01/08/2026
አሁን ባለው የህወሓት ፀብ ጫሪነት የተከበሩ ዶክተር ኣብርሃም በላይ ለትግራይ ህዝብ ያስተላፉትን መልእክት ወደ አማርኛ መልሰነዋል።
"የኋላ ቀር የህወሓት ቡድን ዕድሜአቸው ያበቃ የትግራይ ሕዝብ ደመኞች፣ ዕድሜአቸውን ለማራዘም ሲሉ ታዳጊዎችንና ወጣቶችን ይጨፈጭፋሉ!
ዛሬ ሌሊት ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሸረሪና በኩል ጦርነት የከፈተው ይህ ኃይል፣ የትግራይ ወጣቶችንና ታዳጊዎችን በማያውቁትና ዓላማ በሌለው ጦርነት እንደ ቅጠል እንዲረግፉ እያገደላቸው ነው። ይህ በአስቸኳይ ካልቆመ እና ወጣቱ በሙሉ በአንድ አቋም ቆሞ ካላስቆመው የከፋ ውድመት ይከተላል፤ ለመመለስም ፈጽሞ እንቸገራለን፤ ሀገርህን በገዛ ፈቃድህ ለማድመቅና የደካሞች ሕልም ማስፈጸሚያ ለመሆን አትጠመድ።
ይህ ዓላማ የሌለው ጦርነት የሚረዱ አካላት አሉ በሚል ዕውርና ግራ የተጋባ አስተሳሰብ ተመራችሁ፣ ነገ ተስፋ በሆነው ወጣት ላይ የሞት ፍርድ እየፈረዳችሁበት ነው፤ እያለቀሳችሁትም ነው።
ጦርነት ይበቃል! በሃሳብ ዙሪያ እንሰብሰብ። እናንተ ደመኞች፣ የትግራይ ተስፋ ደም ጠጪዎች፤ ቆም ብላችሁ አስቡ፤ ሀገራችንን አታድሙ፣ ወጣቶቻችንን አታሰንክሉ፣ ታዳጊዎቻችንን አታጥፉ። አስፈላጊው ጉዳይ በሰላም እና በውይይት ብቻ ነው የሚፈታው። ጥፋትህን ከሚመኙ ጋር መጣመር ፈጽሞ እብደት ነው።
ለራሳቸው ደጋፊ ምሰሶ የሚያስፈልጋቸው፣ አንዲት ዓርብ የቀረቻቸው አካላት ይደግፉናል ብሎ በታዳጊዎች ሕይወት ላይ መፍረድ ሊቆም ይገባል። ትናንትም ቢሆን ከዚህ ሁሉ ጥፋት በኋላ ነው በሰላም እንወያይ የተባለው፤ ዛሬም ቢሆን ከጥፋት በፊት ለሰላም እጅ መዘርጋት ይሻላል።
ሰላም ወዳድ ሁሉ ጦርነት ይበቃል ይበል፤ ሳንጠፋ እንንቃ። በጦርነት የሚመለስ የሕዝብ ጥያቄ የለም!!
ጦርነት ይበቃል!
ለሰላም እንተባበር!
ዶ/ር አብርሃም በላይ
Via Wedi Shembel