MAYA TV Ethiopia - ማያ

MAYA TV Ethiopia - ማያ ቃል ሀይል አለው! የተረጋገጡ መረጃዎችንና አዝናኝ ፕሮግራሞችን እናደርሳለን! ለወደፊትም ትልቅ ተቋም በመገንባት አቅማችንን እናሳድጋለን!

ትላቋ ኢትዮጵያ ! ኢትዮጵያ ዕምቅ አቅም ያላት ሀገር መሆኗን ከዚህ የ CNN ዜና ትረዳለህ። " ትራምፕ ከአምስት አፍሪካ ሙሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ትልልቆቹን ሀገራት ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ ...
11/07/2025

ትላቋ ኢትዮጵያ !

ኢትዮጵያ ዕምቅ አቅም ያላት ሀገር መሆኗን ከዚህ የ CNN ዜና ትረዳለህ።

" ትራምፕ ከአምስት አፍሪካ ሙሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ትልልቆቹን ሀገራት ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ ፣ ናይጄሪያ አለማሳተፋቸው ... " እያለ ይተነትናል።

* * *

" ኢትዮጵያ ድክሞ ሀገር መስላ የምትታያቸው ሰዎች ብዙሀኑ በደረጄ ሀብተወልድ እና ስታሊን ገብረስላሴ ሰበር ዜና የደስ ደስ የሚገባበዙ ሙዝ ራሶች ናቸው "

ጥቅሱ ከመምሬ Samson Michailovich ' የሰበር ዜና ተስፈኞች ' ከተሰኘው መጽሀፍ የተወሰደ ነው ።

https://edition.cnn.com/2025/07/09/africa/trump-african-leaders-summit-intl?fbclid=IwQ0xDSwLd_1BleHRuA2FlbQIxMQABHtVfDQ5houhA2LP_fAHd-TkBFwvAp8o8bJBmWqXvw89Wp5mEC8AWOJ_dv2I6_aem_4ZlVG7-0E-vq37J2aR9kcA

The White House hosted an “African leaders” summit of sorts this week. But only five countries from the continent of more than 50 nations were welcome to join.

"እግራቸውን በጥይት በሏቸው" አሉ ፕሬዚዳንት ሩቶወጣቶች ሥልጣን እንዲለቁ በሕዝባዊ ተቃውሞ የተነሱባቸው የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ በንግድ ተቋማት ላይ ያነጣጠሩ ተቃዋሚዎችን ፖሊሶች "...
11/07/2025

"እግራቸውን በጥይት በሏቸው" አሉ ፕሬዚዳንት ሩቶ

ወጣቶች ሥልጣን እንዲለቁ በሕዝባዊ ተቃውሞ የተነሱባቸው የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ በንግድ ተቋማት ላይ ያነጣጠሩ ተቃዋሚዎችን ፖሊሶች "እግራቸውን በጥይት እንዲመቱ" ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።

ፕሬዚዳንቱ እነዚህ ተቃዋሚዎች እንዳይገደሉ ነገር ግን መሰናከላቸውን አረጋግጡ ብለዋል።

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች በኬንያ ሰኞ፣ ሰኔ 30/2017 ዓ.ም. በተካሄደው ፀረ-መንግሥት ተቃውሞ 31 ሰዎች መገደላቸውን አስታውቀዋል።

ተቋማቱ ፖሊስ ከመጠን ያለፈ ኃይል ተጠቅሟል ሲሉ ከሰዋል።

"የሌላ ሰው የንግድ ተቋምን ወይም ንብረት ሲያቃጥል የተያዘ ማንኛውም ሰው ፖሊስ እግሩን በጥይት መትቶ ሆስፒታል እንዲያስገባው እና ከዚያም ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት።

አትግደሏቸው፤ ነገር ግን መሰናከላቸውን አረጋግጡ" ሲሉ ፕሬዚዳንቱ ለፀጥታ ኃይሎቻቸው አቅጣጫ አስቀምጠዋል ሲል ቢቢሲ ዘግቧል ።

Ethio fm

የኢትዮጵያ ብር በሩሲያ የባንክ ምንዛሬ ውስጥ ተካተተ!የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ሌሊት ላይ ይፋ ባደረገው መረጃ የኢትዮጵያን ብር በምንዛሬ ዝርዝር ውስጥ አካቷል።ይህም ማለት ብርን ወደ ሩብል እ...
11/07/2025

የኢትዮጵያ ብር በሩሲያ የባንክ ምንዛሬ ውስጥ ተካተተ!

