Addis Star Media አዲስ ስታር ሚዲያ

Addis Star Media  አዲስ ስታር ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Addis Star Media አዲስ ስታር ሚዲያ, TV Network, Addis Ababa.

Description -
Addis Star is an independent online media platform, covering daily breaking news, special news analysis, live entertainment and events and much more.

https://youtu.be/263TuKR1rGY?si=EWGDuuAe-IWw-WdV
12/08/2024

https://youtu.be/263TuKR1rGY?si=EWGDuuAe-IWw-WdV

Maraki Business – is a channel where you can find the latest business news. ማራኪ ቢዝነስ - ወቅታዊ የቢዝነስ ዜናዎችን የሚያገኙበት ቻናል ነው።

** ኤልሳቤት ቦርን የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ  **ኤልሳቤት ቦርን በ30 አመታት ውስጥ የመጀመሪየዋ የፈረንሳይ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ተሾ...
17/05/2022

** ኤልሳቤት ቦርን የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ **

ኤልሳቤት ቦርን በ30 አመታት ውስጥ የመጀመሪየዋ የፈረንሳይ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን በፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ተሾመዋል፡፡ በሀገሪቱ የሰራተኛ ሚኒስትር የነበሩት ኤልሳቤት ቦርን÷ የ61 አመቱን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ዣን ካስቴክስን ተክተው የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚንስትር ሆነው መሾማቸው ተሰምቷል፡፡
ተሰናባቹ የፈረንሳይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዣን ካስቴክስ የፕሬዚዳንት ማክሮን ዳግም መመረጥን ተከትሎ ለአዲሱ መንግስት የለውጥ አካል ለመሆን በሚል ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው መልቀቃቸውን አናዶሉ ዘግቧል፡:

Via Fana

 #ሰበር ዜና‼️ጄነራል ተፈራ ማሞ ታፍኖ ተወስዷል።እስካሁኗ ስዓት ድረስ የት እንዳለ አይታወቅም ስትል ባለቤቱ አረጋግጣለች።አዳዲስ መረጃወችን ተከታትለን እናሳውቃለን።
16/05/2022

#ሰበር ዜና‼️
ጄነራል ተፈራ ማሞ ታፍኖ ተወስዷል።
እስካሁኗ ስዓት ድረስ የት እንዳለ አይታወቅም ስትል ባለቤቱ አረጋግጣለች።
አዳዲስ መረጃወችን ተከታትለን እናሳውቃለን።

G7 ስለኢትዮጵያ ምን አለ? የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ማምሻውን ባወጡት ባለ 46 ነጥብ መግለጫ የኢትዮጵያንም ወቅታዊ ሁኔታ ቀጥር 17 ላይ  አካተዋል፡፡ ዋና ዋና ጉ...
15/05/2022

G7 ስለኢትዮጵያ ምን አለ?

የቡድን ሰባት አባል ሀገራት ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ማምሻውን ባወጡት ባለ 46 ነጥብ መግለጫ የኢትዮጵያንም ወቅታዊ ሁኔታ ቀጥር 17 ላይ አካተዋል፡፡ ዋና ዋና ጉዳዮችም የሚከተሉት ናቸው፡፡

✔-“እርዳታ ለማድረስ የሰብዐዊ ተኩስ አቁም መደረጉ በበጎ የምንቀበለው ነው፡፡ አሁንም ግጭት ወዳለባቸው አካባቢዎች የተሟላ፤ደህንነቱ የተጠበቀ፤ገደቦች የሌሉበት ዘላቂ የእርዳታ አቅርቦች እንዲኖሩ ሁሉንም ወገኖች ማሳሰብ እንወዳለን፡፡”

✔-“በግጭቱ ተሳታፊ የሆኑ አካላት በሙሉ ዘላቂ ተኩስ አቁም እንዲኖርና ለአሳታፊ ብሄራዊ መግባባትና አስተማማኝ ሰላም መሰረት ወደሆነው ፖለቲካዊ መፍትሄ እንዲሄዱ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡”

