Gamo nation

Gamo nation Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo nation, Digital creator, Addis Ababa.
(2)

  😍😍😍
13/04/2026

😍😍😍

ጋሞ ጚንቻ ወደ ኢትዮጵያ ፕ/ሊግ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ማደጉን ተኚትሎ አሁን በጚንቻ ኹተማ ያለው ዚህዝቡ ድባብ🀗
13/04/2026

ጋሞ ጚንቻ ወደ ኢትዮጵያ ፕ/ሊግ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ማደጉን ተኚትሎ አሁን በጚንቻ ኹተማ ያለው ዚህዝቡ ድባብ🀗

ጋሞ ጚንቻ እግር ኳስ ክለብ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚዚር ሊግ አደገ ።
13/04/2026

ጋሞ ጚንቻ እግር ኳስ ክለብ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪሚዚር ሊግ አደገ ።

ዚተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ተቃወመ ሚስቱ እና ቀተሰቊቹ ፊታ቞ውን አዞሩበት!ዚቀድሞ ዚቺካጎ ቡልስ ጋርድ ጃደን ኢቪ ፓስተር ለመሆን ኚቅርጫት ኳስ አለም ራሱን ሊያገል ነው።ጃደን እግዚአብሄር እ...
10/04/2026

ዚተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትን ተቃወመ ሚስቱ እና ቀተሰቊቹ ፊታ቞ውን አዞሩበት!

ዚቀድሞ ዚቺካጎ ቡልስ ጋርድ ጃደን ኢቪ ፓስተር ለመሆን ኚቅርጫት ኳስ አለም ራሱን ሊያገል ነው።

ጃደን እግዚአብሄር እንዳገለግለው እዚጠራኝ ነው ብሏል።

በቅርቡ ጃደን ለግብሚሰዶማዊያን ተብሎ ዹሚኹበሹውን Pride Month ተቃውሞ አስተያዚት ሰጠ።

ጃደን ኢቪ"ዓለም ዚተመሳሳይ ፆታ ጋብቻን ያውጃል? ዚኩራት ወር ብለው ይጠሩታል። ለዓለም ሁሉ ያሳዩታል። በዚመንገዱ እና በዚቢልቊርዱ ያስተዋውቃሉ። ክፋትን ለማክበር ዚኩራት ወራቜንን ተቀላቀሉ ይላሉ። ይሄ ክፋት ነው" ሲል ተናገሚ።

ብዙም ሳይቆይ ቺካጎ ቡልሶቜ ጃደን ኢቪን ኚስብስባ቞ው ቀነሱት። እስኚ አመቱ ማብቂያ ደሞዙን ቢያገኝም በቀዩ ማሊያ ሲጫወት ግን አንመለኚተውም።

ይባስ ብሎ ኚትናንት በስቲያ ግብሚሰዶማያዊያንን በመቃወሙ ብቻ ዹገዛ ባለቀቱ ካትሊን ሳይቀር ፊቷን አዙራበታለቜ። በይፋ ኚባለቀ቎ ጋር ያለኝ ግንኙነት ተቋርጧል ብሏል።

ኢቪ ሶስት ልጆቜ ኚሰጠቜው ሚስቱ በተጚማሪ ቀተሰቊቹም እያገለሉት እንዳሉ ተናግሯል።

ምን ሀሳብ አላቹ?

ገነት ንጋቱንና አንተነህ ተኾርቁን በተመለኹተ.. አርቲስት ገነት ንጋቱና አቶ አንተነህ ተኾርቁ ዚተባሉት ግለሰቊቜ በነበራ቞ዉ ቃለ መጠይቅ ስላሉት ፓስተር መሹጃ እንዳለና በዉስጥ ዚተፃፃፉትፀ ...
09/04/2026

ገነት ንጋቱንና አንተነህ ተኾርቁን በተመለኹተ..

አርቲስት ገነት ንጋቱና አቶ አንተነህ ተኾርቁ ዚተባሉት ግለሰቊቜ በነበራ቞ዉ ቃለ መጠይቅ ስላሉት ፓስተር መሹጃ እንዳለና በዉስጥ ዚተፃፃፉትፀ ታዋቂ ፓስተር እንደሆነና ሌሎቜ ነገሮቜን በመጥቀስ ተናግሚዋል። ዉሞት ኹመሆኑ ባሻገር ይህ ቢሆን ባይሆን ምንም አይጠቅምም!

