ZOBEL TIMES

ZOBEL TIMES ፈጣን ወቅታዊ የተጣሩ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር መረጃዎችን ለተከታዮቻችን እናደርሳለን።
ቤተሰብ ስለሆኑን እናመሰግናለን።�ኢትዮጵያ ትቅደም!!!�

ይድነቃቸው ከበደ ታስሮ ቀረ። ኤርሚያስ መኩሪያ ታስሮ ቀረ። በላይ በቀለ ታስሮ ቀረ። ሌላም ብዙ ሰው ታስሮ ቀረ። ከትናንት የከፋ ጊዜ ላይ መሆናችን የሚታወቀው፣ በፊት ሰው ሲታሰር መደንገጥ፣...
28/08/2023

ይድነቃቸው ከበደ ታስሮ ቀረ። ኤርሚያስ መኩሪያ ታስሮ ቀረ። በላይ በቀለ ታስሮ ቀረ። ሌላም ብዙ ሰው ታስሮ ቀረ። ከትናንት የከፋ ጊዜ ላይ መሆናችን የሚታወቀው፣ በፊት ሰው ሲታሰር መደንገጥ፣ "ፍቷቸው" ማለት ነበረ።

አሁን ሁሉንም ዓይነት ግፍ ተለማምደነው ለብዙ ነገር ግድ የሌለው ይበዛል። ሰው ሲሞት፣ ቁጥሩ እና አገዳደሉም የማይደንቀን ጊዜ ላይ ደርሰናል። ደጅ እንደተሰጣ እቃ ሰው ጠፋ ሲባል ሁሉ መደነቅ እየቀነሰ፣ ሰብዓዊነት ቀስ በቀስ እየቀዘቀዘ መጣ።

በርግጥ መከራ እና ግፍ አዲስ አይደለም። ነገር ግን የአሁኑን የከፋ የሚያደርገው፣ ሁሉንም ከስር ከስር እየጋቱ ያለማምዱናል። ያደነዝዙናል። :-/

Yohanes Molla - ዮሐንስ ሞላ

ከኮለኔል ፈንታው ሙሃቤና ከኮለኔል ሞገስ ዘገየ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ‼እንደሚታወቀው ትዕግስታችን ሆደ ሰፊነታችንና ሃገር ወዳድነታችን እንደ ፍርሃት ተቆጥሮ እኛን መጨ...
05/08/2023

ከኮለኔል ፈንታው ሙሃቤና ከኮለኔል ሞገስ ዘገየ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ አስቸኳይ መግለጫ‼

እንደሚታወቀው ትዕግስታችን ሆደ ሰፊነታችንና ሃገር ወዳድነታችን እንደ ፍርሃት ተቆጥሮ እኛን መጨፍጨፉና ማፈናቀሉ የዕለት ተዕለት ቀላሉ የአበል ስራቸው መሆኑ አልበቃ ብሏቸው በተደጋጋሚ ክልላችንን ሆን ብለው የጦርነት ቀጠና በማድረግ አራሹና መጋቢውን ህዝባችን የሩዝና የዱቄት ተመፅዋችና የሰው እጅ ጠባቂ እንዲሆን ማድረጋቸው አንሷቸው ዛሬም አዲስ ስልት በመንደፍ ህዝባችንን የከፋና ህጋዊ ደሃ ለማድረግ የፌዴራል መንግስቱና የክልሉ መንግስት ተጣምረው በጋራ እየተናበቡ በመስራት ላይ ይገኛሉ።

አሁን ባለው ወቅታዊ ሁኔታና የትግል ምዕራፍ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ድንጋጌ የሚመጣ አንዳችም ሰላም የለም። ምናልባት የከፋ ደህንነትና ስራ አጥነት እንጂ። እንደሚታወቀው አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በሚጣልባቸው ስፍራዎች ላይ ቱሪስትም ሆነ ባለሃብቶች ወደዚያ ስፍራ አቅንተው ጉብኝትም ሆነ አዳዲስ ኢንቨስትመንቶችን እንዳያደርጉ ይገደዳሉ። ይህ ሆነ ማለት በኦሮሚያ ክልል ሰፍኖ በነበረ የጸጥታ ስጋት ቆሞ የነበረውን የቱሪስትና የኢንቨስትመንት ፍሰት ዳግም እንዲያብብና የእኛ እንዲቀጭጭ በር ከፋች የሆነ ሆን ተብሎ ታስቦበት በስሌት የተሰራ የከፋ ውሳኔ ነው። ስለሆነም አጥብቀን እንታገላለን እንጂ በመግልጫ የሚቆም ተራ ትግል አልጀመርንም።

ለመከላከያ ሰራዊታችን ደጀን ለሃገር ካስማ የሆነው ህዝባችን ሳያሳዝናቸው አዝመራውን መዝራት ባለበት ወቅት እንዳይዘረና ነገ በረሃብ እንዲያለቅ ሆን ብለው በማሰብ ማዳበሪያ ጭምር ሲከለክሉት የከረሙትን አርሶ አደሩ ህዝባችንን ዛሬ ጥያቄያችን ይሰማ ባለና የህልውና አደጋችንን መንግስት እስኪያረጋግጥለንና እንዲሁም ገዳዮቻችን እሰኪሰንፉና አቅማቸው ተሟጦ ሳይዳከም ትጥቅ አንፈታም በማለታችን ብቻ ተጨማሪ ምክንያት በመፈለግ ዳግም ክልላችንን ከኢኮኖሚ ተጠቃሚነቱና ከሰላሙ ሊያርቀው የሚችል አዋጅ በማወጅ ኢ-ዴሞክራሲ የሆነ ውሳኔ መወሰንና በመግለጫ ማውጣታቸው ይታወቃል።