✔-“የኤርትራ መንግስት ከሰሜን ኢትዮጵያ ጦሩን እንዲያስወጣ እናሳስባለን፡፡”

✔-“የኢትዮጵያ መንግስት የጋራ ምርመራ ሪፖርትን መነሻ በማድረግ የሚኒስትሮች ግብረ ሀይል ማቋቋሙን እንደግፋለን፡፡ ሁሉም ወገኖች ለአለም አቀፍ የሰብዐዊ መብት ኮሚሽን የባለሙያዎች ቡድን ትብብር እንዲያደርጉም እናሳስባለን፡፡”

✔-“በምስራቅና ደቡባዊ አካባቢ ከስምንት ሚሊየን በላይ ሰዎች ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ያሳደረው ድርቅ በጥብቅ ያሳስበናል፡፡ ሰብዐዊ ድጋፎችን ለማድረግ ቃል እየገባን አለም አቀፍ አጋሮችም ተመሳሳይ እርምጃዎችን እንዲወስዱ እናሳስባለን፡፡ ”

Via: Blue24

 ጎረቤታችን ሶማሊያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ታካሂዳለች።ይህን ተከትሎ የሶማሊያ ፖሊስ ምርጫ እስኪጠናቀቅ በዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ በጸጥታ ሥጋት ሳቢያ ከአስቸኳይ አገልግሎቶች ውጪ ሁሉንም ሕዝባዊ እን...
15/05/2022



ጎረቤታችን ሶማሊያ ፕሬዜዳንታዊ ምርጫ ታካሂዳለች።

ይህን ተከትሎ የሶማሊያ ፖሊስ ምርጫ እስኪጠናቀቅ በዋና ከተማዋ ሞቃዲሾ በጸጥታ ሥጋት ሳቢያ ከአስቸኳይ አገልግሎቶች ውጪ ሁሉንም ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች የሚያግድ የሰዓት ዕላፊ ተግባራዊ አድርጓል።

የታወጀው ሰዓት እላፊ እስከ ሰኞ ጧት ድረስ የሚቆይ ነው ተብሏል።

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት የሚመርጠው የታችኛው እና የላይኛው ምክር ቤቶች በጋራ በሚሰጡት ድምጽ ነው።

ጎሳን መሰረት ባደረገው በዚህ ለ6ኛ ጊዜ በሚካሄድ ቀጥተኛ ባልሆነ ምርጫ 39 እጩዎች ይወዳደራሉ።

ስልጣን ላይ ያሉት ፕሬዝዳንት ሞሐመድ አብዱላሂ መሐመድ (ፍርማጆ) ፣ የቀድሞዎቹን ፕሬዝዳንቶች ሸሪፍ ሼክ አህመድ እና ሀሰን ሼክ ሞሐመድን እንዲሁም የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሀሰን አሊ ኬህሬን ከእጩ ተወዳዳሪዎቹ መካከል ናቸው።

የራስ ገዝዋ የፑንትላንድ ፕሬዝዳንት ሰዒድ አብዱላሂ ዳኒና የቀድሞ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ፋውዛ ዩሱፍ አደንም ለፕሬዝዳንትነት ይወዳደራሉ።

ፋውዛ ዩሱፍ አደን ብቸኛዋ ሴት ፕሬዝዳንታዊ እጩ ናቸው።

የነገው ምርጫ ከአንድ ዓመት በላይ ሲጠበቅ የነበረ ሲሆን በምርጫው አሸንፎ ስልጣን የሚይዘው ፕሬዝዳንት የሰርጎ ገቦች ጥቃትና ረሀብ ያስከትላል ተብሎ የሚያሰጋውን ድርቅ ጨምሮ በርካታ ፈተናዎች የመፍታት ኃላፊነት ይወስዳል።

Via የጀርመን ሬድዮ

በአዲስ አበባ የስምንተኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 30 ይሰጣል ተብሏል።ከተማ አቀፍ የሆነው የስምንተኛ ክፍል ፈተና ከ71ሺ በላይ የሆኑ ተማሪዎችን ከሰኔ 27 እስከ ሰኔ 30 2014 ዓ....
12/05/2022

