Guna Media Service

Guna Media Service Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Guna Media Service, Media/News Company, Addis Ababa.

ሰበር ዜና - አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጠራ !!!***የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በመስቀል አደባባይ ጉዳይ ለመነጋገር አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጠርቷል። በሀገር ውስ...
10/01/2022

ሰበር ዜና - አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጠራ !!!

***

የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በመስቀል አደባባይ ጉዳይ ለመነጋገር አስቸኳይ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ጠርቷል።

በሀገር ውስጥ የሚገኙ ብፁዓን አባቶች በምልዓተ ጉባኤው እንዲገኙ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ለብፁዓን አባቶች የስልክ ጥሪ እያደረገ እንደሚገኝ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

የቅዱስ ሲኖዶሱ ምልዓተ ጉባኤ ነገ ከቀትር በኋላከ 9:00 ሰዓት ጀምሮ እንደሚከናወን ይጠበቃል

ምንጭ
ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል

ፋኖ መዳኛችን ነው።መዘነጣጠሉ አይጠቅምም።
16/12/2021

ፋኖ መዳኛችን ነው።
መዘነጣጠሉ አይጠቅምም።

16/12/2021
የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት መንግሥትና ሕዝባቸው ከኢትዮጵያ ጎን እንደሚቆሙ አረጋገጡ‼️ፕሬዝዳንቱ ይህን ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ...
16/12/2021

የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ማያርዲት መንግሥትና ሕዝባቸው ከኢትዮጵያ ጎን እንደሚቆሙ አረጋገጡ‼️

ፕሬዝዳንቱ ይህን ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ለአንድ ቀን የሥራ ጉብኝት ደቡብ ሱዳን ጁባ ተገኝተው ሲመክሩ ነው፡፡

ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር ደቡብ ሱዳን ሁሌም ከኢትዮጵያ ሰላም፣ መረጋጋት፣ ፀጥታና የግዛት አንድነት መጠበቅ ጎን እንደምትቆም ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማረጋገጣቸውን ነው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ የሚጠቁመው፡፡

ኢትዮጵያ የራሷን ችግር በራሷ አቅም የመፍታት ሙሉ አቅም እንዳላት አገራቸው የማይወላውል እምነት እንዳላት ጠቁመውም በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ ለመግባት መሞከርን በፍፁም እንደማትቀበልም አፅንኦት ሰጥተዋል።ሁለቱ መሪዎች በሁለቱ አገራት የጋራ ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡

የኢትዮጵያ ጦር በሸዋና ደቡብ ወሎ ግንባር በህወሃት ጦር ላይ ስለተቀናጀው ድል ለወደፊቱ ዘለግ አድርጌ እጽፋለሁ። ለአሁኑ ግን በጦርነት የተገኘውን ድል በፖለቲካ ውዝግብ የተነሳ እንዳናጣው ስ...
15/12/2021

የኢትዮጵያ ጦር በሸዋና ደቡብ ወሎ ግንባር በህወሃት ጦር ላይ ስለተቀናጀው ድል ለወደፊቱ ዘለግ አድርጌ እጽፋለሁ። ለአሁኑ ግን በጦርነት የተገኘውን ድል በፖለቲካ ውዝግብ የተነሳ እንዳናጣው ስለሰጋሁ፣ በአንድ ቁልፍ ጉዳይ ላይ ሃሳቤን ላካፍላችሁ ወደድኩ።

በቅርቡ ለተገኘው የጦር ሜዳ ላይ ድል አንደኛው አወንታዊ ምክንያት የአመራር ወጥነት ( unity of command) መፈጠሩ ነው። አጠቃላይ የጦርነቱ አካሄድ በአንድ ሰው የመጨረሻ ውሳኔ ሰጪነት እንዲካሄድ መደረጉ፣ በተለያዩ ምክንያቶች ሊፈጠሩ ይችሉ የነበሩ ውዝግቦችንና መጓተቶችንና አስቀርቷል። ጦርነት በተፈጥሮው ፈጣን ውሳኔን የሚጠይቅ መስክ በመሆኑ፣ የጠ/ሚኒስትሩ በጦር ሜዳው ላይ መገኘት፣ ከፈጠረው የስሜት መነቃቃት በተጨማሪ፣ ውሳኔዎች በፍጥነት እንዲሰጡና እንዲተገብሩ እረድቷል። ከጠ/ሚኒስትሩ በታች የሚገኙ የጦር አመራሮች፣ ብናጠፋ በፖለቲካ አመራሩ እንወገዛለን ብለው ሳይሰጉ፣ በቀጥታ የሚሰጣቸውን ትዕዛዝ ያለ ስጋት እንዲያስፈጽሙ እገዛ አድርጎላቸዋል።

የአመራር ማዕከላዊነቱ መከላከያውን ብቻ ሳይሆን፣ የክልል ልዩ ሃይሎችን፣ ሚሊሺያውንና ፋኖውን ያካተተ በመሆኑ፣ እነዚህን ሁሉ ሃይሎች በአንድ መስመር አሰልፎ በማዋጋት ታላቅ የሚባል ሃይል መፍጠር ተችሏል። እነዚህ ሃይሎች በተበታተነ አመራር ቢንቀሳቀሱ ኑሮ፣ እስካሁን የተገኘው ድል ባልተመዘገበም ነበር። (በደብረታቦር ግንባር ተፈጥሮ በነበረው የአመራር ክፍተት፣ ህወሃት ጊዜያዊ ድል እንድታገኝ እረድቷት እንደነበር አንረሳውም። )