ያለዉን ሰዉዬ ቢጠቁም እንደ ማሕበሚሰብፀ እንደ ሕዝብ እንደ ቀተ ክርስቲያን እንድናዉቅ እንጂ በራሱ ወንጀል ሆነ ማለት አይደለም። ይህን ሰዉ ነፃ ያደርገዋል ማለት አደለም!! ማስሚጃ ያለዉን ቢያቀርብ እንኳ!

ዚፓስተሩን ስም ቢጠቅስ ስሜ ጠፋ ሲል ፓስተሩ በግል ዚሚያስኚብሚዉ መብት እንጂ ሌላ አካል ዹሚጠይቀዉ አይደለም። ስለዚህ በድርሰት ያሰናዱት ዚስም ማጥፋት ቢሆንም ዚአንድ ፓስተር ስም ቢጠቅሱ ዚሚያተርፋ቞ዉ አደለም።
አንድ ሰዉ ግብሚሰዶም እንድፈጜም ጠይቆኛል ማለት በራሱ ወንጀል አደለም። ዹፈጾመ ወይም ዹሞኹሹ ነዉ ዹሕጉ ቋንቋ! ስለዚህ አንድ ሰዉ ግብሚ ሰዶማዊ ነዉ ማለት ወይም በራሱ ወንጀል ማለት አደለም! ዹሕጉን ነዉ እያወራናቜሁ ያለዉ! መፈጾም ወይም ሲፈጜሙ መገኘትፀ መሞኹር ነዉ ወንጀል! በሌላ ሁኔታም ሆነ በፈቃድ መፈጾም ነዉ ወንጀል! (ኚታቜ በልጥፎቹ ይመልኚቱ)

ስለዚህ ግለሰቡን ጠቁም አትጠቁም ዹሚለዉ ሃሳብ ምንም ስለማይጠቅም ለክርክር ባይቀርብ መልካም ነዉ። b/c በዚህ ዉስጥ ፓስተሩ ይሄኛዉ ነዉ ቢልና ዚአንዱን ስም ቢጠቅስ ግለሰቡና አቅራቢዋ በሕግ ላይጠዹቁ ነዉ ማለት ነዉ? ስለዚህ ኹጠቀሰ እንዲሁ ለማወቅ መልካም ቢሆንም ለሕግና ኹዚህ ኚተያዘዉ ጉዳይ ጋር ግን እነሱን ነፃ ለማዉጣት አይጠቅምም!! እነሱ ዚፈጞሙት ወንጀል ኃይማኖቱን እንጂ በግለሰብ ላይ ዚፈጞሙት አደለም! በገነት ንጋቱና በአንተነህ ዹተደሹሰዉ ምልልስ በራሱ ነዉ ወንጀል ዹሆነዉ!

ሌላዉ ነገር በዉስጥ ዹተፃፃፍነዉ ምናምን ዹሚለዉ ያ እነሱን ነፃ ለማድሚግ በሕግ ተቀባይነት ያለዉ ማስሚጃ አይደለም። ዹተፃፃፍነዉን á‹­á‹€ ነዉ ዚተናገርኩት ቢልም በሕግ ሚገድ ማስሚጃ አይሆንም። እንደ መኚላኚያ ሆኖ ቢቀርብ እነሱን ለማዳን ቅቡልነት ዹለዉም! ግለሰቡ ራሱ በዉስጥ እያወራዉ ዹነበሹ ቢሆን እንኳ እሱ ስለመሆኑ ማስሚዳት አይቻልም። ካለመቻሉ ባለፈ ራሱ አዉርቶት ቢሆን እንኳ ኚማዉራት ዹዘለለ ወንጀል ዹተሞኹሹ ነገር በሌለበት ግብሚሰዶማዊ ስለነበሚ ነዉ ያወራዉና ሕግ እነኚህን ነፃ አድርጎ ያኛዉን ይቀጣዋል ያስጠይቀዋል ማለት አደለም። ባይሆን ዚላካ቞ዉን ግለሰብም ይሁን ተቋም ይንገሩን!
እንዲ ኹሆነማ ያወሩት ነገር ትክክል ነዉ ነበሹ ዚጎንጀ ፓስተሮቜ ያደርጋሉ ብሎ እንደማገዝ እንደማስተባበል ዹሚቆጠር ነዉ ዚሚሆነዉ። ስለዚህ ማስሚጃ ዚፓስተር ስም ይጥቀስ ገለመሌ ኹሚለዉ አስተያዚት መዉጣት ያስፈልጋል። ቢያቀርብም ነፃ አያደርጋ቞ዉምና!

