Gamo nation

Gamo nation Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gamo nation, Digital creator, Addis Ababa.
(2)

አሁን ባለው የህወሓት ፀብ ጫሪነት የተከበሩ ዶክተር ኣብርሃም በላይ ለትግራይ ህዝብ ያስተላፉትን መልእክት ወደ አማርኛ መልሰነዋል።"የኋላ ቀር የህወሓት ቡድን ዕድሜአቸው ያበቃ የትግራይ ሕዝብ...
01/08/2026

አሁን ባለው የህወሓት ፀብ ጫሪነት የተከበሩ ዶክተር ኣብርሃም በላይ ለትግራይ ህዝብ ያስተላፉትን መልእክት ወደ አማርኛ መልሰነዋል።

"የኋላ ቀር የህወሓት ቡድን ዕድሜአቸው ያበቃ የትግራይ ሕዝብ ደመኞች፣ ዕድሜአቸውን ለማራዘም ሲሉ ታዳጊዎችንና ወጣቶችን ይጨፈጭፋሉ!

​ዛሬ ሌሊት ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም በሸረሪና በኩል ጦርነት የከፈተው ይህ ኃይል፣ የትግራይ ወጣቶችንና ታዳጊዎችን በማያውቁትና ዓላማ በሌለው ጦርነት እንደ ቅጠል እንዲረግፉ እያገደላቸው ነው። ይህ በአስቸኳይ ካልቆመ እና ወጣቱ በሙሉ በአንድ አቋም ቆሞ ካላስቆመው የከፋ ውድመት ይከተላል፤ ለመመለስም ፈጽሞ እንቸገራለን፤ ሀገርህን በገዛ ፈቃድህ ለማድመቅና የደካሞች ሕልም ማስፈጸሚያ ለመሆን አትጠመድ።

​ይህ ዓላማ የሌለው ጦርነት የሚረዱ አካላት አሉ በሚል ዕውርና ግራ የተጋባ አስተሳሰብ ተመራችሁ፣ ነገ ተስፋ በሆነው ወጣት ላይ የሞት ፍርድ እየፈረዳችሁበት ነው፤ እያለቀሳችሁትም ነው።

​ጦርነት ይበቃል! በሃሳብ ዙሪያ እንሰብሰብ። እናንተ ደመኞች፣ የትግራይ ተስፋ ደም ጠጪዎች፤ ቆም ብላችሁ አስቡ፤ ሀገራችንን አታድሙ፣ ወጣቶቻችንን አታሰንክሉ፣ ታዳጊዎቻችንን አታጥፉ። አስፈላጊው ጉዳይ በሰላም እና በውይይት ብቻ ነው የሚፈታው። ጥፋትህን ከሚመኙ ጋር መጣመር ፈጽሞ እብደት ነው።

​ለራሳቸው ደጋፊ ምሰሶ የሚያስፈልጋቸው፣ አንዲት ዓርብ የቀረቻቸው አካላት ይደግፉናል ብሎ በታዳጊዎች ሕይወት ላይ መፍረድ ሊቆም ይገባል። ትናንትም ቢሆን ከዚህ ሁሉ ጥፋት በኋላ ነው በሰላም እንወያይ የተባለው፤ ዛሬም ቢሆን ከጥፋት በፊት ለሰላም እጅ መዘርጋት ይሻላል።

​ሰላም ወዳድ ሁሉ ጦርነት ይበቃል ይበል፤ ሳንጠፋ እንንቃ። በጦርነት የሚመለስ የሕዝብ ጥያቄ የለም!!

​ጦርነት ይበቃል!
​ለሰላም እንተባበር!

ዶ/ር አብርሃም በላይ

Via Wedi Shembel


አሁን ላይ ሸረሪና ምን አዲስ ነገር አለ?በኢትዮጵያ በኩል በወልቃይት ጠገዴ ዞን (ቃብትያ ሁመራ ወረዳ) ስር በሚገፕው ሸረሪናና በረከት በተባሉ የድንበር ቀጠናዎች በዛሬው ዕለት ማለዳ ከባድ ...
01/08/2026

አሁን ላይ ሸረሪና ምን አዲስ ነገር አለ?