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ሌሊት ላይ ይፋ ባደረገው መረጃ የኢትዮጵያን ብር በምንዛሬ ዝርዝር ውስጥ አካቷል።

ይህም ማለት ብርን ወደ ሩብል እንዲሁም ሩብልን ደግሞ ወደ ብር መመንዘር የሚያስችል ዕድልን ይሰጣል።

በዚህም መሰረት ባንኩ ለ100 የኢትዮጵያ ብር 57.5872 ሩብል ወይም ለ1 ብር 0.575872 ሩብል የምንዛሬ ተመን አስቀምጧል።

ባንኩ ለኢትዮጵያ ብር ምንዛሬ ተመን የኮድ ቁጥር 230 የሰጠ ሲሆን በየዕለቱም የምንዛሬ ተመኑን የሚያሳውቅ ይሆናል።

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የኢትዮጵያን ብር ጨምሮ የ12 ሀገራት ገንዘቦች ከሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ጋር ያላቸውን ይፋዊ የምንዛሪ ተመን ለማስቀመጥ ውሳኔ ላይ መድረሱን ከቀናት በፊት ማስታወቁ ይታወሳል።

በጌትነት ተስፋማርያም

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ “ብር” ከዛሬ ሐምሌ 3 ጀምሮ “ከሩብል” ጋር ይፋዊ የምንዛሪ ተመን በማውጣት በሀገሪቱ ጥቅም ላይ እንደሚውል አስታወቀ!!  | የኢትዮጵያ መገበያያ ገንዘብ ብር ከዛሬ ...
10/07/2025

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ “ብር” ከዛሬ ሐምሌ 3 ጀምሮ “ከሩብል” ጋር ይፋዊ የምንዛሪ ተመን በማውጣት በሀገሪቱ ጥቅም ላይ እንደሚውል አስታወቀ!!

| የኢትዮጵያ መገበያያ ገንዘብ ብር ከዛሬ ሐምሌ 3 ጀምሮ ከሩሲያ መገበያያ ገንዘብ ሩብል ጋር ይፋዊ የምንዛሪ ተመን ወጥቶለት በቀጥታ በምንዛሬ ደረጃ ጥቅም ላይ እንደሚውል ተገለጸ።

የሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ የኢትዮጵያ ብርን በውጭ ምንዛሪ ዝርዝሮቹ ውስጥ በይፋ ማካተቱን ተከትሎ ከዛሬ ከሐምሌ 10 ቀን 2025 ዓ.ም. ጀምሮ በይፋ ተቀብሎ እና ጥቅም ላይ እንዲውል እንደሚደረግ አስታውቋል።

ከዛሬ ሐምሌ 10 ቀን ጀምሮ የኢትዮጵያን ብር ጨምሮ የ12 ሀገራት መገበያያ ገንዘቦች ከሩሲያ ማዕከላዊ ባንክ ጋር ያላቸውን ይፋዊ የምንዛሪ ተመን በማስቀመጥ መጠቀም እንደሚጀምር።

ማዕከላዊ ባንኩ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የሀገሪቱ የመገበያያ ገንዘብ ሩብል ከሌሎቹ የ12 ሀገራት መገበያያ ገንዘብ ጋር ያለውን ዕለታዊ የምንዛሬ ተመን ይፋ ያደርጋል።

የባንግላዴሽ ታካ፣ የባህሬን ዲናር፣ የቦሊቪያ ቦሊቪያኖ፣ የኩባ ፔሶ፣ የአልጄሪያ ዲናር እና የኢራን ሪያል የመገበያያ ገንዘቦችን ከሩሲያው ሩብል ጋር ያላቸው ይፋዊ የምንዛሪ ተመን ውሳኔ በባንኩ በኩል ይፋ ይደረጋል ተብሏል።

