Peace & Security Adminstration Office at Lideta W10

Peace & Security Adminstration Office at Lideta W10 For peace and security
control

01/01/2026

፨ሰላም ማለት ምን ማለት ነው?፨

ሰላም ማለት፡- በየትኛውም መልኩ ከማንኛውም ሰላምን ሊያውኩ ከሚችሉ ሁከትና ሌሎች ተግባራት፣ ከስጋት ሙሉ በሙሉ ነፃ ሆኖ መኖር ሲሆን ምንም እንኳን በሰላም ለመኖር ከጦርነት፣ ከሁከት፣ ከግጭትና ከብጥብጥ ወዘተ ከመሳሰሉት የሰላም ተፃራሪዎች ሁሉ ነፃ መሆን ቢሆንም
በአጠቃላይ የሰላም ፅንስ ሀሳብ ከግጭት ሙሉ በሙሉ ነፃ መሆን ማለት ሳይሆን በማንኛውም መልኩ ነፃ በሆነ መንገድ አለመግባባቶች ሲፈጠሩ አብሮ በሚኖረው ማህ/ሰብ መካከል በመተሳሰብ፣ በመደጋገፍ፣ በመወያየትና በመቻቻል በአንድነት መኖር መቻልና ችግሮች በሚፈቱበት ደረጃ ላይ ማድርስ መቻል ነው፡፡
፨የሰላም እሴት ምንድን ነው?
የሰላም እሴት ማለት የባህሪ የአመለካከት የአኗኗር ወዘተ የእሴቶች ስብስብና ዘይቤ ነው፡፡
የሰላም እሴት ከጦርነት ከአመፅ ከሽብር ወዘተ ከመሳሰሉት ባህሎች /ተግባሮች/እነዚህን ተግባራት ማንኛውንም ከሁከትና ብጥብጥ የሚጸየፍ የተፈጠሩ ግጭቶችን ሁሉ በውይይትና በመግባባት የመፋታት ባህል መሻጋገር ማለት ነው፡፡
👉ዜጎች አለመግባባትን በሰላማዊ ውይይትና ድርድር እንዲሁም ከማንኛውም ሁከት ነፃ በሆነ መልኩ መፍታት የሚቻልበትን ጥበብ ከተገነዘቡ፣ አሉታዊ የሆኑ ደንብና ስርዓቶችን ሲቀርፉ ሰላም መገንባታቸውን ያሳያል፡፡
👉ህ/ሰቡ በዘልማድ ከሚደነግገው የወንዶች የበላይነት ወደ ህገ-መንግስታዊ የፆታ እኩልነት የአመለካከት አድማሱን በማስፋት ግንዛቤውን ሲይዝ የሰላም ባህል ተሸጋጋሪ መሆኑን ያሳያል፡፡
👉በህ/ሰቡ (በዜጎች) ዘንድ የሚታዩ መከፋፈሎች ተቀርፈው አንድነት እና መተሳሰብ በዜጎችና በግለሰቦች ዘንድ ተፈጥሮ ሲታይ የሰላም እሴት ተምሳሌትን ያሳያል፡፡
👉በማንኛውም ወቅትና ጊዜ ዲሞክራሲያዊ ትግልና ተሳትፎ በነፃነት የመግለጽ ስርዓት በሰፊው ሲለመድ እና በህ/ሰቡ (በዜጎች) ሲተገበሩና ተቀባይነታቸው ሲጎለብት የሰላም እሴትን ያሳያሉ፡፡
👉ግልፀኝነትና ተጠያቂነት የሰፈነበት ግልጽ ግንኙነት ሲኖርና ዜጎች እንደ መርህ ወይም መመርያ ሲጠቀሙበት ማየት የሰላም እሴት ተምሳሌትን ያሳያል፡፡
👉 ሁሉም ሰው ሰብአዊ መብትን ማክበር የተለመደ ተግባር ሆኖ ሲታይ፣ መንግስት በህጋዊ መንገድ የዜጎችን ደንብና ስርዓት መሰረት ባደረገ መልኩ ስልጣንን በአግባቡ ሲጠቀም ማየት እና መገልገል የሰላም እሴትን ያሳያል፡፡
👉 መንግስት ኢ-ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ ስልጣንን ከማራዘም እና ከማጠናከር ይልቅ አለም አቀፋዊ ለሆኑ የዜጎች ህግና መብት መከበር ተሳትፎና ድጋፍ ሲያደርግ መመልከት የሰላም እሴትን ያመላክታል፡፡
👉 በዜጎች ደንብና ስርዓት ለውጥ ውስጥ እድገት ከገንዘብ እና ከሃብት አቅም ይልቅ ለማህ/ሰቡ ማህበራዊ፣ ኢኮኖማያዊና ፖለቲካዊ እድገትና ለውጥ በማተኮር ፍትሃዊና ዘላቂነቱ የተረጋገጠ አካባቢያዊ መስተጋብር ሲኖር የሰላም እሴት ያሳያል፡፡ በሌላ መልኩ የሰላም አደናቃፊዎች ደግሞ
1️⃣የግል አረዳድ
2️⃣የተዛባ ግላዊ ቅድመ ትንቢያ
3️⃣ አድሎአዊ አሰራር እና ማግለል
ነገሮችን አስቀድሞ አጠቃሎ ማየት ሲሆን ብዙውን ጊዜ የሰላምና የግጭት ትንተና እንደማሳያ ነው፡፡

