ሰኔ 30 ቀን ከመድረሱ በፊት ኤሊየት አንደርሰን እና ያንኩባ ሚንቴህን ለኖቲንጋም ፍረስት እና ብራይተን በመሸጥ የነጥብ ቅጣት ከማስተናገድ መትረፋቸው አይዘነጋም።
__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

ቻይና ትንንሽ ድሮኖችን በአየር ላይ ማስወንጨፍ የሚችል አዲስ ድሮን ይፋ አደረገችሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ቻይና "ጂው ቲያን" (Jiu Tian) የተሰኘ አዲስ እና ኃይለኛ የጄት...
01/07/2025

ቻይና ትንንሽ ድሮኖችን በአየር ላይ ማስወንጨፍ የሚችል አዲስ ድሮን ይፋ አደረገች

ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ቻይና "ጂው ቲያን" (Jiu Tian) የተሰኘ አዲስ እና ኃይለኛ የጄት ድሮን ይፋ አድርጋለች።ይህ ድሮን ትንንሽ ድሮኖችን በአየር ላይ ማስወንጨፍ የሚችል ሲሆን፣ እንደ እውነተኛ የእናት መርከብ ያገለግላል ተብሎለታል።

ይህ ድሮን በAVIC (Aviation Industry Corporation of China) የተሰራ ሲሆን፤እስከ 10 ቶን የሚመዝን እና፣ ከቻይና ትልልቅ ሰው አልባ አየር ስርዓቶች አንዱ ነው ተብሎለታል።

እንዲሁም ድሮኖችን ለማስወንጨፍ የሚያስችል ሞጁላር "ሃይቭ ሞዱል" (Hive Module) የተገጠመለት እና ራዳር፣ የላቁ ሴንሰሮች እና የጦር መሳሪያ ማስቀመጫዎች አሉት ተብሎለታል።

በንድፉ የአሜሪካንን A-10 ዋርትሆግ (Warthog) እና OV-10 ብሮንኮ (Bronco) አውሮፕላኖችን ይመስላል የተባለ ሲሆን፤ ጂው ቲያን ለስለላ፣ ለጥቃት እና ለኤሌክትሮኒክስ ጦርነት ትልቅ አቅም ነው የተባለው፡፡
__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

ኤሎን ማስክ በትራምፕ ሪፐብሊካን "ትልቅ፣ ቆንጆ ሂሳብ" ላይ ትችታቸውን አጠናክረው ቀጥለዋልሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የስፔስኤክስ እና ቴስላ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤሎን ማስክ በት...
01/07/2025

ኤሎን ማስክ በትራምፕ ሪፐብሊካን "ትልቅ፣ ቆንጆ ሂሳብ" ላይ ትችታቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል

ሰኔ 24 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የስፔስኤክስ እና ቴስላ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኤሎን ማስክ በትራምፕ ሪፐብሊካን አስተዳደር የቀረበውን "ትልቅ፣ ቆንጆ ሂሳብ"("big, beautiful bill,") የተባለውን የህግ ረቂቅ በተመለከተ በX ገጻቸው ላይ ትችታቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል። ማስክ የህግ ረቂቁን "እብደት የተሞላበት ወጪ" ሲሉ የገለፁት ሲሆን፣ የመንግስትን የዕዳ ጣሪያ በ$5 ትሪሊዮን ከፍ እንደሚያደርገው በመግለጽ ስጋታቸውን አንጸባርቀዋል።

ማስክ በX ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ፣ "ይህ እብደት የተሞላበት ወጪ ነው! የዕዳ ጣሪያውን በ5 ትሪሊዮን ዶላር ማሳደግ እብድነት ነው።" ብለዋል። በተጨማሪም፣ ማስክ አሁን ባለው የፖለቲካ ሁኔታ እርካታ እንደሌላቸው በመግለጽ፣ አዲስ የፖለቲካ ፓርቲ ለመመስረት እንደሚያስቡ ፍንጭ ሰጥተዋል።

ይህ የኤሎን ማስክ ትችት የመጣው፣ በቅርቡ የሪፐብሊካን ፓርቲ ትልቅ የመንግስት ወጪዎችን የያዘ የህግ ረቂቅ ማቅረቡን ተከትሎ ነው። የህግ ረቂቁ ዝርዝር ይዘት እስካሁን በግልጽ ባይታወቅም፣ ማስክ ያነሷቸው ስጋቶች ግን በX ተጠቃሚዎች ዘንድ ከፍተኛ ውይይት አስነስተዋል።

