Esea Tube

Esea Tube Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Esea Tube, Media/News Company, Addis Ababa.

24/11/2025

እንኳን በደህና መጣችሁ ወደ ሚዛናችን ሚዲያእዚህ ቻናል ላይ፣ በየጊዜው በሚለዋወጠው ዓለማችን ውስጥ ስላሉት ወቅታዊ ጉዳዮችና አዳዲስ ዜናዎች ጥልቅ ትንተና እና አስተማማኝ መረጃ እና.....

ሁለት ህፃናትን አግታ 25 ሺህ ዶላር የጠየቀች ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች! ቦሌ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ — ሁለት ንጹሐን ህፃናትን በአስገድዶ የመያዝ ወንጀል ተጠርጥራ ገንዘብ የጠየቀች ...
08/11/2025

ሁለት ህፃናትን አግታ 25 ሺህ ዶላር የጠየቀች ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለች!

ቦሌ ክፍለ ከተማ፣ አዲስ አበባ — ሁለት ንጹሐን ህፃናትን በአስገድዶ የመያዝ ወንጀል ተጠርጥራ ገንዘብ የጠየቀች ግለሰብ በቦሌ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ተይዛ ምርመራ እየተካሄደባት መሆኑ ተገለጸ።

የህፃናቱ ወላጆች ወ/ሮ ሽኩሪያ አብዱል ራሽድ እና ባለቤቷ ጥቅምት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የታመመ ልጃቸውን ለማሳከም ከድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ፣ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ወደሚገኝ የህክምና ተቋም ይመጣሉ።

ከዶክተር ቢሮ ሲወጡ፣ የ5 እና የ10 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሮቢና እና ተሲያ የተባሉ ሁለት ሴት ልጆቻቸውን ያጣሉ። ከልጆቹ ጋር የነበረችው ሂክራም ረሽድም በቦታው ላይ አልነበረችም።

ወላጆቹ ለካራማራ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ወዲያውኑ ሪፖርት ያደርጋሉ። የፖሊስ ምርመራና ክትትል ቡድን ሂክራም ረሽድ ህፃናቱን ይዛ ወደ ኦሮሚያ ክልል፣ ምስራቅ ሸዋ ዞን፣ ባቱ (ዝዋይ) ከተማ መሄዷን ደረሰበት።

ፖሊስ ወደ ስፍራው እያመራ ባለበት ወቅት፣ ተጠርጣሪዋ ለወላጆቹ በስልክ መልእክት በመላክ 25,000 የአሜሪካ ዶላር ወይም 4 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ብር እንዲልኩላት፣ አለበለዚያ ልጆቹን እንደማትለቅ አስፈራራች።

የካራማራ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ከባቱ (ዝዋይ) ከተማ ፖሊስ መምሪያ ጋር በመቀናጀት ባደረገው ፈጣን ክትትል፣ ተጠርጣሪ ሂክራም ረሽድ በቁጥጥር ስር ዋለች። ህፃናቱ ምንም አይነት አካላዊ ጉዳት ሳይደርስባቸው ጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. በሠላም ወደ ወላጆቻቸው ተመልሰዋል።

ፖሊስ ወንጀል ፈፃሚዋ ከህፃናቱ ወላጆች ጋር ያላትን ዝምድና ተጠቅማ ወንጀሉን መፈፀሟን ገልጿል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ህፃናትን በመያዣነት በመያዝ ጥቅም ለማግኘት የሚፈጸሙ ወንጀሎች እየተስተዋሉ ሲሆን፣ ወንጀሉ የሚፈፀመውም ቅርብ ግንኙነት ባላቸው ግለሰቦች ነው።

ወላጆች ተገቢውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልእክቱን አስተላልፏል። የቅርብ ሰዎችንም ቢሆን ከመጠን ያለፈ እምነት ከመስጠት እንድንቆጠብ አሳስቧል።

Via አዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ መምሪያ

08/11/2025

የምርጫ ቦርድ የጌታቸው ረዳን 'ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ' ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ለሕዝብ ይፋ አደረገየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጅ የተሰጠውን ሥልጣን በመጠቀም፣ በአቶ ጌታቸው ረዳ...
08/11/2025