በኢትዮጵያ በኩል በወልቃይት ጠገዴ ዞን (ቃብትያ ሁመራ ወረዳ) ስር በሚገፕው ሸረሪናና በረከት በተባሉ የድንበር ቀጠናዎች በዛሬው ዕለት ማለዳ ከባድ የተኩስ ልውውጥ መከሰቱ ከስፍራው ተገልጷል።

የወጡ ዘገባዎች እንደሚያመላክቱት፣ ግጭቱ የተነሳው ከሱዳን ድንበር በኩል አካባቢውን በኃይል ለመቆጣጠር አልመው የገቡ የሕወሓት «አርሚ 70» ታጣቂዎች በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ላይ የከፈቱትን ትንኮሳ ተከትሎ ነው ተብሏል።

📌 የሕወሓት «አርሚ 70» ታጣቂዎች በሱዳን አቅጣጫ ሰርገው በመግባት በበረከትና ሸረሪና መስመር በቀላል መሳሪያዎች ትንኮሳ የጀመሩ ሲሆን፣ አላማቸውም ወልቃይት፣ ማይካድራ እና ሁመራን በመቆጣጠር ለቀጣይ የፖለቲካ ድርድር መደራደሪያ ማድረግ እንደነበር ተጠቅሷል።

📌 ትንኮሳውን ተከትሎ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በመድፍ እና በድሮን የታገዘ መጠነ-ሰፊ የአፀፋ እርምጃ የወሰደ ሲሆን፤ በጥቃቱ የተሳተፉት ታጣቂዎች አብዛኛው ክፍል መደምሰሱንና ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተመልክቷል።

📌 ከሁመራ ወደ በረከት እና ሸረሪና አቅጣጫ በተደረገው የከባድ መሳሪያ ተኩስ ምክንያት በሁመራ ከተማ ያሉ መኖሪያ ቤቶች ድረስ መንቀጥቀጣቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል።

📌በሌላ በኩል ሕወሓት የደረሰበትን ከባድ እርምጃ ተከትሎ ባወጣው መግለጫ፣ የፌደራል መንግሥቱ ሲያካሂድ የቆየውን ከበባ ወደ ወታደራዊ እርምጃ በማሳደግ በሸረሪና አቅጣጫ ጦርነት ከፍቶብኛል ሲል ሲቪል ማህበረሰቡና ደጋፊዎቹ ለትግል እንዲዘጋጁ ጥሪ አቅርቧል።

📌አሁን ላይ ሸረሪና በሀገር መከላከያ ሰራዊቱ ቁጥጥር ስር እንደሚገኝ ከአካባቢው የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል።

Wasu Mohammed - Video

"ህፃናት እንኳ ለመኖር የሚጠየፏት ሀገር ፈጥረናል"             እግር ኳስ ተጫዋች እንደሀገር ችግር ዉስጥ ነን፣በፍፁም ይሄ ለኛ አይገባም ነበር።ህዝብ በከፋ የሰላም እጦት መሄጃ አጥቷ...
30/07/2026

"ህፃናት እንኳ ለመኖር የሚጠየፏት ሀገር ፈጥረናል"

እግር ኳስ ተጫዋች እንደሀገር ችግር ዉስጥ ነን፣
በፍፁም ይሄ ለኛ አይገባም ነበር።

ህዝብ በከፋ የሰላም እጦት መሄጃ አጥቷል፣
አስከፊ የንሮ ዉድነት አለ፣ ቆም ብለን ማሰብ አለብን
መሪዎች ከቅዥት አለም መዉጣት አለባቸዉ፣
መሬት ላይ እየሆነ ያለዉን ነገር የማየት ግዴታ የነሱ ነዉ።
ስለእድገት ያወሩናል እዉነታዉ ግን ህፃናት እንኳ ለመኖር የሚጠየፏት ሀገር ነዉ የፈጠርነዉ።

ጌታነህ ከበደ
የቀድሞ የኢትዮጽያ ብሄራዊ ቡድን አጥቂ

በመንግሥት በተገነቡ መንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ግብር ሊከፍሉ ነዉየምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ ይህ ግብር በተሽከርካሪ ባለቤቶች ላይ የሚጣል ሲሆን፥ተሽከርካሪ...
30/07/2026

በመንግሥት በተገነቡ መንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ግብር ሊከፍሉ ነዉ

የምጣኔ ሀብት ባለሙያ የሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ ይህ ግብር በተሽከርካሪ ባለቤቶች ላይ የሚጣል ሲሆን፥ተሽከርካሪዎቹ በመንግስት በተገነቡ መንገዶች ላይ ስለሚንቀሳቀሱ በየዓመቱ የሚከፈል ይሆናል ብለዋል።

ይህም ከመደበኛው የተሽከርካሪ ዓመታዊ ምርመራ ወይም ቦሎ ጋር ተያይዞ ሊመጣ የሚችል ግዴታ ነው።

የምጣኔ ሀብት ባለሙያዉ እንደገለፁት፥ግብር አጣጣሉም እንደ ተሽከርካሪዎቹ ዓይነትና እንደሚያመነጩት ጭስ (ካርቦን) ሊለያይ እንደሚችል ተናግረዋል።