የኢትዮጵያ ብር ከሩሲያ ሩብል ጋር በቀጥታ ለመገበያየት መበቃቱ የሀገራቱነ የተጠናከረ ግንኙነት ያመላክታል ተብሏል።

በዶላር የውጭ ምንዛሬ ክምችት እጥረት ለሚፈተነው የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ አማራጭ ተደርጎ መቅረቡ ተጠቁሟል።

በቪዛ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የውጪ ዜጎች ከተሰጣቸው ቀነ ገደብ ካለፉ ቅጣት ይጠብቃቸዋል!!  የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በቪዛ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የየትኛውም ሀገር ዜጎች ከተሰጣቸው ቀነ ገደብ ...
10/07/2025

በቪዛ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የውጪ ዜጎች ከተሰጣቸው ቀነ ገደብ ካለፉ ቅጣት ይጠብቃቸዋል!!

የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በቪዛ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የየትኛውም ሀገር ዜጎች ከተሰጣቸው ቀነ ገደብ ካለፉ ቅጣት ይጠብቃቸዋል አለ።

የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው የዓመቱን ዲፕሎማሲያዊ ተግባራት እና ሳምንታዊ ክንውኖችን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም በቀጣዮቹ ሳምንታት በአዲስ አበባ የሚካሄዱ ዓለም አቀፍ ጉባዔዎችን በብቃት ለማስተናገድ ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡

ሁለተኛው የተባበሩት መንግስታት የስርዓተ ምግብ ጉባዔ ከሐምሌ 20 እስከ 22 ቀን 2017 እንዲሁም እስከ 25 ሺህ ተሳታፊዎች ይስተናገዱበታል ተብሎ የሚጠበቀው ሁለተኛው የአፍሪካ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባዔ በጳጉሜን ወር እንደሚስተናገድ ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ ጉባዔዎቹን ብሔራዊ ጥቅሟን ባስጠበቀ መልኩ ለማስተናገድና ተሞክሮዎቿን ለማካፈል በዝግጅት ላይ መሆኗን ተናግረዋል።

ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን ሊከተሉ የሚገባቸውን ጥንቃቄ በተመለከተ መልዕክት ያስተላለፉት ቃል አቀባዩ፤ በትምህርት እና በጉብኝት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ሁሉም ኢትዮጵያውያን የተሰጣቸውን ጊዜ እንዳያሳልፉ አስገንዝበዋል።

ቀነ ገደቡን የሚያሳልፉ አካላት በተደረገው የህግ ማሻሻያ መሰረት ከባድ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው አስረድተዋል።

በቪዛ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የየትኛውም ሀገር ዜጎች ከተሰጣቸው ቀነ ገደብ ካለፉ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው የገለጹት አምባሳደር ነብያት፤ ቅጣቱ ህጉን ተላልፈው የሚገኙ የኢትዮጵያ መኖሪያ መታወቂያ ካርድ የሌላቸው ትውልደ ኢትዮጵያውያንንም ያካትታል ነው ያሉት።

Via FMC

‹‹እንግሊዘኛ የት ነው የተማርከው?›› በማለት ትራምፕ የላይቤሪያውን ፕሬዝደንት ጠየቁ፡፡ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ትራምፕ ትላንት 5 የአፍሪካ አገራት መሪዎችን ጠርተው አነጋግረዋል፡፡ ውይይቱ ...
10/07/2025

‹‹እንግሊዘኛ የት ነው የተማርከው?›› በማለት ትራምፕ የላይቤሪያውን ፕሬዝደንት ጠየቁ፡፡ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ትራምፕ ትላንት 5 የአፍሪካ አገራት መሪዎችን ጠርተው አነጋግረዋል፡፡ ውይይቱ ከመጀመሩ በፊት ትራምፕ መሪዎቹ ራሳቸውን እንዲስተዋውቁ እድል ይሰጧቸዋል፡፡