ምንጭ፦ማህበራዊ ሚዲያ

በልደታ ክ/ከተማ የጂ+5 ፖሊስ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆናልበልደታ ክ/ከተማ የባልቻ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የጂ+5 ህንፃ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል።በማስጀመሪያ...
30/12/2025

በልደታ ክ/ከተማ የጂ+5 ፖሊስ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆናል

በልደታ ክ/ከተማ የባልቻ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ የጂ+5 ህንፃ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ዝግጁ ሆኗል።

በማስጀመሪያው ፕሮግራም ላይ ንግግር ያደረጉት የልደታ ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ልዕልቲ ግደይ እንደተናገሩት ባለፍት የለውጥ ዓመታት መንግስት ቅድሚያ ሰጥቶ ሲሰራባቸው ከነበሩ ተግባራት ውስጥ አንዱና መሰረታዊው ሰላምን ማረጋገጥ ነው ብለው በዚህም ሰላም አስተማማኝ፣ ፅኑና ጠንካራ የሚሆነው ህዝባዊ መሰረት ሲኖረው ነው በማለት የፀጥታ መዋቅሩና ማህበረሰቡ ተቀናጅተው የሚሰሩበትን አሰራር ዘርግቶ ሰላም እንዲሰፍን አድርጓል በማለት ገልፀዋል።

ሰላም ህዝባዊ መሰረት እንዲኖረው ከማድረግ ባለፈ ተቋሙን በአሰራር እና በአደረጃጀት በማዘመን ወቅቱን ያማካለ እንዲሆን ማድረግ ተችሏል ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚዋ በዚህም በሰላሟና በልማቷ የአለም አይኖች ያረፉባት የቱሪዝም ማዕከል የሆነች አዲስ አበባን እውን ማድረግ ተችሏል በማለት ገልፀዋል።

መንግስት በራስ አቅም ከሚሰራቸው ልማቶች በተጨማሪ የበጎ ፈቃደኛና ሀገር ወዳድ ባለሀብቶችን አቅም በመጠቀም የተለያዩ የልማት ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል ዋና ስራ አስፈፃሚዋ።

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ፍስሀ ጥበቡ እንደተናገሩት ከተማችን አዲስ አበባ ሰላሟ እና ደህንነቷ የተረጋገጠ ልማቷ የተፋጠነ እንዲሆን በትኩረት ሲሰራ ነበረ ብለው በዚህም በቆራጥ እና በጠንካራ ነዋሪዎቿና የፀጥታ መዋቅር ሰላሟን አስተማማኝ ማድረግ ተችሏል ሲሉ ተናግረዋል።

ከተማችን በተፈጠረው ሰላም የተለያዩ ስብሰባዎች የሚደረጉባትና የቱሪዝም መዳረሻ ሆናለች ያሉት አቶ ፍስሀ ይህንን ሰላም አጠናክሮ ለማስቀጠል መንግስት ምቹ ሁኔታን እየፈጠረ አሰራርን ደግሞ እያዘመነ ይገኛል በማለት ገልፀዋል።

የልደታ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ያሲን ሁሴን በበኩላቸው ዛሬ የተመረቀው ፖሊስ ጣቢያ እጅግ ታማኝ ሆነን የተሰጠንን ኃላፊነት በላቀ ትጋት
እንድንፈፅም ያስችላል በማለት ገልፀዋል።

የልደታ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ቶሎሳ ድሪባ እንደተናገሩት የበለፀገች ኢትዮጲያን እውን ለማድረግ አንዱና ዋነኛው የፀጥታ ተቋም ግንባታ ነው ብለው በዚህም አሰራሩን ማዘመን እና ምቹ የስራ ቦታ የመፍጠር ስራ እየተከናወነ ነው መሆኑን ተናግረዋል።