አንዳንድ ተንታኞች፣ ማስክ በተደጋጋሚ በX ገጻቸው ላይ የፖለቲካ አስተያየቶችን ሲሰጡ መቆየታቸውን ሲገልጹ፣ አዲስ ፓርቲ የመመስረት ዛቻቸው ግን የፖለቲካ ገበያውን የማነሳሳት ዓላማ ያለው ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ።

ሌሎች ደግሞ፣ ማስክ በዩናይትድ ስቴትስ እየጨመረ የመጣውን የመንግስት ዕዳ እና የበጀት እጥረት በተመለከተ ያላቸውን ስጋት የሚያሳይ ነው ብለው እንደሚያምኑ እየተገለጸ ነው ።

ኤሎን ማስክ አዲስ ፓርቲ ለመመስረት የገቡትን ቃል በተግባር ላይ ያውሉ ይሆን የሚለው ጉዳይ እያነጋገረ ይገኛል፡፡
__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

 #ስፖርትአርሰናል ኤብሬቺ ኤዜን ለማስፈረም ንግግሮችን በይፋ ጀመረስኔ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሰሜን ለንደኑ ቡድን አርሰናል ፉክክሩን እየመራው የሚገኝ ቡድን ሲሆን ከተጫዋቹ ወኪ...
30/06/2025

#ስፖርት

አርሰናል ኤብሬቺ ኤዜን ለማስፈረም ንግግሮችን በይፋ ጀመረ

ስኔ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) የሰሜን ለንደኑ ቡድን አርሰናል ፉክክሩን እየመራው የሚገኝ ቡድን ሲሆን ከተጫዋቹ ወኪሎች ጋር የመጀመሪያ ንግግሮች ማድረጋቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ተጫዋቹን ለማግኘች መሟላት ያለባቸው መስፈርቶች ምንድን ናቸው የሚለው ማጣራታቸውን ለማወቅ ተችሏል።

ኤዜ በበርካታ ክለቦች እንዲፈለግ ያደረገውን እንቅስቃሴ በዚህ የውድድር ዘመን ከክ/ፓላስ ጋር እያሳለፈ ይገኛል።

አምና የክለቡ አጋሩ የነበረው ማይክል ኦሊሴ ወደ ባየርሙኒክ ማቅናቱን ተከትሎ...

ሙሉ ዘገባው እዚህ ይገኛል 👉 https://t.me/menaharia_fm

__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63

የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

  ቼልሲዎች ጆአዎ ፔድሮን ለማስፈረም ከስምምነት ላይ ደርሰዋልሰኔ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ይሄ ብራዚላዊ በብራይተን ቤት አመርቂ እንቅስቃሴን እያደረገ የሚገኝ ተጫዋች ነው። የስፔኑ...
30/06/2025



ቼልሲዎች ጆአዎ ፔድሮን ለማስፈረም ከስምምነት ላይ ደርሰዋል

ሰኔ 23 ቀን 2017(መናኸሪያ ሬዲዮ) ይሄ ብራዚላዊ በብራይተን ቤት አመርቂ እንቅስቃሴን እያደረገ የሚገኝ ተጫዋች ነው። የስፔኑ ጋዜጣ todo fijaes አርሰናል እና ቼልሲ ይህንን ተጫዋች ለማስፈረም ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸው መዘገቡ አይዘነጋም።

የአርሰናል ፍላጎት ከፍላጎት ሊዘል አልቻለም ፤ ቼልሲዎች ግን ጆአዎ ፔድሮ ላይ ያላቸውን ፍላጎት መሬት በማውረድ ተጫዋቹን ለማስፈረም እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ለማወቅ ተችሏል።

የ23 አመቱ ብራዚላዊ አጥቂ ሳቢሳዎቹን ከተቀላቀለ በኋላ አስደናቂ ጊዜን እያሳለፈ ይገኛል። ባጠቃላይ ባደረጋቸው 52 ጨዋታዎች 16 ጎል ሲያስቆጥር 9 ኳስ አመቻችቶ ማቀበል ችሏል። ይሄ ተጫዋች ባሳለፍነው ክረምትም ስሙ ከአርሰናል ጋር ሲያያዝ እንደነበር አይዘነጋም አሁን ግን የብሪጅ ቆይታው ጥያቄ ምልክት ውስጥ የወደቀው ኒኮላስ ጃክሰንን ሊተካ የሚችለው ተጫዋች ስለመሆኑ ለማወቅ ተችሏል። ጆአዎ ፔድሮ ሜዳ ላይ የሚለፋ እና ጥሩ የስራ ትጋት ያለው ከኳስ ጋም ከኳስ ውጪም ምቾት የሚሰማው ጥሩ አቅም ያለው ተጫዋች ነው።

የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ እግርኳስን በቀጣይ አመት የሚጫወቱት ቼልሲዎች ስብስባቸውን በዛ ደረጃ ዝግጁ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ።

ብራዚላዊው አጥቂ ወጥነት ባለው መልኩ ለፋቢያን ኸርዝለሩ ቡድን ግልጋሎት ሲሰጥ የቆየ ተጫዋች ነው። ጆአዎ ፔድሮ ወደ ትልቅ ክለብ ማቅናት የሚችልበት አቅም ላይ እንደሚገኝ ነው የሚያምነው ፤ ከዛ በተጨማሪ ተጫዋቹን የሚፈልጉት ቡድኖች ስብስብ ጥልቀት እና ጥራት መሰረት ያገደገው የዝውውር ፖሊሲአቸው ላይ የፊት ገጽ መሆን የሚችል አይነት ተጫዋች ነው።

ተመራጩ ደግሞ ጆአዎ ፔድሮ ሆኗል። ይሄን ተጫዋች ለማስፈረም ቼልሲዎች ወደ 69 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የሚያደርጉ ሲሆን እስከ 2032 በስታም ፎርድ ብሪጅ የሚያቆየውን ውል ይፈርማል ተብሎ ይጠበቃል።

ቼልሲዎች በዝውውር መስኮቱ በንቃት እና በስፋት እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ። እስካሁን የሊያም ዴላፕ እና የማማዱ ሳርን እና ዳሪዮ ኤሱጎ እና የጂሚ ጊትንስን ዝውውር ማጠናቀቃቸው የሚታወቅ ጉዳይ ነው።

__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63

የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

 #ትንታኔ ከኢራን ብሔራዊ የቀብር ስነስርዓት በስተጀርባ 👉 https://youtu.be/_KHk75lifcw  በትዕግስቱ በቀለ
30/06/2025

#ትንታኔ

ከኢራን ብሔራዊ የቀብር ስነስርዓት በስተጀርባ 👉 https://youtu.be/_KHk75lifcw

በትዕግስቱ በቀለ

ኢራን በእስራኤል ጥቃት ለተገደሉባት ወታደራዊ አዛዦቿ ብሔራዊ የቀብር ሥነ ሥርዓት አካሄደች፡፡ኢራን ለ12 ቀናት በዘለቀው የእስራኤል ግጭት የተገደሉ ወታደራዊ አዛዦች እና የኒውክሌር ....

ዳርፓ በ8.6 ኪ.ሜ ርቀት በሌዘር ገመድ አልባ ኃይልን በማስተላለፍ ሪከርድ ሰበረሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)የአሜሪካው የመከላከያ የላቀ የምርምር ፕሮጀክቶች ኤጀንሲ (DARPA) ...
30/06/2025

ዳርፓ በ8.6 ኪ.ሜ ርቀት በሌዘር ገመድ አልባ ኃይልን በማስተላለፍ ሪከርድ ሰበረ

ሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)የአሜሪካው የመከላከያ የላቀ የምርምር ፕሮጀክቶች ኤጀንሲ (DARPA) በገመድ አልባ ኃይል ማስተላለፍ ታሪክ መስበር ችሏል::

ኤጀንሲው 800 ዋት የሚሆን ኃይል በሌዘር አማካኝነት ከ8.6 ኪሎ ሜትር በላይ በማስተላለፍ አዲስ ሪከርድ አስመዝግቧል። ይህ በሰኔ 2025 በኒው ሜክሲኮ የተደረገው ሙከራ፣ የPOWER ፕሮግራማቸው አካል ሲሆን፣ ለ30 ሰከንዶች የዘለቀ እና ከ1 ሜጋጁል በላይ ኃይል አስተላልፏል ነው የተባለው። ይህ ቀደም ሲል የነበሩትን ሪከርዶች ሁሉ ያጠፋ ነው ተብሎለታል፡፡

ይህ ስኬት የረጅም ርቀት፣ ከፍተኛ መጠን ያለው ኃይልን በኃይለኛ ሌዘር እና በልዩ ተቀባይ (receiver) አማካኝነት ማስተላለፍ አሁን ተቻለ ማለት እንደሆነ ተመላክቷል። ይህም ኃይልን ያለ አካላዊ ግንኙነት (physical connections) በማስተላለፍ ረገድ ትልቅ እመርታ እንደሚያሳይ ተጠቁሟል፡፡