ስለሆነም ህዝባችን የታቀደለትን በሲስተም አደህይቶ የማስገበር ሴራ ቀድሞ በማውቅ የጀመረውን ሁሉን አቀፍ ህዝባዊ ትግል አጠንክሮ በመቀጠል የታቀደለትን ሴራ በጣጥሶ እንደሚወጣና ዳግም ሰላሙን በአጭር ጊዜ በክንዱ አረጋግጦ ወደ ነበረበት ሰላም እንደሚመለስ በፅኑ እናምናለን።

ማሳሰቢያ:-
▪1ኛ...በተቆጣጠርናቸውና ወደፊትም በምንቆጣጠራቸው ከተሞች ላይ ተሸናፊውና ተስፋ የቆረጠው የቀድሞው ስርዓት ጣር ላይ ስለሚገኝ በመንፈራገጥ ብዙ ውድመቶች ሊያስከትል ስለሚችሉ የጣሩንም የግነዛውንም የቀብሩንም ሂደት በጥንቃቄ ማድረግ ይጠበቅብናል።

▪2ኛ...ከተሞችን በመቆጣጠር ሂደት ውስጥ ተመሳስሎ መዝረፍም ሆነ ከማህበረሰቡ ሊለየን የሚችልን ማንኛውንም ጥፋት መፈፀም እስከ ወዲያኛው የሚያሸኝ አጸያፊ ተግባር መሆኑ እንዲታወቅ ማሳወቅ እንፈልጋለን።

▪3ኛ...በመንግሥት የጸጥታ ተቋም ውስጥ ማለትም በፖሊስ በሚሊሻና በመከላከያ ተቋም ውስጥ የምታገለገሉ አባሎችን ይፋዊ የትግል ጥሪያችንን ተቀብላችሁ እንድትቀላቀሉን ዛሬም ጥሪያችንን እናቀርባለን።

▪4ኛ...ህዝባችን በጀመረው መራር የህልውና ትግል ምክኒያት ለዚህ እንደተዳረገ ለማስመሰል የሚደረግን ለካድሬ ሸፍጥ ጆሮ ባለመስጠት ወደ ፊት ፀንቶ በመታገል ራሱንና ህዝቡን ነፃ እንዲያወጣና እስካሁን ከሆነው በላይ የሚሆነውም የሚደርስበትም አንዳች መከራ የለምና በተራ መግለጫ እንዳይደናገጥና የጀመረውን ትግል አጠናክሮ እንዲቀጥል አበክረን እናሳስባለን።

▪5ኛ...በሁሉም አቅጣጫ ያለ ፋኖ ከእንግዲህ ለሚኖረን መራር የህልውና ትግል ለዘመቻው ስያሜ እየሰጠን የራሳችንን ታሪክ በደማችን እየጻፍን የምንሄድበት ቁመና ላይ መድረሳችንን እናበስራለን።

▪6ኛ...ከመቼውም ጊዜ በላይ እያሳየን ያለነውን የመነጋገር የመደማመጥና የመከባበር ፍቃደኝነታችንን ከዚህ በላይ አጠናክረን እንድንቀጥል በታላቁ ህዘባችን ስም እንለምናለን አደራም ማለት እንወዳለን።

በመጨረሻም ላንጨርስ የጀመርነው ትግል የለምና እንኳን በእናንተ ተራ መግለጫ በያዛችሁት ግዙፍ ሰራዊት የሚበረግግ ትንሽ ልብ የለንምና ህዝብን ከማሸበር ስራ ብትወጡ ለማለት እንወዳለን::

ቅዳሜ 29/12/2015 ዓም
ጋሸና ሰሜን ወሎ ዞን

ጎጃም ከባህርዳር ጀምሮ ወደ ደጀን የሚዎስደውን አውራ መንገድ ሁሉም ቦታዎች ላይ ጠርቅማለች።ጎጃም ማለትም ደንበጫ፣ቡሬ፣የጁቤ፣ፈረስ ቤት፣ደጋ ዳሞት፣ፍኖተ ሰላም፣አማኑኤል፣ጅጋ፣የጨረቃ፣መራዊ፣ማ...
02/08/2023

ጎጃም ከባህርዳር ጀምሮ ወደ ደጀን የሚዎስደውን አውራ መንገድ ሁሉም ቦታዎች ላይ ጠርቅማለች።

ጎጃም ማለትም ደንበጫ፣ቡሬ፣የጁቤ፣ፈረስ ቤት፣ደጋ ዳሞት፣ፍኖተ ሰላም፣አማኑኤል፣ጅጋ፣የጨረቃ፣መራዊ፣ማርቆርስ በአገዛዙ የኦህዴድ/ኦነግ ሰራዊት ሙሉ ጦርነት ውስጥ ናቸው።