በአዲስ አበባ የስምንተኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 30 ይሰጣል ተብሏል።

ከተማ አቀፍ የሆነው የስምንተኛ ክፍል ፈተና ከ71ሺ በላይ የሆኑ ተማሪዎችን ከሰኔ 27 እስከ ሰኔ 30 2014 ዓ.ም ለመፈተን መዘጋጀቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታውቋል፡፡

በአጠቃላይ ሰባ አንድ ሺ ስድስት መቶ ስልሳ አንድ የስምንተኛ ክፍል ተማሪዎች ለማስፈተን ዝግጅቱን እያጠናቀቀ መሆኑን በትምህርት ቢሮ ፈተና ዝግጅት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ ተናግረዋል።

የፈተና ዝግጅቱ ተጠናቆ የህትመት ስራዉ የተዘጋጀ ሲሆን በእለቱ የማሰራጨት ስራ ብቻ እንደሚቀርም ገልጸዋል፡፡

የፈተናዉን ምዝገባ በተመለከተ የተማሪዎች የአድሚሽ ካርድ በሚቀጥለው ሳምንት በየትምህርት ቤቶቹ እንደሚላክ እና ለተማሪዎቹም እንደሚተላለፍ ተናግረዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለስምንተኛ ክፍል ፈተና 211 የመፈተኛ ጣቢያዎች የተዘጋጁ ሲሆን ጣቢያዎቹን ምቹ ናቸው የሚለውን ምልከታ እየተደረገ መሆኑን በማንሳት ቁጥሩ ከፍ አልያም ዝቅ ሊደረግ እንደሚችል አቶ ዲናኦል አብራርተዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

ሶስት ሴቶችን የገደለው ወንጀለኛ ማረሚያ ቤት ውስጥ ማግባት እንደሚፈልግ ገለጸ።የ53 ዓመቱ ሌቪ ትዳሩን ለመመስረት የከተማዋን አስተዳዳሪ የመጨረሻ ይሁንታ ማግኘት አለበት።ወንጀለኛው ማርሻ ማ...
12/05/2022

ሶስት ሴቶችን የገደለው ወንጀለኛ ማረሚያ ቤት ውስጥ ማግባት እንደሚፈልግ ገለጸ።

የ53 ዓመቱ ሌቪ ትዳሩን ለመመስረት የከተማዋን አስተዳዳሪ የመጨረሻ ይሁንታ ማግኘት አለበት።
ወንጀለኛው ማርሻ ማኮኔል፣ ኤምሊ ዴላግራንዴ እና ሚሊ ዶውለር የተባሉ ሴቶችን በጭካኔ በመግደል ጥፋተኛ ተብሎ ሁለት የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት ነበር።

የቀድሞው የፍትህ ሚኒስቴር ሮበርት በክላንድ ዘ ሰን ለተባለው ጋዜጣ ሲናገሩ ሰርግ የመደገስ ሀሳቡ ''ለማመን የሚከብድ ነው'' ብለዋል።
''የ13 ዓመቷ ሚሊ የሰርግ ቀኗን ማየት ሳትችል ነው የገደላት። እሱ ደግሞ ሰርግ ለመደገስ ማሰቡ ትክክል አይመስለኝም'' ብለዋል።

ወንጀለኛው ከሁለት ዓመታት በፊት በጽሁፍ ታገኘው የነበረችው ግለሰብ ጋር እንደተቀራረቡና በተደጋጋሚ ትጎበኘው እንደነበር ዘ ሰን ዘግቧል።

ወንጀለኛው ከሁለት ዓመታት በፊት በጽሁፍ ታገኘው የነበረችው ግለሰብ ጋር እንደተቀራረቡና በተደጋጋሚ ትጎበኘው እንደነበር ዘ ሰን ዘግቧል።
ከሰሞኑ ደግሞ ልትጎበኘው ስትመጣ ተንበርክኮ የታገቢኛለሽ ጥያቄውን ማቅረቡ ተዘግቧል።