በመሆኑም ግለሰቊቹ በወንጌል አማኙ ማሕበሚሰብ ላይ ዚጥላቻና ዚነቀፌታን ስም ለመቀባት ያደሚጉትን ወንጀል በተመለኹተ ሌላ ግለሰብ ፓስተር አለ ሲሉ ጠቆሙ አልጠቆሙም አሁን ኚተያዘዉ ጉዳይ ጋር ዚሚያገናኘዉ አንዳቜም ዹሚፈይደዉ ነገር ዹለም!!
ዓላማቾዉ ዚቀተ እምነታቜንንፀ ዹአማኙን ስም ማጥፋት ነዉና በዚሁም ለሌሎቜ ጭምር ማስተማሪያ እንዲሆኑ በሕግ አግባብ ሂደቱ ቀጥሎ ለጥፋታ቞ዉ ተገቢ ዹሆነ ቅጣት እንዲያገኙ ማድሚግ አግባብ ነዉ ዹሚሆነዉ!

ግለሰቡ ታማሚ ነኝ ለሚለዉ በአሁኑ ሰዓት ማሚሚያ ቀቶቻቜን ኚቀድሞ በተሻለ ሕክምና ዚሚሰጥባ቞ዉፀ በአገር ዉስጥ ደሞ እስኚ ኹፍተኛ ሆስፒታል ሕክምና ለሚያስፈልጋ቞ዉ እንዲያገኙ በማድሚግ ዘምነዋልና በዚያ ሚገድ ስጋት አይግባዉ! እንዲህ ተብሎ ኹሕግ ተጠያቂነት ማምለጥ አይቻል

ስም በማጠልሞታ቞ው ክ ስ  ተመሰሚተባ቞ው! ***ዚኢትዮጵያ ወንጌል አማኞቜ አብያተክርስቲያናት ካውንስል፣ በወንጌል አማኝ ክርስቲያኖቜ እና ተቋማት ስም ላይ ጥላሞት ዚሚቀቡ አካላትን በህግ ለመ...
09/04/2026

ስም በማጠልሞታ቞ው ክ ስ ተመሰሚተባ቞ው!
***
ዚኢትዮጵያ ወንጌል አማኞቜ አብያተክርስቲያናት ካውንስል፣ በወንጌል አማኝ ክርስቲያኖቜ እና ተቋማት ስም ላይ ጥላሞት ዚሚቀቡ አካላትን በህግ ለመጠዹቅ ዚመጀመሪያውን እርምጃ መውሰዱን አስታወቀ።

ካውንስሉ ክ ሱ ን ዹመሰሹተው

* በወ/ሮ ገነት ንጋቱ እና
* በአቶ አንተነህ ተኾርቁ መካኚል በተደሹገ ቃለ-መጠይቅ ዙሪያ ነው።

በቃለ-መጠይቁ ላይ ዚቀሚቡት ሃሳቊቜፊ

* ለእምነቱ ተኚታዮቜ ካላ቞ው ጥ ላ ቻ ዚመነጩ ና቞ው።

* ዹወንጌል አማኞቜን መንፈሳዊ ገጜታና ክብር ዹ ሚ ያ ጎ ድ ፉ ና቞ው።

* ማንነታ቞ው በግልጜ ያልተጠቀሰ ግለሰቊቜን በጅምላ በ መ ወ ን ጀል ዚእምነቱን ተኚታዮቜ ገጜታ ዹ ሚ ያ በ ላ ሹ ናቾው ብሏል::

ካውንስሉ ባወጣው መግለጫ፣ ግለሰቊቹ ያሰራጩት መሹጃ በማስሚጃ ያልተደገፈና ሆን ተብሎ ዚቀተክርስቲያንን ስም ለማጠልሞት ዹተደሹገ ተግባር መሆኑን ገልጿል። በመሆኑም ጉዳዩን ወደ ህግ በመውሰድ በይፋ ክ ስ መመስሚቱን አሚጋግጧል።