ይሁን እንጂ "የገባው አይወጣም" ሲሉ በፋፁም ኩራት ገልፀውልናል።

የገባው የስርዓቱ ወታደር እጁን እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቦለታል።

ጎንደር በዋናነት ደ/ታቦር ጦርነት ውስጥ ናት።

አማራው ላይመለስ ተነስቷል።

Wogderes Tenaw ወግደረስ ጤናው

ዛሬ 8 ሰአት ፍርድቤት ቀርበው የነበሩት ጋሽ ታዲዎስ ታንቱ የችሎት ውሎ ፦ለመከላከያ ምስክርነት ቀርቦ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ፍርድቤቱ ለመከላከል ደብዳቤ ፅፈን ከመከላከያና ከሀገ...
31/07/2023

ዛሬ 8 ሰአት ፍርድቤት ቀርበው የነበሩት ጋሽ ታዲዎስ ታንቱ የችሎት ውሎ ፦

ለመከላከያ ምስክርነት ቀርቦ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ፍርድቤቱ ለመከላከል ደብዳቤ ፅፈን ከመከላከያና ከሀገር ደህንነት አኳያ በምን ጉዳይ ይመስክር የሚለውን ወስነን በቀጣይ ቀጠሮ ትቀርባለህ ተብሎ ምስክርነትቱ አልተደመጠም።

የኢ/ኦ/ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን 4 ጊዜ ቢጠሩም ባለመቅረባቸው ተጠያቂነት የሚያስከትል ስለሆነ በቀጣዩ ቀጠሮ የአዲስአበባ ሀገረስብከት ስራአስኪያጅ እንዲቀርቡ ትዛዝ ተሰጥቷል።

ከዚህ በፊት የመከላከያ ምስክር ሆነው ቃል የሰጡት የሰብዓዊ መብት ኮሚሽነር ዶክተር ዳንኤል ቃል በሰጡበት ወቅት የተቀዳው ቅጂ በደንብ ስለማይሰማ በቀጣዩ ቀጠሮ ቀረበው ድጋሚ ምስክርነትቸው እንዲደመጥ

ቀጣዩ ቀጠሮ ለሚቀጥለው አመት ጥቅምት 19 ፤ 20 ፤21 እንዲሆን በማለት የዛሬው ውሎ ተጠናቋል።

የታሪክ ምሁሩና ጋዜጠኛው ጋሽ ታዲዎስ ታንቱ የታሰሩት አምና ግንቦት/2014 ዓ.ም ነበር። ከአንድ አመት በላይ ምስክር እንኳን አዳምጠው አልጨረሱም። በጋሽ ታዲዎስ እስር ላይ ሽመልስ አብዲሳ "እዛው ይበሰብሳታል እንጂ መቼም አይወጣም" ማለቱ ይታወሳል።

Via Kura Gebre

~ "ትልቁ አሸናፊነት የሚጀምረው አንድነታችን ላይ ነው። በአማራነት ጥላ መሠባሰባችን ላይ ነው።  የጥላቻ: የልዩነት ግንብን ማፈራረሱ ላይ ነው። ጠላቶቻችን  እሳርና ጭድ ናቸው ብለው ሲያስቡ...
30/07/2023

~ "ትልቁ አሸናፊነት የሚጀምረው አንድነታችን ላይ ነው። በአማራነት ጥላ መሠባሰባችን ላይ ነው። የጥላቻ: የልዩነት ግንብን ማፈራረሱ ላይ ነው። ጠላቶቻችን እሳርና ጭድ ናቸው ብለው ሲያስቡን አንድ ሁነን ለቁርስ እናስባቸዋለን። በሃሳብ በተለያዩ መንገድ ተለያይቶ የነበረው በባትሪ ተፈላልጎ ተገናኝቷል።

አሁን የቤት ስራችንን አጠንክረን እንሰራለን። በጎን ጠላትን እየመከትን በጎን እንደራጃለን። የተበታተነውን አደረጃጀት በማጥበብ እንሰበስበዋለን።

ጎንደር ዛሬ አንዲት ሻለቃ ተመስርታለች። ከሰዓታት በፊት በሚዲያ እንደገለፅናት አፄ ፋሲለደስ ሻለቃ ትባላለች። ሻለቃዊ የከተማ ወጣቶችን ክንፍ የያዘች ሲሆን ተጠሪነቷም ለቴዎድሮስ ፋኖ ብርጌድ ነው። የቴዎድሮስ ፋኖ ብርጌድ በርካታ የጦር መሃንዲሶችንና የትግል ልምድ ያላቸውን አይደክሜ ወጣቶችን ያቀፈ ብርጌድ ነው።

ጠላት እየመከትን ጎን ለጎን እንደራጃለን!

የፈራ ይመለስ

አማራ ያሸንፋል!

የችሎት ጥቆማ!የታሪክ ምሁሩ ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ በነገው ዕለት ሀምሌ 24 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ።የምትችሉ ሁሉ ነገ ልደታ ምድብ ችሎት ...
30/07/2023

የችሎት ጥቆማ!

የታሪክ ምሁሩ ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ በነገው ዕለት ሀምሌ 24 ቀን 2015 ዓ/ም ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ።

የምትችሉ ሁሉ ነገ ልደታ ምድብ ችሎት ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመገኘት አጋርነታችሁን እንድታሳዩ!

ፍትህ ለታሪክ ምሁሩ ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ!