የምርጫ ቦርድ የጌታቸው ረዳን 'ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ' ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ለሕዝብ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጅ የተሰጠውን ሥልጣን በመጠቀም፣ በአቶ ጌታቸው ረዳ ካሕሳይ አመራር የቀረበለትን የአዲስ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ለሕዝብ ይፋ ማድረጉን አስታውቋል

ቦርዱ ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት፣ የምዝገባ ጥያቄው የቀረበለት ፓርቲ "ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት)" በሚል ስያሜ ሲሆን፣ በእንግሊዝኛ ደግሞ "Tigray Democratic Solidarity Party (Solidarity)" በመባል ይታወቃል።

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ይህን ያደረገው "በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011" መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት ስላለው እንደሆነ የገለፀ ሲሆን በዚኹ መሠረት እነአቶ ጌታቸው ረዳ ካሕሳይ “ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ወይም Tigray Democratic Solidarity Party (Solidarity)“ በሚል ስያሜ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ያቀረቡ በመሆኑ፤ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 68 ንዑስ አንቀጽ 2 እና 3 መሠረት በፓርቲው ስም፣ ዐርማ ወይም ሌሎች ጉዳዮች ተቃውሞ ያለው ሰው፤ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከዛሬ ከጥቅምት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ14 ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን ለቦርዱ ጽሕፈት ቤት እንዲያቀርብ ቦርዱ አሳውቋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

08/11/2025

የጋዜጠኛ ገነነ ባለቤትን ጨምሮ ተጠርጣሪዎች ፍርድ ቤት ቀረቡ!

👮‍♂️ አስራ አራት ቀን ቀጠሮ ጠየቀ፤ ፍርድ ቤትም ጥያቄውን ተቀበለ!!

👉 በጋዜጠኛና ደራሲ ገነነ መኩሪያ ሞት የተጠረጠሩ ግለሠቦች ባለፈው ሀሙስ በቁጥጥር ስር ዋሉ።
ባለቤቱ ወ/ሮ አስቴር አየለ፣ አቶ ይታየው (ምትኬ) እንዲሁም የዋካና ሆቴል ባለቤት በፌዴራል ፓሊስ መያዛቸው ተረጋግጣል። ተጠርጣሪዎቹ ትላንት አርብ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

👉 የፌዴራል ፓሊስ የወንጀል ምርመራ ቡድን አባሎች ተጠርጣሪዎች ላይ የተጠናከረ ምርመራ ለማድረግ ተጨማሪ የአስራ አራት ቀን ጊዜ ቀጠሮ እንዲሠጠው ጥያቄ አቅርባል።

ፍርድ ቤቱ ፓሊስ የተጠየቀውን የምርመራ ቀን አስመልክቶ ፈቃድ ሰጥቷል። አዲስ አበባ የሚገኙ የናይል ስፖርት ሚዲያ ታማኝ ምንጮች ተከታዩን መረጃ አድርሠውናል። " በኢትዬጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች ዘንድ ጉዳዩ ልዩ ትኩረት እንደተሠጠው አረጋግጠውለናል።

👉 የጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ ህልፈተ ህይወት ምክንያትን የሚያጣራ የምርመራ ቡድን ተቋቁማል።
የኮሚቴው አባሎች በየጊዜው የሚደርስቡበትን እያንዳንዱን የምርመራ ሂደት ለተቋሙ ከፍተኛ ኃላፊዎች ያሳውቃሉ።

👉 የተዳፈኑ የሚመስሉ ውስብስብ ወንጀሎችን አፈንፍነው በማጋለጥ የረጅም ጊዜ ልምድ እና ዕውቀት ባካበቱ አባሎች የተዋቀረ የምርመራ ቡድን መዋቀሩን ለመስማት ችለናል። ጉዳዩ የፌዴራል ፓሊስ ጠቅላይ አዛዥ በሆኑት በኮሚሽነር ጄኔራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ልዩ ትኩረት እንደተሠጠው የናይል ስፖርት ሚዲያ ምንጮች አረጋግጠውልናል።