ኹዚሁ ጋር ተያይዞ ካውንስሉ ዚሚኚተሉትን ጥብቅ ማሳሰቢያዎቜ አስተላልፏል፡-

1.በተለያዩ ዚማህበራዊ ሚዲያ መድሚኮቜ ሙያዊ ስነ-ምግባርን ባልተኚተለ መልኩ ዚእምነት ተኚታዮቜን ገጜታ ዹ ሚ ያ በ ላ ሹ ስራዎቜ እንዲቆሙ።

2.ዚነፃነት ድንበርን በማለፍ ዚእምነት ተቋማትን ክብር ዚሚነኩ አካላት ኚድርጊታ቞ው እንዲቆጠቡ፣ ካልሆነ ግን ተመሳሳይ ዹህግ እ ር ም ጃ እንደሚጠብቃ቞ው አስገንዝቧል።

Via ዚኢትዮጵያ ወንጌል አማኞቜ አብያተክርስቲያናት ካውንስል
"ዹወንጌል አማኞቜ ድምጜ!"

✍ጉርሻ page🌎🌎🌎

ዚነዳጅ አቅርቊት ጫና ለመቋቋም መንግስት ያሳለፈውን ውሳኔ መሰሚት በማድሚግ ምርትን በፍትሐዊነት እያኚፋፈልን ነው-ዚነዳጅ ማደያዎቜ አዲስ አበባፀመጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)ፊዚመካኚለኛው ምስ...
05/04/2026

ዚነዳጅ አቅርቊት ጫና ለመቋቋም መንግስት ያሳለፈውን ውሳኔ መሰሚት በማድሚግ ምርትን በፍትሐዊነት እያኚፋፈልን ነው-ዚነዳጅ ማደያዎቜ

አዲስ አበባፀመጋቢት 27/2018 (ኢዜአ)ፊዚመካኚለኛው ምስራቅ ወቅታዊ ሁኔታን ተኚትሎ ዚነዳጅ አቅርቊት ጫና ለመቋቋም መንግስት ያሳለፈውን ውሳኔ መሰሚት በማድሚግ ምርትን በፍትሐዊነት እያኚፋፈሉ እንደሚገኝ ዚነዳጅ ማደያዎቜ ገለጹ።

ዚኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) በአዲስ አበባ ዚተለያዩ ዚነዳጅ ማደያዎቜ ባደሚገው ቅኝትፀ ማደያዎቹ ዚሚራገፈውን ነዳጅ በፍትሐዊነት ለተጠቃሚዎቜ እያኚፋፈሉ እንደሚገኙ ተመልክቷል።

ዚመካኚለኛው ምስራቅ ግጭትን ተኚትሎ በርካታ ዹዓለም ሀገራት በነዳጅ አቅርቊት ላይ ዹተፈጠሹውን መስተጓጎል ለመቋቋም ጥብቅ ዚቁጠባ መመሪያዎቜን በማውጣት ላይ ይገኛሉ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ፊ በወቅታዊ ሁኔታው ሳቢያ በነዳጅ አቅርቊት ሰንሰለት ላይ ዹተፈጠሹውን ቜግር ለመቋቋም ዜጎቜ ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀሙ ማሳሰባ቞ው ይታወቃል።

ይህንንም ተኚትሎ ዚንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስ቎ር ዚአቅርቊት ሰንሰለቱን በቁጠባና በጥብቅ ቁጥጥር መምራት ዚሚያስቜል ዹተፅዕኖ መቋቋሚያ ውሳኔዎቜን አስተላልፏል።

ዚንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትሩ ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር)፥ ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ይፋ እንዳደሚጉትፀበነዳጅ አጠቃቀም ሚገድ ለሚኚተሉት ዘርፎቜ ቅድሚያ እንዲሰጥ መመሪያ ተላልፏል፩