ZOBEL TIMES

30/07/2023

ነፃ በወጡ አካባቢዎች እንዲህ እየሆነ ነው። የዐማራ ልዩ ኃይል ከነ ሙሉ ትጥቁ፣ እውቀቱ፣ ወኔውና ጀብዱው ከጀግናው በተፈጥሮ ነፍጠኛ ከሆነው አራሽ፣ ቀዳሽ፣ ተኳሽ ፋኖ ጋር መቀላቀሉ ትግሉን ወደፊት እያስፈነጠረው ነው።

የገበሬው ማዳበሪያና ምርጥ ዘር መከልከል ለፋኖ ጥሩ ከለላ ነው የሆነው።ስንቅ ከመስጠት አልፎ መንገድ መምራት፣ጠላት ሲመጣ በጋራ ማጥቃት፣ መመከትም ተጀምሯል።

"የጥንት የደርግ ወታደሮች፣በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ተሳታፊ የነበሩ ወታደሮች፣አሁን ካለው መከላከያ፣ፌደራል ፖሊስ እና ሪፐብሊካን ጋ ር የኮበለሉ ዐማሮች ፋኖን መቀላቀል የፋኖን አደረጃጀት አሳድጎታል።

ሥልጠና ከገጠር ወጥቶ ከተማ አስፓልት ላይ የሚሰጠው ከተሞ ችን ከብአዴን እና ከዐቢይ፣ብራኑ ጁላ ጦር ነፃ ስላወጡ ነው። አሁ ን ፋኖ ነፃ ባወጣቸው ከተሞች ላይ ወጣት ሆኖ አረቄ መገሸር፣ጠ ላ ሲያንቃርር መዋል፣ጫት እና ሺሻ ሲጠቀም፣ሴት ሲያሳድድ መዋ ል ክልክል እየሆነ ነው።ወጣት ያውም ጤነኛ ከሆነ ሳይወድ በግ ዱ ትግሉን ይቀላቀላታል።ማንም ሞቶ ይሄን ጀዝባ የሃገር ሸክም ነፃ አያወጣም።

አሁን ትልቁ እሾክ የዐማራ ጎታች ወጣት ፀረ ዐማራ ዲቃላ ብአዴን ነት ያለው ነፃ ባልወጡ የዐማራ ከተሞች ላይ ብቻ ነው።በተለይ ባ ሕርዳር ቁማር ቤቱ እንደሞላ ነው።ጃምቦ ቤቱ እና ቤቴንግ ጢቅ እ ንዳለ ነው።የባህርዳር ከነማ እና የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ደጋፊ ማኅበራት ውስጥ ያሉ ጎታቾች የትየለሌ ናቸው። በማርቆስ ቢንጎ ቤት፣በጎንደር ድራፍት ቤት፣ በደሴ ጫት ቤት፣ በደብረ ብርሃን አረቄ ቤት የተከማቸውን ድንዙዝ የዐማራ ወጣት እንዲህ ልክ የሚያገባ ው ኃይል ሊመጣ ግድ ይላል።በተለይ የባህርዳር ቁማር ቤት ሊታ ሰብበት ይገባል።

• ድል ለዐማራ ፋኖ✊✊✊
ዘመድኩን በቀለ

አንድነት ሃይል ነው አፄ ፋሲለደስ ሻለቃ ተመሰረተየአማራ ፋኖ በጎንደር ቴዎድሮስ ብርጌድ አፄ   ፋሲለደስ ሻለቃ በዛሬው ዕለት ሃምሌ 23/2015 ዓ/ም በይፋ ተመሰረተ።ይህንን ምስረታ አስመል...
30/07/2023

አንድነት ሃይል ነው አፄ ፋሲለደስ ሻለቃ ተመሰረተ

የአማራ ፋኖ በጎንደር ቴዎድሮስ ብርጌድ አፄ ፋሲለደስ ሻለቃ በዛሬው ዕለት ሃምሌ 23/2015 ዓ/ም በይፋ ተመሰረተ።

ይህንን ምስረታ አስመልክቶ ከዚህ ቀደም በርካታ ስራ ሲሰራ የቆየው ቴዎድሮስ ብርጌድ ዛሬ አፄ ፋሲለደስን ሻለቃ ሲያቆም ሻለቃ መሪ አድርጎ የሾመው
👉ፋኖ ተስፍሽ መንጌና
ምክትል ሻለቃ
👉ፋኖ ናሁሰናይ አንዳርጌን አድርጎ ሰይሟል።

የአማራ ፋኖ በጎንደር ቴዎድሮስ ብርጌድ አመራርና አባላቶች በምስረታው ተገኝተው ይህን መሰል ለአማራ የጀርባ አጥንት የሚሆኑ ወጣቶችን መልምሎ ወደዚህ ሻለቃ ስያካትት ከኮብልስቶን እሰከ ነፍጥ የታጠቀውን ነባር ታጋይ ተካታችና መሪ ያደረገ መሆኑ ይበል የሚያስብልና ትግሉን ለማሻገር የስራ ድርሻ ቅብብሎሽ ማሳየቱ ዘመናዊ እና ስልታዊ ትግል መሆኑን በማሳወቅ በአንድነት እንደሚሰሩ የጋር ወሳኔ አሳርፈዋል።
Kidusie Z FasilKenma Fentahun