የአገሪቱ የፍትህ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ በበኩላቸው ''ሰርጉን ለመደገስ ይፋዊ ጥያቄ የቀረበ ሲሆን ከዚህ በፊት በምንሰራበት አሰራር እየተጠና ነው'' ብለዋል።

ቢቢሲ አማርኛ

ሱዳን ፤ ከኢትዮጵያ እና ከኤርትራ በምትዋሰንበት ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ከሰላ ከተማ የጎሳ ግጭት መቀስቀሱን ተከትሎ ሰዓት እላፊ ጣለች፡፡ሰዓት እላፊው በኑባ እና ቤኒ ዓምር ጎሳዎች መካ...
12/05/2022

ሱዳን ፤ ከኢትዮጵያ እና ከኤርትራ በምትዋሰንበት ድንበር አቅራቢያ በምትገኘው ከሰላ ከተማ የጎሳ ግጭት መቀስቀሱን ተከትሎ ሰዓት እላፊ ጣለች፡፡

ሰዓት እላፊው በኑባ እና ቤኒ ዓምር ጎሳዎች መካከል ግጭት መቀስቀሱን ተከትሎ ትናንት ረቡዕ ምሽት ጀምሮ የተጣለ ሲሆን ለ24 ሰዓታት ይቆያል ተብሏል፡፡

ሌላ አዲስ ውሳኔ እስከሚሰጥ ድረስ ሰዓት እላፊው እንዲከበርም የከተማዋ ባለስልጣናት አሳስበዋል፡፡

ደም አፋሳሽ ነበር የተባለለትን ግጭት የሃገሪቱ መንግስት የጸጥታ ኃይሎች ገብተው እስኪያስቆሙት ድረስ የሰው ህይወት መጥፋቱ እና ጉዳቶች መድረሳቸው አል ዐይን ኒውስ ዘግቧል።

የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘ። የኢፌዴሪ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን ለዚህ ታሪካዊ ላሉት ስኬት እንኳንደስ ያላችሁ ብለዋል። የቡና ምርት ...
12/05/2022

የኢትዮጵያ ቡና በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ 1 ቢሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሪ አስገኘ።

የኢፌዴሪ የግብርና ሚኒስትር ኡመር ሁሴን ለዚህ ታሪካዊ ላሉት ስኬት እንኳን
ደስ ያላችሁ ብለዋል። የቡና ምርት ኢትዮጵያ ለዓለም ገበያ ከምታቀርባቸው የግብርና ምርቶች መካከል ግንባር ቀደም ሆኖ ቀጥሏል።

ሀገሪቱ በተለይም ወደ ቻይና የምትልከው የቡና ምርት በከፍተኛ መጠን አድጓል። በፈረንጆቹ 2021 ዓመተ ምህረት ላይ ቻይና ከኢትዮጵያ ያስገባቸው የቡና ምርት መጠን ከቀደመው ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ196 በመቶ አድጓል።

በቅርቡ የኢትዮጵያን የቡና ምርት በቻይና ገበያ የበለጠ ለማስተዋወቅ በተዘጋጀ መድረክ ላይ የሀገሪቱ የቡና ማህበር እንዳስታወቀው፥ በቻይና ከትላልቅ ከተሞች እስከ መለስተኛ ከተሞች የቡና ተጠቃሚዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ ዕድገት ያሳየ ሲሆን፥ ይህም ለኢትዮጵያ ቡና አምራቾች እና ላኪዎች ሰፊ የገበያ ዕድል መፈጠሩ ተመልክቷል።

ሚኒስትሩ ባለፉት የበጀት ዓመቱ ወራት የተገኘው የውጭ ምንዛሪ ምን ያህል የቡና መጠን ወደ ውጭ ተልኮ እንደሆነ አልጠቆሙም።

FBC

ታሊባን አፍጋናውያን ሴቶች ከዐይናቸው ውጭ ሙሉ በሙሉ መሸፈን አለባቸው ማለቱን ተከትሎ የጸጥታው ምክር ቤት ሊሰበሰብ ነውታሊባን አፍጋናውያን ሴቶች የፊት ገጽታቸውን ሙሉ በሙሉ የሚሸፍን ልብስ...
12/05/2022