በዚህም መሠሚት ፊ
👉ነዳጅ ዚሚያጓጉዙ ተሜኚርካሪዎቜ በማደያ ዚቅድሚያ ቅድሚያ እንዲሰጣ቞ው

👉ኚፍተኛ አምራቜና ዚኀክስፖርት ድርጅቶቜ በቀጥታ ፣

👉ልዩ ትኩሚት ዚሚሹ ዚመንግሥትና ዹግል ፕሮጀክቶቜ በቀጥታ፣

👉ዚገቢና ወጪ ንግድን ጚምሮ መሠሚታዊ ዚፍጆታ ምርቶቜን ዚሚያጓጉዙ ተሜኚርካሪዎቜ

👉ግብርናን ዚሚያዘምኑ ትራክተሮቜ፣

👉ዚኚተማና ሀገር አቀፍ ዚብዙሃን ትራንስፖርት ተሜኚርካሪዎቜ

👉እንዲሁም በናፍጣ ዚሚሰሩ ሌሎቜ ለህብሚተሰብ አገልግሎት ዚሚሰጡ ተሜኚርካሪዎቜ በቅድሚያ እንዲያገኙ ዚሚያደርግ ዚቅድሚያ ዚነዳጅ አጠቃቀም አሠራር ዹሚተገበር መሆኑን መግለፃቾው ይታወቃል።

ዹገርጂ ኖክ ነዳጅ ማደያ ሥራ አስኪያጅ መልካሙ ሲያልፍ ለኢዜአ እንደገለጹትፀ ማደያው በመንግሥት ዚወሚዱ መመሪያዎቜን በአግባቡ በመተግበር ላይ ይገኛል።

በተለይም ቅድሚያ እንዲሰጣ቞ው ለተወሰነላቾው ድርጅቶቜ ሕጋዊነታ቞ውን በማሚጋገጥ አገልግሎት እዚሰጡ መሆኑን ገልጞዋል።

በካዛንቺስ ዹኩላ ነዳጅ ማደያ ሠራተኛ መሰሚት ወንድም በበኩላ቞ውፀ ለኅብሚተሰቡና ለሀገር ልማት ወሳኝ ለሆኑ አካላት በወጣው አሠራር መሠሚት እያቀሚቡ መሆኑን አብራርተዋል።

ዚሰባራ ባቡር ቶታል ነዳጅ ማደያ ሱፐርቫይዘር ባዬ መኮንንፀነዳጅን ኚባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት በፍትሐዊነት እያኚፋፈሉ እንደሚገኝ ተናግሚዋል።

ሚኒስ቎ሩ ኅብሚተሰቡ ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀም፣ዚታዳሜ ኃይል አማራጮቜን እንዲኚተልና ዚእግር ጉዞ ባህልን እንዲያጎለብት ጥሪ አቅርቧል።

በተጚማሪም ዚሕዝብ ትራንስፖርትን በመጠቀምና በነዳጅ ግብይት ላይ ዚሚስተዋሉ ሕገ-ወጥ ተግባራትን በማጋለጥ ሚገድ ዜጎቜ ኚመንግሥት ጋር ተባብሚው እንዲሠሩ ማሳሰቡ ይታወሳል።

ዚማደያዎቹ ዚሥራ ኃላፊዎቜም በመካኚለኛው ምስራቅ ዹተፈጠሹው ዹሰላም መደፍሚስ በሀገር ላይ ዹሚኖሹውን አሉታዊ ጫና ለመቀነስ ሁሉም ሰው በኃላፊነት ስሜትና በትዕግሥት ሊንቀሳቀስ እንደሚገባ አሳስበዋል።

#ኢዜአ

በአዲስ አበባ በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዚሺሻ ማስጚሻ ቁሶቜ በቁጥጥር ስር ውለው ተወገዱአዲስ አበባ | መጋቢት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በቩሌ ክፍለ ኹተማ በተለያዩ...
05/04/2026

በአዲስ አበባ በሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዚሺሻ ማስጚሻ ቁሶቜ በቁጥጥር ስር ውለው ተወገዱ

አዲስ አበባ | መጋቢት 27 ቀን 2018 ዓ.ም ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ በቩሌ ክፍለ ኹተማ በተለያዩ ወሚዳዎቜ ሲካሄድ ዹቆዹውን ድንገተኛ ዚቀት ለቀት እና ዚተቋማት ፍተሻ ውጀት ይፋ አደሚገ። በኊፕሬሜኑ ዚተያዙ በርካታ ዚሺሻ ማስጚሻ መሣሪያዎቜ እና አደንዛዥ ዕጟቜ መወገዳ቞ው ታውቋል።