ድል ለአማራ ነፃነት ናፋቂዎች👊

ፋኖ እንደ አቦ ሸማኔ እየተወረወረ ከብልጽግና የጸዳ ቀጠና እየፈጠረ ነው።  ስር የምትገኘው የአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ  #መኮይ ከተማ በጀግናው የህዝብ ልጅ  #ፋኖ ቁጥጥር ስር ገብታለች።💪💪💪💪
29/07/2023

ፋኖ እንደ አቦ ሸማኔ እየተወረወረ ከብልጽግና የጸዳ ቀጠና እየፈጠረ ነው።

ስር የምትገኘው የአንፆኪያ ገምዛ ወረዳ #መኮይ ከተማ በጀግናው የህዝብ ልጅ #ፋኖ ቁጥጥር ስር ገብታለች።💪💪💪💪

አስከተማ የአማራ ፋኖ አቀባበል ተደርጎለታል።በዛሬው ዕለት አስከተማ እና መቄትን ሙሉ በሙሉ በአማራ ፋኖ ላስታ አውራጃ አሳምነው ብርጌድ ተቆጣጥሯል።ምስራቅ አማራ ቀጠና በአንድ ዕዝ ይመራል። ...
29/07/2023

አስከተማ የአማራ ፋኖ አቀባበል ተደርጎለታል።

በዛሬው ዕለት አስከተማ እና መቄትን ሙሉ በሙሉ በአማራ ፋኖ ላስታ አውራጃ አሳምነው ብርጌድ ተቆጣጥሯል።

ምስራቅ አማራ ቀጠና በአንድ ዕዝ ይመራል።

ብአዴን እስከዘላለሙ ይቀበራል።

ድል ለአማራ ሕዝብ‼️

Via = Mulugeta Anberber

 #መቄት !ህዝባዊ ፖሊስ ከህዝብ ጋር ፋኖን በደስታ ሲቀበሉ! 🔥  #ፋኖነት💚💛❤️
29/07/2023

#መቄት !
ህዝባዊ ፖሊስ ከህዝብ ጋር ፋኖን በደስታ ሲቀበሉ! 🔥

#ፋኖነት💚💛❤️

በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአማራ ፋኖ በጎንደር የተሰጠ መግለጫ!ለተከበርከው የአማራ ሕዝብ በሙሉ!  የአማራ ህዝብ ካለፈው 40 አመት የቀጠለ ጥቃት በብልፅግና ስርዓት ቀጥሏል የአማራ ህዝብ በደ...
29/07/2023

በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከአማራ ፋኖ በጎንደር የተሰጠ መግለጫ!

ለተከበርከው የአማራ ሕዝብ በሙሉ!

የአማራ ህዝብ ካለፈው 40 አመት የቀጠለ ጥቃት በብልፅግና ስርዓት ቀጥሏል የአማራ ህዝብ በደሙ በአጥንቱ በገነባት ሀገር ውስጥ ሀገር አልባ እና ተሳዳጅ ተደርጎ ባይተዋር ሆኗል፤ ይህ የዛሬ እውነት ነው። እንዲሁም የመዋቅራዊ ጭቆና ውስጥ ገብቷል። ይህን ጭቆና አድራጊዎች ደግሞ ትናንት የህዋሀትን አምባገነናዊ ስርዓትን ለመገርሰስ አብረናቸው ስርዓታዊ ለውጥ ለማምጣት እና እኩልነት ለማስፈን የታገልነው የዛሬዎቹ ተረኞች የኦህዴድ /ኦሮሙማ/ ተረኛ አምባገነናዊ መሪዎች ናቸው።

ስለዚህ የአማራ ፋኖ በጎንደር ይህን አምባገነናዊ ስርዓት ጭቆና ለመገርሰስና እስከ ወዲያኛው መቀመቅ ውስጥ ለመክተት ለተከበርከው የአማራ ህዝብ የሚከተሉትን የአቋም መግለጫዎች ማሳዎቅ ይፈልጋል:-

፩ኛ. ለመላው የአማራ ሕዝብ፦

ለተከበርከው በሸዋ በወሎ በጎጃም በጎንደር እንዲሁም በመላ ሀገሪቱ የምትገኝ ህዝባችን እየተደረገብህ ያለውን መዋቅራዊ ጥቃትና ማሳደድ በወል ተረድተህ፤ ለመጨረሻው መጀመርያ ሁሉን አቀፍ ትግል እራስክን እንድታዘጋጅና እንድትነሳ እንዲሁም በጎጥ ሊከፋፍሉህ ከሚሞክሩ የውስጥም የውጭም ጠላቶችህን አጀንዳ ወደ ጎን በመተው አሁን እያደረክ እንዳለህው አንድ አማራዊ ስነ ልቦና ጥቃት አደራሹንና ሴራ ጠማቂውን ፀረ አማራ የብልፅግና አገዛዝ ስርዓትን በፅኑ እንድታገል ስንል በጥብቅ ማሳሰብ እንፈልጋለን።

በተጨማሪም ከአብራክህ የወጣውን የቁርጥ ቀን ደራሽ የሆነውን የፋኖ አደረጃጀት በሞራል በግብዕት በትጥቅና ስንቅ አብረህ ለመታገል ቁርጠኛ አቋም እንድትይዝ ስንል በድጋሚ አማራዊ ጥሪያችን እናስተላልፍልሃለን።

