11/08/2023
አዲስ እየተደረጃ በሚገኘዉ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በክላስተር ቢሮ ክፍፍል ላይ የዞኑ ህዝብ ማግኘት የሚገባውን ቢሮ ያላስገኘ እና ፍትሐዊ ያልሆነ የቢሮ ክፍፍል በመሆኑ ሂደቱ ፍትሃዊ በሆነ አካሄድ እንዲደራጅ የዱራሜ ከተማ ምክር ቤት አባላት ጠየቁ።
የዱራሜ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አካሂዷል።
በጉባኤውም አዲስ እየተደራጃ በሚገኘዉ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በክላስተር ቢሮ ክፍፍል ላይ ዞኑ ማግኘት የሚገባውን ተቋም ያለማግኘት እና ሚዛናዊ ያልሆነ የቢሮዎች ክፍፍል በመሆኑ በፍጹም መታረም ያለበት እንደሆነ ተገልጿል።
አባላቱ እኩል የመልማት ፣ የመበልፀግና የማደግ መብት እንዲከበርላቸው በራሳቸው እና በወከለዉ ህዝብ ስም ኢ-ፍትሃዊ የክላስተር አደረጃጀት ሂደቱ ፍትሃዊ በሆነ አካሄድ እንዲደራጅ ጠይቀዋል።
አዲስ እየተደራጀ በሚገኘዉ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በክላስተር ቢሮ ክፍፍል ላይ ዞኑ ማግኘት የሚገባውን ቢሮ ያለማግኘት እና ሚዛናዊ ያልሆነ ክፍፍል በመሆኑ ሊታረም እንደሚገባም ጭምር አንስተዋል።
በመጨራሻም የምክር ቤቱ አባላት በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል በክላስተር አደረጃጀት ያለዉን ኢ-ፍትሃዊ አደረጃጀቱን በሙሉ ድምፅ በመቃወም እና ይህም በቀጣይ ለሚመለከተው አካል እንዲቀርብ በመጠየቅ የዱራሜ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 12ኛ አስቸኳይ ጉባኤ ተጠናቋል።
#ዘገባው የዱራሜ ከተማ አስተዳደር መንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ነው!