👉 በቀደምትነት በጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ ሞት ዙሪያ ምርመራ ያደረገው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደነበረ ይታወሳል። በቅርቡ ለአዲስ አበባ ፓሊስ ወንጀል መከላከል ክፍል በጋዜጠኛ ገነነ ህልፈተ ህይወት ዙሪያ ጥያቄ ላቀረቡ የስፖርት ጋዜጠኞች አጥጋቢ ምላሽ ሳይሠጥ መቀረቱ የሚዘነጋ አይደለም። በተለይ አንድ ኃላፊ
" ከሞተ ሶስት ዓመት ለሆነው ሠው የሞት ምክንያቱን መጠየቅ አይገባቹሁም" የሚል ምላሽ ሰጥተው ነበር። የእኝህ የአ፡አ ፖሊስ ባልደረባ የሆኑ መኮንን ምላሽ በርካቶችን አስቆጥቷል።

👉 አሁን በቁጥጥር ስር የሚገኙት የጋዜጠኛ ገነነ ባለቤት አራት ጋዜጠኞችን በስም ማጥፋት በፍርድ ቤት ክስ መስርተል። ጋዜጠኛ ገነነ ራሱን አጥፍቷል በሚል የአዲስ አበባ ፖሊስ ማረጋገጫ እንደሰጣቸው በክሳቸው አካተው ነበር።
ከእዚህ ቀደም በጋዜጠኛ ገነነ መኩሪያ ህልፈትን አስመልክቶ የተሠጡት ምክንያቶች በወዳጆቹና በቤተሠቦቹ ዘንድ ተቀባይነት ሊያገኙ አልቻሉም።

👉 የጋዜጠኛ ገነነ ታናሽ ወንድም የሆነው አቶ አለማየሁ መኩሪያ የወንድሙ አስክሬን ወጥቶ ምርመራ እንዲደረገበት ለፌዴራል ፓሊስ ጥያቄ ማቅረቡ ተሠምቷል።

ጉዳዩ ተዳፍኖ እንዳይቀር የኢትዬጵያ ፌዴራል ፖሊስ በተጠናከረ ሁኔታ ምርመራ በመጀመሩ ሊመሠገን ይገባዋል።

📌የዳዊት መለሰ አልበም የሚለቀቅበት ቀን ታወቀድምጻዊ ዳዊት መለሰ የመጨረሻ አልበሙን በ1995 ዓ.ም ለአድማጮች ያቀረበ ሲሆን ለዓመታት ተጨማሪ አልበም ሳይሰራ ቆይቷል።ከሰሞኑም ድምጻዊ ዳዊት...
08/11/2025

📌የዳዊት መለሰ አልበም የሚለቀቅበት ቀን ታወቀ

ድምጻዊ ዳዊት መለሰ የመጨረሻ አልበሙን በ1995 ዓ.ም ለአድማጮች ያቀረበ ሲሆን ለዓመታት ተጨማሪ አልበም ሳይሰራ ቆይቷል።

ከሰሞኑም ድምጻዊ ዳዊት መለሰ አዲስ አልበሙን እንዳጠናቀቀ እንዲሁም የሚለቀቅበት ቀን እንደተቆረጠለትም ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

ይህ ከሁለት አስርት ዓመታት በኃላ ለአድማጮች የሚቀረበው አልበም "ምስጢር" የተሰኘ ርዕስ ተሰጥቷል።

ከቀናትም በፊት ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የአልበም ማድመጫ ሥነሥርዓት ተከናውኗል።

ከአልበም ማድመጫ ሥነሥርዓት በኃላም ድምጻዊው በማህበራዊ ትስስርና ገፁ" ሚስጢር የተሰኘውን መጪውን አልበሜን በማካፈል ክብር አግኝቻለሁ።ሚስጢር የዘፈን ስብስብ ብቻ አይደለም። ታሪክ ነው። በመሥራት ላይ 20 ዓመታት ያለፈው። ለሁላችሁም በጣም በቅርቡ እስከ ማካፍላችሁ አጅግ ጓጉቻለሁ" ሲል ጽፏል።

08/11/2025

...

08/11/2025

...

08/11/2025

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Esea Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share