፪ኛ. ለመላው አማራ ፋኖ፦

ትናንት የከፈላችሁትን መሰዋዕትነት ለዛሬ የአማራ ህዝብ በዚህ ሁኔታ ለመገኘቱ ትልቅ አስተዋዕፆ አለው። ይህ በእንዲህ እንዳለ በሁሉም አካባቢ ለምትገኙ የአማራ ፋኖ አደረጃጀትና አባላት የሚከተሉትን መልዕክቶች ማስተላለፍ እንፈልጋለን።

~ ሀሳዊያን ፋኖ ነን ባዮች ቀንደኛ የአማራ ህዝብ ጠላት የሆነውን የብአዴን ቅጥረኞች ሰለባ እንዳትሆን እራስክን ከእውነተኛ የህዝብ ልጅ ከሆኑት ከአስራታዊያን ከጎቢያዊያን እንዲሁም ከአሳምነው እውነተኛ የህዝብ ልጆች ጋር በማድረግ እንድትታገልና እራስክንም መከራ የበዛበት ህዝብህንም ከተጋረጠበት ባርነት ነፃ እንድታዎጣ ስንል እናሳስባለን። እንዲሁም በጊዚያዊ ጥቅም ተታለህ እራስክን ሁሌም በአዴን ሰራሽ ለሆነ ርካሽ የፖለቲካ ፕሮፖጋንዳ ተጋላጭ ሳትሆን ፍፁም ልክ በሆነ አማራዊ ስነልቦና በመነሳት ህዝባዊ ትግል እንድታደርግ እንዲሁም ሁሌም ዝግጁ በመሆን እራስክን በአካላዊና ስነ ልቦናዊ ጥንካሬ እንድትጠብቅ ስንል ጓዳዊ ጥሪ እናቀርብልሃለን።

፫ኛ. ለአማራ ህዝብ ማህበራዊ/ሀይማኖታዊ / ተቋማት፦

እንደሚታወቀው የኦሮሙማ ሰልቃጭ/አውዳሚ / ስርዓት ፖለቲካዊ ሁኔታዎችን አልፎ የመጨረሻ የህዝብ የደም ስር የሆነውን የሀይማኖት ተቋማት መድፈሩ የአደባባይ ሚስጥር ከሆነ ውሎ አድሯል። ይህን እውነታ ሲኖዶስን በማፍረስ መጅሊስን በመከፋፈል ሁሉም የኦሮሙማ የፖለቲካ ሀይሎች ሲተባበሩ አይተናል። ይህ አልበቃ በማለት ይህ የኦሮሙማ ስርዓት ጠባቂ የሆነው የመከላከያ አባላት በጓጃም በደብረ ኤልያስ ገዳም በከባድ መሳርያ የታገዘ ጥቃት በመክፈት ከ550 በላይ መነኮሳትን በግፍ በመጨፍጨፍና ጥንታዊ ቅርሶችን በማውደም እንዲሁም የሸገር ከተማ ማቋቋም በሚል ተረኝነት በርካታ መስጊዶችን አለም እያየ በግፍ አውድሟል።

ይህን እምነት አልባነት አላማው ያደረገው ስርዓት ወደ ጥንታዊቷ ጎንደር በመጓዝ ጓርጓራ ደብረ ሲና ማርያምና ማን እንደ አባ ጥንታዊ ገዳማት አጥቢያዎች ውስጥ ፀረ ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ ሚኒስትሮችንና የክልል ባለስልጣናትን ብሎም የኦነግ ወታደራዊ አመራሮችን በመሰብሰብ /ጭፈራናድግስ/ በማዘጋገት ፍፁም በማን አለብኝነት የህዝብ እና የእምነት ተከታዩን ስነ ልቦና በሚጓዳ መልኩ በፆም ቀን የእርድ ተግባር በመፈፀም ማን አለበኝነቱን አሳይቷል። ይህን አስነዋሪ ድርጊት ሲፈፅም የተቃወሙትን የሀይማኖት አባቶችና የአካባቢው ገበሬዎች ላይ የዘር ማጥፋት ሊባል በሚችል ደረጃ ለሚያምነው/ለሚገብረው/ የደም ግብር መሰዋዕት ተደርገዋል።

ስለዚህም ይህን ጥቃት ለመመከትና ለመቀልበስ በሚደረገው ህዝባዊ ትግል ማህበራዊና ሀይማኖታዊ ተቋማት በግልፅ እንድትቃወሙና ድጋፍ እንድታደርጉ ጥሪ እናስተላልፋለን።

፬ኛ. ለአማራ ብልፅግና አባላት፦

ትናንት ብአዴን ሆናችሁ ለህውሀት ተላልካችሁ የአማራን ህዝብ አንገት በማስደፋትና ርስቶችን አሳልፋችሁ በመስጠት ያደረጋችሁት በደል ሳይደርቅ፤ ዛሬ ደግሞ በደምና በአጥንቱ መስዋዕትነት ያስመለሳቸውን የወልቃይት ጠገዴ እና ራያ አካባቢዎች በህግ አግባብ ሳይመለሱ አምነንና ትናንት ያደረጋችሁትን ግፍ ለታሪክ ትተን መሪ አርገናችሗል ሆኖም ግን ከትናንት ያደረው የተላላኪነትና የክህደት እንዲሁም ራስን ችሎ ያለ መቆም መንፈስ ተጠናውቷቹሁ ዛሬም ከትናንቱ የቀጠለው ክህደታችሁ በባሰ መንገድ ቀጥሏል። ለዚህም ማሳያ፦