የአያት ሪልስቴት ባለቤት አቶ አብይ ማሞ በበኩላቸው ህንፃውን ገንብተን ያስረከብነው ማህበራዊ ኃላፊነታችንን ለመወጣት ነው ብለው በቀጣይም አጠናክረን እንቀጥላለን በማለት ገልፀዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ከማእከል እስከ ወረዳ የሚሰጡ ዋናና ዝርዝር አገልግሎቶች፤
29/12/2025

በአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ከማእከል እስከ ወረዳ የሚሰጡ ዋናና ዝርዝር አገልግሎቶች፤

10/12/2025
በቀን:-15/03/2018 ዓ.ምየሠላም ሰራዊት በየቀጠናው ስምሪት በመውሰድ አካባቢውን በንቃት እየጠበቀ ይገኛል።
25/11/2025

በቀን:-15/03/2018 ዓ.ም
የሠላም ሰራዊት በየቀጠናው ስምሪት በመውሰድ አካባቢውን በንቃት እየጠበቀ ይገኛል።

በቀን:-15/03/2018 ዓ.ም #በኢትዮጵያዊ ማንነትና ባህል የተገራ ትውልድ በመገንባት ሂደት የሠላም ምክር ቤት ማና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሠላምና ጸጥታ አስ...
25/11/2025

በቀን:-15/03/2018 ዓ.ም
#በኢትዮጵያዊ ማንነትና ባህል የተገራ ትውልድ በመገንባት ሂደት የሠላም ምክር ቤት ማና ከፍተኛ መሆኑ ተገለፀ።

የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሠላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በሠላም ምክር ቤት እና የሠላም ሠራዊት አደረጃጀት መመሪያ በማስመልከት ለጸጥታ አስከባሪ አካላት፣ ለሰላም ሰራዊት አባላት፣ ለቅጥር ጥበቃ እና ለሰላም ምክር ቤት ስራ አስፈፃሚ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል።

በስልጠናው የከተማ አስተዳደሩ ደረቅ ወንጀሎችን ለመከላከል፣ የህዝቦችን አብሮነት ለማጠናከር፣ በሠላምና ጸጥታ ዙሪያ የህዝቡን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማጎልበት እና አዲስ አበባን የሠላም ተምሳሌት ለማድረግ ከተፈጠሩ አደረጃጀቶች የሠላም ምክር ቤት እና የሠላም ሠራዊት ዋነኞቹ መሆኑ ተገልጿል።

ሁለቱም አደረጃጀቶች የጸጥታ አስከባሪ አካላት አጋዥ ከመሆን ባለፈ በልማት፣ በመልካም አስተዳደር እና በሰው ተኮር ተግባራት ግንባር ቀደም ተሳታፊ በመሆን እየሰሩ እንደሆነ ተነስቷል።

የሠላም ሰራዊት እና የሠላም ምክር ቤት አደረጃጀት የተቀያየሙትን ከማስታረቅ ባሻገር በኢትዮጵያዊ ማንነትና ባህል የተገራ ትውልድ ለመገንባት ከፍተኛ አስተዋፅዎ ኢያበረከቱ መሆኑ ተገልጿል።

የሠላም ሠራዊቱ ስምሪት በየቀጠናው ተጠናክሮ ቀጥሏል።
20/11/2025

የሠላም ሠራዊቱ ስምሪት በየቀጠናው ተጠናክሮ ቀጥሏል።

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር "ሀገር በቀል የሠላምና መቻቻል ዕሴቶች ለትውልድ ግንባታ" በሚል መርህ በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ ውይይት አካሂዷል በቀን:-28/02/20...
07/11/2025

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር "ሀገር በቀል የሠላምና መቻቻል ዕሴቶች ለትውልድ ግንባታ" በሚል መርህ በተዘጋጀው ሰነድ ዙሪያ ውይይት አካሂዷል

በቀን:-28/02/2018 ዓ.ም

 #የሰላምና የፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት፣የ2018 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድና የአንደኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ከባለድርሻ አካላት ጋር ው...
01/11/2025

#የሰላምና የፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት፣የ2018 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድና የአንደኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደረገ

በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 የሰላምና ፀጥታው አስተዳደር ጽ/ቤት የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2018 በጀት መሪ ዕቅድና የአንደኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አደርጓል።

የ2017 ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት፣ የ2018 መሪ ዕቅድና የአንደኛ ሩብ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቧል።