ይህ ማለት ብዙ ጭስ የሚለቁ አሮጌ ተሽከርካሪዎች ከፍተኛ ግብር እንዲከፍሉ አዳዲሶች ደግሞ ዝቅተኛ እንዲከፍሉ ሊደረግ ይችላል ተብሏል።

ይህ አሰራር በሌሎች አገራት ለምሳሌ በኬንያ፣ በሩዋንዳና በአውሮፓ አገራት የተለመደ ሲሆን፥መንግስት ለመንገድ ጥገና የሚውል ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ ያስችለዋል።

ግብሩ በከተሞችና በክልሎች የሚሰበሰብ በመሆኑ የአካባቢ መስተዳድሮች የራሳቸውን የልማት በጀት እንዲያሳድጉ ትልቅ ዕድል ስለሚፈጥርላቸው በፌዴራል መንግስት ላይ ያለውን የገንዘብ ጫና ይቀንሳል።

ይህ የታክስ ፕሮፖዛል በሚኒስትሮች ምክር ቤት ተዘጋጅቶ ለምክር ቤቱ ለማቅረብ ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል፡፡

አቶ ዋሲሁን አክለዉም ዝርዝር ደንቦችና መመሪያዎች ወጥተውለት ወደ ተግባር እንደሚገባና የኢኮኖሚው የገቢ ምንጭ እንደሚሆን እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

ከዚህ ግብር የሚገኘው ገቢ ከአጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት 0.2 በመቶ ድርሻ ይኖረዋል ተብሎ ይገመታል።

ሊዲያ ደሳለኝ

ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም

🎇የሄንደርሰን እና የዌልቤክ ዝውውር ሚስጢር✨➤ቼልሲ ብዙ ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊዎች ቢኖረውም፣ ለዋንጫ ለመወዳደር የሚያስችል በቂ ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች የለውም።➤ለዓመታት የቼልሲ ቡድን በፕሪ...
29/07/2026

🎇የሄንደርሰን እና የዌልቤክ ዝውውር ሚስጢር✨

➤ቼልሲ ብዙ ተሰጥኦ ያላቸው ታዳጊዎች ቢኖረውም፣ ለዋንጫ ለመወዳደር የሚያስችል በቂ ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች የለውም።

➤ለዓመታት የቼልሲ ቡድን በፕሪሚየር ሊጉ ከወጣት ቡድኖች መካከል አንዱ ነው።

➤ባለፉት አመታት በቼልሲ ቤት ነገሮችን ለማረጋጋት ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች አልነበሯቸውም።

➤ቡድኑ ግልጽ የሆነ የዲሲፕሊን ችግር ነበረበት።

➤ ሄንደርሰን እና ዌልቤክ ምርጥ የእግርኳስ ባህሪ፣ መሪነት፣ አንድነት እና በከፍተኛ ደረጃ ላይ ትልልቅ ዋንጫዎችን የማሸነፍ ልምድ ያላቸው ተጫዋቾች ናቸው።

➤ጆርዳን ሄንደርሰን መልበሻ ክፍሉን በመቆጣጠር የቡድን መንፈስ ያመጣል፤ ለካይሴዶ እና ኤንዞ ፈርናንዴዝ ልምዱን ያካፍላቸዋል።

➤ዳኒ ዌልቤክ ብልህ ተጫዋች ነው፤ ባለፈው የውድድር ዘመን ለብራይተን ከ13-14 የፕሪሚየር ሊግ ጎሎችን አስቆጥሯል።

➤ቼልሲ ሁልጊዜ ታዳጊዎችን ብቻ ከማስፈረም ይልቅ ነገሮችን ሚዛናዊ ለማድረግ ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች ማስፈረሙ ትልቅ ጥቅም አለው።

➤ ሁሉም ስኬታማ ቡድኖች ማለት ይቻላል የመልበሻ ክፍሉን አንድ የሚያደርጉ ልምድ ያላቸው ተጫዋቾችን ይዘዋል።

➤ጆርዳን ሄንደርሰን እና ዳኒ ዌልቤክ የፈረሙት ለመጀመሪያ አሰላለፍ ከሆነ ስህተት ነው፤ ነገርግን ለመሪነት እና ቡድኑን በልምድ ለማገዝ ከሆነ፣ ጥበብ የተሞላበት ዝውውር ነው።

Gondar sport/ጎንደር ስፖርት

🪖 በጦር ሜዳው አዲስ ፈጠራ፦ ዩክሬን ሁለት «AK-74» ጠመንጃዎችን በአንድ ላይ የሚተኩስ ዘመናዊ የሮቦት መሣሪያ አስተዋወቀች!የዩክሬኑ የጦር መሣሪያ አምራች ኩባንያ «ሮቦኒርስ» (Robon...
29/07/2026

🪖 በጦር ሜዳው አዲስ ፈጠራ፦ ዩክሬን ሁለት «AK-74» ጠመንጃዎችን በአንድ ላይ የሚተኩስ ዘመናዊ የሮቦት መሣሪያ አስተዋወቀች!