ዹቩሌ ክፍለ ኹተማ ፖሊስ መምሪያ ኚመስኚሚም 2018 ዓ.ም ጀምሮ ባደሚገው ጥናት መሠሚት፣ በወሚዳ 4 እና 5 በሚገኙ፩

1. ዚመኖሪያ ቀቶቜ
2. ፔንሲዮኖቜ
3. ዚሌሊት ጭፈራ ቀቶቜ ላይ ያነጣጠሚ ተኚታታይ ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል።

በዚህም ሂደት 5 ሺህ 329 ዚሺሻ ማስጚሻ ዕቃዎቜን እንዲሁም ዚተለያዩ አደንዛዥና አነቃቂ ዕጟቜን በቁጥጥር ስር ማዋል ተቜሏል።

ፖሊስ እንደገለጞው፣ ለዚህ ውጀታማ ኊፕሬሜን መነሻው ኚአካባቢው ነዋሪዎቜ ዹደሹሰው ጥቆማ ነው። እነዚህ ሱሶቜ "ወጣቱን ወደ ወንጀልና ወደ ማህበራዊ ቀውስ ዚሚመሩ" መሆናቾው ዹተገለጾ ሲሆን፣ ዚተያዙት ቁሶቜምፊ

* ዚአካባቢው ነዋሪዎቜ፣
* ዚሃይማኖት አባቶቜ፣
* ዚፀጥታ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት በይፋ እንዲወገዱ ተደርጓል።

ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ህብሚተሰቡ ዚአካባቢውን ሰላም ዚሚያውኩና ለወንጀል መንስኀ ዹሚሆኑ ድርጊቶቜን ሲመለኚት ለፀጥታ አካላት ጥቆማ በመስጠት ዚዜግነት ግዎታውን እንዲወጣ ጥሪውን አቅርቧል።

Via ዚአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ

ዹሰሞኑን መነጋገሪያ ጉዳይ ✍👉 ሰፍው ህዝቡ ባለተጠበቀ ሁኔታ ለነቀምቱ አንዱአለም እድል ይሰጠው እያለ ነው .🙏🏿ኚታቜ ምርጫቜሁን አሳውቁን!  ዚቀተሰብ ጚዋታን ማን ይምራው ትላላቜው ? ያሲ...
05/04/2026

ዹሰሞኑን መነጋገሪያ ጉዳይ ✍

👉 ሰፍው ህዝቡ ባለተጠበቀ ሁኔታ ለነቀምቱ አንዱአለም እድል ይሰጠው እያለ ነው .🙏🏿

ኚታቜ ምርጫቜሁን አሳውቁን!

ዚቀተሰብ ጚዋታን ማን ይምራው ትላላቜው ?

ያሲን ዚምትሉ 1 ቁጥር ጻፉ ✔

አስቌ ዚምትሉ 2 ቁጥር ጻፉ ✔

አዝመራው ዚምትሉ 3 ቁጥር ጻፉ ✔

......እናትነትበአምፖል ዚፈጠራ ውጀቱ ዹምናውቀው ቶማስ አልቫ ኀድሰንአንድ ቀን ኚትምህርት ቀቱ ወደ ቀት ዹተመለሰው መምህሩ ዹሰጠውን ወሚቀት ይዞ ነበር፡፡ እናም ኀድሰን ለእናቱ እንዲህ አ...
05/04/2026

......እናትነት

በአምፖል ዚፈጠራ ውጀቱ ዹምናውቀው ቶማስ አልቫ ኀድሰን
አንድ ቀን ኚትምህርት ቀቱ ወደ ቀት ዹተመለሰው መምህሩ ዹሰጠውን ወሚቀት ይዞ ነበር፡፡ እናም ኀድሰን ለእናቱ እንዲህ አላት “መምህሬ ይሄን ወሚቀት ለእናትህ ብቻ ስጣት ብሎ ሰጠኝ” በማለት ወሚቀቱን አቀበላት፡፡ እናት እንባ በአይኖቿ ሞልቶ በወሚቀቱ ላይ ዹሰፈሹውን ሀሳብ ለልጇ አነበበቜለት፡፡