በዚህ ወቅት የ4ቱ አገራት መሪዎች በተለያየ ቋንቋ ራሳቸውን ያስተዋወቁ ሲሆን አምስተኛው የላይቤሪያው ፕሬዝደንት ጆሴፍ ባኮይ ነበሩ፡፡ እኚህ ፕሬዝደንትም ማይክራፎኑን ከጨበጡ በኋላ በእንግሊዘኛ ራሳቸውን አስተዋውቀው ‹‹ላይቤሪያና አሜሪካ ረጅም ጊዜ ያስቆጠረ ወዳጅነት ያላቸው ናቸው፡፡ እኛ እርስዎ ያወጡትን አሜሪካን ሀያል ማድረግ ፖሊሲ እንደግፋለን›› በማለት ይናገራሉ፡፡

ፕራምፕ ይህን ከሰሙ በኋላ ‹‹በጣም ጥሩ እንግሊዘኛ ነው፡፡ ለመሆኑ እንዲህ ውብ አድርገህ እንግሊዘኛን መናገር የለመድከው የት ነው?›› ሲሉ ጠይቀዋል፡፡

ፕሬዝደንት ባኮይ በበኩላቸው ‹‹በላይቤሪያ ውስጥ ነው›› በማለት ይመልሳሉ፡፡ ትራምፕም በማስከተል ‹‹በጣም ይገርማል፡፡ እዚህ ከእኔ ጋር ያሉት የእኔ ሰዎች የአንተን ያህል እንግሊዘኛን የሚናገሩ ሁሉም አይደሉም›› በማለት "አድናቆታቸውን" ገልፀውላቸዋል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ በላይቤሪያ ይፋዊ የስራ ቋንቋው እንግሊዘኛ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በምእራብ አፍሪካ ጠረፍ ላይ የምትገኘው ላይቤሪያ የተመሰረተችው በ1822 ሲሆን ከአሜሪካ ነፃ የወጡ ሰዎች መኖሪያ በመሆንም ትታወቃለች፡፡ የላይቤሪያ ሰንደቅ አላማ ራሱ ከአሜሪካ ጋር ተመሳሳይነት ያለው ነው፡፡
____________
ትራምፕ የአፍሪካ ሃገራት የጋቦን፣ ጊኒ ቢሳዎ፣ ላይቤሪያ፣ ሞሪሸስና ሴኒጋል መሪዎችን ሲያነጋግሩ ጆሯቸው ላይ ማዳመጫ አድርገው ነበር። ፎቶውም ይህን ያሳያል።

ዩክሬን በጦርነቱ ታሪክ ከፍተኛው የአየር ላይ ጥቃት በሩሲያ ተሰንዝሮባታል - ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ዩክሬን በጦርነቱ ታሪክ ከፍተኛው የአየር ላይ ጥቃት በሩሲያ እንደተሰነዘረባት የዩክ...
09/07/2025

ዩክሬን በጦርነቱ ታሪክ ከፍተኛው የአየር ላይ ጥቃት በሩሲያ ተሰንዝሮባታል - ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ

ዩክሬን በጦርነቱ ታሪክ ከፍተኛው የአየር ላይ ጥቃት በሩሲያ እንደተሰነዘረባት የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ ገለጹ።

ዩክሬን እስካሁን ከደረሱባት የአየር ላይ ጥቃቶች የከፋ ነው የተባለው ጥቃት፤ በ728 የሩሲያ ሰው አልባ የጦር አውሮፕላኖች እና በ13 ባላስቲክ ሚሳኤሎች የተደረገ ነው።

በጥቃቱ በርካታ የዩክሬን ከተሞች ጉዳት ደርሶባቸዋል የተባለ ሲሆን፤ ኪየቭ ጠንካራ እና ተደጋጋሚ የሆነውን የሩሲያን የአየር ላይ ጥቃት ባሏት የአየር መቃወሚያዎች ለመከላከል እየሞከረች መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል።