~ ከ500 000 በላይ አማራና ሌሎች ወንድም ኢትዮጵያዊያን ጥረው እና ግረው ያፈሩትን ሀብት ንብረት በአንድ ጀንበር በተረኞች ሲነጠቁና የጅብ ሲሳይ ሲሆኖ ለሆዳችሁ ስትሎ ጆሮ ዳባ ልበስ በሚመስል መልኩ ዝም ብላችኋል ።

~የኦሮሙማ ጌቶቻችሁን ለማስደሰት የአማራ ህዝብ ልጆቹን አዋጦ ጥሪቱን አሟጦ የገነባውን የአማራ ልዩ ሀይል አፍርሳችሁ ጠባቂ አሳጥታችሁ የጠላቶቹ መጫዎቻና መፈንጫ አድርጋችሁታል።

~ የአማራ ህዝብ ለመዋቅራዊ ጥቃት እንዲጋለጥና እራሱን ችሎ እንዳይቆም በራሳችሁ የጥቅም ፖለቲካ ሴራ ውስጥ አስገብታችሁ በጎጥ የአስተሳሰብ ገመድ እንዲጓተት ጊዜና በጀት በመመደብ ለማሻኮት ጥረት በማድረግ ላይ ትገኛላችሁ ይህን የምታደርጉት ህዝባችን ፖለቲካዊ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች በራሱ መንገድ እንዳይመለሱ ፍፀም በፍርሀት ቆፈን ለማስገባት እያደረጋችሁት ያለው ከንቱ ጥረት ይታወቃል።

ሆኖም ግን ዛሬ ትናንት አይደለምና አሁናዊ እውነትን ተረድታችሁ ከመሸም ቢሆን ለአማራ ህዝባዊ ትግል መርህ ተገዢ በመሆን የአማራ ህዝብ የህልውና ትግል እንቅፋት እንዳትሆኑ ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን።

፭ኛ. ለአማራ ሚሊሻ፣ ፖሊስ/አድማ ብተና / አባላት፦

ልክ እንደ እናንተ ሁሉ የአማራ ፋኖ የአማራ እናትና አባት የወለደው የህዝብ ልጅ ነው ሆኖም ግን ህግ ማስከበር በሚል ሰበብ በፋኖ ወንድሞቻችሁ ቃታ እንድትስቡእና ህዝባዊ መጠፊፊት እንዲደርስ በተደጋጋሚ ስልጠናና ተልዕኮ እንስጣችሁ በሚል ተረኞቹ የሸረቡትን ሴራ አክሽፋችሗል በዚህም ህዝቡም ፋኖም ኮርቶባችሗል
ከዚህ በመነሳት በቀጣይም ፋኖ አማራ ለሚያደርገው ህዝባዊ ትግል የበኩላችሁን አስተዋዕፆ እንደተለመደው እንድታደርጉ ስንል እንገልፃለን።

፮ኛ. ለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት / ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን /

በውል ለመተንበይ በሚያዳግት ሁኔታ ሀገራችን ውስብስብ ወደ ሆነ የለየለት አምባገነናዊ ስርዓት ገብታለች ለዚህ ማሳያ ሀገርን ከወንድም ህዝቦች ጋር ያቆመው የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ያለውን ጭፍጨፋ ማሳደድ እና ሀገር አልባ ማድረግ በቅርብ እንደ አስፈፃሚነት ስለምታውቁት ለእናንተ መንገር ለቀባሪ ማርዳት ይሆናል።

በመሆኑም የአማራ ህዝብ የራሱን ህልውና መሰረት አድርጎ ኢትዮጵያን ከመበተን ለመጠበቅ ለጀመረው የህዝባዊ ትግል አጋርነታችሁን እንድታሳዩ ጥሪ እናስተላልፋለን።

፯ኛ. ለአማራ ህዝባዊ ተጋድሎ ታጋዮች እና አስተባባሪዎች፦

ሀገራችን የገባችበትን ምስቅልቅልና መቀመቅ በወል በመረዳት ከፍረጃ በፀዳ አካባቢያዊነትና ሉላዊነትን በጠበቀ የተተነበየ የአማራን ህዝብ ትግል ለስኬት የሚዳርግ ትግል እንድናደርግ ዛሬ ከትናንት በበለጠ ለህዝባችሁ ታስፈልጋላችሁ እናም ላለው አምባገነን ዘረኛ ስርዓት ሰለባ ሳትሆኑ የአማራ ህዝብ ለጀመረው የህልውና ና ኢትዮጵያን ለማዳን ለሚደረገው ትግል የበኩላችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን።

፰ኛ. ለዲያስፖራ ማህበረሰብ፦

በተሳሳተ መረጃና በማህበራዊ ገፅ ፕሮፖጋንዳ ለብአዴናዊያን ሴራ ሳትጋለጡ የአማራ ህዝብ ትግልን በቀናነት በመደገፍ ትግል በሁሉም ዘርፍ ነውና የአማራ ህዝብ እየደረሰበት ያለውን የዘር ፍጅት ለተቀረው የአለም ህዝብና የሰብዓዊ መብት ጠባቂ ተቋማት በማሳወቅ እንዲሁም የአማራ ፋኖን በመደገፍ ህዝባዊነታችሁን እንድታሳዩ ስንል ጥሪ እናስተላልፋለን።

