27/08/2019
FBI/ኤፍ ቢ አይ/ እና የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት መረጃ ለመለዋወጥ ተስማሙ!
የብሔራዊ የመረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ደመላሽ ገብረሚካኤል እና የአሜሪካው የምርመራ ቢሮ ኤፍ.ቢ.አይ ምክትል ዳይሬክተር ቻርልስ ኬብል ኹለቱ ሃገራት የሽብርተኞችን መረጃ ለመለዋወጥ የሚያስችላቸውን ስምምነት ተፈራረሙ።
በኢትዮጲያ የአሜሪካን ኤምባሲ እንዳስታወቀው ነሐሴ 14/2011 በተደረገው ስምምነት በኹለቱ ሃገራት መካከል ያለውን የመረጃ ልውውጥ ስርአት የሚያበጅ እና ኹለቱም ሃገራት ሽብርተኝነትን ለመከላከል የሚያግዛቸው እንደሚሆንም ተገልጿል።
‹‹ስምምነቱ ኹለቱ ሃገራት ያላቸውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ከማጠናከር ባለፈ ሽብርተኝነት ለመከላከል ያግዛል እንዲሁም የሃገራቱን ደኅንነት ያረጋግጣል›› ኤምባሲው ገልጿል።
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