የዩክሬኑ የጦር መሣሪያ አምራች ኩባንያ «ሮቦኒርስ» (Roboneers)፣ በሩቅ ተቆጣጣሪ የሚሠራውን «ሻብሊያ ኬ-2» (ShaBlya K-2) የተሰኘ አዲስ የውጊያ መሣሪያ ኦፊሴላዊ ፈቃድና ምዝገባ አጠናቆ ወደ ሥራ ማስገባቱን ይፋ አደረገ።

ይህ አዲስ የቴክኖሎጂ ውጤት ሁለት «AK-74» ጠመንጃዎችን በአንድ ላይ አጣምሮ በመግጠም የተሠራ ሲሆን፣ ጥንካሬውን በሁለት እጥፍ በማሳደግ በቅርብ እርቀት ለሚገኙ እግረኛ ወታደሮች አስተማማኝ ከለላ ይሰጣል። መሣሪያውን በሩቅ ሆኖ የሚቆጣጠረው ወታደር እንደ ውጊያው ሁኔታ የግራውን ጠመንጃ ብቻ፣ የቀኙን ብቻ ወይም ሁለቱንም በአንድ ላይ በመተኮስ መጠቀም የሚያስችለው አማራጭ ተካቶበታል።

«ሻብሊያ» እ.ኤ.አ በ2014 በበጎ ፈቃደኞች ቡድን መሠረት ከተጣለበት ጊዜ ጀምሮ በዩክሬን ጦር ዘንድ ትልቅ እምነት ከተጣለባቸው ቀደምት የሮቦት መሣሪያዎች አንዱ ነው ተብሏል። አዲሱ የ«ኬ-2» ቅርጽ የመሣሪያውን የጥይት መጠን (Caliber) በመቀነስ የጥይቱን ብዛትና የፍጥነት ሽፋን ለመጨመር ታስቦ የተሠራ ነው ተብሏል።

ቀደም ሲል የነበሩት የሻብሊያ ሞዴሎች አንድ ባለ 7.62 ሚሜ ወይም 12.7 ሚሜ የሜሽን ጋን መሣሪያ ይገጠምላቸው የነበረ ሲሆን፣ «ኬ-2» ግን በተጠጋጋና ርካሽ በሆነ መዋቅር ሁለት ባለ 5.45 ሚሜ ጠመንጃዎችን በመጠቀም በአጭር ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ጥይት ወደ ጠላት ለመተኮስ የሚያስችል ልዩ ብቃት አለው ነው የተባለው።

ይህ ኦፊሴላዊ የቴክኒክ ፈቃድ ማግኘቱ መሣሪያው በስፋት ተመርቶ ለሀገሪቱ የደህንነትና የመከላከያ ኃይሎች በብዛት እንዲሰራጭ መንገድ የሚከፍት ነው ተብሏል።

ምንጭ|

የ10 ዓመት ታዳጊ ለ7 ዓመታት አስገ*ድዶ ከደፈ*ራት በኋላ በስተመጨረሻም በ17 ዓመቷ የገደላት ወንጀለኛ  የሞት ፍርድ ቅጣት ተፈረደበትሚካኤል ሽመልስ' የተባለ ሰው የ10 ዓመት ህፃን  ልጅ...
29/07/2026

የ10 ዓመት ታዳጊ ለ7 ዓመታት አስገ*ድዶ ከደፈ*ራት በኋላ በስተመጨረሻም በ17 ዓመቷ የገደላት ወንጀለኛ የሞት ፍርድ ቅጣት ተፈረደበት

ሚካኤል ሽመልስ' የተባለ ሰው የ10 ዓመት ህፃን ልጅ ላይ ከ1ዐ ዓመቷ ጀምሮ ለዓመታት አስ*ገድዶ መድፈር ወንጀል ይፈጽምባት ነበር፡፡