የአመራር ወጥነት እንዳይኖር ከሚያደርጉ ምክንያቶች አንዱ፣ በአጠቃላይ በግንባር በተሰለፈው ሰራዊት መካከል የፖለቲካ ፍላጎት ያላቸው ሰዎች የሚፈጥሩት ችግር ነው። የፖለቲካ ፍላጎት ያላቸው ሰዎች የሚጨነቁት ራሳቸውን ወደፊት ስለማምጣት ወይም ሁሉም ነገር በራሳቸው ዛቢያ እንዲሽከረከርላቸው በመሆኑ፣ በሰራዊቱ ውስጥ መከፋፈል እንዲፈጠርና የአመራር አንድነቱም እንዲፈርስ ሊያደርጉ ይችላሉ። ይህ ጦርነት ባልተጠናቀቀበት ሁኔታ፣ በግንባር የተሰለፉት ሃይሎች የፈጠሩትን አንድ ወጥ የእዝ ሰንሰለት የሚጎዳ ማንኛውንም አይነት እንቅስቃሴ መንግስት በፍጠነት ማስቆም አለበት። ሊታገሰውም አይገባም።

ይህ ጊዜ እርስ በርስ የምንናቆርበት ሳይሆን፣ በአንድነት ቆመን የመጣብንን አደጋ በመቀልበስ የኢትዮጵያን የወደፊት ታሪክ የምንጽፍበት ነው።

11/12/2021

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የተመራው ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት፣ ዋናውን የወልድያ መቀሌ ጎዳና ቆርጦታል‼️

በክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት፣ በአሸባሪው ወራሪ ላይ በሰነዘሩት ክንደ ብርቱ ማጥቃት፣ በምሥራቅ ግንባር ስትራቴጂያዊ የሆኑትንና ወራሪው በፍጻሜ ዋዜማ ላይ መሆኑን የሚያሳዩትን የዞብል ሠንሠለታማ ተራሮችን ጨምሮ ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን የአርጆ፣ ፎኪሳ እና ቦረን ከተሞችን ተቆጣጥሯል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ የጉራ ወርቄ አካባቢዎችን በመቆጣጠር የወልድያ መቀሌ ዋናውን አውራ ጎዳና በመቁረጥ ጠላት መውጫ አጥቶ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ውስጥ እንዲገባ አድርጎታል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ ግንባር የድሬ ሮቃና የሶዶማ ከፍተኛ ወታደራዊ ጠቀሜታ ያላቸውን ከተሞችና ተራሮች በመቆጣጠር ጥምር ጦሩ ወደ ሐራ ከተማ እየገሠገሠ ይገኛል፡፡

በውጫሌ ግንባር ደግሞ የአምባሰል ከፍተኛ ሠንሠለታማ ተራሮችን ጨምሮ የሮቢትና የጎልቦን፣ በወረባቦ ወረዳ የሚሌ ኮትቻን፣ በሐብሩ ወረዳ የኮልቦን፣ የመርካታና የፋጂን አካባቢዎችን በመቆጣጣር ወደ መርሳ ከተማ እየገሠገሠ ነው፡፡

08/12/2021

Woldia loading

ጠቅላይ ሚኒስተር ዶር  አብይ አህመድ የምርጀመሪያውን ዘመቻ በድል አጠናቀው ለተወሰነ ጊዜ ወደቢሮ መመለሳቸውን አስታወቁ።
08/12/2021

ጠቅላይ ሚኒስተር ዶር አብይ አህመድ የምርጀመሪያውን ዘመቻ በድል አጠናቀው ለተወሰነ ጊዜ ወደቢሮ መመለሳቸውን አስታወቁ።

ክበሩልን!!
03/12/2021

ክበሩልን!!

01/12/2021

ላሊበላ በወገን እጅ!!

01/12/2021

ሰበር ዜና!

አሸባሪው ህወሓት ለተባበሩት መንግስት ድርጅት፣ ለአሜሪካ ለአውሮፓ ህብረት፣ ለአረብ ሊግ ደብዳቤ መፃፉን አልጀዚራ አረብኛ ዘገበ።

ህወሓት አሜሪካና አውሮፓ ህብረት ተመድ አረብ ሊግ የኢትዮጵያ መንግስት ለአስቸኳይ ድርድር እንዲቀመጥና ወደ ትግራይ ክልል እንዳይገባ ጫና እንዲያደርጉለት፣ በደብዳቤው ላይ ጠይቋል። አልጀዚራ ከአንድ የአሜሪካ ዲፕሎማት አገኘሁት ባለው የህወሓት ሚስጥራዊ ደብዳቤ ላይ የአረብ ሊግን ጨምሮ የአውሮፓ ህብረት አሜሪካና ተመድ በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጠንካራ አቋም ይዘው ጫና እንዲያደርጉለት ተማፅኗል።

ከኢትዮጵያ መንግስት በተጨማሪ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ ኢራን፣ ቱርክ እና ሩሲያ ለኢትዮጵያ መንግስት የሚያደርጉት ወታራዊ ድጋፍ እንዲያቆሙ ደብዳቤ የላከላቸው አገሮች እና ተቋሞች ጫና እንዲያደርጉለት ጠይቋል።

(ምንጭ:-ሱሌማን አብደላ)

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Guna Media Service posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share