አማራነታችን በደምና በአጥንት እናፀናለን!!!
ፋኖ አማራ በጎንደር
ሐምሌ 22 ቀን 2015 ዓ.ም
ጎንደር፤ ኢትዮጵያ

የዛሬ አበባዎች የነገ ፍሬዎች ጎበዝ ተማሪ ከሆናችሁ እንደ አዳነች ካድሬ ትሆናላችሁ¡🙌
29/07/2023

የዛሬ አበባዎች የነገ ፍሬዎች ጎበዝ ተማሪ ከሆናችሁ እንደ አዳነች ካድሬ ትሆናላችሁ¡🙌

በዚህ ሰዓት ቀድመው ለሚዘሩ ሰብሎች ማደባሪያ እንዲደርስ እየተሰራ ነው ይላል ሰብል መቸ እንደሚዘራ: እንደሚታረም ( ፀረ አረም እንደሚያስፈልገው) መቸ እንደሚሰበሰብ አያውቁትም። ታድያ ይህ ...
29/07/2023

በዚህ ሰዓት ቀድመው ለሚዘሩ ሰብሎች ማደባሪያ እንዲደርስ እየተሰራ ነው ይላል ሰብል መቸ እንደሚዘራ: እንደሚታረም ( ፀረ አረም እንደሚያስፈልገው) መቸ እንደሚሰበሰብ አያውቁትም። ታድያ ይህ ስረዓት ያልተገረሰሰ ማን ይገረሰሳል?

28/07/2023

"ከተሜዎች" ኑሮ ከተወደደባችሁ ገጠር ግቡ።

አብቹ

ደጉ ባለሀገሩ❤ 💚💛❤️
28/07/2023

ደጉ ባለሀገሩ❤


💚💛❤️

የምስራቅ አማራ ፋኖ፤ የሰሜን ወሎ ኮከቦች፤ መቄት ላይ የአማራ ፋኖን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ነፃነት የራበው፣ ጭቆና የበዛበት ሕዝባችን  በነቂስ ወጥቶ የቁርጥ ቀን ልጆቹ...
28/07/2023

የምስራቅ አማራ ፋኖ፤ የሰሜን ወሎ ኮከቦች፤ መቄት ላይ የአማራ ፋኖን በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ነፃነት የራበው፣ ጭቆና የበዛበት ሕዝባችን በነቂስ ወጥቶ የቁርጥ ቀን ልጆቹን(ፋኖ) በዚህ መልኩ ተቀብሏል።

በዛሬው ዕለት በሰሜን ወሎ ዞን የመቄት ወረዳ፣ የገረገራ ከተማ በአማራ ፋኖ ቁጥጥር ስር ገብተዋል ። የአማራ ፋኖ ገረገራ ክተማ ሲገባ በገረገራ ከተማ የአማራ ሕዝብ ደማቅ አቀባበል ሲደረግለት ህዝቡም ይለያል! ይለያል! ይለያል !ዘንድሮ የብልጽግና ኑሮ በማለት እየጨፈረ ፋኖን መቀበሉን ታውቋል።

በዚህም የህዝቡን ድጋፍና ስሜቱን ያየው የከተማው ፖሊስ እና ሚኒሻ በመበሳጨት ወደ ህዝቡ ለመተኮስ በህንጻወች አናት ላይ ተሰግስገው መቀመጣቸውን የህዝብ ልጅ ለሆነው፣ ለመከታችን፣ አለኝታችን፣ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጅ ( ፋኖ) መረጃው ቀድሞ በመድረሱ አናብስቱ፣ ቅንድብ የማይስተው ፋኖ ተከታታይ ተኩስ ሲተኩስባቸው ሁሉም ተበታትነው እምጥ ይግቡ ስምጥ አልታወቀም።

የአማራ ፋኖ አሁንም እንደዚህ የምታደርጉ የገዥው ስርዓት ታዛዥ የፀጥታ አካላት አደብ ግዙ ! ብትችሉ የአማራ ህዝብ የቁርጥ ቀን ልጅ የሆነውን (ፋኖን) ተቀላቀሉ ፣ ካልቻላችሁ አርፋችሁ ቁጭ በሉ በማለት የመጨረሻ ጥሪያችን እናስተላልፋለን ።

በመቄት ወረዳ በፋኖ ላይ ይሄን ያክል ሴራ እያሴረ ያለው የከተማው የጸጥታ ዘርፍ ሃላፊው አቶ መካሽ መሆኑ ታውቋል። ሆኖም ግን በአስተዋይነቱ የሚታወቀው የአማራ ፋኖ አደረጃጀት የሰውየውን ክፋት በምክር መልክ እንዳለፈው አውቀናል። ብታርፍ ይሻላል‼️

በዛሬው ዕለትም በምስራቅ አማራ ፋኖ ስር የመቄት ወረዳ አንችም ፋኖ ብሎ ተደራጅቶ ታላቅ ተግባራትን እየሰራ ይገኛል።

ድል ለአማራ ፋኖ‼️
ድል ለአማራ ሕዝብ‼️

Via= Mulugeta Anberbere

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ZOBEL TIMES posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ZOBEL TIMES:

Share