ፕሬዚደንት ዜሌንስኪ ጥቃቱን ተከትሎ በሰጡት መግለጫ፤ ሰላምን ለማምጣት እና ተኩስ አቁም ለማድረግ በርካታ ጥረቶች በሚደረጉበት በዚህ ወቅት ሩሲያ ሁሉንም ልፋት መና እያደረገችው ትገኛለች ብለዋል።

ይህ የሩሲያ ጥቃት የተፈጸመው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አቋርጠውት የነበረውን የጦር መሳሪያ ድጋፍ በድጋሚ ወደ ዩክሬን መላክ እንደሚጀምሩ ካሳወቁ ከጥቂት ቀናት በኋላ ነው።

በፈረንጆቹ አዲስ ዓመት መጀመሪያ ላይ በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ሁለት ዙር የተኩስ አቁም ንግግር የተካሄደ ቢሆንም ፤ እስካሁን ይህ ነው የሚባል ፍሬ ሊያፈራ አልቻለም።

በሰለሞን ከበደ

ሰሞኑን በአፍሪካ ቀንድ የተቀያየሩና ይበልጥ አደጋ የጋረጡ ጉዳዮችና መረጃዎች ፍንትው እያሉ ወጥተዋል። ታዋቂው የእስራኤል ጋዜጣ እየሩሳሌም ፖስት ሱዳን ዋነኛዋ የኢራን መሳሪያ መሆኗን በመጥቀ...
09/07/2025

ሰሞኑን በአፍሪካ ቀንድ የተቀያየሩና ይበልጥ አደጋ የጋረጡ ጉዳዮችና መረጃዎች ፍንትው እያሉ ወጥተዋል። ታዋቂው የእስራኤል ጋዜጣ እየሩሳሌም ፖስት ሱዳን ዋነኛዋ የኢራን መሳሪያ መሆኗን በመጥቀስ እርምጃ ሊወሰድባት እንደሚገባ ለእስራኤል መንግስትና ለምዕራባውያኑ አሳስቧል።

"የደህንነት መስርያ ቤቶች መረጃ መሰረት ያደረገው የጋዜጣው መረጃ የሱዳኑ ጀኔራል አልቡርሃን ኢራን ለምትደግፋቸው የቀጠናው ታጣቂዎች በተለይ ለየመን ሁቲዎች መሳሪያ አቀባይ መሆኑን ያብራራል። እስራኤል የምትጠቃው ሱዳን ውስጥ በሚገጣጠሙ ድሮኖች እንደሆነ በማከልም የአልቡርሃን ቡድን የኢራን መሳሪያ ሆኖ እያገለገለ በመሆነ እርምጃ ሊወሰድበት እንደሚችል ወትውቷል።

"በተመሳሳይ ሀአሬትዝ የተሰኘ የእስራኤል ጋዜጣ ኤርትራ በቀጠናው የኢራን አላማ አስፈፃሚ ሆና ፀረ-አሜሪካና ፀረ-እስራኤል አቋም እያራመደች መሆኑን ፅፏል። የዚህ ጋዜጣ መረጃ ለየት የሚያደርገው፣ በጉዳዩ ላይ ዝርዝር የፃፈው ኤርትራዊ ምሁር ሀፍቶም ገብረ እግዚያብሔር ነው። ሰውየው በተደጋጋሚ ኤርትራና እስራኤል አብረው መስራት እንዳለባቸው ሲወተውት የቆየ ሲሆን ኤርትራ ለእስራኤል ህልውና የምትጫወተውን ሚና በማብራራት ይታወቅ ነበር።

"በቅርብ ግን ኤርትራ ለእስራኤል የደህንነት ስጋት መሆኗል የሚያስረዳ መጣጥፍ በጋዜጣ አሳትሟል። እነዚህ ሁለት ጋዜጦች ለፖሊሲ አውጭው ቀላል የማይባል መረጃ የሚመግቡ እንደመሆናቸውና የደህንነት መረጃዎችን ይዘው የሚሰሩ መሆናቸው ኤርትራና ሱዳን በእስራኤል ብቻ ሳይሆን በምዕራባውያኑም ዘንድ አደገኛ መዝገብ ውስጥ መግባታቸውን የሚያመለክት ነው። እነዚህ ሁለት የእስራኤል እውቅ ሚዲያዎች ያጋሩት መረጃ መጀመሪያ በደህንነት ተቋማት በኩልም ሲደረስበት ወዳጅ አገራት የሚጋሩት በመሆኑ አሜሪካም ሆነች የአውሮፓ አገራት ተመሳሳይ አቋም መያዛቸው የማይቀር ነው።"