የዚህ ቴክኖሎጂ አንድምታዎች መካከል የኤሌክትሪክ መኪኖች እየነዱ እያሉ ወይም በመንገድ ላይ በሚቆሙበት ጊዜ ገመድ አልባ ኃይልን በመጠቀም ኃይል ሊሞሉ ይችላሉ ነው የተባለው። ይህም የባትሪዎችን መጠን እና የመሙያ ጊዜን በተመለከተ ያሉትን ገደቦች ሊቀንስ ይችላል ተብሎለታል።
__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ መመሪያን ሰረዘሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀደም ሲል ያወጣውን የገንዘብ ሚኒስቴር፣ ፋይናንስና አስተዳደር...
30/06/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ መመሪያን ሰረዘ

ሰኔ 23 ቀን 2017 (መናኸሪያ ሬዲዮ)የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ቀደም ሲል ያወጣውን የገንዘብ ሚኒስቴር፣ ፋይናንስና አስተዳደር ዲሬክቲቭ ቁጥር MFAD/TRBO/001/2022 “የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ መመሪያ” የሚለውን ሰርዟል። ይህ ውሳኔ ይፋ የሆነው ዛሬ ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም በፀደቀው “የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ (የመሻሪያ) መመሪያ ቁጥር MFAD/TBOND/002/2025” በተባለ አዲስ መመሪያ ነው።

አዲሱ መመሪያ “የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ (የመሻሪያ) መመሪያ ቁጥር MFAD/TBOND/002/2025” በሚል ርዕስ ይታወቃል።

👉የተሻረው መመሪያ: ከዚህ ቀደም የነበረው “የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ መመሪያ ቁጥር MFAD/TRBO/001/2022” ሙሉ በሙሉ ተሽሯል።

👉ጊዜያዊ ድንጋጌ: የሰኔ 2025 የግምጃ ቤት ቦንድ ምደባ (Treasury Bond allotments) በቁጥር MFAD/TRBO/001/2022 መመሪያ መሰረት ያልተገዙት ካሉ፣ አሁንም ተግባራዊ ሆነው ይቀጥላሉ። እነዚህ የግምጃ ቤት ቦንዶች ግዥ እ.ኢ.አ ከሐምሌ 15 ቀን 2025 ዓ.ም. በኋላ መፈፀም የለበትም ተብሏል።

ከዚህ መመሪያ ውጤታማ ቀን በፊት ወይም በአንቀጽ 3.1 በተጠቀሰው መሰረት የተሰጡ የግምጃ ቤት ቦንዶች በቁጥር MFAD/TRBO/001/2022 መመሪያ መሰረት መመራታቸውን ይቀጥላሉ ተብሏል።

ይህ መመሪያ እ.ኢ.አ ከሰኔ 30 ቀን 2025 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል። ይህ መመሪያ በብሔራዊ ባንክ ገዥ አቶ ማሞ እምሬለም ምህረቱ የተፈረመ ሲሆን፣ በሀገሪቱ የገንዘብና የፊስካል ፖሊሲ አፈፃፀም ላይ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።

ቀደም ሲል የነበረው የግምጃ ቤት ቦንድ ግዥ መመሪያ በባንኮች ላይ የተወሰኑ ግዴታዎችን ይጥል ነበር። የአዲሱ መመሪያ ዝርዝር አንድምታዎች እና በገበያው ላይ ሊያመጣ የሚችለው ተፅዕኖ ገና ግልጽ ባይሆንም፣ የፋይናንስ ተቋማት እና የኢኮኖሚ ባለሙያዎች የብሔራዊ ባንክን ቀጣይ እርምጃዎች በትኩረት የሚከታተሉ እንደሚሆን ይገመታል።
__

ሀሳብ እና'ሳ'ፍራለን

👉011-639-28-52
👉011-639-37-63
(https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)
የቀጥታ ስርጭት 👉 https://zeno.fm/radio/menahria-99-1-3pw1/ (https://stream.zeno.fm/yw8poig9iwtuv)

Telegram 👉 https://t.me/menaharia_fm

#መናኸሪያሬዲዮ #መናኸሪያኤፍኤም #ራዲዮ #ሬዲዮ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Menahria f.m 99.1 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Menahria f.m 99.1:

Share