ይህች ምስኪን ይህን ሁሉ ዓመት በዚህ አረመኔ ሰው ስትሰቃይ 'አባትና እናትሽን እገድላለሁ' እያለ በሚያደርስባት ማስፈራራት ሳቢያ ለሰው ለመናገር እንኳ ሳትችል ህመሟን ሸሽጋ ኖራለች፡፡

ይባስ ብሎ በዚሁ አረመኔ ሰው ተደጋጋሚ መደፈር ሳቢያ ስትጸንስ እንድታስወርድ አድርጎ ህይወቷን አደጋ ውስጥም ጥሎት ኖሯል፡፡

በመጨረሻ 17 ዓመት ሲሞላት በደሉ በዝቶባት ለፖሊስ ብታመለክት "ለምን ከሰስሽኝ" ብሎ ያለችበት ቤት ድረስ በመሄድ በቢለዋ 16 ቦታ ወጋግቶ ገድሏታል።

የሚያሳዝነው ነገር ደግሞ የወንጀሉ ሰለባ የሆነችው ታዳጊ የተከሳሹ የቀድሞ ፍቅረኛ ልጅ ነበረች፡፡

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ ወንጀል ችሎት ይህንን ክፉ ሰው 'ከሰው ተደባልቀህ መኖር አትችልም' ብሎ ሞት ፈርዶበታል፡፡

ይህ አረማኔ ሰው የሞት ፍርዲን ተቀብሎታል።
ይህነን ዘገባ ከዚህ ዳግም የቀረበው ምክንያት ወሳኔውን ለማሳወቅ ሰንል ነው ።
ሁል ጊዜ ፍትህ እንዲሰፍን ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ
#ፍትህለሁሉ

23/07/2026




Land of peace & wisdom ❤👌

  ???በቀጣይ መስከረም 2019 አ.ም አድስ ተመራጭ የፓርላማ አባላት ወደ ምክር ቤት ገብተው የመንግስት ምስረታ ስካሄድ ጠቅላይ ሚንስቴር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በስልጣናቸው ባይቀጥሉና አድስ...
23/07/2026

???

በቀጣይ መስከረም 2019 አ.ም አድስ ተመራጭ የፓርላማ አባላት ወደ ምክር ቤት ገብተው የመንግስት ምስረታ ስካሄድ ጠቅላይ ሚንስቴር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በስልጣናቸው ባይቀጥሉና አድስ ጠቅላይ ሚንስቴር ቢሰየም በሀገራችን ምን ልፈጠር የምችል ይመስላችኋል ?

ይሄስ ልሆን ይችላል ቢላችሁ ታስባላችሁ ?

ክረምትን በታሪካዊው ታላቁ ቤተ መንግሥት ያሳልፉ! 🇪🇹በአዲስ አበባ እምብርት የሚገኘው ታሪካዊው ታላቁ ቤተ መንግሥት በአዲስ መልክ ታድሶ፣ ውብነቱና ታሪካዊ ክብሩ ተጠብቆ ለጎብኚዎች ክፍት ከ...
23/07/2026

ክረምትን በታሪካዊው ታላቁ ቤተ መንግሥት ያሳልፉ! 🇪🇹

በአዲስ አበባ እምብርት የሚገኘው ታሪካዊው ታላቁ ቤተ መንግሥት በአዲስ መልክ ታድሶ፣ ውብነቱና ታሪካዊ ክብሩ ተጠብቆ ለጎብኚዎች ክፍት ከሆነ ቆይቷል።

አሁን በኢትዮጵያ የክረምት ወቅት ነው። ይህን ውብ ወቅት በቤት ውስጥ ብቻ ከማሳለፍ ይልቅ፣ ከቤተሰብና ከወዳጆች ጋር ወደ ታላቁ ቤተ መንግሥት በመሄድ የሀገራችንን ታሪክ፣ ባህል፣ ሥነ ሕንፃና የቀድሞ ትውልዶችን አሻራ ከቤተሰቦ ወዳጅ ዘመዶ ጋር በመሆን ይመልከቱ።

የዝናብ ጠብታዎች፣ የአረንጓዴ ስፍራዎች ውበትና የቤተ መንግሥቱ ታሪካዊ ግርማ ተዋህደው፣ የማይረሳ የጉብኝት ትዝታ ይሰጣችኋል።

ታሪክን ማወቅ ራስን ማወቅ ነው። ክረምቱን በታሪክ፣ በውበትና በእውቀት ያሳልፉ። ታላቁን ቤተ መንግሥት ይጎብኙ፤ የኢትዮጵያን ክብርና ታሪክ በአንድ ስፍራ ይመልከቱ! 🇪🇹

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gamo nation posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share