Via Zehabesha

ኢትዮጵያ፣ ኬኒያና ሶማሊያን የሚያገናኝ አዲስ የፋይበር ፕሮጀክት  • ፕሮጀክቱን  ዓለም ባንክ በገንዘብ ይደግፈዋልየኬኒያ መንግሥት በዲጂታል ትስስር ከኢትዮጵያና ሶማሊያ ጋር ለመገናኘት የሚያ...
08/07/2025

ኢትዮጵያ፣ ኬኒያና ሶማሊያን የሚያገናኝ አዲስ የፋይበር ፕሮጀክት

• ፕሮጀክቱን ዓለም ባንክ በገንዘብ ይደግፈዋል

የኬኒያ መንግሥት በዲጂታል ትስስር ከኢትዮጵያና ሶማሊያ ጋር ለመገናኘት የሚያስችል፤ በኢሲኦሎ–ማንዴራ ኮሪደር በኩል ከፍተኛ አቅም ያለው የፋይበር ኦፕቲክ ገመድ ለመዘርጋት አቅዷል።

የአፍሪካ ቀንድ መተላለፊያ ልማት የተሰኘውን ፕሮጀክት ዓለም ባንክ በገንዘብ እንደሚደግፈው ቴክ አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል።

የኬኒያ መንግሥት ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ የግብዐት ግዢዎችን ለመፈፀም እንዲሁም በአይሲቲ መሠረተ ልማትና ትስስር ዘርፍ ውስጥ ካሉ የገበያ ባለድርሻዎች ጋር ምክክር ለመጀመር የቅደመ ገበያ ግንኙነቶችን እያደረገ ነው ተብሏል።

(sputnik)

በህዳሴው ግድብ ምርቃት ላይ ፕሬዝደንት ፑቲን ሊጋበዙ ነው፡፡ የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው መስከረም ወር በሚደረገው የህዳሴ ግድብ ምርቃት ስነስርአት እንዲገኙ ግብዣ ሊላክላቸው...
06/07/2025

በህዳሴው ግድብ ምርቃት ላይ ፕሬዝደንት ፑቲን ሊጋበዙ ነው፡፡ የሩሲያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን በመጪው መስከረም ወር በሚደረገው የህዳሴ ግድብ ምርቃት ስነስርአት እንዲገኙ ግብዣ ሊላክላቸው መሆኑ ተሰማ፡፡

ስፑትኒክ የተሰኘው የሩሲያ ሚዲያ ዛሬ እንደዘገበው በግድቡ መክፈቻ ስነስርአት ላይ ፑቲን እንዲገኙ የኢትዮጵያ መንግስት ግብዣ ሊላክላቸው ይችላል፡፡ ይሁንና ግብዣው ቢላክ ፕሬዝደንቱ ለመገኘት ፈቃደኛ ስለመሆንና አለመሆናቸው ያለው ነገር የለም፡፡ የሩሲያው ፕሬዝደንት ፑቲን በአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት በቀረበባቸው ክስ የእስር ማዘዣ የተቆረጠባቸው መሆኑ ይታወቃል፡፡

በአሁኑ ወቅት በብራዚል እየተካሄደ ባለው የብሪክስ የመሪዎች ስብሰባ ላይ በአካል ያልተገኙትም ለዚህ ነው፡፡ ስለጉዳዩ የተጠየቁት የክሬሚሊን አማካሪ ዩሪ ኡሻኮቭ ‹‹ከአይሲሲ ሁኔታዎች ጋር በተያያዘ ፕሬዝደንት ፑቲን በአካል ብራዚል ለመገኘት አይችሉም›› ሲሉ ባለፈው ሳምንት ተናግረው ነበር፡፡