የወረዳው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጣሂር አማን እንደገለፁት በ2017 በጀት ዓመት መላው የፀጥታ መዋቅሩን በማቀናጀት የወረዳውን ሰላምና ደህነት ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎችን መስራቱን ገልፀው፤በዚህም የተሻለ ውጤት መምጣቱን ገልፀዋል፤ በ2018 በጀት ዓመትም ጥንካሬዎቻችን ማስቀጠል የሚያስችልና ክፍተታችንን ለመሙላት የሚያስችል ዕቅድን በማቀድ ወደ ተግባር ገብተናል ሲሉ አንስተው ፤በ በዚህም በርካታ ስኬታማ ስራዎችን ሰርተናል፤ ህብረተሰቡ የሰላሙ ባለቤት እንዲሆን በማድረግ የተለያዩ ትልልቅ ሁነቶች ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ ማለፍ መቻሉ አንስተዋል፤ ጽ/ቤቱ የሪፎርም ስራ እየሰራ እንደሚገኝና በቀጣይም የተሻሉና ይበልጥ ለህብረተሰቡ ተደራሽ የሚሆኑ ስራዎችን ለመስራት ያስችለናል ብለዋል።

በቀረበው ዕቅድና ሪፖርት ላይ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎችና ሀሳቦች የተነሱ ሲሆን በመድረኩ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል።

📸ልደታ ወረዳ 10 ኮሙኒኬሽን
ጥቅምት 21/2018ዓ.ም

 #ስለሰላም ምክር ቤት ስልጣንና ተግባር ዙሪያ ለስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ግንዛቤ ተሰጠ።  የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር...
22/10/2025

#ስለሰላም ምክር ቤት ስልጣንና ተግባር ዙሪያ ለስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ግንዛቤ ተሰጠ።

የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላትን እንደገና ለማደራጀት፣ስልጣንና ተግባራቸውን ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 64/2011 አንቀፅ 94 ንዑስ አንቀፅ /2/ መሠረት ለስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ስለደንቡ ገለፃ ተሠጥቷል።

ሰላም ምክር ቤቱ ዓላማ፦የም/ቤቱ አባላት ወደ ሕብረተሰቡ በመውረድ የአካባቢያቸውን ሠላም ደህንነት ህዝቡን በባለቤትነት እንዲሳተፍ ማድረግ፣ሁከትና ብጥብጥ የሚጠየፍና ግጭቶችን ያለመግባባቶችን በውይይት የሚፈታ መልካም ዜጋ ማፍራት መሆኑ ተገልጿል።

በቀጣይ ስለ አዋጁ ስልጠና እንዲሰጥና ጠቅላላ ጉባኤ እንዲካሄድ አቅጣጫ አስቀምጠዋል።

ልደታ ወረዳ 10 ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት
ጥቅምት 11/2018ዓ.ም

በቀን 15/01/2018 "የአደባባይ በዓላት በአብሮነት ደምቀን በህብር ከፍ የምንልባቸው የጠንካራ አንድነት መገለጫ እሴቶቻችን ናቸው" በሚል መሪ ቃል የሃይማኖት አባቶች የከተማ፥የክፍለ ከተማ...
25/09/2025

በቀን 15/01/2018 "የአደባባይ በዓላት በአብሮነት ደምቀን በህብር ከፍ የምንልባቸው የጠንካራ አንድነት መገለጫ እሴቶቻችን ናቸው" በሚል መሪ ቃል የሃይማኖት አባቶች የከተማ፥የክፍለ ከተማ፥ የወረዳ አመራሮች ባለሙያዎች እና ምዕመናን በተገኙበት በልደታ ቤተክርስቲያን የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ፡፡

 !!==========================🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር በወረዳው የሚገኙ የሰላም ሰራዊቶች በ...
24/09/2024

!!
==========================
🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹🌼🇪🇹
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳደር በወረዳው የሚገኙ የሰላም ሰራዊቶች በሁሉም ብሎኮች ስምሪት በመውሰድ አካባቢያቸውን በንቃት እንዲጠብቁ በአንድ ማዕከል ስምሪት ተሰጥቷል ።

በስምሪቱ ላይ የክፍለ ከተማ ደጋፊ አመራሮችን እንዲሁም የወረዳው፣አስተባባሪ ኮሚቴና የብሎክ ደጋፊ አመራሮች የተገኙ ሲሆን የሰላም ሰራዊት አባላት ከፀጥታ ኃይሉ እና ከአስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት በየዕለቱ አካባቢያቸውን ለመጠበቅ የሚሰሩት ስራ የሚበረታታ መሆኑ ተገልጿል።

የሰላም ሰራዊቱ በተደራጀ አግባብ በየአካባቢው የሚስተዋሉ የፀጥታ ችግሮችን አስቀድሞ ለመከላከልና አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ከሚመለከታቸው የአስተዳደር አካላትና ከፀጥታ መዋቅር ጋር የሠላም ሰራዊቱ በቅንጅት እየሠራ ይገኛል።

#ለሀገር ሰላም የድርሻዬን እወጣለሁ!

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Peace & Security Adminstration Office at Lideta W10 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category