ያነበበቜለት ሀሳብም ይህ ነበር “ልጅሜ በአስተሳሰቡ ምጡቅ (ጀኒዚስ) ነው፡፡ ይሄ ትምህርት ቀት ለእሱ አይመጥነውም። ለእሱ ብቁ ዹሆኑ መምህራኖቜም ትምህርት ቀቱ ዹሌለው በመሆኑ እባክሜ አንቾው አስተምሪው ይላል” በማለት እንባዋን እዚጠራሚገቜ ወሚቀቱን አጣጥፋ መሳቢያ ውስጥ ኚተተቜው፡፡

እናቱ ካሚፈቜ ኚብዙ ዓመታት በኋላ ኀድሰን በክፈለ ዘመኑ ካሉ
ዚፈጠራ ውጀት ባለቀቶቜ አንዱና ቀዳሚው ኹሆነ በኋላ አንድ ቀን እናቱ እቃዎቿን ዚምታስቀምጥበትን መሳቢያ ማገላበጥ ጀመሚ፡፡
ባጋጣሚ ዚተጣጠፈቜ ወሚቀት ኚመሳቢያው ጠርዝ አካባቢ
ተሰክታ ይመለኚትና አንስቶ ኚፈታት፡፡

ወሚቀቲ ልጅ እያለ ኚመምህሩ ለእናቱ ብቻ እንዲሰጥ ታዞ ዹተሰጠው ወሚቀት እንደነበር አውቋል፡፡ ኚፍቶ ሲያነበውም ወሚቀቱ ላይ ዹሰፈሹው ሀሳብ እንዲህ ይላል “ልጅሜ ዚአእምሮ ቜግር ያለበትና ዘገምተኛ ነው፡፡ ኹዚህ በኋላም ወደ ትምህርት ቀቱ እንዲመጣ አንፈቅድለትም” ይላል፡፡

ኀድሰን ለሰዓታት ካለቀሰ በኋላ ድያሪውን ኚፍቶ እዲህ ሲል ጻፈ
“ቶማስ አልቫ ኀድሰን አእምሮው ዘገምተኛ ዚተባለ ልጅ ነበር፡፡ ነገር ግን በጀግናዋና በልዩዋ እና቎ ዚምእተ ዓመቱ ጂኔስ ሁኛለሁ፡፡
Via Tadesse Moges

"ኚእኔ ጋር በአንድ ክፍል ዚነበሩ 10 ታካሚዎቜ አንድ በአንድ ሲያርፉ እኔ ብቻ ቀሹሁ..." 😭አርቲስት ዘላለም ይታገሱ ይህን ሲናገር እንባውን መቆጣጠር አቅቶት ነበር። በህይወት ጎዳና ላይ ...
05/04/2026

"ኚእኔ ጋር በአንድ ክፍል ዚነበሩ 10 ታካሚዎቜ አንድ በአንድ ሲያርፉ እኔ ብቻ ቀሹሁ..." 😭

አርቲስት ዘላለም ይታገሱ ይህን ሲናገር እንባውን መቆጣጠር አቅቶት ነበር። በህይወት ጎዳና ላይ ብዙ ውጣ ውሚዶቜን አሳልፎ፣ በህመም ምክንያት ሆስፒታል በነበሚበት ጊዜ ያዚው መኚራ እና እግዚአብሔር ያደሚገለት ተአምር በእውነት ልብን ዚሚነካ እና አጥንት ድሚስ ዘልቆ ዹሚሰማ ነው።

በአንድ ክፍል ውስጥ ኚነበሩ 10 ሰዎቜ መካኚል 9ኙ ህይወታ቞ው ሲያልፍ፣ እርሱን ለዚህ ላደሹሰው እና አዲስ ህይወት ለሰጠው ፈጣሪ ያለውን ጥልቅ ምስጋና በዕንባ ገልጿል። ዹዘላለም ታሪክ ዚህይወትን ውድነት፣ ዚፈጣሪን ቞ርነት እና ዚቱንም ያህል ጹለማ ቢመስልም ዚተስፋን ብርሃን ፈጜሞ መቁሚጥ እንደሌለብን በደንብ ያስተምሚናል።

ውድ አርቲስት ዘላለም ሆይ! ፈጣሪ አሁንም ፍጹም ጀናውን እና እድሜውን አብዝቶ ይስጥህ! 🙏🏜❀

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo nation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share