በመሆኑም በስብሰባው ላይ በቪዲዮ ኮንፈረንስ እንደሚሳተፉ ማስታወቃቸው አይዘነጋም፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ኢትዮጵያ የአለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት(አይሲሲ) አባል አይደለችም፡፡ በሮም ፍርድ ቤቱን በተመለከተ የተፈረመውን ስምምነት ባለመፈረሟ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ የማስፈፀም ግዴታ እንደሌለባት ዘገባዎች ገልፀዋል፡፡

ፑቲን ለእኛ ንቀት አለዉ ! ትራምፕ "ፑቲን ዩናይትድ ስቴትስ  ጦርነቱ እንዲቆም ላቀረበችዉ ጥሪ የመለሰዉ ምላሽ ለአሜሪካ  ያለውን ንቀት በግልፅ ያሳያል"/ ትራምፕ/የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ...
05/07/2025

ፑቲን ለእኛ ንቀት አለዉ ! ትራምፕ

"ፑቲን ዩናይትድ ስቴትስ ጦርነቱ እንዲቆም ላቀረበችዉ ጥሪ የመለሰዉ ምላሽ ለአሜሪካ ያለውን ንቀት በግልፅ ያሳያል"/ ትራምፕ/

የዩኤስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ባደረጉት የስልክ ጥሪ በተሰጣቸዉ ምላሽ መከፋታቸዉን ገለፁ ። ሩሲያ በዩክሬን ላይ የምታደርገውን ጦርነት ለማስቆም አትፈልግም ሲሉም ተናግረዋል ።

ሐሙስ ዕለት ከፑቲን ጋር ከተነጋገረ በኋላ ዋሽንግተን ሲመለሱ ለጋዜጠኞች በሰጡት አስተያየት "ዛሬ ከፕሬዚዳንት ፑቲን ጋር ባደረግኩት ውይይት በጣም ተበሳጨሁ, ምክንያቱም እሱ እዚያ ያለ አይመስለኝም, እና በጣም አዝኛለሁ" ብለዋል ።

ለዩክሬን ስለሚደረገው የጦር መሳርያ ድጋፍ በተመለከተም አርብ እለት ከዋሽንግተን ተነስተው ወደ አዮዋ ሲሄዱ ትራምፕ “የጦር መሳሪያዎችን ፍሰት ሙሉ በሙሉ አላቆምንም፣ ነገር ግን ጆ ባይደንን ብዙ መሳሪያዎችን በመላክ የአሜሪካን መከላከያዎች ማዳከም አደጋ ላይ ስለጣለን እንደድሮዉ አንልክም ሲሉ የሚያደርጉትን ድጋፍ መቀነሳቸዉን ለጋዜጠኞች ተናግረዋል ።

የሁለቱን መሪዎች የስልክ ልዉዉጥ ተከትሎ
"አሁንም እንደገና ሩሲያ ጦርነቱን እና ሽብርን የማስቆም አላማ እንደሌላት እያሳየች ነው" ሲል ዘለንስኪ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ተናግሯል ።

አሜሪካ የሁለቱን ሀገራት ጦርነት በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለመፍታት ጥረት እያደረገች ቢሆንም ፑቲን በበኩሉ የግጭቱ "ሥር መሠረቱን" ከተፈታ ብቻ እንደሚያቆም ማስታወቁን ቀጥሏል ። ሩሲያ ስለጉዳዩ ባወጣችው አጭር መግለጫ ዩክሬን ለኔቶ መስፋፋት ይጠቅም ዘንድ ከኔቶ ጥምረት ጋር መቀላቀልን የጀመረችዉን ጉዞ እና የምዕራባውያን ድጋፍ ካላቆመች መቼም እንዴትም ወደ ድርድር እንደማያመሩ አሳዉቀዋል ። ሲል AP የዜና ወኪል ዘግቧል ።

ታዴ የማመይ ልጅ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when MAYA TV Ethiopia - ማያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to MAYA TV Ethiopia - ማያ:

Share