ታሊባን አፍጋናውያን ሴቶች ከዐይናቸው ውጭ ሙሉ በሙሉ መሸፈን አለባቸው ማለቱን ተከትሎ የጸጥታው ምክር ቤት ሊሰበሰብ ነው

ታሊባን አፍጋናውያን ሴቶች የፊት ገጽታቸውን ሙሉ በሙሉ የሚሸፍን ልብስ (ቡርቃዓ) መልበስ አለባቸው ማለታቸውን ተከትሎ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ዛሬ ስብሰባ መጥራቱም ተሰምቷል፡፡

ታሊባን ባሳለፍነው ቅዳሜ ነበር በመካከለኛ እድሜ ላይ የሚገኙና እምብዛም እድሜያቸው ያልገፋ ሴት አፍጋናውያን እይታቸውን በማይከልል መልኩ የፊት ገጽታቸውን ሙሉ በሙሉ የሚሸፍን ቡርቃዓ እንዲለብሱ ያወጀው፡፡

አዋጁ በሼሪዓ ህግ መሰረት የተላለፈ ነው፡፡ ከቅርብ ዘመዶቻቸው ውጭ ወንዶች ቢያገኟቸው እንዳይተናኮሷቸው በማሰብ የተላለፈ ነውም ነው የተባለው፡፡

አል ዓይን አማርኛ

የትግራይ ህዝብ “ለመጨረሻው ምዕራፍ ትግል” እንዲዘጋጅ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥሪ አቀረቡ።ዋዜማ ራዲዮ- የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል ከማዕከላዊው መንግስት ጋር...
12/05/2022

የትግራይ ህዝብ “ለመጨረሻው ምዕራፍ ትግል” እንዲዘጋጅ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥሪ አቀረቡ።

ዋዜማ ራዲዮ- የትግራይ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደብረፅዮን ገብረሚካዔል ከማዕከላዊው መንግስት ጋር ችግሮችን በዲፕሎማሲ ለመፍታት ሲደረግ የነበረው ጥረት “ባለመሳካቱና የሰላም መንገድ በመዘጋቱ የትግራይን ሕዝብ ነፃነት ለማረጋገጥ” የክልሉ ህዝብ እንዲዘጋጅ ጥሪ አቀረቡ።

ደብረፅዮን በመቀሌ ሌሎች የሕወሓት አመራሮች ደግሞ በተለያዩ የትግራይ ዞኖች ከነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የትግራይ ህዝብ አሁን ያለበት የከፋ ስቃይ እንዲቀለበስና የትግራይ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት እንዲረጋገጥ ለማድረግ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰናል ብለዋል።

“ሁሉም የፖለቲካ ችግር በሰላምና በዲፕሎማሲ እንደማይፈታ ብናውቅም አሁን የገባንበት ጦርነት ከመጀመሩ አስቀድመን እንዲሁም በጦርነቱ ወቅት ለሰላም ቅድሚያ ሰጥተናል” ብለዋል ደብረፅዮን በመቀሌ ከነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ላይ።

በአለም አቀፉ ማህበረሰብ አሸማጋይነት ጊዚያዊ ስምምነት ተደርጎ ወደ ክልሉ እህል መድሀኒትና ሌሎች ድጋፎች እንዲገቡ ጥረት ብናደርግም እስከ አሁን ድረስ የተገኘው ድጋፍ ችግሩን ለማቃለል በቂ አይደለም ብለዋል።

መላክ ያለበትን መልዕክት ለሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ባለን የመገናኛ መንገድ አድርሰናል ያሉት ደብረፅዮን የሚመለከታቸው ያሏቸውን አካላት አልዘረዘሩም።

ዋዜማ ሬድዮ

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Addis Star Media አዲስ ስታር ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Addis Star Media አዲስ ስታር ሚዲያ:

Share

Category